Written February 2022
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Wednesday, 2 November 2022
FUD
Tuesday, 25 October 2022
የኩርፍያ ፖለቲካ
«እነ ስብሐት ነጋ ከተፈቱ ጀምሮ የአዲስ አበባ ህዝብ በዐቢይ ላይ አክሩፏል። ሮንድ ማድረርም አቆመ» ተባልኩኝ።
ይህ የፖለቲካችንን መሰረታዊ ችግር ያሚገልጽ አባባል ነው። ህዝቡ ማድረግ የነበረበት፤
1. ተቃውሞውን በሚገባው መግለጽ መንግስት እንዲሰማ እና እንዲገባው
2. እንደዚህ አይነት ነገር እንዳይደገም የመንግስት ስራተኞች፤ ህዝብ ወኪሎች፤ መሪዎችን መወትወት
ይህን ከማድረግ ፋንታ ህዝቡ ምን አደረገ፤
1. መንግስትን በሚያዳክም መልኩ እና ጠላትን በሚያጎለብት መልኩ መንግስትን ተቸ!
2. አክሩፎ እንደ ህጻን እራሱን የሚጎዳ ድርጊቶች ፈጸመ፤ ለምሳሌ አካባቢውን መጠበቅ ተወ!
ለ45 ዓመት በላይ ፖለቲካ ያቃጠለው ህዝብ እንደዚህ የፖለቲካ ደንቆሮ ይሆናል። የመንግስትን እርምጃ ለመቃወም የራሱን ጥቅም ይጎዳል! አካባቢ መጠበቅ ሮንድ ማድረግ ህዝቡን እጅግ ጠቅሟል። ደህንነትን እና አብሮነትን ጨምሯል። ህዝቡ ለዚህ መስክሯል። ስለዚህ ለራሱ ጥቅም ብሎ እነዚህን ስራዎች መቀጠል ነበረበት። ይህ ሎጂካል ነው። ግን ይህን ከማድረግ መንግስትን አክሩፍያለው ብሎ እራሱን መጉዳት ጀመረ።
ህወሓት ይሁን ሌሎች በቀላል ወሬ በህዝባችን የሚጫወቱት ለዚህ ነው። አህያ የሚሉንም ለዚህ ነው። ፖለቲካ አይገባውም። የራሱን ጥቅም አያውቅም። በቀላሉ ከምነግስት ልናፋታው እንችላለን ነው እነ ህወሓት የሚያስቡት። እንሆ ለ27 ዓመት የገዛነው ደንቆሮ ስለሆነ ነው በይፋ የሚሉት።
ሀገራችን ሰላም እንዲኖራት ይህን ነገራችንን ማሻሻል አለብን። መንግስት እያንዳንዱን የፈለግኩት ነገርን ካላደረገ ይፍረስ የሚለውን የመሃይ አስተሳሰብ እንዲጠፋ ማድረግ አለብን። ቀላል ዘመቻ አይሆንም።
Thursday, 16 December 2021
የሃላፊነት ፖለቲካ
የታወቀው የመካከለኛ ምስራቅ ታሪክ ምሁር በርናርድ ልዊስ የአረብ ፖለቲካ ባህል ድክመትን ለመተቸት እንዲህ ብሎ ነበር፤
“When people realize things are going wrong, there are two questions they can ask......One is, ‘What did we do wrong?’ and the other is, ‘Who did this to us?’ The latter leads to conspiracy theories and paranoia. The first question leads to another line of thinking: ‘How do we put it right?’”
ትርጉም፤ «ህዝብ ነገሮች እየተበላሹ እንደሆነ ሲገነዘብ ሁለት አይነት ጥያቄዎችን መጠየቅ ይችላሉ፤ አንዱ «ምን ተሳስተን ነው?» ነው፤ ሌላው ጥያቄ «ማን ነው እንደዚህ ያደረገን ነው?» የመጨረሻው አይነት ጥያቄ ወደ ሴራ፤ ፍረሃትና ጥርጣሬ ይመራል። የመጀመርያው ጥያቄ ግን «እንዴት ነው ነገሮችን የምናስተካከለው» ወደሚለው ይመራል።
የዚህ አባባል ትርጉም ባጭሩ እንዲህ ነው፤ ችግርህን ሙሉበሙሉ የጠላቴ ጥፋት ነው ካልክ ለጠላት ያጋለጡህን የራስህን ድክመቶች አታምንም አታርምም። ጠላትን በቀጥታ በማጥፋት ላይ ብቻ ታተኩራለህ፤ ካቃተህ ተስፋ ትቆርጣለህ።
ምሳሌ፤ ህወሓት ስልጣን ከያዘ ጀምሮ ተቃዋሚዎች መደራጀት ሳይችሉ፤ ገንዘብና አቅም መሰብሰብ ሳይችሉ፤ ምንም አይነት የተደራጀ የህዝብ ድጋፍ መሰብሰብ ሳይችሉ እነዚህ መሰረታዊ የህልውና ችግራቸውን ከማረም ይልቅ ያላቸውን ጊዜና አቅም ህወሓትን በመኮነን ብቻ አባከኑ። በዚህ ምክንያት ተቃዋሚዎቹ ህወሓትን ሊጎዱት አልቻልም። መጨረሻ ላይ ህወሓት የፈረሰው በራሱ ያጠመደው የጎሳ ብሄረተኝነት አደጋ ነው።
ዛሬም የኢትዮጵያዊነት የፖለቲካ ጎራ ተመሳሳይ ስህተት ላይ ይመስለኛል። ችግራችን ሁሉ የህወሓት ጥፋት ነው እያለ የራሱን ችግር እንኳን ለመፍታት ለማመንም ዝግጁ አይመስለኝም። ለምንድነው ህወሓት እንደዚህ ጠንክሮ የሚቀናቀነን? ለምንድነው መጀመሪያውኑ ህወሓት ሊገዛን የቻለው? ህወሓት ከየት ነው የመጣው? እነዚህ ጥያቄዎች ጥይቀን በትክክል ብንመልስ የራሳችንን ድክመቶች አይተን አርመን ህወሓትን በተሻለ ደረጃ መግጠም እንችላለን። ግን አላደረግነውም። በራሳችን ላይ ግምገማ አላደረግንም። ስህተቶቻችንን አላመንም። አላረምንም። በዚህ ምክንያት አላስፈላጊ ዋጋ እየከፈልን ነው።
መሆን የነበረበት እራሳችንን በዚህ መንገድ መገምገም ነበር፤ 1) ማርክሲስት ሆነን እርስ በርስ በመጣላታችንና ሀገሪቷን በማድከማችን እራሳችን ነን ህወሓትን የፈጠርነው ወይንም እንዲፈጠር ሜዳውን ያዘጋጀነው፤ 2) ሀውሓት ለረጅም ዓመታት የገዛን ምክንያት እኛ ቁጥራችን እጅግ አብላጫ ቢሆንም አብሮ መስራትና መደራጀት ስላቻልን ነው፤ 3) ዛሬም የህወሓትን ጦርነት በአጭሩ መጨረስ ያልቻልንበት ምክንያት አንድ ሆነን ተማምነን ተናበን መስራት ስላልቻልን ነው።
