Tuesday 31 July 2018

ከኢትዮጵያ ብሄርተኞች (አንድነት ኃይሎች) የእርስ በርስ መጠፋፋት ታሪክ እንማር!

ኢትዮጵያዊነትን የምናራምድ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ባለፉት 60 ዓመታት በተደጋጋሚ እርስ በርስ መጣላት ሀገራችንን አደጋ ላይ መጣላችን ይታወቃል (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/07/blog-post_15.html)። መቼም በዚህ እፍረታችን ምክንያት የሀገራችንን ችግሮች በሌሎች (ጎሳ ብሄርተኞች፤ የውጭ ኃይሎች ወዘተ) ማሳበብ ሱስ ቢሆብንም እውነቱ የኛ ጥፋት መሆኑን መቀበል ግዴታችን ነው። ለሀገራችን ችግሮች ዘላቂ መፍትሄ የኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች አንድነት እና ታላቅ ተሳትፎ አስፈላጊ መሆኑ የታወቀ ነው።

ከዚህ ጽሁፍ ትምሕርት እንዲሆነን እና ወደ ፊት ስህተቶቻችንን እንዳንደግም ዘንድ ወደ ኋላ ሄጄ እኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች እርስ በርስ የተፋጀንበት ታሪኮችን ማስታወስ እወዳለሁ። ዛሬ በሀገራችን ፖለቲካ ታላቁ ጉዳይ የጎሳ ብሄርተኝነት ስለሆነ እኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ከታሪካችን ተምረን ለሚመጣው የፖለቲካ ሂደት በደምብ መዘጋጀት አለብን። አሁን ያለንን የታሪክ እድል መጠቀም ግድ ነው። እግዚአብሔር ከዚ በኋላ ሌላ እድል ላይሰጠን ይችላልና።

እንሆ ላለፉት 60 ዓመታት የኢትዮጵያ ብሄርተኞች እርስ በርስ መጣላት ታሪክ ዝርዝር፤

1. የነ መንግስቱ ነዋይ እና ግርማሜ ነዋይ የመንግስት ግልበጣ ሙከራ (1953)፤ አስፈላጊ ለውጦችን ለማምጣት ባለው መዋቀር ውስጥ በትእግስት ከመስራት ፋንታ ግርማሜ በውጭ ሀገር በተማረው «ማርክሲዝም» ፍልስፍና ተመስርቶ ወደ «ስር ነቀል ለውጥ» ወይንም አብዮት አመራ። ይህ የተከሰተው ኃይለ ሥላሴ ወደ ሀገራቸው ከተመለሱ ገና 18 ዓመት ካላፈ በኋላ ነው። ኢትዮጵያ ገና አቅም የሌላት ደሃ ሀገር ነበረች። ግርማሜ እና ደጋፊዎቹ ኃይለ ሥላሴ ወደ ውጭ ሀገር እንዲማሩ ከላኳቸው ተማሪዎች ነበሩ። ይህ ነበር የመጀመርያው ጊዜ የኃይለ ሥላሴ የፈረንጅ ትምሕርት ፖሊሲ በራሳቸው ላይ ጥቃት ያመጣባቸው። የኃይለ ሥላሴ መንግስት ከዚህ ተምሮ አስፈላጊ ለውጦችን ከማድረግ ፋንታ ስልጣንን ይበልት ሰበሰባ ለሰላማዊ የፖለቲካ መፍትሄ ከፍተቶችን ዘጋ።

2. የተማሪዎች ንቅናቄ፤ ከነመንግስቱ ነዋይ ግልበጣ ሙከራ በኋላም የኃይለ ሥላሴ መንግስት ተማሪዎችን ለትምሕርት ወደ ውጭ ሀገር መላክ አላቆመም። የኢትዮጵያን ባህል እና ትውፊት ከማስተማር ፋንታ የምዕራባዊ ፍልስፍና እና ሶሺያል ሳየንስ እንዲማሩ አደረገ። እነዚህ ተማሪዎች ኢ-ኢትዮጵያዊ አስተሳሰቦች ይዘው ወደ ኢትዮጵያ መንግስት እና ሌሎች መስርያቤቶች ገቡ። የቀለም ትምሕርት አለአግባብ በመደነቁ ምክንያት «የተማረ ይግደለኝ» የሚለው አባባል ተፈጠረ (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/12/blog-post_7.html)። ይህ እሳት እየተለኮሰም መንግስት በትምሕርትም ደረጃ በፍትህ በተለይም በመሬት ፍትህ ዘርፍ ምንም አላደረገም። የኃይለ ሥላሴ መንግስት የኢትዮጵያ ለረዥም ዓመታት መርዝ የሚሆናት ትውልድ እና ባህል ፈጠረ። የ«ጨቋኝ ተጨቋኝ» አስተሳሰብ እንዲሰፍን አደረገ። የመደብ እና የጎሳ ጦርነት እንዲጀምር አደረገ። ዛሬ የዚህን "legacy" ነው የወረስነው።

3. የደርግ አብዮት፤ በኃይለ ሥላሴ መንግስት ተሃድሶ የሚፈልጉ በርካቶች ነበሩ ግን እድሉ ሳይደርሳቸው የተማሪዎች ንቅናቄ የሚፈልገው ስር ነቀል አብዮት መጣ እና ሀገሪቷን አፈነዳ። በርካታ ልሂቃን ተገደሉ ተሰደዱ። ለኢትዮጵያ ብቻ ስያሆን ለማንም ሀገር የማይሆን የፖለቲካ ፍልስፍና ሰፈነ። መሰረታዊ ነገር እንደ «መሬት ለአራሹ» ወደ «መሬት ለመንግስቱ» ሆኖ ቀረ። ኢትዮጵያ በደምብ ቁልቁል መውረድ ጀመረች። የደርግ በኃይል የተመሰረተ ጨቋኝ አገዛዝ ለጎሳ ብሄርተኞች በንዚን ሆናቸው እና በደምብ መንቀሳቀስ ጀመሩ። ድሮ በቀላሉ በትናንሽ ሰላማዊ ለውጦች መስተካከል የሚችሉት የጎሳ ጉዳዮች ወደ ጦር ሜዳ ገቡ።

4. የኢዲዩ መፈራረስ፤ ማርክሲስት ያልሆኑት የደርግ ተቃዋሚዎች በኢዲዩ ድርጅት ስር ለመታገል ወደ ሱዳን ገቡ። ከሞላ ጎደል አንድ አቋም እና አንድ አመጣጥ ኖሯቸውም እርስ በርስ መስማማት ባለመቻላቸው ከትንሽ ጊዜ በኋላ ተበታተኑ። ይህ በአንድ አቋም ያላቸው ኢትዮጵያ ብሄርተኞች መካከል እርስ በርስ መጣላት ታሪክ እስካሁን እየተደጋገመ ነው።

5. የኢህአፓ፤ መኢሶን፤ ደርግ ግጭት፤ እንዴ ማንኛውም የማርክሲስት አብዮት አብዮተኞ የፍልስፍና፤ የጥቅም እና የስልጣን ልዩነቶቻቸውን በተብ መንጃ ነው እነ ኢህአፓ፤ መኢሶን፤ ደርግ እና ሌሎች የተወጡት። የእነዚህ ድርጅቶች አብዛኛው አባላት በ«አንድ ኢትዮጵያ» የሚያምኑ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ነበሩ። እነ ኢህአፓ በመገንጠል እናምናለን ቢሉም ብዙ ኤርትራ እና ትግራይ ብሄርተኞች ቢኖሯቸውም አብዛኞቻቸው ኢትዮጵያ ብሄርተኞች ነበሩ። መኢሶንም የኦሮሞ ብሄርተኞች ቢኖሩትም አብዛኛው በአንድነት ያሚያምን ነበር። ደርግም እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ስፍራ ነበር። ሆኖም የነዚህ ድርጅቶች መፋጃጀት ለጎሳ ብሄርተኞች ታላቅ ድል ሆነ። የኢትዮጵያ ብሄርተኛው እርስ በርስ ሲተላለቅ የጎሳ ብሄርተኛ እየቀረ ሄደ ካስፈለገ ወደ ሻዕብያ፤ ህወሓት እና ኦነግ ገባ። ቀይ ሽብሩ ካበቃ በኋላ የተቆሳሰለች ኢትዮጵያ ናት የቀረችው። በጎሳ ብሄርተኞች ለመገዛት ዝግዱ የሆነች ደካማ ኢትዮጵያ ናት የቀረችው። ደርግ ከስልጣን ሲወርድ የኢትዮጵያ ብሄርተኛ ልሂቃን ራሱን አጥፍቶ ርዝራዡ ብቻ ነው የቅረው። ብዙሃኑም የፖለቲካ ልቡ ተስብሮ እየተንገዳገደ ነበር። የኢትዮጵያ የወደፊት የጎሰኝነት ዘመን ተወሰነላት።

6. የመላው አማራ እና መላው ኢትዮጵያ ፓርቲዎች ግጭት፤ ደርግ ኤኮኖሚውን ገድሎ፤ ህዝቡን አጥፍቶ፤ የሶቪየት ህብረት ሲፈርስ ገንዘብ አጥቶ እነ ሻዕብያ እና ህወሓትን ወደ መንግስት አስገባ። የኢትዮጵያ ብሄርተኛው ጎራ እራሱን አትፍቶ ሜዳውን ሙሉ በሙሉ ለጎሳ ብሄርተኞቹ ተወ። እነሱም ደንግጠውም ቢሆን ያልጠበቁትም ቢሆን ሜዳውን ለመቆጣጠር ቶሎ ስራ ጀመሩ። የኢትዮጵያ ብሄርተኛ ጎራው ከድንጋጤው በኋላ ልደራጅ ሲል የለመደው አብሮ መስራት አለመቻል እርስ በርስ መጣላት በሽታው እንደገና ተነሳበት። «መላው ኢትዮጵያ» ይህን ወይንም «መላው አማራ» ይሁን አውራ ፓርቲአችን በሚለው ጥያቄ የኛ «ወታደሮች» በ«ጠላት ሜዳ» ላይ እርስ በርስ መጣላት ጀመሩ! ላለመስማማት መስማማት እና በጋራ ጥቅም አብሮ መስራት ፋንታ አንዳችን ብቻ ነው የሚቀረው ብለው እርስ በርስ ተፋጁ እና ሁለቱንም ድርጅቶች («መላው ኢትዮጵያም» «መላው አማራም») አደከሙ። የጎሳ ብሄርተኞች ከዳር ሆነው በሳቅ ሞቱ። ግን አሁንም እኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ጥፋታችንን ከማመን እነ ከመፍታት ፋንታ የጎሳ ብሄርተኞች ጥፋት ነው እነሱ ናቸው ያከፋፈሉን ብለን እንደ ህጻናት አሳበብን። እንሆ ችግራችንን ስላላመንን አልፈታነውም። አልፎ ተርፎ ይህን ስህተትን ወደፊት ለመድገም እራሳችንን አዘጋደን!

