Saturday 30 March 2019

የመሬት ይዞታ፤ የቅርብ እና ሩቅ ሚና ጥያቄዎች

እንደሚታወቀው መሬትን የግል ማድረግ ኤኮኖሚውን ይረዳል። አሁን ደግሞ በመጠኑ የኤኮኖሚ አጣብቅኝ ውስጥ ነን። ዛሬ መሬት የግል ቢሆን መቼ እና ምን ያህል ነው ኤኮኖሚው ላይ ውጤቱ የሚታየው?

መሬት የግል ማድረግ የፖለቲካ ችግር እንዳለው ይታወቃል ስለዚህም ዛሬ priority አይደለም። ሆኖም እንደ አማራ ክልል አይነቱ ዳር ዳሩን እያለ እንደሆነ ይታወቃል። ለምሳሌ የ25 ዓመት ኪራይ (ሊስ) በህግ እንዲስተናገድ አድርጓል። ይህን የ25 ዓመት ኪራይ ወደ 1000 ዓመት ድርስ እንዲፈቀድ ቢደረግ እና ቂራዩን መሸጥ መለወጥ ቢፈቀድ de facto መሬትን የግል አደረገ ማለት ነው። ይህ በአማራ ክልል ወይንም ማንኛውም ይህን አለ ብዙ ፖለቲካዊ ችግር ማድረግ የሚችል ችግር ምን ያሀል የኤኮኖሚ ጥቅም በቅርቡ ሊያመጣለት ይችላል?

አዲስ አበባ እንዲሁ መሬት ከግለሰብ ለ1000 ዓመት መከራየት ይቻላል ኪራዩም መሸጥ መለወጥ ይቻላል ቢባል ምን ያህል ይሆን ጥቅሙ? በመፈናቀል እና መጠቀም ያለው ሚና እሳ?

ጥልፍልፍ ጥልፍልፍ...

https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_21.html

ብርሃኑ ነጋ፤ እስክንድር ነጋ፤ በለጠ ሞላ (አብን)፤ ኤርሚያስ ለገሰ፤ «የአቢይ ደጋፊዎች» አንድ የሚያደርጋቸው የዜግነት ፖለቲካ መሻታቸው ነው። ይህ ታላቅ አንድነት ነው። ልዩነቶቻቸው ከታክቲክ ብዙ አያልፍም። ግን በዙዎቹ ለጋራ እምነት እና ጥቅማቸው ጠንክረው አብረው ከመስራት ፋንታ እርስ በርስ በትናንሽ ጉዳይ መቃረን እና መጣላት ይመርጣሉ። እንሆ አሁንም ግዙፍ የአንድነት ድርጅት አላቋቋምንም! ይህ ነው የመጠላለፍ ፖለቲካ definition።

ንስሀ ያስፈልገናል። የመጠላለፍ ደዌ እንዳለን አምነን ልናስወግደው ይገባል። የ40 ዓመት የህፃንነት ፖለቲን አቁመን ወደ ጥንት አባቶቻችን ብስልነት እንመለስ።

Thursday 28 March 2019

ብራቮ ሰይድ ኑሩ፤ ገበሬዎቻችን መሬት መሸጥ/መግዛት መቻል አለባቸው!

አቶ ሰይድ ገበሬዎቻችን መሬት መሸጥ/መግዛት መቻል እንዳለባቸው በደምብ አድርገው እኛ ብዙሃን በሚገባን ቋንቋ አስረድተዋል። ይህ ጉዳይ በመገናኛ ብዙሃን ታላቅ መነጋገርያ ሊሆን ይገባል። የኤኮኖሚ ጥቅሙ ሊካድ አይቻልም። የስነ ልቦና ጥቅሙም እንዲሁ ገበሬው ከእስር ቤቱ ይፈታልና፤ የማንኛውም አምራች መብት ይኖሯልና። የፖለቲካ ጥቅሙም ግዙፍ ነው። የግጭት መንስኤ የሆነውን የጎሳ ፕለቲካን ይበርዘዋል። ሚዲያዎች፤ ይህን ጉዳይ front and centre አድርጉት።

ስለዚህ የጻፍኳቸው ጽሁፎች፤ ጠቃሚ ከሆኑ...

https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2017/05/our-radical-politicians-land-to-ruler.html (English)

https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_47.html (አማርኛ)

https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_15.html

https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/blog-post_94.html

https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/12/blog-post_10.html


Overtures to the TPLF

Some Amhara nationalists, in the wake of a perceived rise in the power of Oromo nationalism, are making overtures to the TPLF or 'Tigray' for a possible alliance to combat Oromo nationalism. I'm sorry, but this is the height of silliness! It simply repeats our decades long practice of negative-sum politics, as disastrous in the long-term as it is appealing in the short.

First, those who support citizenship federalism should not need the TPLF or anyone else to combat ethnic nationalism. The very fact that some think they need the help illustrates the fundamental problem - the lack of a large and powerful citizenship politics organization. If we had a coherent movement concomitant to our grassroots support, then we would have easily come to a favourable agreement with ethnic nationalists. But our lack of tangible political power makes us flail around looking for help anywhere we can get it, thereby repeatedly building our political house on sand. Inevitably our temporary alliances and escapes end and we're back at throats of former allies.

Second, the TPLF and, dare I say, a significant portion of the Tigrean elite is in the midst of an identity crisis imposed upon them by unfortunate historical circumstances. The advent of Communism, the 1974 revolution, the Dergue's terrible misgovernance, etc., led to the birth of a TPLF with an outlook that stood firmly against the long term interests of Tigreans. Tigray, being a small, industrious, region, stands to benefit from a citizenship based federalism, a multicultural and decentralized federalism but one in which the citizen is primary. Ethnic federalism is completely against the interests of Tigray, because that would result, more or less, in Tigreans not being able to freely live and work outside their region. Yet the TPLF and most Tigrean intellectuals still support ethnic federalism! This is the problem that the rest of us Ethiopians, Ethiopian nationalists and even Amhara nationalists have to tackle, through persuasion and discussion, of course. This will be a long process. However, we should not abort this process by allying with the TPLF in an artificial power play.



Wednesday 27 March 2019

ብራቮ ኤልቲቪ!

እንደዚህ ተቃራኒ አስተያየቶች አብሮ ማምጣት በጣም አስፈላጊ ነው። ነጣጥሎ ቃለ ምልልስ መስጠት ገንቢ አይደለም፤ ትችት እና እሮሮ ብቻ ነው የሚሆነው። አሁን ግን የሀገር ግንባታ ጊዜ በመሆኑ ሃሳብ በሰላሰል እና መፈጨት አለበት። ቀጥሉበት!

Monday 25 March 2019

The Blame Game Does Not Work

Along the way, some of our politicians, intellectuals, and commentators seem to have latched on to the silly idea that with enough negative commentary, they can mobilize a political force to fulfill their aims! "If we criticize Abiy enough, we'll get people to take action against him or he'll be forced to change,", they say.

Well, we have seen over 27 at least that this patently does not work. There was ample propaganda against the TPLF, and yet it was not because of this propaganda that people resisted and revolted. They resisted mainly for one reason - Tigray/TPLF favouritism that they experienced and perceived in their everyday lives. Note, that they experienced and perceived in their everyday lives, not what they were told by opposition media and politicians. Every protest, voiced and silent, was against this 'Tigrean domination'.

When the 'great change' came about, the change agents were not opposition politicians or media, but from within the EPRDF. This amply illustrates how weak the Ethiopian nationalist opposition was (and is). Even after 27 years, it had not mobilized into a powerful enough force to become the main change agent.

One of the reasons for this was the silly strategy of focusing entirely on the 'blame game' on negative propaganda about the TPLF, and completely neglecting the necessary task of mobilizing a powerful Ethiopian nationalist party and/or civic organization. This resulted in no one working on the task of mobilization, an extremely difficult task at that, and no results.

Unfortunately, even today, most of our politicians and commentators are stuck in this same old mentality of focusing on others, this time Prime Minister Abiy, the ODP, OLF, NAMA, etc. Yes, some of our intellectual class have come to understand that we have to focus on our own agency, but these are still few and far between. But this cannot continue like this. Things must change. A powerful, well-funded, and mature Ethiopian nationalist organization is a sine qua non for the survival of the nation, and as such deserves our full attention. Politicians, intellectuals, and commentators, I urge you to stop the blame game; I urge to stop blaming everything on 'others'; and I urge you to dedicate yourselves fully to the task of mobilizing Ethiopian nationalism.

"Naive Abiy Supporters..."

A lot of our political chattering class, and dare I say the general population, has become apprehensive, suspicious, or even downright hostile towards Prime Minister Abiy Ahmed. That's fine, but as usual, the conversation around this issue is neither intelligent nor constructive - it has devolved into a schoolyard argument over Maradona vs Pele or some such silliness.

I submit the following hopefully intelligent and constructive approach to the issue. Either Abiy is:

1) Competent but under severe pressure from ethnic nationalists who hold significant power within his party and Oromia Regional government
2) Under severe pressure but incompetent
3) A secret Oromo ethnic nationalist who's been fooling us all along

Which of the above really does not matter! Because no matter which is the case, the only way forward is for the Ethiopan nationalist political class to organize itself into a powerful, well funded, and tactically intelligent movement. This movement must have the following characteristics:

1) Aim to reduce ethnic nationalism
2) Aim to bring about a citizenship based constitution
3) Reason that ethnic federalism is a not an ideological problem but a practical one - it has been empirically proven to be a constant source of conflict and might cause a failed state
4) Take very moderate and measured positions so as to avoid being a target, and to avoid costly mistakes
5) Cooperate fully and more importantly show and communicate that it is cooperating fully with the government
6) Engage a competent and even clever communication strategy
7) Engage a mass membership and infiltrate all institutions and regions in the country, as all political lobbies do.