እራሳችንን በዚህ መንገድ ከገመገምን የችግሩ መፍትሄን አገኘን ማለት ነው። የፈረንጅ ጸረ ኢትዮጵያ የሆነ እንደ ማርክሲዝም አይነት ፖለቲካዊ አስተሳሰብ ጎጂ እንደሆነ ተረድተን ከዛ አይነት አስተሳሰቦች እራሳችንን እናርቃለን። መተባበርና አንድ መሆን የግድ እንደሆነ ተረድተን ጥርጣሬ፤ መጠላለፍ፤ ምቀኝነት፤ ትእቢት ወዘተን አስወግደን በአንድነት እንሰራለን። እርስ በርስ ያሉንን ትናንሽ ልዩነቶች እንቅፋት እንዳይሆኑን ለትክክለኛው ጊዜ ና መድረክ ትተናቸው በአንድነት እንሰራለን። ለህወሓት ጥቃት ያጋለጡንን መሰረታዊ ችግሮቻችንን አርመን እንገኛለን። ይህንን ካደረግን ጠላትን በቀላሉ እናስወግዳለን።
Monday, 20 September 2021
ምእራቡ ለምን ኢትዮጵያን ኢትዮጵያዊያንን ትንቃለች
Saturday, 14 November 2020
ድላችን ጦር ሜዳ ላይ እንዳይቀር
Sunday, 21 April 2019
ገንቢ ውይይት ከአንዷለም አራጌ ጋር
ለማንኛውም አንድ ሁለት ነጥብ ከዚህ ውይይት... በመጀመርያ አንዱእዓለም ስለ «ሃላፊነት ፖለቲካ» (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/blog-post_30.html) አስረግጦ ተናገረ። የሀገራችን ፖለቲካዊ ይሁን ሌሎች ችግሮች በዋናኝነት የህወሓት ጥፋት ሳይሆኑ የያንዳንዶቻችን ጥፋት ናቸው። በድርጊታችን ወይንም በዝምታችን እያንዳንዶቻችን ጥፋተኛ ነን። (እኔ የምለው) አልፎ ተርፎ ህወሓትንም የወለድነው እኛው ነን (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/blog-post_21.html)። ይህን ሃላፊነት ካልወሰድን መቼም ልንድን አንችልም። ትክክለኛ መልዕክት ነው።
Thursday, 18 April 2019
ገንቢ ትምሕርት ክሙስታፋ ምሐመድ ዑመር
ሁለት ዋና ዋና ነጥቦች፤
፩) በፖለቲካ ፍፁምነት የለም። ፍፁም እውነት እና ፍፁም ውሸት የለም። ፖለቲካ እንደ ሃይማኖት አይደለም። የሁሉም ሃሳብ የተወሰነ እውነት ሊኖረው ይችላል። ስለዚህም የሌላውን ሃሳብ እና አቋም በደምብ መረዳት አለብን። እራሳችንን በሌሎች ቦታ አድርገን በርህራሄ ማሰብ አለብን። ምናልባት ልክ ሊሆኑ ይችላሉ ብለን ማሰብ አለብን። መገተር የለብንም። ለመስማማት መወያየት እና መደራደር አለብን። ይህን ተመልክቶ «ፖለቲካ ሃይማኖት አይድለም» (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/10/blog-post.html) የሚለውን ጽሁፍ ያንብቡ።
በተዘዋዋሪ በፖለቲካ ተደራድሮ ተስማምቶ መኖር ሲቻል በሃይማኖት ረገድ አይቻልም ብለው ሲአስረዱ በሃይማኖት ግን ተቻችሎ፤ ላለመስማማት ተስማምቶ አብሮ መኖር ይቻላል ብለዋል። ግን «ተቻችሎ» ብቻ ሳይሆን ተፋቅሮ መኖር ይቻላል። «ሃይማኖታዊ መቻቻል» (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/04/blog-post_3.html) የሚለውን ጽሁፍ ያንብቡ።
፪) ይህንን ተከትሎ ርዕዮት ዓለምን እንደ ፍፁም ማየት የለብንም። ርዕዮት ዓለም ሰው ስራሽ ነው እና ስህተቶች እንዳሉት ማወቅ አለብን። ርዕዮት ዓለምን እንደ ጣኦት ካመለክን ወደ እልቂት እናመራለን። አቶ ሙስታፋ ብዙዎቻችን «የምናመልከው» ዴሞክራሲም እንደ ጣኦት ከተቆጠረ ታላቅ አደጋ እንደሚያስከትል አስረዳ። በዚህ ዙርያ «ዴሞክራሲ» (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_8.html) የሚለውን ጽሁፍ ያንብቡ።
አልፎ ተርፎ በርዕዮት ዓለም ፍፁም እውነት ወይንም ፍፁም ስህተት የለም ስንል ይህን አባባል በኢትዮጵያ ነባራዊ የፖለቲካ ሁኔታ ስንተገብር አንዱ መደምደምያ የጎሳ ብሄርተኝነት ፍፁም ስህተት አይደለም የሚለው ይሆናል። እኔ የጎሳ ብሄርተኝነት በተለይ የጎሳ ፌደራሊዝም ባልወድም የጎሳ ብሄርተኝነት እና ፌደራሊዝም «ክፋት» ናቸው አራማጆቹም «ክፉ» ናቸው ማለት ተገቢ አይደለም። በነሱ ቦታ ሆኖ አስቦ ተቆቁሮ ነው ወደፊት መራመድ የሚቻለው። በዚህ ረገድ «ተረት ተረት፤ ጎሰኝነት ዘረኝነት ነው» (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/08/blog-post_6.html) የሚለው ጽሁፍ ይመልከቱ።
፫) በመጨረሻ የጎሰኝነትን አደጋ (ይህ የሀገር ብሄርተኝነትንም ሊመለከት ይችላል) «የኔ ጎሳ ሰዎች ንጹ የሌሎች ክፉ» አድርገን መቁጠር ምን ያህል ሃሰት እንደሆነ አቶ ሙስታፋ አስተማሩ። በኔም በሌላም ጎሳ ደጎች እና ክፉዎች እንዳሉ ለማንም ግልጽ ነው። ጥሩ እና ክፉን የሚለየው መስመር በጎሳዎች መካከል አይደለም የሚሄደው፤ በጎሳዎች ውስጥ ነው።
አቶ ሙስታፋ እዚህ ላይ አቆሙ፤ በሃሳቡ አልቀጠሉበትም። መሰረታዊው ነጥብ ይህ ነው፤ ጥሩን እና ክፉን የሚለየው መስመር የሚያልፈው በጎሳዎች መካከል ሳይሆን በያንዳንዶቻችን ልብ መሃል ነው። እነዚህን ሁለት ጽሁፎች ያንብቡ፤ https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/blog-post_21.html እና https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/blog-post_30.html።
Thursday, 11 April 2019
የምኞት ፖለቲካ ሲቀጥል...