7. የቅንጅት ግጭት፤ ወደ ምርጫ 97 ስንገባ ጠ/ሚ መለስ ዘናዊ በተለያዩ ምክንያቶች ነጻ ምርጫ እናሸንፋለን ዓለም ያከብረናል ብለው ነጻ ምርጫ አወጁ። ድንቅ ውሳኔ ነበር አሁንም ይደንቃል። ግን በዛን ግዜ የኢትዮጵያ ብሄርተኛ ጎራው በራሱ ካመጣው ቁስሎቹ ገና አልዳነም ነበር። ጠንካራ ድርጅት ከሀገር ውስጥም ውጭም አልነበረም። የእርስ በርስ ጥሉ እንዳለ ነበር። በዚህም ምክንያት ነው የኢትዮጵያ ብሄርተኛው ወደ አንድ ስምምነት (ቅንጅት) የገባው በመጨራሻው ደቂቃ ከምርጫው ሶስት ወር በፊት! ግን አርፍዶ ቢዘጋጅም እንደምንም አድርጎ የኢትዮጵያ ብሄርተኛው ጎራ በምርጫው ተሳትፎ በሚደንቅ ሁኔታ አሸነፈ። ካሸነፈ ብኋላ የምናውቀው ፈተናዎች አጋጠሙት። እነዚህን ፈተናዎች በደምብ አድርጎ ወደቀ። በሰው የተፈጥሮ ባህሪ ጓዶች አብረው ሲታሰሩ ፍቅራቸው እና ትብብራቸው ይጨምራል። የቅንጅት መሪዎች ሲታሰሩ ጭራሽ እርስ በርስ ተጣሉ!ድርጅቱም ምን ያህል ባዶ እንደነበረ ታየ። ከላይ የተወሰኑ መሪዎች በ100 የሚቆጠሩ ነበሩ ከዛ በታች ግን መዋቅር የሚባል ነገር አልነበረም። መዋቅር ስል በይፋ ብቻ ሳይሆን በልብም አልነበረም። ስለዚህ መንግስት ቅንጅትን ሲያጠቃ በምርጫው 70% እንዳሸነፈ ድርጅት ጥቃቱን ጠንክሮ ከመቋቋም ይልቅ እንደ ምንም ድጋፍ የሌለው ድርጅት ቀለጠ። ቅንጅት አሸዋ ላይ የተገነባ ቤት መሆኑን አየን። ግን ለዚህ ሽንፈት ምክንያት እንደነበረ እንገንዘብ። የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ልሂቃን ከዛ በፊት ለ30 ዓመታት እርስ በርስ መፋጀት ታሪክ ምክንያት በጣም ሳስቶ ነበር። ለዚህም ነው ቅንጅት በተንሽ ግፊት የፈራረሰው። መሪዎቹ "cream of the crop" ሳይሆኑ ካለፈው 30 ዓመት የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ጎራ እርስ በርስ መጨራረስ የተራረፉ ነበሩ። ታሪካችን ምን ያህል እንደ ጎዳን አየን።

8. ዛሬ፤ አሁንም የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ጎራ እጅግ ደካማ ነው። አሁንም ሀገር ውስጥም ውጭም ብዙሀኑን በሚገባው የሚወክል ድርጅት የለውም። ግን ብዙሃኑ አለ ልሂቃን እየታገለ እንደሆነ የሚያሳየው እንደ ጠ/ሚ አብይ አህመድ አይነቱን ሰዎች ከዚህ ብዙሃን መውለዳቸው ነው።  እንጂ ከ27 ዓመት የጎሳ ብሄርተኝነት በኋላ ኢትዮጵያ እውነትም የብሄር ብሄረሰቦች እስር ቤት ብትሆን እና በርካታ የሀገር ብሄርተኛ ባይኖራት እንደ አብይ አይነቱ አይፈጠርም ነበር እንቋን ወደ ስልጣን መግባት። ግን ይህ ብዙሃን ልሂቃን ያስፈልገዋል። እነ ጠ/ሚ አብይ በርካታ እገዛ ያስፈልጋቸዋል። ቢያንስ እንቅፋት አያስፈልጋቸውም!

አንድ እንቅፋት ሊሆን የሚችለው አዲሱ የ«አማራ ብሄርተኝነት» (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/06/blog-post_14.html) ነው። የአማራ ብሄርተኝነት በኢትዮጵያዊነት አምናለው ይላል ግን  የኢትዮጵያ ብሄርተኛውን ጎራ የመከፋፈል እና የማድከም አዝማምያ አለው። የአስተያየት ልዩነት መልካም ነው በአንድ አንድ ነገር ሳይስማሙ አብሮ መስራት ይቻላል። ግን አሁን የሚታየው የአብሮ መስራት አዝማምያ ሳይሆን የጥሎ ማለፍ መንፈስ ነው። የአማራ ብሄርተኛው ጎራ አንዱ መፈከሩ የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ድርጅቶች ዋጋ የላቸውም ነው። ከኢትዮጵያ ብሄርተኛ ድርጅቶች ጋር አብሮ ከመስራት ያጣጥልዋቸዋል። ያው የነ ሻዕብያ፤ ህወሓት፤ ኦነግ ፎቶኮፕይ ማለት ነው። የህዝብን ብሶት በጎሳ ቤንዚን ለኩሶ የፖለቲካ ኃይል ማግኘት ነው። ልክ ህወሓት በመጀመርያ ነባር የጥግራይ ልሂቃንን እንዳጠፋ አንድ አንድ የአማራ ብሄርተኞች የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ድርጅቶችን ማጥፋት ይፈልጋሉ። እንደነ ኢህአፓ/መኢሶን/ደርግ የማርክሲስት ዜሮ ድምር ፖለቲካ ማለት ነው።

ይህ የሚመስልኝ ታሪክን መድገም ነው። የኢትዮጵያ ብሄርተኞች እንደገና እርስ በርስ ሲፋጁ የጎሳ ብሄርተኖች ስልጣን ይቆጣጠራሉ የኢትዮጵያ ብሄርተኛ ብዙሃን እንደገና መሪ አልባ ሆኖ ይጠቃል። ከታሪካችን ብንማር ይበጀናል። በዛሬው የፖለቲካ ለውጥ እግዚአብሔር የማይገባንን እድል ሰጥቶናል። እኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኛ ልሂቃን ምንም የሚጠቅም ነገር ሳናደርግ ከኢህአዴግ መሃል የለማ ቡድን ተነስቶ ለአንድነት መንፈስ ቆሟል። ታላቁ «ኢትዮጵያዊ» ዶናልድ ለቪን ደጋግመው እንዳሉት በርካታ እድሎቻችንን አበላሽተናል (https://scholarworks.wmich.edu/ijad/vol1/iss1/3/)። ይህን እድል ደግሞ ካበላሽን ታሪክ ለዘለዓለም ይወቅሰናል።

Monday 30 July 2018

የብሶት ፖለቲካ

የብሶት (grievance) ፖለቲካ በተማሪዎች ንቅናቄ ዘመን ከ«ጨቛኝ እና ተጨቛኝ» ፖለቲካ አብሮ ወደ ሀገራችን ገብቶ እንሆ ወደ 60 ዓመት ቆይቷል (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/02/blog-post_16.html)። ምንድነው የብሶት ፖለቲካ? ባጭሩ በብሶት፤ ንዴት፤ ቂም፤ ጭቆና፤ በደል ዙርያ የተመሰረተ ፖለቲካ ነው። በአሉታ (negativity) የተመሰረተ ፖለቲካ ነው። በሰለባ ወይንም ተጨቛኝ አስተያየት (victim mentality) የተመሰረተ ነው።

የብሶት ፖለቲካ መፈክሮች እንዲህ ናቸው፤

1. ተበድያለሁ ተጨቁኛለሁ (ማንንም በድዬ አላውቅም)
2. በዳዮቼ ሊክሱኝ ይገባል (እኔ ማንንም ልክስ አይገባም)
3. ዛሬ ላለሁበት ሁኔታ እና ችግር ሙሉ ጥፋተና ሃላፊነት የበዳዮቼ ነው (ዛሬ ላለሁበት ሁኔታ እና ችግር እኔ ምንም ሃላፊነት የለብኝም)
4. የበደሌኝን ማጥፋት ቢቻል ለሁላችንም ይበጀን ነበር
5. መበደሌን ያላመነ እንደ በዳይ ይቆጠር ሊወገዝ ሊጨቆን ይገባዋል

የብሶት ፖለቲካ ምንጭ ምንድነው? በመጀመርያ ደረጃ ምንጩ እውነተኛ ብሶት ነው። የሰው ልጅ በተለያየ ምክንያት ብሶት አለው፤ ይህን መካድ አይቻልም። ለምሳሌ ጭሰኛው መሬቱ ከሱ ወይንም ከአባቱ ወይንም ከአያቱ ተወስዶበት መሬቱን ለወሰደው እንዲገብር ተደርጎ ብሶት ይኖረዋል። ተጨቁኛለሁ ቢል ይገበዋል። የቤት ሰራተኛዋ አለአጋባብ ስራ ሲቆለልባት እንደ ባርያ ስትነዳ ቤተ ክርስቲያንም ለመሄድ ሳይፈቀድላት ሲቆይ ብሶት እየተጠራቀምባት ይሄዳል። ኦሮምኛ ተናጋሪው በቋንቋ ሲቀለድበት እንደ ዝቅተኛ ሰው ሲታይ ብሶት ይይዘዋል።

ግን በኢትዮጵያ የነበረው ያለው ብሶት እንደዚህ አይነቱ ብቻ አይደለም። ሁሉም ሰው በተለያዩ መልኩ ብሶት አለበት። በጎረቤት መካከል ግጭት፤ ቅራኔ እና ብሶት አለ። በአለካ እና ሰራተኛ፤ በአዛዥ እና ታዛዥ፤ በባልደረባዎች መካከል፤ በቤተሰብ መካከል (ምናልባትም ይህ ከሁሉም ይበልጣል) ወዘተ። በሰው ልጅ መካከል ግጭት እስካለ ድረስ ብሶት አለ። ግጭት ደግሞ በተለየዩ መልኩ አይቀርም።

ስለዚህ ጥያቄው ይህን የማይቀረውም ብሶት እንዴት ነው የምናክመው ነው። በርግጠኝነት ይህን ብሶት ወደ ፖለቲካ ምድር ማምጣት ብዙ ጊዜ አደገኛ ነው ፍትሃዊም ላይሆን ይችላል። የኃይለ ሥላሴ ተማሪዎች የተመረዙበት የማርክሲስት ኮምዩኒዝም ፖለቲካ ይህን ነው በመጀመርያ ደረጃ ያደረገው። ዓለምን ወደ «ጨቋኝ እና ተጨቋኝ» ከፋፍሎ ብሶትህን ተወጣ የሚል ፖለቲካ ነው። በዳይህን አጥፋው በማለት ነው። ታላቁ የደቡብ አፍሪካ መሪ ኔልሰን ማንዴላ እንዳሉት "dialectical materialism" (የብሶት ወይንም ጨቋኝ ተጨቋኝ ፖለቲካ መሰረት) ለነፃነት ታጋይ እንደ ፈንጅ ነው»። ይህ ማለት ኃይለኛ መሳርያ ነው ችግሩን የሚፈታ ብቻ ሳይሆን ዙርያውን በሙሉ ድምጥማጡን የሚያጠፋ። የፈንጅ ወርዋሪውይንም፤ ጠቅላላ ህብረተሰቡንም፤ ሌሎች ሀገራትም ሊያጠፋ የሚችል መሳርያ ነው! መቆጣጠር የማይቻል መሳርያ ነው። ያለንን ብሶት ወደ ፖለቲካ አምጥተን በጨቛኝ ተጨቛኝ የብሶት ፖለቲካ እናስተናግደው ከሆነ ሁላችንም ፉንጂ አፈነዳን ማለት ነው። ይህን ነው በሀገራችን ባለፉት 40 ዓመታት ያየነው። ሀገራችንን አፈንድደናል።

በሀገራችን ይህ የብሶት ፖለቲካዊ አሰተሳሰብ በመደብ፤ በጎሳ፤ በሃይማኖት ወዘተ ታይቷል። ዛሬም በሚያሳዝን ሁኔታ እየታየ ነው። አሳዛኝ ነው የምልበት ምክንያት ሁለት ነው፤ 1) ውሸት ነው፤ የሰው ልጅ እራሱን በዋናነት «ተበዳይ» ብሎ ከገለጸ ማንነቱን አጥቷል ማለት ነው። የሰው ልጅ ሊበደል ይችላል ገን «ተበዳይ» ማንነቱ ሊሆን አይገባም። 2) ይህ አስተሳሰብ ቅራኔን፤ ግጭት፤ ማፈናቀል፤ ግድያ ወዘተ ያሰፍናል ሀገርን ያፈርሳል እና ታላቅ እልቂት ያመጣል። እንዴት?