Now let's see how this movement can reduce conflict and bring about a peaceful citizenship-based politics no matter what Abiy is:

1) Abiy is competent but under severe ethnic nationalist pressure - the Ethiopian nationalist organization will bolster him from the other side and strengthen the centre, and this will help Abiy overcome the ethnic nationalists.

2) Abiy is incompetent and under severe pressure - the Ethiopian nationalist organization will tangibly help Abiy manage the pressure and provide candidates to work within Abiy's government. It will also present itself or an associate party as a competent alternative to Abiy in the next election.

3) Abiy is a secret ethnic nationalist - the Ethiopian nationalist organization will slowly and tactfully force him towards its agenda or wrest power away from him.

So no matter what, the only and necessary solution to Ethiopia's current political predicament is for the Ethiopian nationalist political camp to overcome its disastrous 50 year history and organize itself into a serious movement.

If this is the case, why are we spending so much time talking about whether to love or hate Abiy? When whether we love or hate him doesn't matter in the end?

I submit that this is a continuation of Ethiopian nationalist 'opposition' politics of the past 40 years. We are woefully disorganized. From the EDU to the Socialists to Kinijit, we have an endemic disease of infighting. While the likes of the EPLF and TPLF formed strong, competent, and well-funded (raising tens of millions of dollars per year), we spent our time nitpicking our differences and blaming Ethiopia's problems on our 'enemies', instead of taking responsibility for our failures. So, even today, in order to avoid facing our failures, in order to avoid facing our shame, we focus on playing the blame game. Blame Abiy, or blame ethnic nationalists, or blame Ginbot 7, or blame NAMA, and on and on.

But it appears things have come to a head. The TPLF is gone, the field is open, but severe conflict seems around the corner. We Ethiopian nationalists simply have to organize ourselves now. We have to overcome our decades long disease of disorganization.

So, intelligent and constructive political commentators, intellectuals, and politicians, I again humbly ask you to refrain from the silly discussions around Abiy, and dedicate every ounce of your energy towards creating the huge Ethiopian nationalist political/civic machine that our country needs now. No more picking fights with each other. No more blame game. Focus entirely on the task at hand. Otherwise we have no one to blame but ourselves!

Sunday 24 March 2019

የመጠላለፍ ፖለቲካ ቁጥር 1,999,999

መቼስ እኛ ጎሰኝነትን እንጠላለን ህገ መንግስቱ ይቀየር የምንለው የመጠላለፍ ፖለቲካ ባለሙያዎች ነን። ህወሓት የሀገራችን 6%ም የማይሆን ድጋግ ይዞ ለ27 ዓመት ሲገዛን እንኳን መታገል መደራጀትም አቅቶን ቆየን። በተለይ አማራ ክልል ውስጥ የህወሓት ሰዎች አንድ ለመቶ ሺ ሆነው እንደፈለጉት ሲጫወቱብን ማንም ሳናደርግ ቆየን። በዲያስፖራ ያለነውም ከሳንቲሞች በቀር ማዋጣት አልቻልንም ምንም ቁም ነገር ያለው ድርጅትም አልነበረንም። ለማስታወ ያህል የነ ሻቢያ እና ህወሓት ዲያስፖራዎች በዓመት በአስርት ሚሊዮን ዶላር ነበር ለአቋማቸው የሚያዋጡት።

ዛሬም አክራሪ ጎሰኛው ህልውናችንን አደጋ ላይ እያደረገ እኛ እርስ በርስ እንጠላለፋለን። አሁንም የአማራ ብሄርተኞች እና «አንድነት ኃይል» ወዘተ ፉክክር አልበረደም። አቋማችን አንድ ሆኖ፤ «ህገ መንግስቱ ይቀየር» «ጎሰኝነት ይቅር»፤ እንኳን መተባበር በሰላም አብረን መኖር አልቻልንም። ስለ isolated attack አይደለም የማወራው። በየ አይነቱ ሰው አለ። እንደዚህ አይነት ነገሮች ይከሰታሉ። አብን አደረገው አይባልም። ሆኖም እንደዚህ አይነት ድርጊቶች pattern ሆኖዋል። በሁለቱም ወገን ያለው የአለመተባበርን መንፈስ የሚያንጸባርቅ መንፈስ።

አንዱ መፍትሄ ቀላል ነው፤ እንዲህ አይነት ክስተት ሲፈጠር ሁሉም ወገኖች በይፋ ጮክ ብለው ማውገዝ አለባቸው። ይህ ፖለቲካ 101 ይመስለኛል። ደጋፊዎችህ መስመር እንዳይስቱ፤ ሌሎች ባንተ እንዲተማመኑ የሚደረግ ነገር ነው። የጸብ መንፈስን በህብረት መንፈስ መተካት ነው። ማውገዝ ድርጊቱን እኔ ነኝ ያደረግኩት ብሎ ማመን አይደለም፤ ይህ የታወቀ ነገር መሆኑ ሁላችንም እንደምንረዳ ተስፋ አለኝ። ደግሞ ስለተወገዘ ደጋፊ አጣለhu የሚል እንደሌላ ተስፋ አለኝ። አብንን ማንም outflank የሚያደርግ ድርጅት የለም። ማለት አብን ያወገዘው የትም መሄጃ የለውም። ስለዚህ አብን እንደዚህ አይነት ድርጊቶችን ቶሎ ብሎ ማውገዝ አይጎዳውም እጅግ ይጠቅመዋል።

የአንድነት ኃይል ደጋፊዎችም እነ አብንን እንተው። ማለት ከተቸን ወንድማዊ ምክር በያዘ መልኩ ነው እንጂ መበሻሸቁ ያብቃ። አሁን ቁልፍ ጊዜ ነው፤ እንደ ጥንት አባቶቻችን የሰለጠነ እና የሰከነ ፖለቲካ አሁን ግድ ነው። የዓመታት ህጻንነታችን ለውቅቱ አይበጅም።


Thursday 21 March 2019

መንገዳችን ቢለያይም ግባችን አንድ እንደሆነ አንርሳ

ባለፈው ጽሁፌ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2019/03/blog-post_19.html) ግንቦት 7 እና ሌሎች «የዜግነት ፖለቲካ» ፓርቲዎች፤ አዴፓ እና አብን ግቦቻቸው የዜግነት ፖለቲካ እንደመሆኑ ጸጉር መቀንጠስ ትተው መተባበር ቢያንስ አለመጠላለፍ አለባቸው ብዬ ነበር። የሀገራችን ነባራዊ አደገኛ ሁኔታ ስለሚያስገድደን ማለት ነው።

ዋናው ግባችን የዜግነት ፖለቲካ (የዜግነት አስተዳደር ነው)። የጎሳ ፌደራሊዝምን አፍርሰን የብዝሃነት (multicultural and multilanguage) ፌዸራሊዥም ነው የሚበጀን ነው አቋማችን።

የዚህ ግብ ዋና ምክንያት ርዕዮት ዓለማዊ ሳይሆን መረጃ ላይ የተመሰረተ (empirical) ነው፤ የጎሳ ፌደራሊዝም የግጭት መንስኤ መሆኑን ለ28 ዓመት በአምባገነንትም በአንጻራዊ ነፃነትም አይተናል። ሚዛናዊ፤ ለዘብተኛ፤ ዓለም ዙርያ ተሞክሮ ያለው በዜግነት የተመሰረተ ክልሎችን በርካታ መብት የሚጸት ፌደራሊዝም እነዚህን ህልውናችንን ለማጥፋት የደረሱትን ግጭቶች ይቀንሳል። ለዚህ ነው የዜግነት ፖለቲካን የምንፈልገው፤ ግንቦት 7ም፤ አዴፓም፤ አብንም።

ይህን ግብ ለመምታት መደራጀት ግድ እንደሆነ ከምናልባት 50 ዓመታት ብኋላ እየገባን ይመስላል። ገንዘብ እየተሰበሰበ ነው ድርጅት(ቶች) እየተቋቋመ ነው። ይህ ግድ ነው። አሰምርበታለሁ፤ ግድ ነው። አልያ እልቂት ነው የሚጠብቀን።

ግን ወደ ግባችን ስንጓዝ የተለያየ መንገድ እንጠቀም ይሆናል። የተለያየ ስትራቴጂ እና ታክቲክ ማለት ነው። ለምሳሌ፤ አናንዶቻችን ለዘብተኛ አቋም እና በተለይ ለዘብተኛ አነጋገር እና ኮምዩኒካሽን ግድ ነው ጎሰኝነትን ለመቀነስ ብለን እናምናለን (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2019/03/blog-post_15.html)። ሌሎች ደግሞ ጠንቅረን መናገር እና መሟገት አለብን ይላሉ።

ይሁን፤ በዚህ ጉዳይ እንሟገት። ግን ግባችንን አንርሳ። አንጠላለፍ። አንዱ ግድ የሌላውን መንገድ ካልተጠቀምክ አልተባበርህም አይበል። ምን ይደረግ ሰው ነን ፖለቲካ ነው እና አቋም ይለያያል። በፖለቲካ ፍፁምነት የለም።