ግን «ጠ/ሚ አቢይ፤ ጎሰኞቹን በአዋጅ አግታቸው፤ የመንግስት መዋቅርን በሹመት ተቆጣጠር፤ የክልል ጦሮችን በአዋጅ ህገ ወጥ አድርግ፤ ወዘተ» በማለት ይህ ምኞት ሊፈጸም አይችልም። የሀገራችን የፖለቲካ ነባራዊ ሁኔታ ይህን አይፈቅድም። የጎሳ ብሄርተኛ ጎራው የ«ፖለቲካ ኃይል» አለው። ይህ ጎራ የተዋቀረ እና የተቀነባበረ ኃይል፤ በመንግስት መዋቅሮች የተሰገሰገ ኃይል፤ የገንዘብ ኃይል፤ ወዘተ ኃይል አለው። ጠ/ሚ ዓቢይ የእለታዊ ተንታኞች የሰቡትን እርምጃዎች ልውሰድ ካለ የጎሳ ብሄርተኛው ጎራ ቀውስ ያስነሳል። ጠ/ሚ ዓቢይ እንደዚህ አይነት እርምጃዎች ከመውሰዳቸው በፊት በስልት እና ዘዴ የጎሳ ብሄርተኛውን ኃይል ማድከም አለበት። አለበለዛ ነባራዊ ሁኔታን የማይመጥን እርምጃ ይሆናል እና ሁኔታውን ያባብሳል።
የጎሳ ብሄርተኛ ጎራውን ከማድከም እና ማከፋፈል አልፎ ሌላ ዋና እርምጃ ያስፈልጋል፤ ይህ የ«መሃል ፖለቲካው» ወይንም የዜግነት ፖለቲካ ጎራው እጥፍ ድርብ መጠንከር አለበት። ይህ ጎራ መዋቅር፤ ቅንብር፤ የገንዘብ፤ የመንግስት መዋቅር ከውስጥ በኔትወርክ መአስር ኃይል ሊኖረው ይገባል። የዜግነት ፖለቲካ ጎራው እንደዚህ አይነት «የፖለቲካ ኃይል» ሲኖረው የጎሳ ፖለቲካን ለመቀነስ የሚወሰዱ እርምጃዎች ሲወሰዱ የጎሳ ብሄርተኞች የሚነሳውን ሁከቶች መቋቋም ይቻላል። የጠ/ሚ ዓቢይ መንግስት በጎሳ ብሄርተኞች ሲጫን የዜግነት ጎራው ይደፍገዋል። ቀደም ተከተሉ እንዲህ ነው መሆን ያለበት።
ግን አሁን የዜግነት ፖለቲካ ጎራው ገና በቂ አልተደራጀም። ለዚህ ነው የጠ/ሚ ዓቢይ መንግስት አሁንም ከባድ ሁኔታ ውስጥ ያለው። ለዚህ ነው «ከባድ እርምጃ ውሰድ» የሚለው ሃሳብ አጉል ምኞት የሆነው። መጀመርያ የዜግነት ፖለቲካ ጎራው ማለትም «መሃሉ» ጠንክሮ መገኝነት አለበት የጎሳ ብሄርተኞቹን ጫና ለመቋቋም።
ስለዚህ የእለታዊ ተንጣኞች በሙሉ ኃይላቸው ይህ የዜግነት ፖለቲካ ጎራ መደራጀት እና መጠንከር ዋና ተልዕኮአቸው ማድረግ አለባቸው። ለሀገራችን ሰላም ቀድመ ሁኔታ ነው። ማለት ይህ ካልሆነ ምንም አይነት የፖለቲካ መሻሻል ሊመጣ አይችልም።
Monday, 1 April 2019
የህፃንነት ፖለቲካ
በአንድ በኩል ኃይል ያለው የጎሰኛ ጎራ አለ። ኃይል ማለት ኃይለ ቃል አይደለም አንዳንዶች ሁለቱ አንድ ይመስላቸዋልና። «ከተሳደብኩኝ ተሟገትኩኝ» ብሎ የሚያስብ አለ እንጂ። ኃይል ማለት ጎሰኛው በየ መንግስት መዋቅሩ ተሰግስጓል። ገንዘብ አለው። ሚዲያ አለው። መዋቅሮች አለው። ጦር አለው። አካላዊ እና ንብረታዊ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል። ፍላጎቱን በተለያየ መንገዶች ሊያስፈጽም ይችላል። መንግስት ውስጥ የተሰገሰገው በዛ አቅሙ ይጠቀማል። ጦር ያለው በሱ ይጠቀማል። ሚዲያው እንዲሁ። «ኃይል» ማለት ይህ ነው። ጎሰኛው ተጨባጭ (tangible) ኃይል አለው።
የኢትዮጵያ ብሄርተኛ ወይን አንድነት ጎራው ይህ ነው የሚባል ተጨባጭ ኃይል የለውም። መንግስት መስሪያቤት ውስጥ ያለው ቁጥሩ ትንሽ ነው መንግስት የኢህአዴግ ስለሆነ። ጦር የለውም። ሚዲያው ደካማ ነው። ምንም መዋቅር የለውም። ገና እየተደራጁ ያሉ እነ ግንቦት 7 እና ባልደራስ ነው ያሉት። ሌላ ነገር የለም። ሰለዚህ ይህ ጎራ ፍላጎቱን ለማስፈጸም አቅም የለውም። የራሱን መከላከልም አቅም የለውም። መዋቅር እና ኔትወርክ አልዘረጋም። ከሞላ ጎደል ኃይሉ እጅግ አነስተኛ ነው። አልፎ ተርፎ ይህ ጎራ ዋናው hobbyው እርስ በርስ መጠላለፍ እና መጣላት ነው።
ይህ እንደሆን እነ ጠ/ሚ ዓቢይ የሚፈሩት ማንን ነው፤ ጎሰኛውን ነው የኢትዮጵያ ብሄርተኛው? ጎሰኛውን ነው። ገጀራን ዝም ብለው ባልደራስን የሚተቹት ለምንድነው? ባለ ገጀራው ኃይል አለው ባልደራስ የለውም። ግልጽ ነው።
በዚህ ሁኔታ ጠ/ሚ ዓቢይ ላይ መውረድ ምን ዋጋ አለው?! ቢፈልግም ገጀራውን ዝም ብሎ መደምሰስ አይችልም። በዘዴ መሆን አለበት፤ ጊዜ ይፈጃል። እያሳሳቀ ነው ሊያጠፋው የሚችለው። አንዳንዶች እንደሚሉት ከባለ ገጀሮቹ አንዱ ከሆነ ጠ/ሚ ዓቢይ መነጫነጫችን ዋጋ የለውም ማለት ነው።
መፍትሄው አንድ ብቸኛው ነው፤ የአንድነት ኃይሉ «ኃይል» ማጠራቀም አለበት። ከባለ ገጀራው እጥፍ ኃይል ከሌላው ዋጋ የለውም። ይህን ኃይል እስኪያጠራቅም ደግሞ ወደ ጸብ መግባት የለበትም፤ ይህ ቀላል የፖለቲካ ስልት ነው። አንገት ደፍቶ ሁሉንም እንደ አጋር አስመስሎ የኃይል ማጠራቅም ስራውን መስራት አለበት። እንጂ ገና ምንም ኃይል ሳይኖረው ሌሎችን አምበረግጋለሁ ማለት እራስን መጥለፍ ማለት ነው።
ስለዚህ ጠ/ሚ ዓቢይ ላይ የምትወርዱበት፤ ጩሀታችሁ ዋጋ የልውም፤ ጭራሽ ዋጋ ያስከፍላል። እኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ተጨባጭ ኃይል እስኪኖረን እሱ ላይ መጮህ፤ እርስ በርስ ጸጉር መሰንጠቅ ዋጋ የለውም። መጀመርያ ተደራጅተን መዋቅሮች እና ኔትዎርኮች ዘርግተን ከዛ ብኋላ ወደ ሙግት።
(ለምን «ባለ ገጀራ» የሚለውን አሉታዊ አነጋገር ተጠቀምኩኝ? የዚህ ጽሁፍ audience የጎሳ ብሄርተኞች ላይ ኃይለ ቃል የሚጠቀሙ የአንድነት ሰዎች ናቸው። ለአንባቢው የሚመች ቃላቶችን ተጠቀምኩኝ። እነ ለማ መገርሳ ለርዥም ዓመታት «ኦነግ በሽፋን» የሆነውን የኦህዴድ ካድሬዎችን ሲያነጋግሩም እንዲሁ ብትረዷቸው ጥሩ ይመስለኛል።)
Monday, 25 March 2019
The Blame Game Does Not Work
Well, we have seen over 27 at least that this patently does not work. There was ample propaganda against the TPLF, and yet it was not because of this propaganda that people resisted and revolted. They resisted mainly for one reason - Tigray/TPLF favouritism that they experienced and perceived in their everyday lives. Note, that they experienced and perceived in their everyday lives, not what they were told by opposition media and politicians. Every protest, voiced and silent, was against this 'Tigrean domination'.