በመጀመርያ የብሶት ፖለቲካ ሁሉንም አቅመቢስ እና ተበዳይ ያደርጋል (victim)። ሁሉም ተበድያለሁ ይላል ማንም በደልኹኝ አይልም። ሁሉም ካሳ ይገባኛል ይላል ማንም የሚክስ አይኖርም። ሁሉም መቀየም ይገባኛል ይላል ማንም ይቅርታ አይልም። ሁሉም እራሱን አቅመ ቢስ (disempowered) አድርጎ ይቆጥራል ማንም እራሱን እንደ ጎለበተ (empowered) ሰው አይቆጥርም። ይህ ማለት ሁሉም ፈላጊ ሆኖ ሰጭ ወይም አቅራቢ የለም። ይህ አስተሳሰብ ግጭትን ያሰፍናል። ተበድያለሁ ሲል አዎን ብሎ ይቅርታ የሚለው ሲያጣ፤ ካሳ ይገባኛል ሲል የሚክሰው ሳይኖር፤ ሰለባ ነኝ ሲል ፍትህ ሳያገኝ፤ አቅም የለኝም ሲል የሚያጎለብተው ሳይኖር፤ ይህ መሬት የኔ ነው ሲል ሌላውም የኔ ነው ሲል ወዘተ የብሶት እሽቅድድም እና ግጭት ይሰፍናል።

ላለፉት 27 ዓመት ከኢትዮጵያ የሰፈነው የጎሳ አስተዳደር ይህን ክስተት በደምብ ያንጸባረቃል። ሁሉም ብሄሮች ተበድያለሁ አሉ። ለምሳሌ ኦሮሞ ብሄርተኛው ለ150 ዓመት ተበድያለሁ አሁን ቢሻሻልም ገና ዴሞክራሲ ያስፈልገናል፤ ካሳ ያስፈልገናል፤ ታሪክ መስተካከል አለበት፤ አዲስ አበባ የኛ ናት ወዘተ ይላል። ትግሬ ብሄርተኛውም እስካሁን በኢትዮጵያ የብሄሮች እስር ቤት ታስረን ነበር አሁን ነው ነፃ የወጣነው ግን አሁንም በነፍጠኛ እና ጠባብ እንጠቃለን ይላል። በደርግ እና ኃይለ ሥላሴ ዘመን የደረሰብን በደል ምክንያት ካሳ ያስፈልገናል ይላሉ። አዲሱ አማራ ብሄርተኛውም በአቅሙ ተበድያለሁ ለ27 ምናልባትም ለ40 ዓመት የተለያዩ ብሄሮች ሰለቦች ሆነናል ይላል። የሀገራችን ችግር በሙሉ በኛ ይሳበባል ያላል። ዘራችን እየጠፋ ነው "genocide" በኛ በተለየ መጠን ተፈጽሟል ይላል። ሌሎች ብሄር ብሄረሰቦች ነፍጠኛ እያሉ በየ ቦታው ያሳድዱናል ያፈናቅሉናል። ካሳ ይገባናል ይላሉ አማራ ብሄርተኛው።

ግልጽ ነው፤ ሁሉም ተበዳይ በመሆኑ እርስ በርስ ያጋጫል። ለስልጣን፤ ለጥቅም፤ ለመሬት ወዘተ በብሄር ደረጃ ይወዳደራል፤ ይጣላል፤ ይዋጋል፤ ይገዳደላል። የፖለቲካ ውድድሩ በጎሳ እና በብሶት ብቻ የተመሰረተ ነው። እንደዚህ አይነቱ ውድድር ደግሞ ከርዕዮት ዓለም ውድድር ይልቅ ቶሎ ወደ ግጭት እና ጦር ያመራል። እነዚህ ግጭቶች ደግሞ ሀገሪቷን ወደ መፈረካከስ ይወስዳሉ። መረጃውን ላለፉት ቢያንስ 27 ዓመት አይተነዋል። ልደገመው፤ የምለው «ቴኦሪ» አይደለም የብዙ ዓመት ማስረጃ አለን።

መፍትሄው ምንድነው ታድያ? አንዳንድ የጎሳ ብሄርተኞች ይቅርታ ብንጠየቅ፤ ታሪክ ቢስተካከልልን፤ መሬት ቢመለስልን ሁሉም ያበቃል ይላሉ! ግን እንደማይበቃ እናውቃለን፤ የሰው ልጅ አንዴ የሰለባ አስተያየት (victim mentality) ከሰፈነበት ከራሱ ውጭ የሚመጣ ነገር መቼም ከዚህ እስር አስተሳሰብ አይፈታውም። ከውስጡ ከልቡ ብቻ ነው ከሰለባ ወደ አቅም እና ሃላፊነት ያለው ሰው መቀየር የሚችለው። ምንም ይቅርታ እና ካሳ ይህንን ለውጥ ሊያመጣ አይችልም። የልብ ለውጥ ነው የሚያስፈልገው።

ይህንን የልብ ለውጥ እንዴት ይመጣል? ምሳሌ 1። የተበደኩኝ ጭሰኛ ከሆንኩኝ በዳዬን ማጥፋት አይደለም ማሰብ ያለብኝ። መበደሌንም ማቆም አይደለም ማሰብ ያለብኝ። ግቤ መሆን ያለበት ፍትሃዊ የሆነ ኑሮ እና ሁኔታ መፍጠር ነው። ግቤ አሉታዊ ሳይሆን ገምቢ መሆን አለበት። እንዲህ ቢሆን ኖር 40 ዓመት በፊት የጭሰኛ ችግር በ«መሬት ለመንግስት» (አሉታዊ - negative) ሳይሆን በ«መሬት ለአራሹ» (ገምቢ - positive) ይፈታ ነበር። ግን በብሶት ፖለቲካ አሉታዊ አስተሳሰብ ለእውነት የሆኑ ችግሮች የውሸት መፍትሄ ያቀርባል።

ምሳሌ 2። በጎሳ ወይንም ቋንቋ ደረጃ እኔ በቋንቋዬ እና ባህሌ መሰረት ነው መኖር የምፈልገው ከሆነ ያንን ነው ግብ ማድረግ። ሌላውን ጨቋኝ ብሎ መሰየም እና ለማጥፋት መነሳት የብሶት ፖለቲካ አካሄድ ነው። የኦሮሞ ብሄርተኛ ኦሮሚያ ለኦሮሞ የሚለው መፈከር አሉታዊ አካሄድ ነው። ኦሮሚያ ለኦሮሞ ማለት ሌላውን ማስወጣት ወይንም ሁለተኛ ዜጋ ማድረግ ስለሆነ። ሌላውን መጉዳት ስለሆነ። ግን ኦሮምኛ ሀገር ዙርያ ይነገር የሀገር ቋንቋ ይሁን ኦሮሞነታችን ሁሉም ውስጥ ይግባ ማለት ገምቢ የሆነ አመለካከት ነው። የብሶት ሳይሆን የገምቢ ፖለቲካ ነው። ይህ አስተሳሰብ ደግሞ ግጭት ሳይሆን ትብብር የሚጋብዝ ነው።

ስለዚህ ያሉንን በሙሉ ማሀበረሰባዊም ግለሰባዊም ብሶቶች በብሶት ፖለቲካ ሳይሆን በ«ገምቢ ፖለቲካ» ማካሄድ ነው ያለብን። (ጠ/ሚ አብይ «መደመር» ሲሉ ይህን ማለታቸው ይመስለኛል)። የብሶት ፖለቲካ የግጭት እና ህምም ምንጭ በመሆኑ ምክንያት ማስወገድ አለብን። ይህ ማስወገድ የሚጀምረው ከላይም ጠ/ሚ አብይ እንደሚያረጉት ከታችም እኛ ብዙሃን ማደረግ እንዳለብን። ከሁሉም ትምሕርት ደረጃ ይህ የብሶት እና የጨቋኝ ተጨቋኝ አስተሳሰብን አጥፍቶ ወደ ግምቢ አስተሳሰብ መቀየር አለበት። ከአሉታዊ ወደ ገሚቢ መሄድ አለብን። ይህን መልእክት ከሃይማኖት ተቋማትም መንሰራጨት አለበት። የህዝባችን አስተሳሰብ መቀየር አለበት። ወደ ገምቢ ፖለቲካ መምጣት አለብን።

Thursday 26 July 2018

ጉዞው ረዥም ነው

የዛሬው ግድያ የመጀመርያው አይደለም ግን በቅርብ ስለሆነ የተወሰነ ነፃነት የሰፈነው ስለ በፊቶቹ ገና ብዙ አልሰማንም። እኔ እንደ አብዛኛው ብዙሃን ከመንግስት ነክ ነገር ሩቅ ብሆንም በቅርቤ እንደዚህ አይነት ግድያ አጋጥሞኛል።

ያለፈው ነሐሴ ከጎተራ አዲስ አበባ ያለው ሃለሉያ ሆስፒታል ሆኜ አንድ ሰው እንደዚሁ በታቀደ ግድያ በጥይት ተመትቶ ሆስፒታሉ ገባ። ከተወሰነ ቀን በኋላ ሞተ። ከዘዶቹ እንደሰማሁት ምዋቹ ከኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ከጓደኞቹ ጋር ሆነ ሲመለስ ተኳጾች መቱት አንድ ጓደኛው ተጎድቶ አመለጠ።

ማን ሊገለው ይፈልግ ይሆን ሲባል ሟቹ በሙስና ጉዳይ ለመንግስት አካል መረጃ ሰጥቷል አሁንም ሊሰጥ ነበር አሉ። ቢሆንም ለኔ እንደዚህ አይነት "professional" ግድያ መኖሩ አስገረመኝ ምናልባትም አስደነገጠኝ። ብሀገራችን ያልተለመደ ነው በተለይ ፖለቲከኛ ባልሆነ ሰው ላይ።

ይህ ታሪክ ከዚህ በፊት ስላጋጠመኝ የዛሬው ግድያ በጣም አላስደነገጠኝም። ብዙዎች እንዳሉት ወደሽር ወቅት ገብተን ይሆናል ከዚህ ለመውጣት ጊዜ ይፈጃል። አዲሱ አመራር ስለ ደህንነት ነክ ጉዳዮች ከሁላችንም በላይ አውቂ ስለሆኑ መደረግ ያለበትን አበጥረው የሚያውቁ ይመስለኛል። ማድረግ መቻሉ ግን ሌላ ጉዳይ ነው።

ከኛ ከብዙሀኑ የሚጠበቀው አንድነት ነው። በፊትም ችግራችን አንድ አለመሆን ነው አሁንም እንዲሁ። በፊትም ችግራችን ሳር በመቀንጠስ እርስ በርስ መጣላት ነው አሁንም እንደዚሁ። የተከፋፈለ ቤት ይፈርሳል ወይንም በዚህ ጉዳይ አኳያ ለሽብር የተጋለጠ ነው። ስለዚህ ሰከን ያለ የፖለቲካ አካሄድ ለሁላችንም ይበጃል። እንበርታ፤ ጉዞው ረዥም ነው።

ግን ከሁሉም በላይ ለአቶ ስመኘው ነፍስ ይማር ቤተሰቡን ጽናት ይስጣቸው።

Tuesday 24 July 2018

የጠ/ሚ አብይ ነፃ ምርጫ ፍላጎት

በቅርብ ጠ/ሚ አብይ አህመድ ለምሁራን ባደረጉት ውይይት የነፃ የመድበለ ፓርቲ ምርጫ በሁለት ዓመት ውስጥ ማካሄድ እወዳለሁ ብለዋል። ምሁራኑ ቆሞ አጨበጨበ ተብለናል። እውነትም ነፃ ምርጫ ጥሩ ነው አብዛኞቻችን የምንመኘው ነው። ነገር ግን በቂ ቀድሞ ዝግጅቶች ካልተደረጉ ምርጫው የግጭት መፍትሄ ሳይሆን የግጭት ምንጭ እና ማባባሻ ይሆናል (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_8.html)።

