Monday 26 March 2018

አማራጭ የፖለቲካ ልሂቃን ቡድን አለ?

በ2017/5አ.አ የተሳፈ ጽሁፍን አማርኛ ትርጉም

English version: https://asfawdarguemeshal.blogspot.ca/2017/05/alternative-political-elite.html

በ1983 ደርግ ፈርሶ ሻዕብያ ህወሓትና ኦነግ ወደ ስልጣን ሲገቡ መዐቱን ፈርተን ነበር። ምክንያቱም ሻዕብያ ህወሓትና ኦነግን እንደ ጎሳ ብሔርተኞች ሺፍቶች አገረን ለማፍረስ ኢትዮጵያን ለመገነጣጠል የሚመኙ አድርገን ስለቆጠርናቸው።

ዛሬ ከ26 ዓመት በኋላ ኢትዮጵያ ከነ በርካታ ችግሮቿ አሁንም አለች! ኤርትራ ብትገኝጠልም ጸንፈኛ የጎሳ አስተዳደር ቢጫንባትም ኢትዮጵያ ተርፋለች። ዋናው የተረፈችበት ምክንያት ብዙሃኗ ድሮም ዛሬም ባብዛኛው የአገር ብሔርተኛ አገርን ከ«ጎሳ» የሚያስቀድም ስለሆነ ነው። ይህ የህዝባችን ባሕሪ የህወሓትን ጸንፈኛ የጎሳ አቋምን ሊቋቋምና መልሶ ሊገፋው አብቅቶታል። እንደ የድሮ የቱርክ መሪ ከማል አታቱክር ህወሓት የአገር ህዝብን ወደ የማያምንበት አስተሳሰብ በግድ ሊጎትተው ፈለገ ግን ሙሉ ለሙሉ አልተሳካም። ህዝቡ የጎሳ ብሔርተኝነትን ህወሓት እንዳለመው ያህል አልተቀበለውም። በህዝቡ መካከል ኢትዮጵያዊነት አሁንም ጠንክራ ትገኛለች!

በእውነቱ የኢትዮጵያ ህዝብ ህወሓትን አብርዶታል ማለት ይቻላል። ይህን ለመረዳት እስቲ ወደ የኢህአዴግ የመጀመርያ 10 ዓመት ግዛት ወደ ኋላ ሄደን እንመልከት። በዛን ዘመን በተለይ ከኢርትራ ጦርነቱ በፊት «ጠባብ የጎሳ ብሔርተኛ» የሚል አባባል አልነበረም። «ነፍጠኛ» «ትምክህተኛ» በቻ ነበር ህወሓት የሚዘፍነው። ህወሓት ሁሉንም «ጎሳዬ ከኢትዮጵያዊነቴ ይበልጣል» እንዲል ያበረታታ ነበር። «መጀምርያ ኦሮሞ ነኝ ሁለተኛ ኢትዮጵያዊ» ወይም «መጀመርያ ትግሬ ነኝ ሁለተኛ ኢትዮጵያዊ» ማለት የተለመደ ነበር። «ኢትዮጵያዊነት» የሚጠቃ የሚሾፍበት ነበር። አሁን ግን እንደዚህ አይነት ቴአትር ቀንሷል። «ጠባብ» የሚለው ቃል ወደ ፖለኢትካ ቋንቋችን ገባ። ኢህአዴግን ችራሽ ኢትዮጵያዊ እኔና እኔ ብቻ ነኝ ማለት ጀመረ! ህወሓት ድሮ የሚሰብከውን ጸንፈኛ የጎሳ ብሔርተኝነትን ዛሬ እንደ ማነቆ ነው የሚያየው።

ለዚህ ለውጥ የኢትዮጵያ ህዝብ ሊመሰገን ይገባል። የህዝባችን ጠንካራ አገር ፍቅርና የአገር ብሔርተኝነት ነው አገሪቷን ከከባድ አደጋ ጠብቆ በህይወት ይሚያኖራት። አስገራሚ ነገር ግን ይህ የህዝባችን ድል አለ ልሂቃን ጎራ በብዙሀኑ ኃይል በቻ መደረጉ ነው። ከላይ እንደጠቀስኩት በ1983 የፖለቲካ ልሂቃን ሲባል ሻዕብያ ህወሓትና ኦነግ ብቻ ነበሩ ልሂቃንም የወታደር ኃይልም ከነሱ ነበር። ሌላው ወገን የኢትዮጵያ ብሔርተኛ  ወይም «አገር ወዳድ» ጎራ ኃይልም ልሂቃንም አልነበረውም። ይህ ልሂቃን ከአገር ፖለቲካ ጠፍቶ ነበር።