When the 'great change' came about, the change agents were not opposition politicians or media, but from within the EPRDF. This amply illustrates how weak the Ethiopian nationalist opposition was (and is). Even after 27 years, it had not mobilized into a powerful enough force to become the main change agent.
One of the reasons for this was the silly strategy of focusing entirely on the 'blame game' on negative propaganda about the TPLF, and completely neglecting the necessary task of mobilizing a powerful Ethiopian nationalist party and/or civic organization. This resulted in no one working on the task of mobilization, an extremely difficult task at that, and no results.
Unfortunately, even today, most of our politicians and commentators are stuck in this same old mentality of focusing on others, this time Prime Minister Abiy, the ODP, OLF, NAMA, etc. Yes, some of our intellectual class have come to understand that we have to focus on our own agency, but these are still few and far between. But this cannot continue like this. Things must change. A powerful, well-funded, and mature Ethiopian nationalist organization is a sine qua non for the survival of the nation, and as such deserves our full attention. Politicians, intellectuals, and commentators, I urge you to stop the blame game; I urge to stop blaming everything on 'others'; and I urge you to dedicate yourselves fully to the task of mobilizing Ethiopian nationalism.
Thursday, 21 March 2019
መንገዳችን ቢለያይም ግባችን አንድ እንደሆነ አንርሳ
ዋናው ግባችን የዜግነት ፖለቲካ (የዜግነት አስተዳደር ነው)። የጎሳ ፌደራሊዝምን አፍርሰን የብዝሃነት (multicultural and multilanguage) ፌዸራሊዥም ነው የሚበጀን ነው አቋማችን።
የዚህ ግብ ዋና ምክንያት ርዕዮት ዓለማዊ ሳይሆን መረጃ ላይ የተመሰረተ (empirical) ነው፤ የጎሳ ፌደራሊዝም የግጭት መንስኤ መሆኑን ለ28 ዓመት በአምባገነንትም በአንጻራዊ ነፃነትም አይተናል። ሚዛናዊ፤ ለዘብተኛ፤ ዓለም ዙርያ ተሞክሮ ያለው በዜግነት የተመሰረተ ክልሎችን በርካታ መብት የሚጸት ፌደራሊዝም እነዚህን ህልውናችንን ለማጥፋት የደረሱትን ግጭቶች ይቀንሳል። ለዚህ ነው የዜግነት ፖለቲካን የምንፈልገው፤ ግንቦት 7ም፤ አዴፓም፤ አብንም።
ይህን ግብ ለመምታት መደራጀት ግድ እንደሆነ ከምናልባት 50 ዓመታት ብኋላ እየገባን ይመስላል። ገንዘብ እየተሰበሰበ ነው ድርጅት(ቶች) እየተቋቋመ ነው። ይህ ግድ ነው። አሰምርበታለሁ፤ ግድ ነው። አልያ እልቂት ነው የሚጠብቀን።
ግን ወደ ግባችን ስንጓዝ የተለያየ መንገድ እንጠቀም ይሆናል። የተለያየ ስትራቴጂ እና ታክቲክ ማለት ነው። ለምሳሌ፤ አናንዶቻችን ለዘብተኛ አቋም እና በተለይ ለዘብተኛ አነጋገር እና ኮምዩኒካሽን ግድ ነው ጎሰኝነትን ለመቀነስ ብለን እናምናለን (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2019/03/blog-post_15.html)። ሌሎች ደግሞ ጠንቅረን መናገር እና መሟገት አለብን ይላሉ።
ይሁን፤ በዚህ ጉዳይ እንሟገት። ግን ግባችንን አንርሳ። አንጠላለፍ። አንዱ ግድ የሌላውን መንገድ ካልተጠቀምክ አልተባበርህም አይበል። ምን ይደረግ ሰው ነን ፖለቲካ ነው እና አቋም ይለያያል። በፖለቲካ ፍፁምነት የለም።
ግን ትብብር እና አለመጠላለፍ ግድ ነው። አለበለዛ አስፈላጊ የሆኑን ግዙፍ ድርጅቶች እና አቋሞችን ማቋቋም አንችልም፤ ይህ ማለት ግባችን አቅራቢያም አንደርስም፤ ይህ ማለት የጎሳ ፖለቲካ እንደምናየው ሀገራችንን እያቃጠለ ይቀጥላል።
Tuesday, 12 March 2019
ብራቮ ስዩም ተሾመ፤ ጸንፈኞቹ ተደራጅተው የኢትዮጵያዊነት ጎራው አለመደራጀት ነው ሀገራችንን የሚያጠፋው
፩) የ100 ሚሊዮን ብር ቡጀት
፪) አንድ ሚሊዮን አባላት
፫) አንድ ለአምስት አደረጃጀት
ይህን ካደረግን ሰላም ይሰፍናል።
«ዓቢይ ከዳን» የሚለው ትርከት ይጠቅመናል ወይ?
እንደሚገባኝ ይህ ትርክት ሁለት አላማ አለው፤
፩) የአዲስ አበባ ህዝብ እና ሌላው የኢትዮጵያዊነት ጎራውን ለማስነሳት
፪) የዓቢይ መንግስት (እና ለማ እና ኦዴፓ) ላይ ጫና መፍጠር
እስቲ «ዓቢይ ከዳን» የሚለው ትርከት እነዚህን ግቦች ሊያሳካ ይችላል ወይ ብለን እንመልከት...