ግን ትብብር እና አለመጠላለፍ ግድ ነው። አለበለዛ አስፈላጊ የሆኑን ግዙፍ ድርጅቶች እና አቋሞችን ማቋቋም አንችልም፤ ይህ ማለት ግባችን አቅራቢያም አንደርስም፤ ይህ ማለት የጎሳ ፖለቲካ እንደምናየው ሀገራችንን እያቃጠለ ይቀጥላል።

Tuesday 19 March 2019

የግንቦት ፯፤ አዴፓ እና አብን ግብ የዜግነት ፖለቲካ ነው፤ አሁኑኑ ይተባበሩ

የመጨረሻ ዸቂቃ እየደረሰ ስለሆነ ጸጉር ቅንጠሳችንን ትተን ወደፊት እንራመድ።

የግንቦት ፯፤ አዴፓ እና አብን ግብ ከሞላ ጎደል አንድ ነው። ግንቦት ፯ የዜግነት ፖለቲካን ነው ማስፈን የሚፈልገው። በሌላ ቋንቋ ህገ መንግስቱን ከጎሳ አስተዳደር ወደ ብዝሃነት ያለው የዜጋ አስተዳደር መቀየር ነው።

አዴፓ በይፋ አይናገረው እንጂ ወደ ዜግነት ፖለቲካ ማምራቱ የታወቀ ነው። ህገ መንግስቱ በዚህ መንገድ ይቀየር ቢባል አዴፓ ይደግፈዋል።

አብን ደግሞ አንዳንድ መሪዎቻቸው ምንም ቢደነባበሩ ሁለት አላማ አለኝ ብሎ በይፋ ተናግሯል። እነዚህን ፩) የአማራ ህዝብ ጥቅምን ማስከበር እና ፪) ህገ መንግስቱን ወደ ዜግነት አስተዳደር መቀየር።

ስለዚህ ሶስቱ ድርጅቶች፤ ግንቦት ፯፤ አዴፓ እና አብን፤ የዜግነት ፖለቲካ በኢትዮጵያ እንዲሰፍን ይታገላሉ። ታባባሪ ናቸው እና እንደ ታባባሪ አብረው ሊሰሩ ይገባል።

ግቡ የዜግነት ፖለቲካ ነው። የግቡ ምክንያት የጎሳ ፖለቲካ የግጭት መንስኤ ስለሆነ የባህል ብዝሃነት ያለው የዜግነት ፖለቲካ ብቻ ነው ሰላም የሚያመጣው ነው።

ይህን ግብ ለመምታት ሶስቱ ፓርቲዎች የተለያየ መንገድ ይጠቀሙ ይሆናል። ግን ሶስቱም በአንድ አቅጣጫ እየሄዱ ስለሆነ ከመጠላለፍ ተቆጥበው ወደ መደጋገፍ ሊገቡ ይገባል። ለሶስቱም የሚጠቅም ነገር ነው።

በመቸረሻ ግንቦት ፯ ጠንክሮ ድርሻውን ማሟላት አለበት። አዴፓ ጠንካራ ነው፤ አብን አባላትን በደምብ እየሰበሰበ ነው። ግን ግንቦት ፯ ከብዙሃን ድጋፉ አንጻር ገና ነው። መፍጠን አለበት፤ አማራጭ የለም።

ብራቮ ለአዴፓ፤ ከ600 ሚሊዮን በላይ ብር ለተፋናቃይዎች በመሰብሰቡ

እንኳን ደስ አለን። ብራቮ አዴፓ! ብራቮ ለጋሾች! ትብብርን እና ድርጅትን ማጠንከር እንዲህ ነው።

ለጋሾች ግን በዚህ አታቁሙ። አዴፓ ግዴታውን እንዲወጣ ተከታተሉ። ካልተወጣው ደግመን አንሰጥም ብላችሁ አሳስቡ።

አዴፓ ይህን እንደ ጅምር እንጂ እንደ ግብ አትመለከቱ። ስራችሁን በአግባብ ሰርታችሁ ይበልጥ የሆነን መዋቅር እና አቅም ገንቡ!

ግንቦት 7 እና ሌሎች የኢትዮጵያ ብሄርተኞች እና የአዲስ አበባ መሃበራት፤ ከዚህ ድል ተማሩ። እንደዚህ አይነት አስፈላጊ ስራ መስራት ከባድ አይደለም! ይቻላል! እኛም እንደዚህ አድርግን ግዙፍ የአንድነት ድርጅታችንን እናቋቁም። አሁን ምንም መዘግየት አይቻልም። ለ40 ዓመታት በመዘግየታችን ሀገራችንን እጅግ ጎድተናል። አሁኑኑ በአስቸቋይ የግዙፍ ድርጅት ምስረታ ስራችንን ጀምረን እናጠናቅቅ።

Friday 15 March 2019

ለዘብተኛ ብሄርተኞቹን ወደኛ ማምጣት ግድ ነው

በጎሳ ብሄርተኝነት ችግር ያለበት የትም ሀገር የ«አንድነት» ኃይሉ ዋና ስልት (ስትራቴጂ) ለዘብተኛ የጎሳ ብሄርተኞጭኝ ወደሱ ማምጣት። በአንጻሩ ለዘብተኞቹ የጸንፈኞቹን ፕሮፓጋንዳ ተቀብለው ወደ ጸንፈኛው ወገን እንዳይሄዱ ነው። ይህን በዚህ ጽሁፍ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/07/understanding-ethnic-soft-nationalism.html) በሌሎች ሀገር ምሳሌ እየሰጠሁኝ አስረድችያለሁ።

ባጭሩ ለልምንድነው ለዘብተኞቹን መሳብ የሚያስፈልገው? አንድ ጎሳ ሙሉ በሙሉ ጸንፈኛ ብሄርተኛ ከሆነ ልታሸንፈው አትፈልግም ይዞህ ገደል መግባት ስለሆነ የፖለቲካ መንገዱ። ግን ግማሹን (ግማሽ ናቸው እንበል ለዘብተኞቹ) ካሳመንክ የጽንፈኞቹ ኃይል እና ማምጣት የሚችሉት ሀገራዊ ጉዳት እጅግ ይመነምናል። ይህ ከሞላ ጎደል basic ፖለቲካ ነው ዓለም ዙርያ።

ይህን ከተቀበልን በኋላ እንዴት ነው ለዘብተኞቹን ወደ አንድነት መሳብ የሚቻለው ብለን እንጠይቅ። ያው አንዱ መንገድ ፍላጎታቸውን በማሟላት ነው። ለምሳሌ ኦሮምኛ የፌደራል መንግስት ቋንቋ ይህን ስንል ይህ የለዘብተኛ የኦሮሞ ብሄርተኛን ትቅም እና ፍላጎት ለማሟላት ነው። ነገሩ ደግሞ ለሁሉም ጠቃሚ ነውና ሁሉም (ከጸንፈኞቹ በቀር) ተጠቃሚ ይሆናል። ይህ ለለዘብተኞች ፍላጎት መቆርቆር አንድ ስልት ነው።

ከስልት ሌላ ግን ወደ ታክቲክ ስንገባ ለዘብተኞች ወደ ጸንፈኝነት እንዳይሄዱ ማድረግያ አንዱ ዋና ታክቲክ ለዘብተኛ ውይይት ነው። ኃይለ ቃል፤ ዘለፋ፤ ስድብ ወዘተን ከንግግራችን እጅግ ማራቅ ነው።

ጸንፈኞቹ እንድንሳደብ እና ኃይለ ቃል እንድንጠቀም እጅግ ይፈልጋሉ! እጅግ እጅግ ይፈልጋሉ! ከአንድነት ኃይሉ እንደዚህ አይነት ንግግር ከመጣ ለዘብተኞች ተበሳጭተው ወደ ጽንፈኛው ጎራ እንደሚወስዳቸው ጽንፈኞቹ አበጥረው ያውቃሉ። ከላይ በጠቀስኩት ጽሁፌ እንደ ምሳሌ እንደሰጠሁት በካናዳ የቄቤክ ብሄርተኞች ከአንድነት ፖለቲከኛ ስድብ እና ዘለፋ ጓግተው ይጠብቁ ነበር። አንዱ ተሳስቶ ኃይለ ቃል ከተናገረ ደግሞ ወድያው ሚዲያውን ይሞሉበት ነበር! እንዲህ ነው የአንድነት እና ሀጎሳ ብሄርተኝነት የፖለቲካ ጨዋታ።

ለዚህ ነው ከላይ በምታዳምጡት የታማኝ በየነ ቃለ ምልልስ ታማኝ መጮህ እና መተቸት ቀላል ነው ግን አደጋ ነው የሚለው። በደምብ ባይገልጸውም ሃሳቡ ይህ ነው።

በሌላ በርዕዮት ዓለም ፖለቲካ መሰዳደብ እና መወንጀል አለ። አንዳንዴ መስደብ እና ማዋረድ ስለሚያዋጣ ነው የሚያደርጉት። መራጮች ስድቡን እና ትችቱን ተከትለው አምነው ሰዳቢውን ወገን ይመርጣሉ። ሆኖም ግን አንዳንዴ አድግራጊውን ጎድጦ ይሸነፋል። ግን ከዚህ አያልፍም።

