Thursday 18 October 2018

ኢትዮጵያን የሚገላት የአንድነት ኃይሉ ነው (ክፍል 4)

በ1983 ደርግ ሲፈርስ እና ሻዕብያ፤ ህወሓት እና ኦነግ ስልጣን ሲይዙ እኛ ኢትዮጵያዊ ብሄርተኞች («አንድነት ኃይሎች») ደነገጥን። ሁለት በፍፁም ያልተበቅናቸው ክስተቶች፤ አጥፊው ደርግ ፈራረሰ እና የትም አይደርሱም የሚባሉት «ሺፍቶቹ» ስልጣን ያዙ! እኛ በአብዮት እና ሽብር የተጎሳቆልን ተመልካቾች (debilitated bystanders) ሆነን ቀረን።

ሆኖም የተወሰነ ነፃነት ሰፍኗል ብለን የፖለቲካ እንቅስቃሴ ጀመርን። ያው የእርስ በርስ አለመስማማት ጠባያችን እንደገና እንቅፋት ሆነን። EDU, COEDF, AAPO, AEUP, MEDHIN, ቅንጅት, Ethiopian Review, Ethiopian Register, Ethiopolitics, EEDN፤ ሁሉም በእርስ በርስ ግጭት ተንገላተው የፈረሱ ተቋሞች።

እኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኖች ተባብረን የዜግነት መዋቅሮች መዘርጋት ባለመቻላችን ሜዳውን ለሌሎች ተውን። ግን ጥልቁ ችግር በኢትዮጵያዊነት የሚያምን ህዝብ ብዙ መኖሩ ነው። ይህ ብዙሃን ባይኖር እና ሁሉም በጎሳ ድርጅቶች ቢወከል ሁሉም ተወክሏል እና መዋቅራት አሉት ማለት ይቻላል። ግን እንዲህ አይደለም። በኢትዮጵያዊነት የሚያምን ብዙሃኑ ብዙ ልሂቃኑ እና ተቋሙ ትንሽ እና ደካማ። ይህ ነው የኢትዮጵያ distorted ፖለቲካ።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!