Tuesday 25 October 2022

የኩርፍያ ፖለቲካ

«እነ ስብሐት ነጋ ከተፈቱ ጀምሮ የአዲስ አበባ ህዝብ በዐቢይ ላይ አክሩፏል። ሮንድ ማድረርም አቆመ» ተባልኩኝ።

ይህ የፖለቲካችንን መሰረታዊ ችግር ያሚገልጽ አባባል ነው። ህዝቡ ማድረግ የነበረበት፤

1. ተቃውሞውን በሚገባው መግለጽ መንግስት እንዲሰማ እና እንዲገባው

2. እንደዚህ አይነት ነገር እንዳይደገም የመንግስት ስራተኞች፤ ህዝብ ወኪሎች፤ መሪዎችን መወትወት

ይህን ከማድረግ ፋንታ ህዝቡ ምን አደረገ፤

1. መንግስትን በሚያዳክም መልኩ እና ጠላትን በሚያጎለብት መልኩ መንግስትን ተቸ!

2. አክሩፎ እንደ ህጻን እራሱን የሚጎዳ ድርጊቶች ፈጸመ፤ ለምሳሌ አካባቢውን መጠበቅ ተወ!

ለ45 ዓመት በላይ ፖለቲካ ያቃጠለው ህዝብ እንደዚህ የፖለቲካ ደንቆሮ ይሆናል። የመንግስትን እርምጃ ለመቃወም የራሱን ጥቅም ይጎዳል! አካባቢ መጠበቅ ሮንድ ማድረግ ህዝቡን እጅግ ጠቅሟል። ደህንነትን እና አብሮነትን ጨምሯል። ህዝቡ ለዚህ መስክሯል። ስለዚህ ለራሱ ጥቅም ብሎ እነዚህን ስራዎች መቀጠል ነበረበት። ይህ ሎጂካል ነው። ግን ይህን ከማድረግ መንግስትን አክሩፍያለው ብሎ እራሱን መጉዳት ጀመረ።

ህወሓት ይሁን ሌሎች በቀላል ወሬ በህዝባችን የሚጫወቱት ለዚህ ነው። አህያ የሚሉንም ለዚህ ነው። ፖለቲካ አይገባውም። የራሱን ጥቅም አያውቅም። በቀላሉ ከምነግስት ልናፋታው እንችላለን ነው እነ ህወሓት የሚያስቡት። እንሆ ለ27 ዓመት የገዛነው ደንቆሮ ስለሆነ ነው በይፋ የሚሉት።

ሀገራችን ሰላም እንዲኖራት ይህን ነገራችንን ማሻሻል አለብን። መንግስት እያንዳንዱን የፈለግኩት ነገርን ካላደረገ ይፍረስ የሚለውን የመሃይ አስተሳሰብ እንዲጠፋ ማድረግ አለብን። ቀላል ዘመቻ አይሆንም።

Monday 24 October 2022

ስደተኛን መቀበድ፤ በጎነት ወይንም ጥቅም

የዋህ ስለሆንን የካናዳ መንግስት የህወሓትን መሪዎች በስደተኝነት ከተቀበለ ካናዳ እንዴት በጎ አገር ነው ብለን እናስባለን። የምዕራባውያን አገራት ፕሮፓጋንዳ በዓስለም ታሪክ አንደኛ መሆኑ የሚመሰክረው እንዴት ለራሳቸው ጥቅም የሚያደርጉትን ነገር እንደ በጎነት አድርገው የማሳየት እና ሌሎችን የማሳመን ችሎታቸው ነው!