በተለመደው የፖለቲካ «ቴኦሪ» የሀገር ራእይ በህገ መንግስት ይገለጻል። ስለዚህ አንድ አዲስ ሀገር ሲፈጠር (እንደ ኤርትራ 24 ዓመት በፊት) ወይንም ወደ «ዴሞክራሲ» ሲሸጋገር አንድ የሽግግር ውየንም ሽማግሌዎች ቡድን ይቋቋም እና የህዝቡን እና የልሂቃኑን አስተያየት እና ራእይ ይሰበስባል። በዚህ ሂደት መሰረት ህገ መንግስት ይደነገጋል (ወይንም ያለው ይታደሳል)። ህገ መንግስቱ እንደ ሀገሩ ህዝብ የመሃበራዊ ስምምነት ይሰራል። ይህን ተመስርቶ ምርጫ ይቃሄዳል ውጤቱም ይከበራል። ይህ ነው የቴኦሪው አካሄድ።

ግን አብዛኛው ጊዜ እንደዚህ አይሳካም! የቅርብ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ታሪኮች ይመሰክራሉ። ህገ መንግስት ተደንግጎ «ዴሞክራሲ» አልመጣም። ሌላ ጥሩ ምሳሌ የግብጽ ሀገር የቅርብ ታሪክ ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/blog-post_8.html)። ታሪኩ ባጭሩ እንዲህ ነው። ተቃዋሚዎች ለረዥም ዓመታት እርስ በርስ ባለመተማመን እና ባለመስማማት በጦር ስራዊቱ የሚደገፈው የሙባረክ (የሳዳትም) መንግስት በስልጣን ቆየ። ተቃዋሚዎች የማይስማሙበት ምክንያት ህብረተሰቡ የተከፋፈለ ስለሆነ ነው። «ለዘብተኛ» ሙስሊም፤ «አክራሪ» ሙስሊም»፤ ክርስቲያን፤ ሃብታም፤ ደሃ፤ ኮምዩኒስት፤ ነጋዴ እያለ ተከፋፍሏል ክፍፍሉ በፖለቲካ ፓርቲዎች ይንጸባርቃል። ሙባረክም ሲገዛ አንዱን ጎራ ከአንዱ ጎራ እያጣላ ወይንም ባላቸው ጥል እየተጠቀመ ነበር።

ከዓመታት በኋላ በ2003 ተቃዋሚዎቹ ተስማሙና ይህ ስምምነታቸው የህዝብ አብዮትን ለማካሄድ እና ለማሳካት አበቃቸው። የተቃዋሚው ልሂቃን እና ብዙሃን የሙባረክን በጦር ኃይሎች የተመሰረተውን መንግስትን ገለበጠ። ዓለም አጨበጨበ። ተቃዋሚዎች ተሰብስበው ምርጫ ለማድረግ የሚያስፈልጋቸውን ቀድሞ ስምምነቶች አድርገው ምርጫ አካሄዱ። «ለዘብተኛ/አክራሪ» የሚባለው የሙስሊም ወንድማማቾች ፓርቲ አሸነፈ እና በፓርቲዎቹ ስምምነት እና ባለው ህገ መንግስት መሰረት ስራ ጀመረ። ግን ሌሎቹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሙስሊም ወንድማማቾች አገዛዝን እየተጠራጠሩ እየተቃወሙ መጡ። ወደ የከረረ እና የማይፈታ ግጭት ገቡ። መጨረሻ ላይ እነዚህ ፓርቲዎች እና ተከታዮቻቸው ይህ የሙስሊም ወንድማማቾች መንግስት ከሙባረክ መንግስት አይሻለንም ብለው ደመደሙ። መጀመርያ ላይ የገለበጡት ጦር ኃይልን እባካችሁ ተሳስተን ነበር ይህን መንግስት ገልብጡልን ብለው ጠየቋቸው። «ዴሞክራሲ» በግብጽ አበቃ። ዛሬ የግብጽ ጦር ኃይሎት ተመልሰው የአምባገነን ስርአት መስርተዋል።

ይህ ታሪክ የሚያስተምረን ሁለት ነበር ነው። 1) «ዴሞክራሲ» እና «ምርጫ» በራሱ ፍቱን አይደለም በሀገሩ ራእይ ቀድሞ መስማማት ያስፈልጋል። 2) የሀገሩን ራአይ የሚገልጽ ህገ መንግስት ወይንም ሌላ ቀድሞ ስምምነት ቢራቀቅም የልብ ስምምነት ከሌለ በወረቀት የተጻፈ ዋጋ የለውም። ለምን ብነል ይህን ስምምነት የሚያስከብር የበላይ ኃይል የለም። ሀገ መንግስቱን በግድ አክብሩ የሚል የዓለም የበላይ መንግስት የለም! ከስምምነቱ በኋላ የልብ ስምምነት ባለመኖሩ አንዱ የስምምነቱ (ግዙፍ) አካል ሌቀዳደው ከፈለገ ምንም ማድረግ አይቻልም። ስምምነቱ የሚደነገገው ሁሉም የተስማሙበትን እንዲያቁ ነው እንጂ በግድ ለማስከበር አይደለም።

ይህን ሁሉ ተገንዝበን ጠ/ሚ አብይ ነፃ ምርጫ ላማካሄድ መጀመርያ ሀገር አቅፍ ራእይ እንዲመሰረት ማድረግ አለባቸው። ቴኦሪው እንደሚለው የተለያዩ ህዝብ ወቃዮችን ሰብሰበው ስለ ህገ መንግስቱ እና ምርጫው አካሄድ ስምምነት እንዲኖር ማድረግ አለባቸው። የልብ ስምምነት እንዲኖር ማድረግ አለባቸው። ልድገመው፤ የልብ ስምምነት ማድረግ አለባቸው። ይህን በተወሰነ ወራት ማድረግ ይችላሉ ወይ ነው ጥያቄው።

አንዱ ትልቅ እንቅፋት የሚመስለኝ በአሁኑ ኢትዮጵያ በቂ ህዝብን የሚወክል ተቋማት የሉም። ተቃዋሚ ፓርቲዎች እጅግ ደካማ ናቸው። ማንን እንደሚወክሉ እነሱም እኛም ለማወቅ ይከብደናል። አቅምም መዋቅርም የላቸውም። ተከፋፍለዋልም። በተጨማሪ ሁለቱ ትልቅ የፖለቲካ ጎራዎች የኢትዮጵያ ብሄርተኞች እና የጎሳ ብሄርተኞች የተራራቁ ናቸው። እንኳን እርስ ብሰር ውስጣቸውም አይስማሙም አንድ ሀገራዊ ራእይ የላቸውም።

በኔ እየታ በዚህ ጉዳይ ላይ ብዙ ስራ ይጠበቃል። ተቃዋሚዎች መጎልበት አለባቸው። ምናልባት 1500 ፊርማ ፋንታ 100,000 ፊርማ ነው የሚያስፈልፈው እንደ ተቃዋሚ ለመመዝበብ ማለት ያስፈልግ ይሆናል በግድ ትብብረና አቅም ለማጎልበት። ምናልባት ከመንግስት የተወሰነ ድጎማ ሊያስፈልጋቸው ይችላል። ዋናው ግን የመወያያ መድረክ እና ጊዜ፤ በተለይም ጊዜ፤ ያስፈልጋቸዋል። ምናልባት መጀመርያ የከተማ እና የክልል ምርጫዎች እንደ ሙከራ ማካሄድ ያስፈልግ ይሆናል። እንደዚህ አይነት ብዙ ነገሮች መታሰብ አለባቸው። ይህን ሁሉ ስል ደግሞ የኢህአዴግ ውስጣዊ ጉዳይ አለ…።

ስለዚህ ነፃ ምርጫ ሁላችንም የምንፈልገው ነገር ቢሆንም እዛ ለመድረስ ሂደቱ ትልቅ ጥንቃቄ ያስፈልገዋል። ቀድሞ ሁኔታዎች በደምብ በማያሻማ ሁኔታ እስኪሟሉ ምርጫ አለማካሄድ ነው የሚመረጠው። ዋናው ነበር ምርጫው ሳይሆን የህዝብ ለህዝብ በሀገራችን ራእይ ያለ ስምምነት ነው። ያንን ስምምነት በትክክሉ ገደረስንመት ሌላው ሁሉ በቀላሉ ይሳካል።

Wednesday 18 July 2018

ለመላው ለሀገራችን ጤንነት የአዲስ አበባ ህዝብ እንደ ከብት መነዳት አቁሞ ለፖለቲካ ህልውናው ሃላፊነት መውሰድ አለበት

የአዲስ አበባ ህዝብ እንደ ማንኛውም የኢትዮጵያ ህዝብ ለረዥም ዓመታት በማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ጭቆና ተጎድቷል። ከቤቱ ከመረቱ ከሰፈሩ ተፈናቅልዋል፤ መሬቱ ለባለ ሃብቶች አለ አግባብ ተሰጥቷል፤ ከከተማ ውጭ ባዶ መሬት ላይ ተጥሏል (ከገበሬ የተነጠቀ መሬት)፤ ውሃ መብራት ወዘተ ቢከፍልበትም አብዛኛው ጊዜ ይቋረጥበታል፤ ደካማ የመንግስት አገልግሎት ነው ያሚሰጠው፤ ጉቦ አምጣ ተብሎ ይገደዳል ወዘተ። ይህ ሁሉ እየደረሰበት ከሞላ ጎደል ዝም ብሏል።

ከአዲስ አበባ ውጭ ቄሮ፤ ፋኖ ወዘተ ላለፉት ሶስት ዓመት የፖለቲካ ለውጥ እንዲመጣ ኢህአዴግ ላይ ታላቅ ህዝባዊ ጫና አድርገዋል። የኦሮሚያ እና የአማራ ክልል ገዦች የሆኑት ኦህዴድ እና ብአዴን ደግሞ ኢህአዴግን ከውስጥ ተቆጣጥረው ይህ ለውጥ እንዲከናወን በመሪነት ደረጃ ሰርተዋል። ይህ ሁሉ ሲሆን ግን የአዲስ አበባ ህዝብ ከሞላ ጎደል ብዙ አላደረገም ምናልባትም ተመልካች ነበር ማለት ይቻላል።

በርግጥ የአዲስ አበባ ህዝብ በፖለቲካ በተለይም በተቃውሞ ሰልፍ አይነት እንቅስቃሴዎች አለመሳተፉ ጥሩ ምክንያቶች አሉት። ትልቅ ከተማ ስለሆነ ህዝቡ ከተለያዩ ቦታዎች የሰፈረ ስለሆነ መተማመን፤ አብሮነት እና መደራጀት ከባድ ነው። የቅንጅት ጊዜ አመጽ እና ተከትሎ የመጣውን የመንግስት ጭቆናን በደምብ ያስታውሳል። በተወሰነ ደረጃም በደርግ ዘመን የነበረውን ቀይ ሽብርን ህዝቡ አልረሳም። አልፎ ተርፎ አዲስ አበባ ጥቅጥቅ ያለ ከተማ በመሆኑ ችግር ከመጣ እልቂቱ ብዙ እንደሚሆን ህዝቡ ያውቃል። በዚህ ምክንያቶች የአዲስ አበባ ህዝብ በፖለቲካው አንጀቱ እያረረ ቢሆንም ዝም ብሏል።