፩) «ጠላቶችን» በኃይል በመተቸት ህዝቡን ማነቃቃት እና ማስነሳት ኢሳት እና ሌሎች ለረዥም ዓመታት የሞከርነው ስልት ነው። አልሰራም ነው የምለው። የፖለቲካ ለውጡ የመጣው ህዝቡ የትግሬ የበላይነት እና የህወሓት ጭቆና ስለበቃው ነው። የበቃው ደግሞ «እየተቆንክ ነው» ስለተባለ አይደለም፤ የለት ኑሮው ስለሆነ ነው። ይህ የሚያሳየን የ«ለቅሶ ፖለቲካ» ማለትም ጨቋኝን መተቸት እና ስለ ጨቋኝ ማልቀስ ህዝቡን አያስነሳም። ስለዚህ አሁንም «አቢይ ከዳን» ማለት ህዝቡን አያስነሳም። ህዝቡ አሁን የሚያስፈልገው ጠላት አይደለም፤ ጠላቱን ያውቃል።
፪) የዓቢይ መንግስት ይህን አይነት ጫና አይመልስም። መንግስቱ/ኦዴፓ ጸንፈኞቹን የሚያስተናግደው አምኖበት ነው፤ ተገዶ ነው፤ ወይንም የረዥም እቅድ ስልት ይህን የወረ ጫና ምንም አይቀይረውም። በጸንፈኝነቱ አምኖበት ከሆነ ከኃይል በቀር ምንም አይመልሰውም። ተገዶ ከሆነ አሁንም ኃይል ነው አስገድዶ የሚመልሰው። ስልት ከሆነ ደግሞ አሁንም የኛን ጫና ignore ማድረግ ግድ ይሆንበታል ግቡ እስኪሳካ።
ሰልዚህ «ዓቢይ ከዳን» የሚለው ትርክት ግቦቹን አያሟላም። እርግት ለስሜታዊ ጩኸት እና እሮሮ ይመጫል። ግን ሰከን ብለን ካሰብነው ጥቅም የለውም።
አልፎ ተርፎ ጉዳት አለው። እንደተለመደው ገመደራጀት ስራችን distract ያደርገናል። ለ27 ዓመት እየጮህን ችግራችንን ህወሓት ላይ እያሳበብን መደራጀት አልቻልንም። እነ ዓቢይ መጥተው ህወሓትን አባረሩልን። አሁንም የመደራጀት አለምቻል በሽታችን ላይ ከማተኮር ፋንታ የ«አቢይ ከዳን» ትርክት ላይ ካተኮርን የትም እንቀራለን።
ሌላው ጉዳት ለፖለቲካዊ የዋህነት/ጅልነት እጃችንን መስጠት እና ትክክለኛ ግንዛቤ ማጣት ነው። የዓቢይ መንግስት የህወሓትን አገዛዝ ለመድገም ነው ከመጀመርያ የተነሳው ማለት እጅግ የተንሸዋረረ አመለካከት ነው። ፖለቲካ የalliance ጉዳይ ነው። ከማን ጋር ነው የምንጋራው እና ጥቅማችን የሚመሳሰለው የሚለውን ነገር አብጥረን ማወቅ አለብን። እና ዓቢይን ከነ ኦነግ ጋር መቀላቀል አደገኛ የዋህነት ነው።
ስለዚህ ሰከን እንበል። ይህ ሁሉ ችግር የመታው ባለመደራጀታችን ነው። የአንድ ዓመት እድል አልፎናል። እስካሁን የኢትዮጵያዊነት ኃይሉ እና/ወይንም የአዲስ አበባ ህዝብ 100 ሚሊዮን ብር በጄት ያለው እና ሚሊዮን አባል ያለው ድርጅት መፍጠር ነበረበት። የፓርቲ አባላትን አሰልጥኖ ቢያንስ አዲስ አበባን በአንድ ለአምስት መቆጣጠር ነበረበት። በየመዋቅሩ ሰው ነአ ድር መዘርጋት ነበረበት። ይህን ሁሉ አላደርገንም። ባልማረጋችን ነው ችግሮች የቀጠሉት። አሁንም «ዓቢይ ከዳን» ብለን ማልቀስ ይህንን ግብ አያመጣም። ዋና ግባችን ላይ ብናተኩር ይሻላል።
Saturday, 9 March 2019
የአዲስ አበባ ህዝብ መደራጀት ምን ይመስላል?
ተእልኮ፤ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች መብት እና ጥቅም ለማስከበር የሚሰራ ድርጅት።
መሰረታዊ አቋሞች፤ ፩) አዲስ አበባ በአዲስ አበባ ነዋሪዎች ነው መገዛት ያለበት ፪) አዲስ አበባ ከጎረቤት ኦሮሚያ ክልል በተገቢው መልካም እና ገንቢ ግንኙነት ሊኖረው ይገባል ፫) የአዲስ አበባ ህዝብ መብቶች መከበር አለበት ፬) መካከለኛው እና ለዘብተኛው መንገድ መቅደም አለበት፤ ጸንፈኝነት ለአዲስ አበባ ህዝብ ጎጂ ነው።
የአደረጃጀት ሂደት፤ ፩) 100 የአዲስ አበባ ባለሃብቶች ሰብስቦ ከያንዳንዱ 10 ሚሊዮን ሰብስቦ መሰረት ማድረግ ፪) ሰፊ የንቃት እና የአባል መለምለም ሂደት አካሄዶ አንድ ሚሊዮን አባላት ማግኘት ፫) አዲስ አበባን በአንድ ለአምስት አሰራር ሁሉንም የህብረተሰብ እና ኤኮኖሚ ክፍል መቆጣጠር።
ስልቶች፤ ፩) አንድነት፤ የሃሳብ ልዩነቶች በአግባቡ ተንሸራሽረው መፍትሄ ይገኛሉ። ድርጅቱ ጸብ፤ ቂም፤ ሹክሹክታ ወዘተ ይጸየፋል ፪) ግልጽነት፤ ሚስጥርነት ድክመትን ያመጣል። የድርጅቱ ስራ በሙሉ የግልጽነትን ፈተና መቋቋም አለበት፤ ሚስጥር ከወጣ የሚጎዳ ድርጅት መሆን የለበትም ፫) ተሳታፊነት፤ ድርጅቱ አባላት እንዲሳተፉ መጣር አለበት አባሉ የድርጅቱ ባለበትነት እንዲሰማው።
የሰለጠነ እና የሰከነ ፖለቲካ መንፈስ፤ ለቅዋሜ የሚይመች አቋም፤ ድርጅቱ ኢ-ስሜታዊ ሆኖ የሚወስደው አቋም እና የሚያንጸባርቀው ሃሳብ ማንኛውንም ፈተና የሚቋቋሙ መሆን አለበት። ምሳሌዎች፤
፩) ልዩ ጥቅም ጉዳይ፤ «እንዴት ለኦሮሞ/ኦሮሚያ ልዩ ጥቅም ይኑር ትላላችሁ» ከማለት ምንድነው ልዩ ጥቅም ብሎ ወደ ውይይት መግባት። የኦሮሚያ ልዩ ዞን ነዋሪዎች የአዲስ አበባ አገልግሎትን ማግኘት ይችላሉ፤ የኦሮሚያ ነጋዴዎች በአዲስ አበባ እንደ ነዋሪ መነገድ ይችላሉ፤ ወዘተ አይነቱ ልዩ ጥቅም እንደ ማንኛውም ሜትሮፖሊታን ከተማ ተገቢ ነው። እስቲ ሌላ ምን ልዩ ጥቅም አለ ብሎ መወያየት ነው የድርጅቱ መንገስ።