የጠፋው ምክንያት ይህ ልሂቃን ጎራ የረዥም ዓመት የራስ ማጥፋት ዘመቻ አካሄዶ ስለነበር ነው። ከ1950 አካባቢ ጀምሮ የኃይለ ሥላሴ ተማሪዎችና ልሂቃን በእርስ በርስ መተላለቅ በራስ ማጥፋት ምኞት መለከፍ ተጥቅቶ የራሱን ማጥፋት ስራ ብ1983 አብዮቱ አጥናቀቀ። እራሱን አንዴ አድሃሪ አንዴ ፍዩዳል አንዴ ኢህአፓ አንዴ ምኤሶን አንዴ ኢዲዩ አንዴ ደርግ ወዘተ እያለ እርስ በርስ ተፋጅቶ እራሱን ገደለ።

ለዚህም ነው ሽዐብያ ህወሓትና ኦነግ በ1983 በስልጣን ጉዳይ መደራደር ሲጀምሩ የኢትዮጵያ ብሔርተኛ ወቂል የፖለቲካ ወይም የጦር ኃይል ያልነበረው። ለኢትዮጵያ የሚቆምላት ልሂቃን አልነበረም። ልሂቃኑ ይህ ስራን ለብዙሓኑ ተውወው ግን ብዙሃኑ ስራውን በአቅሙ ሰርቷል።

ዛሬም የኢትዮጵያ ብሄርተኛ ልሂቃን ጎራ ከሞላ ጎደል የለም። ይህ ሊደንቀን አይገባም። የፖለቲካ ልሂቃን ባንዴ አይነሳም፤ የረዝም ዓመትና የትውልድ ውጤት ነው። የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ልሂቃን ጎራ በ1983 የራሱን ማጥፋት ዘመቻ አጠናቅቆ ከዝያ ወዲህ ኢህአዴግ እንዳይነሳ ብቻ ነው ያደረገው። ስለዚህ ይህ ልሂቃን ዛሬ በሽተኛ የቀጨጨ ከወላጆቹ ከአባቶቹ ተለይቶ ምንም ውርስ ግንኙነት ዬሌለው ህጻን ይመስላል።

ለዚህ የልሂቃኑ ችግር ምክንያት ይኢህአዴግ ጭቆና ብቻ ነው? በፍጹም! ቢሆን ኖሮ ቢያንስ በውጭ አገር ኢህአዴግ በማይደርስበት ቦታ ይህ ልሂቃን ጠንክሮ ይገኝ ነበር። ግን የለም። በተጨማሪ የቅንጅት የምርጫ 1997 ቀውስ የተፈጠረው በኢትዮጵያ ብሄርተኛ ልሂቃኑ መሆኑን እናውቃለን። ልሂቃኑ ባለመብሰሉ ምክንያት ያስከተለው የእርስ በርስ ቅራኔ ነው ቅንጅትን ያፈረሰው። ዛሬም አገር ውስጥም ውጭም የቅንጅት ርዥራዞችና ተከታዮቻቸው እየተፋጅን ነው። እነዚህ መረጃዎች ለኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ልሂቃኑ ድክመት በቂ መረጃ ናቸው።

ስለዚህ የኢህአዴግ ጭቆና ነው የኢትዮጵያ ብሄርተኛ ልሂቃንን ያደከመው ማለት አይቻልም። ኢህአዴግም ቢጠፋ ይህ ልሂቃን ጠንክሮ ይገኛል ቃልን እራሳችንን ማታለል ነው። የልሂቃኑ ውድቀት ረዝም ዓመት የፈጀ ውስብስብ ታሪክ ነው። በዚህ ረገድ ይህ ልሂቃንን ከሞት ለማስነሳት እንደዚሁ ረዝም ጊዜ ሊፈጅ ይችላል። አንድ ልሂቃን ጎራ ባንዴ መጎልበት አይቻልም። ግን እስከዛ ብዙሃኑ ልቆ ሄድዋልና መሪ ይፈልጋል።

ስለዚህ ወዴት ነው ማምራት የምንችለው? የጎሳ ብሄርተኝነት እንዲቀንስ፤ ጭቆና ኢፍትሓዊነት፤ የስነ መግባር እጦትና ሙስና በአገራችን እንዳይኖር፤ ፖለቲካና ሌሎች ጉዳዮችን በሰላም የምንወያይበት መድረክ የምንፈልግ ምን እናድርግ? አገራችን ህዝቦቿ በምትወደው በምታከብረው መንግስት እንድትገዛ የምንመኝ ምን እናድርግ? አገር ወዳድ መንግስት የምንፈልግ ምን እናድረግ?