አሁን ግን የፍርሃት ዘመን አልፏል የነፃነት ዘመን ነው ተብሎ የአዲስ አበባ ህዝብ ለጠ/ሚ አብይ ድጋፍ ተብሎ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ አካሄደ። ይህ ጥሩ እርምጃ ነበር ግን ከመቶ እርምጃዎች ገና የመጀመርያው ነው። የሚቀጥለውን እርምጃ መውሰድ አለበት፤ የአዲስ አበባ ህዝብ ለራሱ የፖለቲካ ህልውና ሃላፊነት መውሰድ መቻል አለበት። ክፍለ ሀገር በሚደረገው ወይንም ፖለቲከኞች በሚወስኑለት ዝም ብሎ መነዳት ማቆም አለበት። የራሱን ውሳኔዎች ወስዶ ማስረገጥ አለበት። ይህን ማድረግ ያለበት ለራሱ ብቻ ሳይሆን ለመላው ለሀገሪቷ ጤንነት ነው። አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ቁንጮ በመሆኗ ለመላው ሀገሪቷ አቋሟን የማሳየት እና የማስረገጥ ሃላፊነት አለበት። አለበለዛ አዲስ አበባ የሙስና፤ የሃላፊነት አልባ፤ የማጭበርበር፤ የተገዥ ወዘተ ስፍራ ይሆንና ለመላው ኢትዮጵያ ፖለቲካ እንደ ቻንሰር ትሆናለች።

የአዲስ አበባ ህዝብ በፖለቲካ ህልውናው ሃላፊነት መውሰድ አለበት ማለት ምንድነው? ባጭሩ አቋሙን እና ፍላጎቱን ለማስረገጥ በፖለቲካ መልኩ መደራጀት አለበት። የአዲስ አበባ የፖለቲካ ድርጅትን ማቋቋም አለበት ወይንም በሌላ የፖለቲካ ድርጅት ስር ሆኖ አቋሙ በደምብ እንዲንጸባርቅ ማድረግ አለበት።

ዛሬ የአዲስ አበባ ህዝብ ብዙ አንገብጋቢ የህልውና ጉዳዮች አሉት። የነባሩን ደካማ አስተዳደር ከነሙስናው እና ሌብነቱ ማስቀየር አለበት ሃላፊነት እና ግልጽነት እንዲሰንፍ ማድረግ አለበት።  ከከተማው ዙርያው ያለው ከኦሮሚያ ክልል ያለው ግንኙነትን ማስተካከል አለበት። ለሚመጡት ረዥም ዓመታት ሰው ከበየ ክፍለ ሀገሩ እንደ ጎርፍ ወደ አዲስ አበባ ስለሚገባ እንዴት ነው የከተማው መስፋፋት የሚስተናገደው? በምን መልኩ ይስፋፋ የሚለው ትልቅ ጥያቄ ነው። የከተማው ጠረፍ ይስፋ ወይንም እንድ ሆኖ ሁለት መንግስት ያለው «ሜትሮፖሊታን» ከተማ ይሁን? የኦሮሚያ «ልዩ ጥቅም» የሚባለው ጉዳይ ይስተናገድ አይስተናገድ በምን መልኩ የሚለው ትልቅ ጥያቄ ነው። ለተፈናቀሉት የኦሮሚያ ገበረዎች የአዲስ አበባ ህዝብ እዳ አለው ወይንም የስርአቱ እዳ ነው የከተማውም ህዝብ ምናልባትም ይበልጥ ዋጋ ከፍሎ ስለተፈናቀለ (ከውድ መሬት ማለት ነው)? ኦሮምኛ የአዲስ አበባ ሁለተኛ ቋንቋ ይሁን ውየንስ በቂ ተናጋሪ የለውም ወይንም መጀመርያ የፌደራል ቋንቋ ይሁን። መሬት መሸት መለወጥ ይፈቀድ እና የመንግስት ማፈናቀል እና በሊዝ መስጠት ያቁም የመሬት ገበያው ይጠራ ዘንድ?

እነዚህ እና በርካታ ሌሎች አንገብጋቢ ጉዳዮች ስላሉት የአዲስ አበባ ህዝብ እነዚህን ማስተናገድ የሚችለው በመደራጀት ብቻ ነው። ለምን በነፃ ምርጫ ህዝቡ ፍላጎቱን አይገልጽም ትሉ ይሆናል። በመጀመርያው ነፃ ምርጫ እንዲኖር የህዝቡ ግፊት ያስፈልጋል እንጂ እነ ጠ/ሚ አብይ ዝም ብለው ሊያደርጉት አይችሉም። ብዙ የፖለቲካ ጫናዎች አሉባቸው ድርጅታቸውም መንግስቱም ገና አልጠራምና የማጣራት ስራ ላይ ናቸው። ግን ህዝቡ ቢደራጅ እና ጉዳዩን ቢገፋበት ለነ ጠ/ሚ አብይ ታላቅ እርዳታ ነው ይሚሆነው። እንደዚህ አይነቱን እርዳታ ይፈልጉታል ይጠቅማቸዋል የሚያስቸግሯቸውን ኃይሎችን ለማስወገድ ይጠቅማቸዋል።

በመጨረሻ ይህንን የጻፍከው በአዲሱ ከንቲባ ሹመት ተነስተህ ነው ትሉኝ ይሆናል። እውነት ነው! በርካታ ሰዎች ይህን አሿሿም ሲቃወሙ ስምቼአለሁ። ግን የተለመደው የህፃን ለቅሶ መቃወም ነው የሰማሁት። እንደ ሚና እና ሃላፊነት የሌለው ዝም ብሎ ማልቀስ ትርጉም የለውም። ችግር ካለ እርምጃ መውሰድ ነው አለበለዛ እንደ ህፃን ታሳዥ ሆኖ መቀር ነው። ባህላችን መቀየር አለበት። አሁን ለመነጋገር እና ለመደራጀት ሜዳው ክፍት ነው። ስለዚህ የአዲስ አበባ ህዝብ መሪዎች፤ ባለ ሃብቶች፤ ሽማግሌዎች፤ ፖለቲከኞች ወዘተ ተሰብስበው ጉዳዩን ተነጋግረውበት ለህዝቡ ህልውና ግድ የሆነውን የአዲስ አበባ ህዝባዊ ድርጅት ያቋቁሙ። «ዴሞክራሲ» ይህ ማለት ነው!!

Monday 16 July 2018

Understanding Ethnic 'Soft Nationalism' for Ethiopian Nationalists

I find in our discussions of the "ethnic question" - of Ethiopian vs ethnic nationalism and the various shades in between - a lack of understanding of the various shades between, which we normally call 'soft nationalism'.

For Ethiopian nationalists, there are three spots on the Ethiopian - ethnic nationalist spectrum. These are 1) radical ethnic nationalists who want nothing but secession, 2) those who like the radicals consider Ethiopia a prison of nations but consent stay within Ethiopia so long as Ethiopian satisfies their demands, and 3) Ethiopian nationalists.

But the situation is of course far more complex - the spectrum is not discrete with three spots - it is continuous - various shades, like I said above. And, more importantly, individuals and even groups shift often from one position on the spectrum to another. Their opinions are not fixed in stone - they change depending on various factors.

I will use an example from Quebec 'ethnic' nationalism in Canada, which I've previously discussed here (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2017/05/using-canada-to-understand-ethiopian.html). Before having given up on their dream of secession, which has become impossible due to demographic changes, Quebec nationalists used to monitor public opinion polls in order to time when to call a referendum on secession. Generally speaking, when the economy was good, polls would indicate relatively low support for secession, say 35%. This would not be a good a time to call a referendum. But when the economy dipped, support for secession would pass the 50% mark, reaching 60% or so. In this situation, if the timing was right, the Quebec nationalist party would win the provincial election and soon hold a referendum. This was the political pattern in Quebec from the early to mid 1970's to a few years ago.

The interesting point here for us Ethiopian nationalists is why the support for secession would range from 35% to 60%. Who are these people that change their minds? Are they ethnic nationalists? Or ethnic nationalists one day and Canadian nationalists the next? What makes them change their minds? Is it just the economy or are there other factors.

This group of people is what I call here the soft nationalists. And you can imagine that they were the primary target of politicians on both sides of the Quebec secession debate since the hardcore ethnic nationalists and hardcore Canadian nationalists were pretty much reliable in their opinions. But whoever managed to get the soft nationalist 'swing vote' would win. You can see that the soft nationalist constituency is extremely important in the struggle between country and ethnic nationalism.

Though we have had no polls taken in Ethiopia, anecdotally we have seen the same kind of thing happen in Ethiopia in the Abiy Ahmed era. Some Oromos who only some months ago were ethnic nationalists, because of the ascendancy of Oromos such as Abiy and Lemma Megersa to political prominence, and because of their positive and empowering rhetoric, have changed positions from ethnic nationalism and moved towards Ethiopian nationalism. However, if circumstances change, these people could swing back to ethnic nationalism.

What is the mindset of soft nationalists? They like all of us identify to some degree with their ethnicity and to some degree with Ethiopianism. Various circumstances can change which identification they lean towards. For example, if the economy is good - if they are happy - they tend to prefer the status quo. If their is some sort of ethnic conflict, this will push them to identify more towards their ethnicity. If some prominent Ethiopians start spewing anti-Oromo rhetoric they will get insulted and move towards their ethnicity. If they see Oromos in positions of leadership, or if they see Afan Oromo and other aspects of their identity prominently featured in our politics and culture, they will move towards Ethiopian nationalism. This is basically how soft nationalism works - it is fluid based on various factors.

Here I will add another example from recent Ethiopian history - that of Eritrea. When Eritrea was confederated with Ethiopia, a vast majority of Eritreans happily supported this move and considered themselves Ethiopia. As various factors changed negatively, including the ending of the confederation, but most importantly the terror of the Dergue regime, the huge support for Ethiopia turned towards support for secession! What a turnaround and what a lesson, if we would learn from it.

It's clear that this soft nationalist constituency group is very important for Ethiopian nationalists in our struggle against radical ethnic nationalism and the conflict that it generates. It is important that in we focus on soft nationalists in our political discourse to ensure that they come to and remain on the side of Ethiopian nationalism and to ensure that we don't push them into the arms of ethnic nationalists. How do we do this?

1. Ensure good governance and a decent economy. The Dergue basically pushed Eritreans out by making Ethiopia an unlivable country for all. While Ethiopian nationalists react to this via civic protest, soft nationalists react to such stress by becoming more ethnic nationalist.

2. Ensure the ethnic demands of soft nationalists are addressed. Some might call this 'appeasement', I would call it political realism. For example, given at least 35% of Ethiopia's population is Oromo-speaking, making Afan Oromo an official federal language makes sense not just as appeasement but to strengthen Ethiopia.

3. Ensure diplomatic rhetoric around the issue of ethnic nationalism and avoid statements that ethnic nationalists can use to swing soft nationalists their way. For example, if someone insults or says something considered insulting about Oromos, this will be eagerly used as political fodder by the ethnic nationalists to illustrate that Ethiopian nationalists are racists and elitists. So this must be avoided at all costs. I should add here that I have found certain officials of Patriotic Ginbot 7 especially adroit at this tactic (see this article: http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/11/some-basics-on-interacting-with-ethnic.html). As an aside, during the two Quebec referendum campaigns, the ethnic nationalist side would careful monitor all statements by Canadian nationalists looking for some sort of insult or slight that they could use in their campaign. At the same time, the Canadian nationalist side would expend significant resources trying to prevent this!

So, to sum up, there is such a political phenomenon as soft nationalism. For the Ethiopian nationalist constituency and leadership, it is important to understand this and address soft nationalists concerns in order to bring them towards Ethiopian nationalism. This strategy is in my opinion a must in keeping radical ethnic nationalism at bay in Ethiopia.