ጎሰኝነት ያለው ፖለቲካ ግን የተለየ ነው። በጎሳ ፖለቲካ ኃይለ ቃል እና ስድብ ሰውን ከማሳመን ይልቅ ይገፈትራል! ኢሳት ለ24 ሰአት (ተገቢም ቢሆን) ስለ ኦሮሞ ብሄርተኞች ጽንፈኝነት ከተናገረ ማንንም ኦሮሞ ወደሱ አያመጣም፤ ችግራሽ ይገፈትራቸዋል። የጎሰኝነት ፖለቲካ ባህሪ እንዲህ ነው። ኃይለ ቃል ጸንፈኞቹን ነው የሚጠቅመው። ለዘብተኛ ንግግር ይጎዳቸዋል።

አላማችን ለዘብተኞቹን ወደኛ ለማምጣት ከሆነ ይህን ትጠንቅቀን ማወቅ አለብን። በንግግር በላቸው የሚለው አስተሳሰብ የተሳሳተ ነው። ፖለቲካን አለማወቅ ነው። የሚቀጥለው ጊዜ እንደ ግንቦት 7 አይነቶቹ ለምን «አልቾሃችሁም» ከማለት ይህን አስታውሱ።

Thursday 14 March 2019

ምሁⶂቻችን እና ልሂቃኖቻችን እንዴት እንደተደናቀፉ

ጣልያን፤ የፈረንጅ የቀለም ትምህርት እና ርዕዮት ዓለም አምልኮ፤ እና አብዮት እንዴት የምሁራን ማህበረሰባችንን እንደመነመነ።

https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_38.html

ገንቢ ውይይት ከስዩም ተሾመ እና መንግስቱ አሰፋ

ይህን ገንቢ ውይይትን ተመልከቱ። ስዩም ተሾመ እና መንግስቱ አሰፋ ይህን ውይይታቸውን ዘውትር ቢያደርጉት ጥሩ ይመስለኛል። በተለይ የተለያዩ የህገ መንግስት ቅያሬዎችን ቢያሰላስሉ ጥሩ ይመስለኛል። ወደ እንደዛ አይነት ተግባራዊ ውይይት ሲገባ ደግሞ የተለያዩ እውነታዎች እና አስተያየቶች ይወጣሉና።

Tuesday 12 March 2019

የአዲስ አበባ ህዝባዊ ድርጅት

በጄት፤ 100 ሚሊዮን ብር
አባል ቁጥር፤ አንድ ሚሊዮን
አደረጃጀት፤ አንድ ለአምስት
አካሄድ፤ ስልታዊ
ውጤት፤ ሰላም

ብራቮ ስዩም ተሾመ፤ ጸንፈኞቹ ተደራጅተው የኢትዮጵያዊነት ጎራው አለመደራጀት ነው ሀገራችንን የሚያጠፋው

ይህን ውይይት በድምብ አዳምጡት። ጸንፈኞቹ ገጀራ ይዘው ህዝቡንም መንግስትንም ሲያስፈራሩ የኢትዮጵያዊነት ጎራው ምንም ፖለቲካ ኃይል ያለው አደረጃጀት የለውም። እነ ዓቢይ ጸንፈኞቹን ትተው ኢትዮጵያዊነትን ቢከተሉ ኦዴፓ ሲዞርባቸው የሚመኩት የኢትዮጵያዊነት ኃይል የለም! ጎበዝ፤ እረ ቶሎ ብለን እንደራጅ።

፩) የ100 ሚሊዮን ብር ቡጀት
፪) አንድ ሚሊዮን አባላት
፫) አንድ ለአምስት አደረጃጀት

ይህን ካደረግን ሰላም ይሰፍናል።

«ዓቢይ ከዳን» የሚለው ትርከት ይጠቅመናል ወይ?

የኢሳት ተንታኞች ኤርሚያስ ለገሰ እና ሃብታሙ አያሌው አቢይ እየዋሸላቸው ኦዴፓ የክህደት ስራ ሰሩ የሚል ትርክት ጀምረዋል። ይህ ትርክት ለኢትዮጵያዊነት ኃይሉ እና ለአዲስ አበባ ህዝብ ትግል ይጠቅማል ዋይ ነው ጥያቄው?

እንደሚገባኝ ይህ ትርክት ሁለት አላማ አለው፤

፩) የአዲስ አበባ ህዝብ እና ሌላው የኢትዮጵያዊነት ጎራውን ለማስነሳት
፪) የዓቢይ መንግስት (እና ለማ እና ኦዴፓ) ላይ ጫና መፍጠር

እስቲ «ዓቢይ ከዳን» የሚለው ትርከት እነዚህን ግቦች ሊያሳካ ይችላል ወይ ብለን እንመልከት...

፩) «ጠላቶችን» በኃይል በመተቸት ህዝቡን ማነቃቃት እና ማስነሳት ኢሳት እና ሌሎች ለረዥም ዓመታት የሞከርነው ስልት ነው። አልሰራም ነው የምለው። የፖለቲካ ለውጡ የመጣው ህዝቡ የትግሬ የበላይነት እና የህወሓት ጭቆና ስለበቃው ነው። የበቃው ደግሞ «እየተቆንክ ነው» ስለተባለ አይደለም፤ የለት ኑሮው ስለሆነ ነው። ይህ የሚያሳየን የ«ለቅሶ ፖለቲካ» ማለትም ጨቋኝን መተቸት እና ስለ ጨቋኝ ማልቀስ ህዝቡን አያስነሳም። ስለዚህ አሁንም «አቢይ ከዳን» ማለት ህዝቡን አያስነሳም። ህዝቡ አሁን የሚያስፈልገው ጠላት አይደለም፤ ጠላቱን ያውቃል።

፪) የዓቢይ መንግስት ይህን አይነት ጫና አይመልስም። መንግስቱ/ኦዴፓ ጸንፈኞቹን የሚያስተናግደው አምኖበት ነው፤ ተገዶ ነው፤ ወይንም የረዥም እቅድ ስልት ይህን የወረ ጫና ምንም አይቀይረውም። በጸንፈኝነቱ አምኖበት ከሆነ ከኃይል በቀር ምንም አይመልሰውም። ተገዶ ከሆነ አሁንም ኃይል ነው አስገድዶ የሚመልሰው። ስልት ከሆነ ደግሞ አሁንም የኛን ጫና ignore ማድረግ ግድ ይሆንበታል ግቡ እስኪሳካ።

ሰልዚህ «ዓቢይ ከዳን» የሚለው ትርክት ግቦቹን አያሟላም። እርግት ለስሜታዊ ጩኸት እና እሮሮ ይመጫል። ግን ሰከን ብለን ካሰብነው ጥቅም የለውም።

አልፎ ተርፎ ጉዳት አለው። እንደተለመደው ገመደራጀት ስራችን distract ያደርገናል። ለ27 ዓመት እየጮህን ችግራችንን ህወሓት ላይ እያሳበብን መደራጀት አልቻልንም። እነ ዓቢይ መጥተው ህወሓትን አባረሩልን። አሁንም የመደራጀት አለምቻል በሽታችን ላይ ከማተኮር ፋንታ የ«አቢይ ከዳን» ትርክት ላይ ካተኮርን የትም እንቀራለን።

ሌላው ጉዳት ለፖለቲካዊ የዋህነት/ጅልነት እጃችንን መስጠት እና ትክክለኛ ግንዛቤ ማጣት ነው። የዓቢይ መንግስት የህወሓትን አገዛዝ ለመድገም ነው ከመጀመርያ የተነሳው ማለት እጅግ የተንሸዋረረ አመለካከት ነው። ፖለቲካ የalliance ጉዳይ ነው። ከማን ጋር ነው የምንጋራው እና ጥቅማችን የሚመሳሰለው የሚለውን ነገር አብጥረን ማወቅ አለብን። እና ዓቢይን ከነ ኦነግ ጋር መቀላቀል አደገኛ የዋህነት ነው።

ስለዚህ ሰከን እንበል። ይህ ሁሉ ችግር የመታው ባለመደራጀታችን ነው። የአንድ ዓመት እድል አልፎናል። እስካሁን የኢትዮጵያዊነት ኃይሉ እና/ወይንም የአዲስ አበባ ህዝብ 100 ሚሊዮን ብር በጄት ያለው እና ሚሊዮን አባል ያለው ድርጅት መፍጠር ነበረበት። የፓርቲ አባላትን አሰልጥኖ ቢያንስ አዲስ አበባን በአንድ ለአምስት መቆጣጠር ነበረበት። በየመዋቅሩ ሰው ነአ ድር መዘርጋት ነበረበት። ይህን ሁሉ አላደርገንም። ባልማረጋችን ነው ችግሮች የቀጠሉት። አሁንም «ዓቢይ ከዳን» ብለን ማልቀስ ይህንን ግብ አያመጣም። ዋና ግባችን ላይ ብናተኩር ይሻላል።

የሰከነ አስተያየት ስለ ዓቢይ እና ኦዴፓ

ስሜታዊ መሆን አይበጅም... ይህን የፍፁም ፈቃዱ ትክክለኛ ትንታኔ ያንብቡ።

(https://www.facebook.com/fitsum.fikadu.96/posts/2138544319567816)

ቁምነገሩ ጦርነቱን ማሸነፍ ነው

በቅድምያ በአደጋው ለተጎዳነው ሁሉ ፈጣሪ መፅናናት ይሁነን እላለሁ።አዎ እርሱው ፈጣሪ ኢትዮጵያዬን እንዲህ ካለው ሃዘን ሁሌም ይጠብቅልን እያልኩ በሰሞኑ የፖለቲካችን ፈተና ዙሪያ እንዲህ እንደሚከተለው ልል ወድጃለሁ።