፪) ኦሮሙማ በአዲስ አበባ፤ ከቋንቋ በላይ ኦሮሙማ የለም። ስለሆንም አዲስ አበባ በኦሮሚያ ልዩ ዞኖች በመከበቧ ኦሮምኛ የከተማዋ ሁለተኛ ቋንቋ ብትሆን መልካም ነው። በኦሮሚያ ልዩ ዞኖች አማርኛ እንደሚሰራው በአዲስ አበባ ኦሮምኛ ሊሰራ ይገባል።
፫) «የአዲስ አበባ ባልቤት ኦሮሚያ ነው»፤ ይህ አባባል ኢ-ዴሞችራሲያዊ ነው። የማንኛውም ቦታ ባለቤት ነዋሪው ነው። አዲስ አበባም ይሁን ልዩ ዞኖቹ ነዋሪዎቻቸው ናቸው የፖለቲካ ባለቤቶቹ። አለበለዛ ወደ አምባገነነት ገባን ማለት ነው።
፬) ተፈናቃዮች፤ የኦሮሞ ገበሬም ሌሎች የአዲስ አበባ እና ዙርያ ተፈናቃዮች በሙሉ ጉዳያቸው ይታይ። ማን ተፈናቀለ ምን ያህል ካሳ ተሰጠው ማን ካድሬ/መሪ በምዝበራ ተጠቀመ። ከምርመራው በኋላ እርምቶች ይደረጉ። አልፎ ተርፎ መሬት የግል ይሁን የሚለውን አቋም ድርጅቱ ያራምድ። መሬት የግል ቢሆን ኖሮ መፈናቀል የሚባል አጸያፊ ነገር አይኖርም ነበር። አልፎ ተርፎ አዲስ አበባ ዙርያ ያለው ኦሮሞ እና ሌሎች ገበሬዎች እጅግ ሃብታም ይሆኑ ነበር መሬ ታቸውን በመሸጥ። መንግስት 100,000 ብር ካሳ የሚሰጠው ግለሰብ የገበያ ዋጋውን አንድ ሚሊዮን ብር ሊሰጠው ይችላል።
የአዲስ አበባ ህዝብ ማለት...
ሳያርስ ሳይዘራ የክረመ ገበሬ አዝመራ ሳይኖረው እግዚአብሔርን የሚያማርር።
አትንቶ የማያውቅ ተማሪ ፈተናውን ሲወድቅ አስተማሪውን የሚወቅስ።
ወዘተ።
የአዲስ አበባ ህዝብ (ከነ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ) ለዓመታት በትንሿ ህወሓት የተገዛው የራሱን የቤት ስራ ስላልሰራ ነው። ይህ የቤት ስራ ተደራጅቶ ለራስ መብት መቆም ነው።
ካሁን ወድያ የአዲስ ህዝብ ካልተደራጀ ለሚደርስበት ጉድ ከራሱ በቀር ማንም ጥጠያቂ አይኖርም። የአምስት ሚሊዮን ህዝብ ከተማ መቶ ሚሊዮን ብር በጀት፤ አንድ ሚሊዮን አባል ያለው ድርጅት ማቋቋም ካልቻለ በቅኝ ግዛት መገዛት ይገባዋል አይቀርለትምም።
Friday, 1 March 2019
የአዲስ አበባ ጉዳይ እና የሃላፊነት ፖለቲካ
ይህ ሁኔታ ምክንያት አለው፤ የኢትዮጵያዊነት ጎራው በአብዮቱ ጀምሮ እርስ በርስ ተገዳድሎ ልሂቃኑ እራሱን አጥፍቶ እስካሁን አላገገመም። (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/1.html፤ https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/2.html፤ https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/3.html፤ https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/4.html)። ቢሆንም በዚህ አካሄድ መቀጠል አይቻልም። ሌሎችን «ፍላቶእ እና መብታችንን አስከብሩልን» ብለን እየለመንን መቀጠል አይቻልም።
አሁን የሚያስፈልገን ከ«ለቅሶ ፖለቲካ» ወጥተን፤ ከህጻንነት እና ብሽተኝነት ወትጠን ወደ «ሃላፊነት ፖለቲካ» መግባት አለብን። ግድ ነው፤ አማራጭ የለም። እነ ለማ ይሁን አቢይ ይሁን ህወሓት ይሁን ግንቦት 7 ይሁን አብን ወዘተ እንዲህ አድርጉልን ብለን መለመን አይቻልም። ካሁን በኋላ ሁላችንም «ይህ ይሁን»፤ «ይህ ይደረግ»፤ «እከለ ይውደም» ወዘተ ከማለት ወደ «እኔ ይህን አደርጋለው» የሚለው አመለካከት መግባት አለብን። ልመና በቃ፤ የራሴን እጣ ፈንታ እራሴ ወስነዋለው ወደሚለው መግባት አለብን።
የአዲስ አበባ ጉዳይ የዚህ የአስተሳሰብ እና ተግባር ለውጥ አስፈላጊነት በደምብ ይገልጻል (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_97.html)። ልሂቃኖቻችን እስካሁን እነ ኢህአዴግን፤ ህወሓትን፤ ኦዴፓን፤ የኦሮሞ ብሄርተኞችን፤ አዴፓን፤ ጥ/ሚ አቢይን፤ ፕሬዚደንት ለማን፤ ወዘተ እባካችሁ እንዲህ እንዲያ አድርጉ አታድርጉ እያሉ ለው ዓመት ይጮሃሉ። ግን አንድ የሚባል የአዲስ አበባ ህዝብን ጥቅም የሚያንጸባርቅ እና ለማስከበር የሚሯሯት ድርጅት የለም? የአዲስ አበባ ህዝብ ህልውናውን ለሌሎች ሰጥቶ ሌሎቹ የሚፈልጉትን ሲአደርጉ ልሂቃኑ ያለቅሳል! ይህ ምን ማለት ነው? የአዲስ አበባ ህዝብ እራሱን አደራጅቶ ፍላጎቱን እና መብቱን ዘርዝሮ ማስከበር ካልቻለ እነዚህ የማይወክሉት ተቋሞች የፈለጉትን ያደርጋሉ። ይህ እኮ እጅግ basic የሆነ ነገር ነው።
እስከ ዛሬ የኛ ልሂቃን እና ሚዲያ ይህን መሰረታዊ ጉዳይ ትተው በማልቀስ እና መለመን ነው የዋሉት። የራሳችንን ጥፋት (አለመደራጀት) ላለማየት ትብሎ ህልውናችንን አደጋ ውስጥ ከትተናል! ይህ ሁሉ ችግር ስላልተደራጀን ነው እና እንደራጅ ከማለት ሌሎች ስለሚያደርጉት እናለቅሳለን። ይህ ለቅሶ ምንም ለውጥ አላመጣም አያመጣምም። ህዝባችን በንዴት እንዲደራጅ አላደረገም። ይባስ ሌሎች ላይ ጣት በመጠቆም የራሳችንን ጥፋት እንዳናይ ስበብ ሆኖናል። ጉርጓዳችንን ይበልጥ እንድንቆፍር አድርጎናል።