Sunday 15 July 2018

የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ጥፋታችንን ካላመንን ካላስተካከልን ኢትዮጵያን ዳግም እንሸጣታለን

ያለፉት 60 ዓመት የኢትዮጵያ ብሄርተኛ የፖለቲካ ጎራው ታሪክ እጅግ አሳዛኝ እና አሳፋሪ ነው። ከዛ በፊት እስከ ወደ 1955 ሀገራችን ዓለም ዙርያ የተከበረች ነበረች። በዲፕሎማሲ፤ በሀገራዊ ኃይል ወዘተ ከአቅሟ በላይ የምትሰራ ነበረች። አንድ አንድ ምሳሌዎች፤

1. የበርካታ የዓለም ሀገሮች ተቃውሞ በላቀ የዲፕሎማሲ ስራ አሸንፋ ኤርትራን ወደ ኢትዮጵያ መለሰች። ይህ የዲፕሎማሲ ድል ከሀገራችን ከአቅማችን አስር እጥፍ በላይ ነበር ግን አደረግነው።

2. የአፍሪካ ቁንጮ ሆንን ሁሉም የአፍሪካ ሀገራት እኛን እንደ ምሳሌ ያይን ነበር። በዲፕሎማሲ እና ሀገር ኃይል ደረጃ ብቻ ሳይሆን በታሪክ እና ባህል። ይህ ክብሬታ ለኢትዮጵያ ብዙ ጠቅሟታል።

3. በዓለም ዙርያ ያሉት ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያኖች ስብሰባ አቀደች የኦሪዬንታል ኦርቶዶክስ ስብሰባውን አከናወነች ስምምነቶች አስፈጸመች።

ከ1955 አካባቢ በኋላ ግን እኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኖች እርስ በርስ በመጣላት ሀገራችንን ድራሹን አጥፍተናል። መጀመርያ አስፈላጊ የፖለቲካ ለውጦች ባለማድረግ ቀጥሎ ልዩነቶቻችንን በጡንቻ በማካሄድ ሀገራችንን አሳልፈን ለጎሳ ብሄርተኞች ሰጠን። የመጨረሻ ውጤት ምን ሆነ ሻዕብያ እና ወያኔ የሀገራችን 10%ን ወክለው ኢትዮጵያን ተቆጣጠሩት። ይህ ለኛ 90% እጅግ አሳፋሪ ክስተት ነበር አሁንም ነው።

ይህ ታሪክ እንዳለ ሆኖ አሁን ያለፉትን ስህተቶቻችንን ለማርም የሀገራችን ሆደ ሰፊ ብዙሃን እና እግዚአብሔር ዳግም ለማረም እድሉን ሰጥተውናል። ሆንም አንታረምም ብለናል። ዋናው እና መሰረታዊ ችግራችን ያለፉትን አሳፋሪ ድርጊታችንን አለማመናችን ነው ሰው ችግሩን ካላመኑ መፍትሔ አያገኝምና። ጥፋቶቻችንን ላለማምን እና ለመደበቅ ብለን ይመስለኛል ሁል ጊዜ ለችሮቻችን ወያኔ፤ ሻዕብያ፤ ኦነግ፤ «አሜሪካ»፤ ሩሲያ፤ ኤርትራ፤ «አራብ ሀገራት» ወዘተን የምንወቅሰው። እኛ የገዛ ቤታችንን በር ከፍተን እነዚህ ደብተው እንደፈለጉት ሲያደርጉ በራችንን እንዴት ተከፈተ እንዝጋው ከማለት ለሚን ይገባሉ ብለን መጮህ! ዋናው ጣፍቱ የኛ እንደሆነ እናውቃለን ግን እፍረታችን ከባድ ነው መሸሽ ብቻ ነው የምንፈልገው።

ለማስተዋስ ያህል ባለፈው ኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት አንድ የኤርትራ የጦር አዛዥ ያለው ነገር አለ። አንድ ኤርትራዊ አስር ኢትዮጵያዊ ዋጋ አለው ብሎ ፎከረ። ይህ አዲስ ፉከራ አልነበረም በደርግ ጦርነት ላይ የተመሰረተ ነው። የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ምን ያህል እንደተናቁ ነው የሚያሳየው። ድሮ ኤርትራ በሰላም ያጠቃለልን ዛሬ ይቀልዱምን ጀመረ። እስከ ዛሬ በጦር ሜዳ ብቻ ሳይሆን በሌሎች የፖለቲካ ዋይንም የንግድ ዘርፎች በሙሉ ኤርትራዊዎችም ትግሬዎችም እደዚህ ያስባሉ። እኛ ደደብ አህዮች እነሱ አስር እጥፍ ጎበዝ። ከኢትዮጵያዊዎች ብልጥ፤ ጠንካራ፤ የተማርን ወዘተ ነን ብለው ያስባሉ። ይህ የተሳሳተ አስተሳሰብ ግን የነሱ ጥፋት አይደለም። በፍፁም የነሱ ጥፋት አይደለም። እኛ እርስ በርስ ተጨራርሰን እራሳችንን ከታላቅ ህዝብ እና ሀገር ወደ ደካማ ለማኝ ስላወረድን እነሱ የሚያዩትን እውነታ ነው የሚናገሩት። ይህ ለኛ እጅግ አሳፋሪ ነው።

የሰው ልጅ ግን እፍረቱ ስለሚያሳምመው ሊደብቀው ይፈልጋል። ለችግሮቹ ሃላፊነት ከመውሰድ ሁል ጊዜ በውነትም በውሸትም ሌሎችን ይወነጅላል። እኛም አሳፋሪ ድርጊቶቻችንን እና ውድቀታችንን ለመደበቅ ያህል ለ27 ዓመት መጀመርያ ሻዕብያን፤ ኦነግን፤ ወያኔን ወዘተ እየወቀስን ቆይተናል። አሁንም እግዚአብሔር የማይገባንን ጠንካራ የድሮ ዘመን አይነት ኢትዮጵያዊ መሪ ልኮልን አሁን ላሉን ችግሮች ህወሓትን እንወቅሳለን! እንደ ወቀሳችን መጠን ህወሓት ማንም የማይሳነው ግዙፍ ኃይል እንዲመስለን አድርገናል! (ግን 6% ነው የሚወክለው እንላለን!) የራሳችንን ድክመንት ለመሸፈን ላለማየት ለህወሓት የሌለውን አቅም ፈጠርንለት የሌለውን ጥንካሬ ሰየምንለት።

አሁንም እዛው ላይ ነን። አሁንም ከኢትዮጵያ ብሄርተኛ ፖለቲከኛ ተንታኝ አስር ጽሁፎች ካነበብን አስሩም ስለ «ሌሎች»፤ ወያኔ፤ ጎሰኞች፤ ኦነጎች ወዘተ ለቅሶ ነው። እንጂ አንድም ስለራሳችን ጥፋቶች እና ማረምያኦች የሚናገር የሚጽፍ የለም። ኢሳትን ከተመለከትን ስለ«ጠላት» ለቅሶ ነው። ጋዜቶች ሌሎች ማህበራዊ ሚዲያዎች እንዲሁ። የኛ የ«ተፎካካሪ» ድርጅቶች ወሬም እንዲሁ ምናላባትም ይብሳል። እንደ ሚና እና አቅም የሌላው ተጨቋኞች ማልቀስ፤ ማልቀስ፤ ማልቀስ።

እንደዚህ በማድረግ ለራሳችን ጥልቅ የሆነ የእፍረት ጉድጓድ ቆፍረናል። የራሳችን ህልውና በራሳችን ሳይሆን በሌሎች የተቆጣጠረ ነው ብለናል። እነዚህ ሌሎች ደግሞ ከኛ እጅግ አናሳ የሆኑ ናቸው። ይህ አስተሳሰብ ግልጽ የሆነ የዝቅተኝነት መንፈስ እንዲያድርብን አድርጓል። እውነት ነው በተፈጥሮ ሻ'ዕብያዎች፤ ወያኔዎች፤ ኦነጎች ወዘተ ከኛ ይሻላሉ ይበልጣሉ ብለን አምነናል! ይህን የተሳሳተ እምነት የገባንበት ለችግሮቻችን በሙሉ እነሱን ፈላጭ ቆራች እራሳችንን አቅመ ቢስ ስለምናደርግ ነው። ይህ የዝቅተኝነት መንፈስ የሚፈጥረውን እፍረት ለመሸፈን ደግሞ እንደገና እነሱ ላይ እንወርዳለን ከእፍረታችን ለመሸሽ ብለን። ይህ "vicious cycle" ሆኖናል ማቆም ያልቻልነው ሱስ ሆኖናል። የድሮ መሪዎቻችን (ከነ ስህተቾቻቸው) ይህን ቢያዩ ኢትዮጵያዊ መሆናችንን የሚያምኑ አይመስለኝም።

እግዚአብሔር ችር ነው እና አሁን በራሱ የሚኮራ፤ ሃላፊነት የሚወስድ፤ ጥፋቱን የሚያምን፤ ለጥፋቶቹ ንስሃ ገብቶ ይቅርታ የሚጠይቅ፤ ሌሎችን ለራሱ ጥፋቶች እና ችግሮች ከመውቀስ እራሱን በተገቢው ወቅሶ መፍትሔውን ፈልጎ አግኝቶ ስራ ላይ የሚያውል ጀግና መሪ ሰጥቶናል። ለኛ ለኢትዮጵያ ብሄርተኞች ምሳሌ ሊሆን የሚገባን መሪ። ከ60 ዓመት ጥፋታችን በኋላ አሁንም እራሳችንን ለማረም እድል ተሰጥቶናል። ይገርማል!

አሁን የ60 ዓመት ጥፋታችን ውጤት ግልጽ ሊሆንልን ይገባል። እኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ተዝናንተን አድሃሪ፤ ተራማጅ፤ ደርግ፤ ኢዲኡ፤ ኢህአፓ፤ ሜሶን ወዘተ እየተባባልን ተጨራረስን። ባቃጠልነው ባዶ ሜዳ የጎሳ ብሄርተኞች ገቡ። አሁንም የሀገራችን ታላቅ የፖለቲካ ችግር የጎሳ ብሄርተኝነት ነው ብለን እናምናለን ላለፉት 27 ዓመት ያመጣውን ግጭቶች አይተናልና። ስለዚህ የእርስ በርስ መጣላታችን የመስማማት እና አብሮ መስራት አለመቻላችን ምን አይነት ውጤት እንደሚያመጣ እናውቃለን። በዚህ ምክንያት ጎሰኝነትን ለመቀነስ ለማጥፋት ከፈለግን እኛ የሀገር ብሄርተኞች አንድ መሆነ እንዳለብን የእርስ ብሰር ችግሮቻችንን መፍታት መችሃል እንዳለብን ለጋራ ጥቅም አብሮ መሰለፍ እንዳለብን ግልጽ ሊሆንልን ይገባል። ግልጽ ብቻ ሳይሆን ብቸኛ መንገዳችን እንደሆነ ሊገባን ይገባል። አማራጭ የለንም።

ካሁን ወድያ ከማህላችን ጣት መጠቆም ስለ ሻዕብያ፤ ወያኔ፤ ጎሰኞች ወዘተ ማልቀስ ክልክል ይሁን! ክልክል ይሁን! ይህ አስተሳሰብ ነው ወደ ኋላ የሚጎትተንና። እንደ ጠ/ሚ አብይ ችግር ሲያጋጥምን እራሳችንን ምን አድርገን ነው ይህ ችግር የገጠመን ነው ማለት ያለብን። ወሬዎቻችንን፤ አነጋገራችንን፤ አስተሳሰባችንን፤ ጽሁፎቻችንን እንቀይር። ሌሎች አጎልብተን ስለነሱ በኛ ያላቸውን ሚና ከማውራት እራሳችንን አጎልብትን እንገኝ እራሳችን ለራሳችን አለቃ ነን ችግር ካለን እንፈታለን እንበል። ያህን አይነት ባህል ማዳበር አለብን የ60 ዓመት የውድቅ ልምድ ለመቀየር። ታላቅ ስራ ነው ግን እድለኛ ነን እንደ አብይ አይነቱ የጎላ ምሳሌ ሰጥቶናል።