የዶ/ር አብይ ቡድን ማለቴ ቲም ለማ ሃገርን አንድ ለማድረግ ከፍተኛ ትግልና ውጥረት ውስጥ ሆኖ ይታየኛል።ጁሃር (ኦነግ፣ ቄሮ) እነርሱን (ማለትም ቲም ለማን) ከኦሮሞ ህዝብ ጋር ለማጣላት ጠንክሮ እየሰራ መሆኑን አምናለሁ። እነርሱም ይህ ስለገባቸው ህውሃትን ቀስ በቀስ ድባቅ የመቱበትን ያንኑ የተለመደ ለዘብተኛ የሚመስል ግን ውስጠ ወይራ አካሄዳቸውን እየተገበሩበት ይገኛሉ። እነዚህ ብልህ መሪዎች መሬት እስከሚይዙ ድረስ ለህውሃት ተገዢና ተልመጥማጭ መስለው እንዴት አዘናግተው በጡረታ ስም ገሸሽ በማድረግ ከዚያም ጊዜ ጠብቀው እነዛኑ አይነኬ መሣይ የህውሃት መሪዎች ወደ ማሰር ውስጥ እንደገቡ ሳስብ፤ ይሄ በስሜት የሚነዳው ህዝባችን በሚፈልገው ፍጥነት ባለመሄድ ውስጥ ውጤት እንዳለ ያሳዩኛል።የእነዚህ ሰዎች አካሄድ ልክ እንደ ሺቭ ኬራ አባባል ዓይነት ነው።ማለትም፦ አሸናፊነት ማለት እያንዳንዱን የጦር ግንባር ማሸነፍ ማለት ሳይሆን ጦርነቱን ማሸነፍ ማለት ነውና።

ጁሃር በዚህም በእዛም ብሎ፤ "እኛ ከየኦሮሞ ህዝብ ጥቅምና አጀንዳ ይልቅ የምናስቀድመው የኢትዮጵያ ህዝብን አጀንዳና ጥቅም ነው" ብለው ዛሬውኑ በአደባባይ እንዲናገሩ ለማድረግ ያልወጋጋቸው ቦታ የለም። ም/ቱም ለእርሱ እንዲህ ማስባል ማለት እነርሱን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እስካሁንም በጥርጣሬ እያያቸው ካለው ከቄሮና ፅንፈኛ የኦሮሞ ብሄርተኞች ጋር ሙሉ ለሙሉ ማቆራረጥ እናም ቦታቸውን (ምርጫ ባስፈለገ ጊዜም ሆነ በአዘቦቱ ጊዜ) በኦነግ ማስቀማት ብሎም የእራሱን ርካሽ ተወዳጅነት በአክራሪ ኦሮሞ ብሄርተኞቹ መካከል ያለስጋት ማስፈን መሆኑን ስለሚያውቀው ነው።በከፍተኛ ፈተናና ጫና ውስጥ ያሉት ኢትዮጵያውያኑ ብልሆቹ መሪዎች ግን ገብቷቸዋልና፤ ቪዥናቸውን ከዳር ማድረስ እንዳለባቸው ስለሚያውቁ መረጋጋት ያለበትን በማረጋጋትና ባላንስ በመስራት ስራ ላይ ናቸው።

ኢትዮጵያውያኑ መሪዎች አዲስ አበባን ለኢትዮጵያውያን ሁሉ ብቻ በእኩል እንድትሆን እንደሚመኙ ግልፅ ማሳያው እኮ፤ መጀመሪያውኑ የኮንዶሚኒየም ዕጣ ማውጣታቸው ነው።ከዚህ በተጨማሪም አገር ሰላም ብሎ የኮንዶሚኒየም እጣ ያወጣው ደግሞ የኦዴፓ አባላቸው ማለትም ታከለ ሆኖ ሳለ ወዲያውኑ የጁሃር ጫጫታ ወደ ደም ማፋሰስ ሊሻገር መሆኑ ሲገባቸው፤ ፅንፈኞቹን ለማረጋጋትና የኦሮሞን ህዝብ ለማሳመኛ የሚሆናቸውን ጊዜ ለመግዛት የሆነ ዓይነት መግለጫ "በሌላኛው" የኦዴፖ ገፅ አውጥተው ጉዳትን ተከላክለዋል። ዳሩ ግና በስሜት የሚንቀለቀለው የህዝባችን አካል ጠረጠራቸው። እነርሱ ግን ምንተዳቸው፤ ግባቸው የብሄር ፖለቲካን ከኢትዮጵያ ምድር ለመጨረሻ ጊዜ ማጥፋት ነውና፤ ይኸው ውጥናቸው ሲሳካ ለሁሉ ምላሽ ይሆነናል በሚል ተስፋ አሁንም ዋና ስራቸው ላይ ናቸው። አዎ በብሄር ፖለቲካ ሃገራቸውን እንዲህ ቁምስቅሏን በማሳየት እያንገላታት ያለውን ኢህአዴግንም ሆነ ኦዴፓቸውን ፍርስርስ አድርገው በህብረብሄራዊ ፓርቲ መተካት ደግሞ፤ የለዘብተኛ መሳይ አካሄዳቸው የመጨረሻ ግብ በዚያውም የጁሃርም ሆነ የኦነግ አሊያም የወላጃቸው የህውሃት ወይም ደግሞ የሌሎች ዘረኛ መሰሎቻቸው ሁሉ ሃሳቦች ግብአተ መሬት እንዲሁም የኢትዮጵያዬ ትንሳዔ መሆኑ ገብቷቸዋልና፤ ለስኬቱ ትግልና ጫና ውስጥ ናቸው። እኛስ የት ነን?

Sunday 10 March 2019

ለማ መገርሳ ልክ ነው፤ የዴሞግራፊ ለውጥ ግድ ነው

ከዚህ በፊት እንደጻፍኩት የጎሳ ብሄርተኝነትን ከፖለቲካችን ለመቀነስ እና ለማጥፋት የዴሞግራፊ ለውጦች ማምጣት ግድ ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/curbing-ethnic-nationalism-via_26.html)። ምከንያቱ ባጭሩ እንዲህ ነው...

የጎሳ ብሄርተኝነት ህዝብ ውስጥ በተለይ የኦሮሞ ህዝብ ውስጥ በደምብ እንደገባ ሁላችንም ገብቶናል። በልሂቃን ደረጃ ብቻ ሳይሆን በብዙሃን ደረጃም። ይህን ጎሰኝነት በስብከት እና ልመና ማጥፋት አይቻልም። የተም ሀገር የጎሳ ብሄርተንኘት አንዴ ከሰፈነ የሚቅንሰው ነገር ፖለቲካዊ ድርድር ሳይሆን የዴሞግራፊያዊ ለውጥ ብቻ ነው። በኢትዮጵያ የሚያስፈልገው የዴሞግራፊ ለውጥ በኦሮሞ እና ሌላው ኢትዮጵያዊ መካከል መቅላቀል እና ውህደት (integration and assimilation) ነው። ህዝቡ ተቀላቅሎ ተጋብቶ ተዋልዶ የቅይጥ ባህል እና ህዝብ መጨመር አለበት። በዚህ መንገድ የጎሳ ብሄርተኛው ጎራ እያነሰ ይሄዳል የፖለቲካ ኃይሉም ይመነምናል። ይህን የሚያስፈጽም አንድ ፖሊሲ ኦሮምኛ የህገር ሙሉ ቋንቋ ማድረግ ነው። ይህ ኦሮሞዎች ከኦሮሚያ ወደ ሌላው ኢትዮጵያ እንዲፈልሱ ይጋብዛል። ለምሳሌ ኦሮምኛ ለማስተማር ወደ አማራ ክልል ይመጣሉ። ይህ ፈልስት መቀላቀልን እና መወሃድን ያመጣል። ከላይ የጠቀስኩት ጽሁፍ ባጭሩ ይህን ነው የሚለው።

በቅርቡ ለማ መገርሳ ስለኦሮሞ ህዝብ ወደ ከተማ መፍለስ እናለበት ያሉት ነገር ከዚህ ጋር አብሮ ይሄዳል። ለምሳሌ አዲስ አበባ ዙርያ የሚኖረው ባብዛኛው ኦሮሞ ነው። አዲስ አበባ ባደገች ቁጥር በሜትሮፖሊታን ከተማው ያለው የኦሮሞ ህዝብ ቁጥር እየጨመረ መሄዱ አይቀርም። ከላይ በጻፍኩት አንጻር ይህ የኦሮሞ ህዝብ በአዲስ አበባ መብዛት አይቀሬም ብቻ ሳይሆን እንደ ጥሩ ነገር ነው መታየት ያለበት። ከተማው ህዝቡን ይቀላቅለዋል እና ያዋህደዋል። ይህ ውህደት የጎሳ ብሄርተኝነትን ይቀንሳል። ስለዚህ ኦሮሞዎችን ወደ አዲስ አበባ እና ሌሎች ከተሞች እንዲፈልሱ ያለው የኦዴፓ እቅድ ጥሩ ነው ማለት ይቻላል።