አሁን ግን አንዳንዶች መራራ የሆነውን መድሃኒት ውጠን ወደ ፊት መራመድ እንዳለብን የገባቸው ይመስላል።
ከዚህ ከኢሳት ዝግጅት የአዲስ አበባ ህዝብ መዋናነት መደራጀት አለበት ትባለ። ያለመደራጀታችን ጥፋታችንን አመንን ማለት ነው፤ ይህን ማመን ነው መራራው መድሃኔት። ካመንን በኋላ ሙሉ አቅማችንን ወደ መደራጀት ስራ ማሰለፍ ነው ያለብን። ካሁን ወድያ አንዳች የልሂቃን እና ሚዲያ ደቂቃ በእሮሮ፤ ለቅሶ፤ እና ልመና መጥፋት የለበትም። ሙሉ አቅማችን ወደ መደራጀት።
ምን ማለት ነው የመደራጀት ስራ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/blog-post_18.html)? ብዙ ሚስጥር የለውም፤ የህዝብ የማህበራዊ እና ፖለቲካዊ መደራጀት ለሺዎች ዓመታት የተደረገ ነገር ነው። የአዲስ አበባ ህዝብ «የአዲስ አበባ ህዝቦች ድርጅት» ያስፈልገዋል። የዚህ ድርጅት (ድርጅቶች) ተእልኮ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን ጥቅም ማስከበር ነው። ቀላል ተእልኮ ነው፤ ሌላ ጣጣ አያስፈልገውም። ድርጅቱ በርካታ (በመቶ ሺዎች የሚቆጠር) አባላት ያስፈልጉታል። ባለ ሃብቱ በደምብ መሳተፍ አለበት። ስብሰባ፤ ሰርቬ፤ ምርጫ፤ ወዘተ የሚያካሄድ መሆን አለበት። አባላቶቹ በየ ማህበራዊ ዘርፍ፤ በየ መስርያቤት፤ በዬ ሰፈሩ የሚሰሩ እና የሚኖሩ መሆን አለባቸው። ድርጅቱ ሰፊ ኔትወርክ ኖሮት «የሚፈራ» ማለትም አቅም ያለው መሆን አለበት። በተለያዩ የከተማው ጉዳዮች፤ መብራት፤ ውሃ፤ መንገድ፤ ደህንነት፤ ጤንነት፤ መፈናቀል፤ ውክልና፤ ወዘተ የሚሰራ መሆን አለበት። በዴሞክራሲያዊ መልኩ የአባላቱን ፍላቶ የሚያውቅ፤ የሚያስከበር እና የሚወክል መሆን አለበት።
ይህ ድርጅት ሲኖር፤ ዛሬ ቢኖር ስለ አዲስ አበባ ያለው ጭቅጭቅ አይኖርም ነበር። ሁሉም ተሳታፊዎች የአዲስ አበባ ህዝብ ፍላጎትን አበጥረው ያውቃሉ። የሁሉም አቋም ሰልሚታወቅ የፖለቲካ ድርድሮች በግልጽ እና በጽጋ ይካሄዱ ነበር። የለገጣፎ ሰዎች አይፈናቀሉም ነበር። ጉዳዩ ገና ሲነሳ ድርጅቱ ተሳትፎበት ድርድር ተደርጎበት በሰላም በሁሉም የሚያስማማ መልኩ ይፈታ ነበር። የኦሮሚያ «ልዩ ጥቅም» ጉዳይም እንዲሁ። ወካይ ድርጅት ቢኖርን «ልዩ ጥቅም» ብለን አናለቅስም ነበር። ድሮውኑ ተደራድረን የልዩ ጥቅም ትርጉም ላይ ተስማምተን ነገሩ በሰላም ይወሰን ነበር። ወዘተ።
የአዲስ አበባ ችግር የመጣው በህወሓት ምክንያት አይደለም። በኦሮሞ ብሄርተኞች ምክንያት አይደለም። መሰረታዊ ችግሩ የአዲስ አበባ ህዝብ እርስ በርስ ተስማምቶ አለመደራጀቱ ነው። ይህን አምነን አንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ለቅሶ እና ልመናችንን ትተን ሙሉ አቅማችንን ወደ መደራጀት ማዋል አለብን። አለበለዛ በየበታችንነት እና ተገዥነት ስሜት እንደተገዛን እንቀጥላከን። መገዛት ማለት የራስን እጣ ፈንታ ለሌሎች መተው እና በራስ ህይወት ሃላፊነት አለመውስውድ ነው። ይህ ላለፉት በርካታ ዓመታት ጉዞአችንን ይገልጻል።
Friday, 22 February 2019
የጅልነት ፖለቲካ
ለነገሩ ይህ (ይቅርታ አድርጉልኝ) የጅልነት ፖለቲካ አካሄድ ነው። የሚበጃቸው የነበረው የአዲስ አበባ ህዝብን ሳያስቀይሙ ሳይነሳሱ ቀስ ብለው ውስጥ ለውስት ስራቸውን መስራት ነበር። ግን የጡንቻ አካሄድ መርጠው የአዲስ አበባ ህዝብን ያናድዳሉ እና ተነስቶ እንዲደራጀና መብቱን እንዲያስከበር ያደርጉታል።
ይህ ነው የጅልነት ፖለቲካ። ግን ምና ያመጣሉ ነው ይህን የሚያደርጉት! የአዲስ አበባ ህዝብ እና ጠቅላላ የኢትዮጵያ ብሄርተኛ ጎራው ምን ያመጣል ነው። ስለዚህ ማን ነው ጅሉ። እኛ ነን።
ለገጣፎ ለሚከሰተው የአዲስ አበባ ህዝብ ሃላፊነት አለብን
በህወሓት ዘመን ደግሞ ለ«ልማት» እና «ኢንቬስትሜንት» ተብሎ የበርካታ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ንብረት በምንግስት ተነጥቋል። አንዳንዱ ባዶውን ቀረ። አንዳንዱ እጅግ አነስተኛ ካሳ ተሰጥተው። ሌላው ከከተማ ውጭ ባዶ መሬት ላይ ተወረወረ። ይህ ሁሉ ሲከሰት የአዲስ አበባ ህዝብ (በጅምላ ለማውራት) ምንም አላደርገም። እርግጥ መጮህ እና መደራጀት ሊያሳስር እና ሊያስገድል ይችል ነበር። ግን ገንዘብ ሰብስቦ ለተፈናቀሉ ተጎጂዎች መስጠት ምንም ቅጣት አያስቀጥልም ነበር። ከኔ ጀምሮ አንዳችን ይህን አላደረግንም። የባለንጀሮቻችንን ህምም ዝም ብለን ተመለከትን።
ዛሬም እንዲሁ። ለገጣፎ የሚኖሩ ወንድም እህቶቻችን ቤቶቻቸውን እያጡ እያለ ከመጮ ሌላ ምንም አናደርግም። አንረዳቸው፤ አንደራጅ። ትንሽ ጉዳዩ ያናደደን ካለን መንግስት ላይ ጣታችንን እንጠቁማለን!