አንድ አገር የሌአ እገር የተሰደደ መሪ የሚቀበለው ዋጋ ስለሚያገኝበት ነው። አንድ፤ ብዙ እውቀት እና ችሎታ ያለው ሰው ያገኛል። ይህ ሰው እውቀቱን፤ ሚስጠሮችን፤ ምክሮችን ለአዲስ ባለሟሎቹ ይሰጣል! ሁለት፤ የተቀባይ አገሩን «በጎነት» ፕሮፓጋንዳ ያስመሰክራል።

የህወሓት ያረጁ መሪዎች ለካናዳ ምን ይሰሩለታል ብላችሁ ትጠቅቁ ይሆናል? እኛ የዋሆች ነን እኮ እንደዚህ በአጭሩ የምናስበው። ብልሃት ያላቸው መንግስታት እያንዳንዱን ትንሽ ነገር ዋጋ ይሰጡታል ያጠራቅማሉም። ሁሉም አብሮ ሲደመር ትልቅ ክምችት ይሆናል።

ዓለም እንደዚህ ነው እውነቱ። በዚ በኩል የዋህ ባንሆን ይሻላ።

መልካም አስተዳደር በአማራ ክልል

 እንደሰማሁት ከ2011 ጀምሮ በአማራ ክልል በቀበሌ ደረጃ ህዝቡ የሚያስተዳድረውን የመንግስት ሹማምንቶችን በገምገም እና ካስፈለገ ማጋለጥ ጀመረ። ህዝቡ «መንግስት የህዝብ ተወካይ እና አገልጋይ ነው» ይሚለው መርህ ገብቶት መርህውን በተግባር ማዋል ጀመረ። መልካም አስተዳደር እንዲኖር እኛ እንደ ህዝብ ስራ መስራት አለብን ሃላፊነትም አለብን ብሎ አመነ። ጥሩ ንቃት ነው።

ይህን ተከትሎ ህዝቡ ሙሰኞችን መጠቆም እና ማጋለጥ ጀመረ። ግን እንደሰማሁት መንግስት ሙሰኞቹን ለፍርድ ከማቅረብ ይልቅ ወደ ሌላ ቦታ ወስዶ ሌላ ብዙ ጊዜ የተሻለ ሹመት ሰጣቸው። ህዝቡ ይህንን ተመልክቶ ታዝቦ ተስፋ ቆረጠ። በአስተዳደሩ ሃላፊነት አለብኝ ማለት ተወ እና ወደ ድሮ «አክሩፎ ዝምታ» ገባ። ሙስናው እንደገና ጀመረ።

በዚህ ታሪክ ማን ተጎዳ ብለን ከጠየቅን መልሱ ግልጽ ነው፤ ህዝቡ እና ክልሉ ነው ተጎጂው። መፍትሄ ደግሞ ከተጎጂ ነው መመንጨት ያለበት። መፍትሄው ቀላል ነው። ህዝቡ የኢ-ሙስና ትግሉን መቀታል እና ማጠንከር አለበት። ልሂቃኑ፤ ሚዲያ እና «አንቂው» ደግሞ ትግሉን መደገፍ አለበት። የፍርድ ሂደቱን ተከታትሎ ሙሰኞች የት እንደደረሱ ማጋለጥ እና ተካውሞ ማስነሳት አለበት። ተቃውሞ መንግስት ላይ ሳይሆን ሙሰኞቹ እና የሙሰኞቹ አገልጋዮች ላይ ማነጣጠር አለበት። «መንግስትን ስለምንደግግ ከነዚህ መንግስትን የማይወክሉ ሙሰኞች ልናጸዳው ይገባል» አይነት የስራ መፈክር (mission) ሊኖረው ይገባል።

ለአንድ ህብረተሰብ ጥንካሬ መልካም አስተዳደር ቁልፍ ነው። መተማመን ቁልፍ ነው። አንድነት ቁልፍ ነው። አለነዚህ ህዝቡ የተበታተነ እና ግለኛ ይሆናል ለጠላቶች ተጋላጭ ይሆናል። 

የአማራ ልሂቃን በዚህ ዋና ጉዳይ ላይ በሙሉ አቅሙ ቢሳተፍ እራሱንም ህዝቡንም ይጠቅማል። ሌሎች የማይጥቅሙ የሚጎዱ አጄንዳዎችን ትተን።