በይፋ ንቅናቄዎች ድርጅቶች ፓርቲዎች ማቋቋም እንደማይሆን ግልጽ ነው! እስር ጽቃይ ሞትም ሊያደርስ ይችላል። በ50 ዓመት እራስ ማጥፋት ዘመቻ ምክንያት የደከመ የተቃዋሚው ልሂቃን እንደዚህ አይነቱን ጭቆና ሊቋቋመው አይችልም። ያለፉት 26 ዓመት ታሪክ ይህን አሳይቶናል። ከዚህ የተለየ የርቀቀ አካሄድ ያስፈልጋል።

ይህ አካሄድ ያለው የፖለቲካ ሥርዓት ማለትም ኢህአዴግ ውስጥ ገብቶ ውስጥ ሆኖ መታገል ነው። ዛሬ ኢህአዴግ ብቸኛ አቅም ያለው የፖለቲካ መዋቅር ስለሆነ ይህን መዋቅርን ተቆጣጥሮት የለውጥ አጋር ማድረግ ነው ስራችን የሚሆነው።

«አይሆንም» ይላሉ ተስፋ ቆራጮቹ! ህወሓት ይህን መቼም አይፈቅደም ይላሉ በዛው አፋቸው ህወሓት የአገራችን 8% ብቻ ነው የሚወክለው ይላሉ! ግን 8% በጣም ትንሽ ስለሆነ 92% የሆነው ህዝብ ትንሽ ብቃት ቢኖረውም ሁኔታውን ለመቀየር በቂ ነው። እንደ የሩስያ መሪ ቭላዲሚር ፑቲን ከነበረው ሥርዐት ውስጥ ሆነው ማንነታቸውን ደብቀው ሙሉ ስልጣን እስከሚይዙ ፕሬዚደንት ሆኖ ሩሲያን 180 ዲግሬ የቀየራት ኢትዮጵያ ውስጥም እንደዚህ ማድረ ይቻላል። መቼም እንደ እባብ ልባሞች እንደ ርግብም የዋሆች መሆን ያስፈልጋል! በመጀመርያ ካለው የፖለቲካ አዝማምያ ጋር አብሮ መሄድ ያስፈልጋል። ቀስ በቀስ ራስን ባለማጋለጥ የፖለቲካ ተከታይነትና ኃይል ማከማቸት ያስፈልጋል። በስልጣን ደረጃ ከፍ ባለ ቁጥር ባለው የስልጣን መጠን መጠቀም ፍላጎትን ማስፈጸም ይችላል። በዚሁ ረገድ ህሊና ያለው ሰው የፓርቲውን ፖለቲካ እየተከተለ ሰው ላይ ጉዳት ሳይፈጽም ኢፍትሃዊ ድርጊቶች ሳያደርግ በብልጠት ስራውን መስራት ይችላል። የፖለቲካ ተጎጂዎችንም ሊረዳ ይችላል።

ይህ አይነቱ ስራ ታላቅ የፖለቲካ ብስለትና ሙያ ይጠይቃል ከባድ ስራ ስለሆነ። ግን ለጊዜው በኢትዮጵያ የፖለቲካ ሁኔታ ብቸናው መንገድ ነው። አለበለዛ ቅጭ ብሎ ከእግዚአብሔር መብረቅ መጠበቅ ወይም ህዝባዊ አመጽ መጠበቅ ይሆናል። መቆጣጠር የማይቻል ለአገር ይበልጥ አስጊ የሆነ ችግርን መጠበቅ ይሆናል።

ስለዚህ በኔ አመለካከት የኢትዮጵያን ፖለቲካ ወደ ጥሩ መንገድ ለመምራት ፍላጎት ያላቸው የኢትዮጵያ ብሄርተኛ የሆኑ ግለሰቦች በኢህአዴግ ቀመጠቀም ብዙ አማራጭ የላቸውም። አማራጭ ሊሆን የሚገባው የኢትዮጵያ ብሄርተና ልሂቃን ድርጅት ከ50 ዓመት የራስ ማጥፋት ዘመቻው ገና አልዳነም። ይህ አይነት ድርጅት ወይም ንቅናቄ አጠንክሮ ለማቁቋም እስካሁን አልቻልነውም የረዝም ዓመት ስራ ነው የሚሆነው። ሌሎች አማራጮች እንደ መንግስት ላይ የዓለም አቀፍ ተጽእኖ ማስነሳት ወይም የተቃዋሚ ፓርቲ ማቋቋም እስካሁን አልሰሩምና ውጤታማ አልሆኑም። ስለዚህ ወደ መሳካት የሚችለው ስራ እንግባ፤ ኢህአዴግ ዙርያውን ሰርጎ ገብተን እንቆጣጠረውና በዛ መንገድ ለውጥ እናምጣ።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!