በመጨረሻ አንድ የጠ/ሚ አቢይ ምሳሌ ልጥቀስላችሁ። ከኢሳያስ ጋር ያለውን ግንኝነት እንየው። እራሱን እንደ ታናሽ ወንድም ትሁት አድርጎ ነው የሚያሳየው። እራሱን ዝቅ ያደርጋል ለምሳሌ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሲመጣ እራሱ ጠቅላይ ሚኒስጤር ሆነ ይቀበላል። የ100 ሚሊኦን ህዝብ መሪ ሆኖ ወደ ስድስት ሚሊዮንዋ ኤርትራ መጀመርያ እሱ ነው የሄደው። ለምን። ይህን ማድረግ የሚችሉ በራሱ ስለሚተማመን ነው። ሁኔታውን እራሱ እንደሚቆጣጠር ስለሚያውቀው የራሱን አጀንዳ ማስረገጥ እንደሚችል ስለሚያውቅ እራሱን ዝቅ ማድረግ ምንም አይመስለውም። በራሱ የሚኮራ ብቻ ነው እራሱን ዝቅ ማድረግ የሚችለው። ሌሎቻችን በራሳችን የምናፍር ሰውው ገበናችንን ያቅብናል ብለን የውሸት ጭምብል አድርገን እንኮፈሳለን። አያችሁ እንዴት በራስ ሃላፊነት መውሰድ ሌሎችን ለራስ ችግር ሌሎችን አለመወንጀል እራስን እንደሚያጎለብት። ሌላው መንገድ እራስን አቅመ ቢስ ያደርጋል። ለራስ ሃላፊነት መውሰድ ግን ያጎለብታል። ዶ/ር አብይም የፖለቲካውን ጉልበት ከዚህ ነው የሚያገኘው። እስቲ ትንሽም እንማር!

Friday 13 July 2018

The Great Obang!

Ever since I've known him, Obang Metho has been preaching peace, love, and reconciliation. I think it's fair to say that many of us thought him naive. How in the hell can peace, love, and reconciliation work? We need power, justice, and retribution.

Well, what a delight it is that Obang has now found a leader, Dr Abiy Ahmed, even more naive than him! So naive that he's made peace, love, and reconciliation work.

Congratulations, Obang!

But, as you say, it's time to get down to work. There are many possible sources of division and instability in Ethiopia, particularly ethnic nationalism. We Ethiopian nationalists have to work overtime to remove the disease of division from ourselves so that we can confront ethnic nationalism from a position of strength, but in a peaceful, positive, constructive, empathetic, and just way.

Obang's latest interview on ESAT: https://www.youtube.com/watch?v=UJP05Mzp6f4

ገዱ አንዳርጋቸው እና «ነባር ብአዴኖች»

ገዱ አንዳርጋቸው ብአዴንም ኢህአዴግም ላደረጉት ጥፋቶች በሙሉ ይቅርታ ጠይቋል። ካሁን ወድያ ለህዝብ ተጠሪ እንሆናለን ህግ አክባሪም እንሆናለን አናሸብርም ብሏል። የ«ለማ ቡድንን» እና አብይ አህመድ ደግፎ ኢህአዴግንም መንግስትም እንዲቆጣጠሩት አድርጓል። የነ አቢይ አህመድ ደጋፊ ሆኖም እየሰራ ነው። ይህ ሁሉ ግልጽ ነው ሁላችንም ያየነው ነው።

ይህ ሁሉ ሆኖ ገዱ ትላንት ተነስቶ የብአዴንን ነባር አመራር አሞገሰ ተብሎ ጩሄት አይገባኝም። ምን ነው ለመፍረድ የምንቸኩለው? ሰውን ይሆን እንዲህ ያለው ብለን እራሳችችን አንጠይቅም? እኛም እንደዚህ በችኮላ እንዲፈረድብን እንወዳለን?

ጠ/ሚ አብይ አህመድ ከመቀለ ያሉትን እናስታውስ። «ዎርቅ»! «ወልቃይት የዲአስፖራ ጉዳይ አለበት»! አንዳንዶቻችን ወረድንባቸው። ለምን? የሚሉትን ያውቁ ነበር። የነበርውን ህዝብ ለማስደሰት ህወሓቶችን የፖሮፓጋንዳ አቅም ማሳጣት ነበር። የፖለቲካ ስልት ነበር። እና በውቅቱ ሰርቷል። እንኳን መከለ ሄድው የትግራይን ህዝብ አሞገሱ!

እሺ ያኔ ብዙዎቻችን አብይ አህመድን የለማ ቡድንንም በደምብ አናውቋቸውም ነበር። አሁን ግን ለብዙ ዓመት ከኢህአዴግ ውስጥ ታግለው ድርጅቱን እንደተቆጣጠሩት እናውቃለን። ዋዛ አይደሉም ከኛ ድርብ እጥፍ የሚሰሩትን ያውቃሉ እኛ ያማናውቀውን በርካታ መረጃዎች አላቸው። ስለዚህ ቶሎ ከመፍረድ እራሳችንን መቆጠብ አለብን። አላማትች አንድ ስለሆነ መደገፍ አለብን እንጂ ትናንሽ የማንስማማበት ነገሮችን ካደረጉ ማኩረፍ የለብንም። አለበለዛ አብሮ መስራት አይቻልም።

የገዱም እንደዚሁ። እነ በረከትን ያሞሳቸው። እስኪ በቃቸው ቂቤ ይቀባቸው ምን ቸገረን። ለጊዜው ለፖለቲካ ከተመቸው እሰየው። ነው አሁንም እነ በረከትን እንፈራለን ገዱ ከሃዲ ነው ብለን እንፈራለን!! እንደዚህ ከሆነ ችግራችን ካሰብነው በላይ ነው። በስመ ጥርጣሬ ክፍፍል እና አለመረጋጋት አምጥተን እንደልማዳችን ተከፋፍለን ልንገዛ ነው ማለት ነው። እስቲ ትንሽም የፖለቲካ ስልታችንን እናዳብር።

በመጨረሻ ለፖለቲካችን ገዱ ላይ መጮሁ ጥሩ ነው። የድሮዎቹን ምን ያህል እንደሚጠሉ እና ምን ያህል ቦታ እንደሌላቸው ጡረታ ብቻ እንደሚጠብቃቸው ያስረግጥላቸዋል። ግን እኔ የምፈራው ይህ ገዱ ላይ የተሰነዘረው ጩሀት እንደዚህ አይነት ስልታማ ሳይሆን የእውነት ቅሬታ እና ንዴት ነው። ባይሆን ይሻላል። ከነ ገዱ ጋር አብረን መስራት አለብን ስራቸው ጥሩ እስከሆነ ብአዴንንም ገብተን መቆጣጠር አለብን። አማራ አንድ መሆን አለበት። የ50 ዓመት እርስ በርስ መጋጨት መከፋፈል የፖለቲካ ስልት እና ትብብር አለማወቅ ማብቃት አለበት።

በረከት ስምዖን ይዙር!

በረከት ስምዖን አማራ ክልልን እየዞረ ገንዘብ እያደለም ድጋፍ እየሰበሰበ ነው ይባላል? ታድያ ምን አለ ይህን ቢአደርግ። ምንድነው የምንፈራ። ሰዎቻችንን ይገዛል ብለን ነው? ያሳምናል ብለን ነው?

በረከት በገንዘብ እና ሀሳብ የራሳችንን ሰዎች ከገዛ ካሳመነ ይህ ስለኛ ምን ይነግረናል። ምን አይነት ህዝብ ነን ማለት ነው? በገንዘብ እና ውሸት የምንገዛ ህዝብ ነን? እንዲህ ከሆነ ደግሞ መሰረታዊ እና መታረም ያለው ችግር የበረከት መዞር ነው ወይንም የኛ በገንዘብ እና በ ውሸት መገዛት ነው? 

ግልጽ ነው፤ ችግሩ እኛ ነን መፍትሄው እራሳችንን ማስተካከል ነው። አለበለዛ የኛ ህዝብ በገንዘብ እና ውሸት ሀሳብ ስለሚገዛ በረከትን እናባረው ከሆነ መሰረታዊ ችግራችንን አንፈታም። በርከት ቢጠፋ ሌላ ደግሞ ይመጣል። ሌላ ተቃዋሚ፤ ሌላ የ«አማራ ጠላት»፤ ሌላ ሽብርተኛ ወዘተ። የራሳችንን ችግር ካልፈታን ለአደጋ እና ክህደት ሁልጊዜ የተጋለጥን እንሆናለው። ልድገመው፤ የራሳችንን ችግር ካልፈታን ለአደጋ እና ክህደት ሁልጊዜ የተጋለጥን እንሆናለው።

ለኔ ስለ በረከት ዙረት መቸገር እጅግ እጅግ አሳፋሪ ነው። አንድ ህዝብ የማይወደው አማራ ነኝ ኤርትራዊ እየዞራ ሊበጠብጣችን ይችላል ማለት እኛ እጅግ ደካማ እና ቀሽም ነን ማለት ነው። ባሁኑ ጊዜ ያውም ሰፃነት የሰፈነበት በረከት ምንም ጡንቻ የሌለበት እንዴት ነው የምንፈራው? ያስንቃል። 

ወንድሞች እህቶች እንደዚህ አይነት አስተሳሰብ ያስንቃል። ያስንቃል። እንደዚህ ነው እነ ህወሓትን ያሞላቀቅናቸው። ትንሽ ሆነው በቀላሉ ሊገዙን እንደሚችሉ ያመኑት ገና አንዳቸውን ስናይ ሊበጠብጠን ነው ብለን ስንሸማቀቅ ሲያዩ ነው። ይህን ውሸት ማድረግ አለብን። በረከት ስምዖን እየዞረ ሰውን እያሳመነ ከሆነ እኛ ያን ሰው አንዳያምን ማድረግ አለብን። የክህደት መንፈስ፤ የመታለል መንፈስ፤ የመገዛት መንፈስ ከኛ እንዲጠፋ ማድረግ አለብን።

ድሮ ኩሩ ህዝቦች ነበርን። አንድ ሽፍታ ያጠፋናል ብለን አንፈራም ነበር። በራሳችን በራሳችን ህዝብ እንኮራ እንተማመን ነበር። አንድ ወቅት ግን እርስ በርስ መፈጃጀት ስንጀምር በራሳችን መተማመኑን ያቆምን ይመስለኛል። ከዛ ወዲህ በአንድ ክፍል ውስጥ 100 ሆነን ተግኝነት አንድ «ጠላት» ከመጣ ያንን አንድ ጠላት እንደ 100 ሃይል መፍራት ጀመርን። ይህን አስተሳሰብ ካልቀየርን ኢትዮጵያም አማራም አዲዮስ። በተዘዋዋሪ ለዚህ ነው እነ ሻ'ዕብያ እና ወያኔ አንዳችን የ10 አማራ ዋጋ አለው የሚሉት። ትንሽ ሆነን እናሸማቅቃቸዋለን የሚሉት።

ስለዚህ በረከት ስምዖን ይዙር። ከተማ ለከተማ ይዙር ጉቦ ይስጥ ወሬውን ያውራ። መብቱ ነው። እኛ ለህልውናችን ግዴታ የሆነውን ራሳችንን እናስተካክል እናስተምር አንድነት እናምጣ። ልድገመው፤ አንድነት እናምጣ። አንድ ከሆንን እንደ ብረከት አይነቱ 10,000 ሆነውም እየዞሩ ጉቦዋቸውን ቢያድሉ ዋጋ አይኖረውም። ይህ አይነት አንድነት ከሌለን ለዘላለም በቀላሉ የምንሸነፍ ሰዎች ነው የምንሆነው።