አሁን ከኛ ከኢትዮጵያ ብሄርተኞች ጎራ የሚጠበቀው ይህ እቅድ በምንፈልገው በአውንታዊ መስመር እንዲካሄድ ነው። «የጎሳ ጌቶዎች» ወይንም የአንድ ጎሳ ሰፈሮች እንዳይፈጠሩ፤ እውነታዊ ውህደት እንዲኖር፤ ሌላው ህብረተሰብ ኦሮምኛ እንዲማር፤ አድሎዋዊነት እንዳይኖር፤ ወዘተ መስራት አለብን። ሌላው ከኛ የሚጠበቀው ነገር የኦሮሞዎች መብት እና ፍላጎት በአዲስ አበባ እንደሚከበረው የሌሎች ዜጎች መብት እና ፍላጎት በኦሮሚያ እንዲከበር መሟገት እና ማስፈጸም ነው። አልፎ ተርፎ ኦሮሙማ (የኦሮሞ ባህል) በአዲስ አበባ እና መላው ኢትዮጵያ እንዲንጸባረቅ በመስማማት in exchange የጎሳ ፌደራሊዝም ሀገ መንግስቱ እንዲቀየር መሟገት እና መደራደር አለብን። ይህን ለማድረግ ታላቅ አቅም እና መደራጀት ይጠበቅብናል።

ነገሮችን ሁሉ በአውንታዊ መልኩ እንደ opportunity ማየት የአሸናፊነት ምልክት ነው። ኦዴፓ ኦሮሞን ወደ አዲስ አበባ እንዲሄድ እናበረታታለን ሲል እኛ እሰየው ብለን በሂደቱ ተሳትፈን እኛ የምንፈልገው መልክ እንዲይዝ ማድረግ አለብን። ከውጭ እያየን በፍርሃት ከማልቀስ ጉዳይ ውስጥ ገብተን መምራት ነው ያለብን።

ስለዚህ ለማ መገርሳ ልክ ነው፤ የዴሞግራፊ ለውጥ ግድ ነው። በዚህ መንገግድ ብቻ ነው መቀላቀል እና መዋሃድ የሚመጣው። በዚህ መንገድ ብቻ ነው አሁን በህብረተሰባችን የሰፈነው ጎሰኝነት ከረዥም ዓመታት በኋላ እንዲቀንስ እና እንዲጠፋ ማድረግ የሚቻለው።

Saturday 9 March 2019

የአዲስ አበባ ህዝብ መደራጀት ምን ይመስላል?

ይዽርጅጥ ጽም፤ «የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ድርጅት»

ተእልኮ፤ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች መብት እና ጥቅም ለማስከበር የሚሰራ ድርጅት።

መሰረታዊ አቋሞች፤ ፩) አዲስ አበባ በአዲስ አበባ ነዋሪዎች ነው መገዛት ያለበት ፪) አዲስ አበባ ከጎረቤት ኦሮሚያ ክልል በተገቢው መልካም እና ገንቢ ግንኙነት ሊኖረው ይገባል ፫) የአዲስ አበባ ህዝብ መብቶች መከበር አለበት ፬) መካከለኛው እና ለዘብተኛው መንገድ መቅደም አለበት፤ ጸንፈኝነት ለአዲስ አበባ ህዝብ ጎጂ ነው።

የአደረጃጀት ሂደት፤ ፩) 100 የአዲስ አበባ ባለሃብቶች ሰብስቦ ከያንዳንዱ 10 ሚሊዮን ሰብስቦ መሰረት ማድረግ ፪) ሰፊ የንቃት እና የአባል መለምለም ሂደት አካሄዶ አንድ ሚሊዮን አባላት ማግኘት ፫) አዲስ አበባን በአንድ ለአምስት አሰራር ሁሉንም የህብረተሰብ እና ኤኮኖሚ ክፍል መቆጣጠር።

ስልቶች፤ ፩) አንድነት፤ የሃሳብ ልዩነቶች በአግባቡ ተንሸራሽረው መፍትሄ ይገኛሉ። ድርጅቱ ጸብ፤ ቂም፤ ሹክሹክታ ወዘተ ይጸየፋል ፪) ግልጽነት፤ ሚስጥርነት ድክመትን ያመጣል። የድርጅቱ ስራ በሙሉ የግልጽነትን ፈተና መቋቋም አለበት፤ ሚስጥር ከወጣ የሚጎዳ ድርጅት መሆን የለበትም ፫) ተሳታፊነት፤ ድርጅቱ አባላት እንዲሳተፉ መጣር አለበት አባሉ የድርጅቱ ባለበትነት እንዲሰማው።

የሰለጠነ እና የሰከነ ፖለቲካ መንፈስ፤ ለቅዋሜ የሚይመች አቋም፤ ድርጅቱ ኢ-ስሜታዊ ሆኖ የሚወስደው አቋም እና የሚያንጸባርቀው ሃሳብ ማንኛውንም ፈተና የሚቋቋሙ መሆን አለበት። ምሳሌዎች፤

፩) ልዩ ጥቅም ጉዳይ፤ «እንዴት ለኦሮሞ/ኦሮሚያ ልዩ ጥቅም ይኑር ትላላችሁ» ከማለት ምንድነው ልዩ ጥቅም ብሎ ወደ ውይይት መግባት። የኦሮሚያ ልዩ ዞን ነዋሪዎች የአዲስ አበባ አገልግሎትን ማግኘት ይችላሉ፤ የኦሮሚያ ነጋዴዎች በአዲስ አበባ እንደ ነዋሪ መነገድ ይችላሉ፤ ወዘተ አይነቱ ልዩ ጥቅም እንደ ማንኛውም ሜትሮፖሊታን ከተማ ተገቢ ነው። እስቲ ሌላ ምን ልዩ ጥቅም አለ ብሎ መወያየት ነው የድርጅቱ መንገስ።

፪) ኦሮሙማ በአዲስ አበባ፤ ከቋንቋ በላይ ኦሮሙማ የለም። ስለሆንም አዲስ አበባ በኦሮሚያ ልዩ ዞኖች በመከበቧ ኦሮምኛ የከተማዋ ሁለተኛ ቋንቋ ብትሆን መልካም ነው። በኦሮሚያ ልዩ ዞኖች አማርኛ እንደሚሰራው በአዲስ አበባ ኦሮምኛ ሊሰራ ይገባል።

፫) «የአዲስ አበባ ባልቤት ኦሮሚያ ነው»፤ ይህ አባባል ኢ-ዴሞችራሲያዊ ነው። የማንኛውም ቦታ ባለቤት ነዋሪው ነው። አዲስ አበባም ይሁን ልዩ ዞኖቹ ነዋሪዎቻቸው ናቸው የፖለቲካ ባለቤቶቹ። አለበለዛ ወደ አምባገነነት ገባን ማለት ነው።

፬) ተፈናቃዮች፤ የኦሮሞ ገበሬም ሌሎች የአዲስ አበባ እና ዙርያ ተፈናቃዮች በሙሉ ጉዳያቸው ይታይ። ማን ተፈናቀለ ምን ያህል ካሳ ተሰጠው ማን ካድሬ/መሪ በምዝበራ ተጠቀመ። ከምርመራው በኋላ እርምቶች ይደረጉ። አልፎ ተርፎ መሬት የግል ይሁን የሚለውን አቋም ድርጅቱ ያራምድ። መሬት የግል ቢሆን ኖሮ መፈናቀል የሚባል አጸያፊ ነገር አይኖርም ነበር። አልፎ ተርፎ አዲስ አበባ ዙርያ ያለው ኦሮሞ እና ሌሎች ገበሬዎች እጅግ ሃብታም ይሆኑ ነበር መሬ ታቸውን በመሸጥ። መንግስት 100,000 ብር ካሳ የሚሰጠው ግለሰብ የገበያ ዋጋውን አንድ ሚሊዮን ብር ሊሰጠው ይችላል።

የአዲስ አበባ ህዝብ ማለት...

በሩን ከፍቶ የሚያድር ሰው ዘራፊው ሲመጣበት እባክህ አትዝረፈኝ ብሎ የሚለምን።

ሳያርስ ሳይዘራ የክረመ ገበሬ አዝመራ ሳይኖረው እግዚአብሔርን የሚያማርር።

አትንቶ የማያውቅ ተማሪ ፈተናውን ሲወድቅ አስተማሪውን የሚወቅስ።

ወዘተ።

የአዲስ አበባ ህዝብ (ከነ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ) ለዓመታት በትንሿ ህወሓት የተገዛው የራሱን የቤት ስራ ስላልሰራ ነው። ይህ የቤት ስራ ተደራጅቶ ለራስ መብት መቆም ነው።

ካሁን ወድያ የአዲስ ህዝብ ካልተደራጀ ለሚደርስበት ጉድ ከራሱ በቀር ማንም ጥጠያቂ አይኖርም። የአምስት ሚሊዮን ህዝብ ከተማ መቶ ሚሊዮን ብር በጀት፤ አንድ ሚሊዮን አባል ያለው ድርጅት ማቋቋም ካልቻለ በቅኝ ግዛት መገዛት ይገባዋል አይቀርለትምም።

Monday 4 March 2019

ተረት ተረት፤ አዲስ አበባ የኦሮሞ ገቤሬዎችን አፈናቅሏል

1. የአዲስ አበባ ህዝብ ምንም ፖለቲካዊ ውሳኔ አድርጎ አያውቅም። በኢህአዴግ (ከነ ኦህዴድ) የተገዛ ህዝብ ነበር። ስለዚህ የአዲስ አበባ ህዝብ ማንንም አላፈናቀለም። አፈናቃይ ካለ ኢህአዴግ ከነ ኦህዴድ ነው።