ከዛ ይልቅ እራሳችን ላይ ነው መፍረድ ያለብን። የአዲስ አበባ ህዝብ ለባለንጀራው በአግባቡ ቢራራ እስካሁን ተደራጅቶ የህ አይነት ግፍ እናይከሰት ማድረግ ይችል ነበር (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2019/02/blog-post_22.html)። ግን አላደረገውም፤ አላደረግነውም።
ስለዚህ ጥፋቱ በዋነኝነት የኛ የአዲስ አበባ ህዝብ ነው። ጣቶቻችንን ሌሎች የማይሰሙን ላይከመጠቆም ስራችንን ሰርተን ተደራጅተን እርስ በርስ ብንጠባበቅ ለሁሉም፤ ለጎጂዎቻችንም ለመላው ሀገራችንም፤ ጠቃሚ ነበር። ለችልተኛችን ንስሃ ገብተን ወደ ስራ እንግባ። ሌላ መፍትሄ የለም!
የአዲስ አበባ ህዝብ ካልተደራጀ ለገጣፎ ይደጋገማል
የለገጣፎ ነዋሪዎች መፈናቀል ድርጊት በምንም ሚዛን እጅግ አሳፋሪ እና ለሁላችንም ጎጂ መሆኑ ግልጽ ያልሆነለት... ይቅርታ አድርጉልኝ እና የድሮ የፖለቲካ ደንቆሮ ነው።
ሆኖም እንደዚህ አይነት መፈናቀል እና ተመሳሳይ ክስተቶች ለ27 ዓመታት ሲካሄዱ ቆይተዋል። ወደ ኋላ ከሄድንም ደርግ የ«ከበርቴዎችን» ቤት እና መሬት አለ ፍትህ፤ ሚዛን፤ እና ርህራሄ ቀምቷል።
የአዲስ አበባ ህዝብ ይሁን ሁሉ ያትዋል አሳልፏልም። በርካታ ሰለቦች አይተናል። ግን አንዴም ጣታችንን አንስተን እንርዳችሁ፤ ይህ ክስተት እንዳይደገም ተደራጅተን ለእርስ በርሳችን እንቁም ብለን አናቅም። ይሉቅንስ ወይ ተባብረናል፤ አንገታችንን ደፍተናል፤ ወይንም ለተጎጂዎች ከመራራት ፋንታ ፈርደንባቸዋል።
በዚህ ምክንያት አሁንም ባለንጀሮቻችን፤ ጎረቤቶቻችን፤ ወንድም እህቶቻችን እጣ ፈንታቸው ከሆነ መሬት እና ቤቶቻቸውን ይነጠካሉ። ዛሬ ለገጣፎ ነው ነገ ሌላ ቦታ። የኦሮሚያ መንግስት ተወካዮች ይቀጥላል ብለዋል።
የአዲስ አበባ ህዝብ እንደዚህ አይነት ኢ-ሰባዊ ድርጊቶች እንዲቆሙ ከፈለገ ከመደራጀት በስተቀር ምንም ማድረግ አይችልም። መቾህ፤ ቂም መያዝ፤ ማዘን ወዘተ ብዙ ዋጋ የለውም። አንድ እና አንድ ምርጫ ብቻ ነው ያለው፤ መደራጀት።
ምን ማለት ነው መደራጀት? መቼስ ፖለቲከኞቻችን ሊያውቁ እና ሊያስተምሩን ይገባል ግን እስቲ ለኛ ብዙሃን በምሳሌ መልኩ ልዘርዝረው። ልብ፤ እውቀት፤ እና ገንዘብ ያላቸው «የአዲስ አበባ ዜጎች ድርጅት» የሚባል ያቋቁማሉ። የድርጅቱ ተዕልኮ የአዲስ አበባ ህዝብን ፍላጎትን እና ደህንነትን ለማስከበር መሟገት ይሆናል። ድርጅቱ በየ ቀበሌው፤ በየ ህዝብ ዘርፍ (ነጋዴ፤ ሞያተኛ፤ አስተማሪ፤ እናቶች፤ ወዘተ) አባላት እና ገንዘብ ይመለምላል። ትምሕርት ያስተምራል። በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አባላት ይሰበስባል። እነዚህ አባላት በዬ ህብረተሰብ ክፍል እና መንግስት መስርያቤቶች ያሉ ይሆናሉ እና በይፋም በህቡም ለድርጅቱ እና ለአዲስ አበባ ህዝብ ተጽዕኖ ማድረግ የሚችሉ ይሆናሉ። እንድነ ለገላፍቶ አይነት ክስተት እንደሚካሄድ ሲታወቅ ይህ ድርጅት በሁሉ ዘርፍ ተጽዕኖ ያደርጋል። እንደዚህ አይነት የማፈናቀል እና ሌላ ህዝቡን የሚጎዳ እቅድ እንዳይታሰብ ያደርጋል።
አሁን የደረደርኩት ምሳሌ አዲስ እንዳልሆነ መቼስ ሁላችንም እናውቃለን። ዓለም ዙርያ ለሺ ዓመታት ፖለቲካ በዚህ መልኩ ነው የሚካሄደው። እንኳን የሰላም ፖለቲካ የጦር/ኃይል ፖለቲካም እንዲሁ ተደራጅቶ ነው የሚሰራው። ስለዚህ የአዲስ አበባ ህዝብ ማድረግ ያለበት የተለየ እና በተለየ መልኩ ከባድ ነገር አይደለም። ለአካባቢ ጥቅም መደራጀት ቀላል እና የተለመደ የሰው ልጅ አካሄድ ነው።
ታድያ ለምንድነው የአዲስ አበባ ህዝብ እስካሁን ያላደረገው? በነ ግምት የአዲስ አበባ ህዝብ ይሆን ሁሉም የኢትዮጵያ (ሀገር) ብሄርተኞች ከ66 አብዮቱ እና ሽብሮቹ እስካሁን አላገገመም። አብዮት ተከታታይ ትውልዶች እንደሚያተፋ ይታወቃል በሀገራችንም እንዲሁ የኢትዮጵያ ብሄርተኛ ጎራውን እርስ በርስ አፋጅቶ ድምጥማጡን አጥፍቷል። ስለዚህ የአዲስ አበባ እና ጠቅላላ የኢትዮጵያ ብሄርተኛ ፖለቲካ አሁንም እጅግ ደካማ ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_38.html)።
ይህ እንደሆነ እውነታው የአዲስ አበባ ህዝብ ካልተደራጀ እንደ ለገጣፎ አይነት ኢ-ሰባዊ ክስተቶችን ማቆም እንደማይቻል ነው። የአዲስ አበባ ህዝብ ደጋግሞ ይረገጣል። ከመደራጀት በቀር ምንም መፍትሄ የለም። ለመድገም ያህል እሮሮ ማሰማት፤ ማልቀስ፤ መርገም፤ መለፍለፍ ወዘተ ዋጋ የለውም። ከባዱ የመደራጀት ስራ ግድ መሰራት አለበት።