2. ከአዲስ አበባ የተፈናቀሉት ባብዛኛው ኦሮሞ ቢሆንም የተወሰኑ አማሮች እና የሌላ ጎሳ አባላት ነበሩ።

3. ካአዲስ አበባ ውስጥ የተፈናቀሉት ደግሞ ከሁሉም ጎሳ ነበሩ። እነዚህ የአዲስ አበባ ተፈናቃዮች ከአዲስ አበባ ዙርያ የተፈናቀሉት ገበሬዎች ይበልጥ ተበድለዋል በደልን በገንዘብ ከተረጎምነው። ከካዛንቺስ 50 ካሪሜትር ቦታው የተፈናቀለው ምናልታብት ሁለት ሶስት ሚሊዮን ብር ነው ያጣው። ከቡልቡላ የተፈናቀለው ገበሬ የዚህ ሩብም አልከሰረም።

4. ገበሬዎች እና ሌሎች «ተፈናቀሉ» ስንል መንግስት የማይመጥን ትንሽ ካሳ ሰጥቷቸው በግድ ከመሬታቸው አስነሳቸው ነው። አድግራጊው የአዲስ አበባ ህዝብ ያልመረጠው የአዲስ አበባ መንግስት ውየንም አብዛኛው ጊዜ የኦህዴድ መንግስት ነው። ገበሬውን አነስተኛ ካሳ ሰጥቶት ለኢንቬስተር በከፍተኛ ዋጋ ሽጦ ትርፉን ኪስ አስገብቷል። ለዚህ የአዲስ አበባ ህዝብ ትጠያቂ አይደለም፤ ኢህአዴግ እና ኦህዴድ ናቸው።

5. ታላቁ ግን ማንም የማያነሳው ጉዳይ የሀገራችን የመሬት ፖሊሲ ነው። መሬት የመንግስት በመሆኑ ነው ገበሬዎችም ሌሎችም የሚፈናቀሉት እና «ተፈናቀሉ» የሚባለው። አዲስ አበባ ሲሰፋ (እንደ ከተማ ይሁን እንደ metropolis) ዙርያ ያሉት ገበሬዎች ዋና ተጠቃሚ ነበር መሆን ያለባቸው፤ ይሆኑም ነበር መሬት የግል ቢሆን። አዲስ አበባ ዙርያ ያሉት ገበሬዎች ከተማው እየሰፋ ስለሄደ መሬታቸውን በእጅግ ውድ ዋጋ ሊሸጡ እና ሊጠቀሙ ይችላሉ። ቡልጋ ያለው ገበሬ የመሬቱ ዋጋ አንድ ብር በካሬ ቢሆን ይው መሬት አዲስ አበባ ዙርያ መቶ ብር ሊሆን ይችላል። በዚህ መንገድ ነው የትም ሀገር ከተማ ሲሰፋ ዙራይ ያሉት ገበሬዎች ሎተሪ እንዳሸነፉ የሚቆጠረው። ግን ኢትዮጵያ ገበሬው መረቱን መሸት ስለማይፈቀድ እና መንግስት ሲፈልግ መንጠቅ ስለሚችል ከተማ ዙርያ ያለ ገበሬ ጭራሽ ይሰጋ! ስለዚህ በዚምህ ረገድ ጥፋቱ የአዲስ አበባ ህዝብ ሳይሆን የኢህአዴግ እና ኦህዴድ የመሬት ፖሊሲ ነው። አዲስ አበባ ዙርያ ያሉ ገበሬዎች በኢህአዴግ/ኦህዴድ ምክንያት በሚሊዮኖች የሚቆጥር ብር አጥቷልና!

የጎሳ ፌደራሊዝም ችግር አንድ ነው፤ የግጭት መንስኤ ነው!

ዛሬ አንድ ሁለት ውይይቶች ስለ ሀገራችን «የጎሳ ፌደራሊዝም» ተመልክቼ ነበር። ውይይቶቹ ያተኮሩት በጎሳ ፌደራሊዝም እንደ ጽንሰ ሃሳብ ነው። ተናጋሪዎቹ ታሪክን እና ርዕዮት ዓለምን ፈትሸው የጎሳ ፌደራሊዝም ለሀገራችን ይበጃል ወይንም አይበጅም ብለው ተከራከሩ። Of course ውይይት/ክርክሩ የትም አልደረስም። The participants, as usual, talked right past each other።

በመጀመርያ ደረጃ አንዱ የሌላውን ፍላጎት የማይረዳበት ውይይት ውይይት አይደለም። ስለ ጎሳ ፌደራሊዝም የሉን ውይይቶች እንዲህ ናቸው። እኛ አቋማችንን እንናገራለን ሌላውም እንዲሁ አንድ ሌላው አይገባውም ውይይቱም ባለመግባባት ያልቃል።

ይህ የሚሆንበት አንዱ ምክንያት የውይይት እና ቅራኔ መፍታት ስልት በማጣት ነው። ግን አሁን ማተኮር የምፈልገው እዚህ ላይ አይደለም። ሁለተኛው ምክንያት ነው፤ ይህ ደግሞ የጎሳ እና ማንነት ጉዳይ ስሜታዊ በመሆኑ ለውይይት አይመችም። አይሆምም ማለት ይቻላል። «እኔ መጀመርያ ኦሮሞ ነኝ ቀጥሎ (ምናልትባት) ኢትዮጵያዊ» ሲል አንዱ ሌላው «እንዴት እንዲህ ትላለህ» ብሎ ሁለቱም በስሜታቸው ይመራሉ። አንዱ ሌላውም ማሳመን አይችልም።

ለዚህ ነው በጎሳ ፌደራሊዝም ጉዳይ ታሪክን እና ርዕዮት ዓለምን ፈትሸን መከራከር የትም የማያደርሰን። በጎሳ ፌደራሊዝም የሚያምን እና የጎሳ ፌደራሊዝምን የሚጠላው ሁለቱም ምክንያቶች በመሰረቱ ስሜታዊ የማንነት ናቸው። እነዚህን በርዕዮት ዓለም እና ታሪክ (in the eye of the beholder) ማስታረቅ አይቻልም።

ሁለቱን ጎራዎች ለማግባበት ወደ ሌላ level መሄድ ያስፈልጋል። ይህ ደረጃ እንዲህ ነው፤ እኔ የጎሳ ፌደራሊዝም ለኢትዮጵያ አይሆንም የምልበት ምክንያት ታሪክ እና ርዕዮት ዓለም ሳይሆን በ evidence ምክንያት ነው። የ24 ዓመት ታሪክ ከነ ያለፈው አንድ ዓመት የለውጥ ዘመን ታሪክ የሚያሳየው የጎሳ ፌደራሊዝም የግጭት መንስኤ መሆኑ ነው። የጎሳ ፌደራሊዝም በጎሳዎች መካከል በርካታ ግጭቶች እንዲኖሩ አድርጓል። ሰዎች በጎሳቸው ምክንያት የሚጎዱበት ዘመን አምጥቷል። ይህ ጉዳት ለተወሰኑ ጎሳዎች ብቻ ሳይሆን በመላው ሀገሩ ነው። ለዚህ በርካታ የ25 ዓመት evidence አለ።

ለዚህ ነው የጎሳ ፌደራሊዝም መቀየር አለበት ብለን መከራከር ያለብን። የ24 ዓመት የጭቆና እና የአንድ ዓመት የአንጻራዊ ነጻነት መረጃ የሚያሳየን የጎሳ ፌደራሊዝም ህግ እና መንፈስ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎቻችንን እንደጎዳ ነው። ሶማሌ በሶማሌነቱ፤ ኦሮሞ በኦሮሞነቱ፤ ጊዴኦ በጊዴኦነቱ፤ አማራ በአማራነቱ፤ አንዋክ በአንዋክነቱ፤ ወላይታ በወላይታነቱ፤ ስዳማ በሲዳማነቱ፤ ወዘተ ተጎድቷል። የጉዳት ፈጻሚዎቹም እንዲሁ የተለያዩ ናቸው። «ህወሓት» ወይንም የህወሓት አሽከሮች ብቻ አይደሉም ጨቋኞቹ። ህዝቡ እራሱ ይጭቋቆናል። ለዚህ በርካታ መረጃ አለን።

አንድ ታካቅ መራጀ ደግሞ የሁሉም ጎራ ፖለቲከኞች «ካልተጠነቀቅን እርስ በርስ እንፋጃለን» ማለታቸው ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/blog-post.html)! የጎሳ ፌደራልዚምን የሚደግፉትም የማይደግፉትም የጎሳ እልቂት is right around the corner ብለው ደጋግመው ይነግሩናል። ለጎሳ ፌደራሊዝም ከዚህ የባሰ indictment የለም!

ስለዚህ ለ«ዜግነት ፖለቲካ» ደጋፊዎች እና ሌሎች የዚህ የጎሳ ፖለቲካ የሚጠሉ ሰዎችን የምመክረው፤ ስሜትን በሃሳብ አትከራከሩ፤ የትም አትደርሱም። በመሰረቱ የጎሳ ፌደራሊዝም ሰውን የሚጎዳ ባይሆን ምን ችግር አለው? ምንም። የጎሳ ፌደራሊዝም ኢትዮጵያን በሰላም ቢያስተዳደር እኔ የሚጀመርያ ደጋፌው ሆን ነበር። ግን አይደለም። ሃቁ ይህ ነው። የጎሳ ፌደራሊዝም የምንጠላው የግጭት እና ጭቆና መንስኤ ስለሆነ ነው። ይህ ደግሞ በመረጃ የተመሰረተ statement ነው። ክርክራችን በታሪክ እና ርዕዮት ዓለም የተገደባ ሳይሆን ሙሉ በሙሉ መረጃ የተመሰረተ ነው። ይህ መከራከርያ መንገድ ነው አዋጪ ብዬ የማስበው።

Friday 1 March 2019

የአዲስ አበባ ጉዳይ እና የሃላፊነት ፖለቲካ

በተለያዩ ጽሁፎቼ የኢትዮጵያ ፖለቲካ መሰረታዊ ችግር የ«ኢትዮጵያዊነት» ጎራው ለራሱ እጣ ፈንታ ሃላፊነት አለመውሰዱ ነው ብያለሁ። ላለፉት 50 ዓመታት ተደራጅቶ ፍላጎቶቹን አጣርቶ ከማስከበር ይልቅ ህልውናውን ለሌሎች ትቷል። ሃላፊነት ለሌሎች መታው ባህል አድርጎታል። ይህ አካሄድ የ«ለቅሶ ፖለቲካ» ብሄ ሰይምዬዋለሁ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/blog-post_16.html)።

ይህ ሁኔታ ምክንያት አለው፤ የኢትዮጵያዊነት ጎራው በአብዮቱ ጀምሮ እርስ በርስ ተገዳድሎ ልሂቃኑ እራሱን አጥፍቶ እስካሁን አላገገመም። (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/1.htmlhttps://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/2.htmlhttps://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/3.htmlhttps://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/4.html)። ቢሆንም በዚህ አካሄድ መቀጠል አይቻልም። ሌሎችን «ፍላቶእ እና መብታችንን አስከብሩልን» ብለን እየለመንን መቀጠል አይቻልም።

አሁን የሚያስፈልገን ከ«ለቅሶ ፖለቲካ» ወጥተን፤ ከህጻንነት እና ብሽተኝነት ወትጠን ወደ «ሃላፊነት ፖለቲካ» መግባት አለብን። ግድ ነው፤ አማራጭ የለም። እነ ለማ ይሁን አቢይ ይሁን ህወሓት ይሁን ግንቦት 7 ይሁን አብን ወዘተ እንዲህ አድርጉልን ብለን መለመን አይቻልም። ካሁን በኋላ ሁላችንም «ይህ ይሁን»፤ «ይህ ይደረግ»፤ «እከለ ይውደም» ወዘተ ከማለት ወደ «እኔ ይህን አደርጋለው» የሚለው አመለካከት መግባት አለብን። ልመና በቃ፤ የራሴን እጣ ፈንታ እራሴ ወስነዋለው ወደሚለው መግባት አለብን።

የአዲስ አበባ ጉዳይ የዚህ የአስተሳሰብ እና ተግባር ለውጥ አስፈላጊነት በደምብ ይገልጻል (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_97.html)። ልሂቃኖቻችን እስካሁን እነ ኢህአዴግን፤ ህወሓትን፤ ኦዴፓን፤ የኦሮሞ ብሄርተኞችን፤ አዴፓን፤ ጥ/ሚ አቢይን፤ ፕሬዚደንት ለማን፤ ወዘተ እባካችሁ እንዲህ እንዲያ አድርጉ አታድርጉ እያሉ ለው ዓመት ይጮሃሉ። ግን አንድ የሚባል የአዲስ አበባ ህዝብን ጥቅም የሚያንጸባርቅ እና ለማስከበር የሚሯሯት ድርጅት የለም? የአዲስ አበባ ህዝብ ህልውናውን ለሌሎች ሰጥቶ ሌሎቹ የሚፈልጉትን ሲአደርጉ ልሂቃኑ ያለቅሳል! ይህ ምን ማለት ነው? የአዲስ አበባ ህዝብ እራሱን አደራጅቶ ፍላጎቱን እና መብቱን ዘርዝሮ ማስከበር ካልቻለ እነዚህ የማይወክሉት ተቋሞች የፈለጉትን ያደርጋሉ። ይህ እኮ እጅግ basic የሆነ ነገር ነው።

እስከ ዛሬ የኛ ልሂቃን እና ሚዲያ ይህን መሰረታዊ ጉዳይ ትተው በማልቀስ እና መለመን ነው የዋሉት። የራሳችንን ጥፋት (አለመደራጀት) ላለማየት ትብሎ ህልውናችንን አደጋ ውስጥ ከትተናል! ይህ ሁሉ ችግር ስላልተደራጀን ነው እና እንደራጅ ከማለት ሌሎች ስለሚያደርጉት እናለቅሳለን። ይህ ለቅሶ ምንም ለውጥ አላመጣም አያመጣምም። ህዝባችን በንዴት እንዲደራጅ አላደረገም። ይባስ ሌሎች ላይ ጣት በመጠቆም የራሳችንን ጥፋት እንዳናይ ስበብ ሆኖናል። ጉርጓዳችንን ይበልጥ እንድንቆፍር አድርጎናል።

አሁን ግን አንዳንዶች መራራ የሆነውን መድሃኒት ውጠን ወደ ፊት መራመድ እንዳለብን የገባቸው ይመስላል።


ከዚህ ከኢሳት ዝግጅት የአዲስ አበባ ህዝብ መዋናነት መደራጀት አለበት ትባለ። ያለመደራጀታችን ጥፋታችንን አመንን ማለት ነው፤ ይህን ማመን ነው መራራው መድሃኔት። ካመንን በኋላ ሙሉ አቅማችንን ወደ መደራጀት ስራ ማሰለፍ ነው ያለብን። ካሁን ወድያ አንዳች የልሂቃን እና ሚዲያ ደቂቃ በእሮሮ፤ ለቅሶ፤ እና ልመና መጥፋት የለበትም። ሙሉ አቅማችን ወደ መደራጀት።

ምን ማለት ነው የመደራጀት ስራ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/blog-post_18.html)? ብዙ ሚስጥር የለውም፤ የህዝብ የማህበራዊ እና ፖለቲካዊ መደራጀት ለሺዎች ዓመታት የተደረገ ነገር ነው። የአዲስ አበባ ህዝብ «የአዲስ አበባ ህዝቦች ድርጅት» ያስፈልገዋል። የዚህ ድርጅት (ድርጅቶች) ተእልኮ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን ጥቅም ማስከበር ነው። ቀላል ተእልኮ ነው፤ ሌላ ጣጣ አያስፈልገውም። ድርጅቱ በርካታ (በመቶ ሺዎች የሚቆጠር) አባላት ያስፈልጉታል። ባለ ሃብቱ በደምብ መሳተፍ አለበት። ስብሰባ፤ ሰርቬ፤ ምርጫ፤ ወዘተ የሚያካሄድ መሆን አለበት። አባላቶቹ በየ ማህበራዊ ዘርፍ፤ በየ መስርያቤት፤ በዬ ሰፈሩ የሚሰሩ እና የሚኖሩ መሆን አለባቸው። ድርጅቱ ሰፊ ኔትወርክ ኖሮት «የሚፈራ» ማለትም አቅም ያለው መሆን አለበት። በተለያዩ የከተማው ጉዳዮች፤ መብራት፤ ውሃ፤ መንገድ፤ ደህንነት፤ ጤንነት፤ መፈናቀል፤ ውክልና፤ ወዘተ የሚሰራ መሆን አለበት። በዴሞክራሲያዊ መልኩ የአባላቱን ፍላቶ የሚያውቅ፤ የሚያስከበር እና የሚወክል መሆን አለበት።

ይህ ድርጅት ሲኖር፤ ዛሬ ቢኖር ስለ አዲስ አበባ ያለው ጭቅጭቅ አይኖርም ነበር። ሁሉም ተሳታፊዎች የአዲስ አበባ ህዝብ ፍላጎትን አበጥረው ያውቃሉ። የሁሉም አቋም ሰልሚታወቅ የፖለቲካ ድርድሮች በግልጽ እና በጽጋ ይካሄዱ ነበር። የለገጣፎ ሰዎች አይፈናቀሉም ነበር። ጉዳዩ ገና ሲነሳ ድርጅቱ ተሳትፎበት ድርድር ተደርጎበት በሰላም በሁሉም የሚያስማማ መልኩ ይፈታ ነበር። የኦሮሚያ «ልዩ ጥቅም» ጉዳይም እንዲሁ። ወካይ ድርጅት ቢኖርን «ልዩ ጥቅም» ብለን አናለቅስም ነበር። ድሮውኑ ተደራድረን የልዩ ጥቅም ትርጉም ላይ ተስማምተን ነገሩ በሰላም ይወሰን ነበር። ወዘተ።

የአዲስ አበባ ችግር የመጣው በህወሓት ምክንያት አይደለም። በኦሮሞ ብሄርተኞች ምክንያት አይደለም። መሰረታዊ ችግሩ የአዲስ አበባ ህዝብ እርስ በርስ ተስማምቶ አለመደራጀቱ ነው። ይህን አምነን አንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ለቅሶ እና ልመናችንን ትተን ሙሉ አቅማችንን ወደ መደራጀት ማዋል አለብን። አለበለዛ በየበታችንነት እና ተገዥነት ስሜት እንደተገዛን እንቀጥላከን። መገዛት ማለት የራስን እጣ ፈንታ ለሌሎች መተው እና በራስ ህይወት ሃላፊነት አለመውስውድ ነው። ይህ ላለፉት በርካታ ዓመታት ጉዞአችንን ይገልጻል።