Thursday 12 July 2018

የቤት ሰራተኛ

አንድ ጓደኛዬ «የቤት ሰራተኛዬን እንደ ቤተሰብ ነው የምቆጥራት። ካስፈለገ እንጀራ መጋገርም ቤት ማጽዳትም እረዳታለሁ። ግዴታ ትምሕርትቤት እንድትማር አደርጋታለሁ…» ብሎ ነገረኝ። ምን ነው ይህ ያልተለመደ እንክብካቤ ብዬ ስጠይቀው እንዴት ለልጆቼ እንጀራ ጋግራ የምታበላውን አልንከባከባትም አለኝ! እውነት ነው፤ ሌሎቻችን እንዲሁ ቢገባን።

አንድ ሰሞን የቤት ሰራተኛ ፍለጋ አዲስ አበባን ከደላላ ወደ ደላላ ዚርን! ደላሎቹ ምን እንርዳችሁ ብለው በጉጉት ይጠይቁናል። የቤት ሰራተኛ ስንላቸው ፈገግራቸው የጠፋል። ሹፌር ወይንም የቀን ሰራተኛ ወዛደር ብንላቸው ይሻላቸው ነበር ብዙ አላቸው። ግን የቤት ሰራተኛ የላቸውም፤ ለነሱም ብርቅ ሆነዋል።

ብዙ የማቃቸው ቤተሰቦች አዲስ አበባም ከገጠር ከተሞችም የቤት ሰራተኞቻቸው በየ ሁለት ሶስት ወር ይለቃሉ አዲስ መቅጠር ይሆንባቸዋል። ወይንም ለመቅተር የገንዘብ አቅም የላቸውም። ወይንም ከመቀቃየር ተስፋ ቆርጠው አለ ሰራተኛ ይኖራሉ።

ዛሬ በአዲስ አበባም በመላው ኢትዮጵያ የቤት ሰራተኛ ጠፍቷል። ወይንም በትክክለኛ አገላለጽ (እጅግ) ተወዷል። ለምን ይሆን? የ ኤኮኖሜ ምክንያቶች አሉ። የሰው ኃይል በጠቅላላው ተወዷል። ዛሬ የቀን የግንባታ ሰራተኛ በወር ወደ 3000 ብር ሊሰራ ይችላል። እንዲሁም የቤት ሰራተኛ ደሞዝ ጨምሯል። ሁለተኛ ምክንያት ዛሬ ሴት ልጆች ከድሮ ይልቅ በትምሕርታቸው ይገፋሉ። የገጠር ወይንም የድሃ ቤተሰብ ልጆቻችው እንዲማሩ ይፈልጋሉ እንጂ በልጅነታቸው ሰራተኛ እንዲሆኑ አይሰጧቸውም። ሶስተኛ ምክንያት ወደ አረብ ሀገር ሄዶ መስራት ነው። የአራብ ሀገር ክፍያ ይበልጣል ወደ «ውጭ» ሀገር መሄድም ምንም ችግር እንደሆነ መረጃ ቢኖርም ያጓጓል ይመስለኛል። በነዚህ ምክንያቶች የቤት ሰራተኞች ተወደዋልም አይገኙምም።

ከኤኮኖሚ ምክንያቶች በተጨማሪ ለቤት ሰራተኛ መጥፋት ማህበረሰባዊ ምክንያር አለ እና እዚህ ላይ ነው ማተኮር የምፈልገው። ዛሬ አንድ ሴት በህንጻ ጽዳት ስራ 2000 ብር በ ወር ታገኛለች። ከዚህ ብር የቤት ኪራይ፤ መጓጓዣ (ትራንስፖርት) እና የምግብ ወጪዎቿን ትከፍላለች። 1000 ከተረፋት ትልቅ ነገር ነው። ነይ በ2000 ብር የቤት ሰራተኛ ሁኚ የቤት ኪራይ፤ የመጓጓዣ እና የምግብ ወጪ አይኖርሽም ብንላት እምቢ ትላለች። ለምን ይሆን? ስራው ከባድ ስለሆነ አይደለም  እትፍ ከባድ አይደለም። ነፃነቱ ይሆን እሱም 1000 ብር የሚያዋጣት አይመስለኝም። ምንም አይነት የሚመች የስራ ሁኔታዎች ብትዋዋልም የቤት ሰራተኛ መሆን አትፈልግም። ታድያ ምንድነው ምክንያቱ?

እኔ እንደሚመስለኝ ዋናው ምክንያት በባህላችን የቤት ሰራተኝነት እንደ ዝቅተኛ የሚናቅ ስራ ስለምንቆጥረው ነው። ይህን የዝቅተኝነት እና የመንናቅ ስሜት እጅግ ብዙ ብር ካልሆነ ብር አይተካውም። ተጎድቼ ውጭ ብሰራ ይሻለኛል ለብዙ ብር ከሰው ቤት ከምሰራ ነው ያለን አስተሳሰብ።

እስቲ ወደ ኋላ ሄደን የቤት ሰራተኞቻችንን እንዴት እንደምንይዝ እንደነበር እናስታውስ። 16 ሰዓት በቀን ይሰራሉ ለሌላው 8 ሰዓት ተጠሪ ናቸው። በወር አንድ ቀን እረፍት ቢኖራቸው ነው ይህም ላይከበር ይችላል። ኦርቶዶክስ ክርስትያን ነን የምንለው እንኳን እሁድ ቀን እረፍት መስጠት ቅዳሴም እንዲያስቀድሱ አንፈቅም (ከዚህ በላይ አሳዛኝ ነገር አላቅም)። እንደ ሰው ሳይሆን እንደ ባርያ እንጮህባቸዋለን እናጎሳቁላቸዋለን። እንደማንም ሰው አድገው ወደፊት ማግባት እና ቤተሰብ ማፍራት እንደሚፈልጉም አንገነዘብም ልንገነዘብም አንፈልግም። ከቤተሰቦቻቸው ርቀው በመኖራቸው እኛ እንደ ሁለተኛ ቤተሰባቸው መሆን እንዳለብን አናስብም። በጠቅላላ ለራሳችን የማንወደውን እናደርግባችዋለን ለራሳችን የምንወደውን አናደርግላቸውም።

ይህ ስር የሰደደ ባህል ሆኖ የቤት ሰራተኛ እጅግ ዝቅተኛ ስራ መሆኑ ሁላችንም አሰሪዎችም ሰራተኞችም እናውቃለን። በዚህ ምክንያት ይመስለኛል በርካታ ሴቶች ከቤት ሰራተኛ ስራ የሚርቁት። ብዙ ብር ቢከፈላቸውም ከገንዘብ አንጻር ቢያዋጣቸውም «ዝቅተኛነቱን» «ውርደቱን» አይፈልጉትም።

የቶሎ የስራ መቀያየር ጉዳይሳ? ለምንድነው ብዙ የዘመኑ የቤት ሰራተኛዎች ገና ወር ሁለት ወር ሳይቆዩ ለቀው ወደ ሌላ ቤት የሚሄዱት። አንዱ ምክንያት የኤኮኖሚው ነው። ብዙ ስራ ስላለ የደሞዝ ጭማሬ ቶሎቶሎ ያገኛሉ። ሌላው ምክንያት ግን እንደሚመስለኝ የቤት ሰራተኝነት የማይፈለግ ስራ በመሆኑ ብዙ ችግር እና የማመዛዘን ድክመት ያላቸውን ሴቶች ናቸው ወደዚህ ስራ የሚገቡት። ይህ ምክንያት የስራ መቀያየራቸውን ብቻ ሳይሆን ሌሊችን ችግሮች እንደ ሌብነት ወዘተ ያስረዳል።

ለረዥም ዘመን የቤት ሰራተኞቻችንን ጎድተናል። በተዟዟሪ ሙሉ መሃበረሰባችንን ጎድተናል። የጎጂ የአሰሪ እና የንቀት ባህላችን ከትውልድ ወደትውልድ አስተላልፈናል። የአሁኑ የሰራተኛ እጥረት እስኩመጣ ድረስ ጥፋቶቻችን አልታዩንም ይሆናል ግን አሁን ጎልተው ሊታየን ይገባል። ጥፋታችንን አይተን አምነን መጸጸት፤ ንስሃ መግባት እና ይቅርታ መጠየቅ የሚኖርብን ይመስለኛል ይህን ጎጂ ባህላችንን በቋሚነት ለማስወገድ። ይህ ለህላችንም ለጠቅላላ ህብረተሰባችን ሰላም እና ፍቅርም አስፈላጊ ይመስለኛል።

Wednesday 11 July 2018

Towards an Integrated Ethiopia

Decades ago we used to be presented with a stark choice between a "unitary" state speaking Amharic, assimilating all other ethnic groups, and with nearly everything controlled by the central government, and approximately 85 separate nations, one for each of our ethnic groups! And unfortunately all debate revolved around these caricatures, and we never got anywhere.

Today, thankfully things have changed. We have, fortunately or unfortunately, data from 27 years of the radical experiment called ethnic federalism, where as much as was realistically possible, regions were drawn along ethnic lines and ethnicity ("nations, nationalities, and peoples") became the foundation of the Ethiopian state. I would say that these 27 years have shown us conclusively that this formula is one of ethnic strife, conflict, war, ethnic competition, ethnic-motivated mass dislocations, etc.

Some would say that what we have had is fake or bastardized ethnic federalism in which the TPLF ruled as a dictatorship and never really implemented the constitution in practice. This is certainly true to some extent, but enough was implemented to see the results. Ethnic based regions were created, ethnic based identity cards were encouraged in many regions, and there was some degree of self rule in the regions. Moreover, most of the ethnic conflicts throughout Ethiopia have not been related to TPLF dominance. Instead, they have been occurring between non-Tigrean ethnic groups. Take for example Amharas and other "non-locals" being evicted from various regions, or being hunted down and murdered in the name of retribution for historical injustices. Or conflicts between Gedeo and Guji, or Oromo and Somali, or Qemant and Amhara, or Agew and Amhara, etc. There are plenty of examples. It is clear that the placement of ethnicity at the centre of political life resulted in conflict and ethnic political competition, which is always a recipe for disaster. Despite the fact that the ethnic federalism experiment was not perfectly tried out, we have seen enough to know that it cannot work for Ethiopia.

As I say this, I have to add that the even EPRDF itself recognized a couple of years ago that this was the case. The main catalyst for this recognition was that the ethnic hatred inculcated by ethnic federalism started to target Tigreans more and more. The combination of ethnic federalism and the EPRDF's beloved developmental state was proving untenable. The public's resentment against the ruling class, as represented by the EPRDF, was not only based on politics and class, but on ethnicity - on anti-Tigrean sentiment. The resentment became virulent, and the EPRDF knew that things could not continue as is without full blown ethnic war. Hence the beginning of the opening of the EPRDF, and in particular the TPLF, to changes that eventually brought about Prime Minister Abiy Ahmed and his team to power.

So I think today it is clear that the ethnic federalism formula as we have it, even if implemented 'perfectly', is not a good solution for Ethiopia because it brings about conflict. Not because it is inherently unjust, but because we have evidence that it does not work and it results in concrete strife and misery. Why has it not worked? A few reasons... First, there is in many parts of Ethiopia ethnic resentment and historical baggage. Ethnic-based governance only exacerbates this. Second, a significant portion of our incapable political elite wish to use ethnic competition as a way to political power and have no qualms about encouraging ethnic conflict. Third, there has been over hundreds or thousands of years significant integration and even assimilation in Ethiopia, resulting in a large constituency not interested in ethnicity, but nevertheless persecuted by ethnic politics for historical grievance reasons and for not signing on to the ethnic ideology. For these and other reasons, and given the evidence we have, the current ethnic federalism formula should, in time, be abandoned.

Abandoned for what? For many of us, the choice today is between 1) an integrated and synthesized Ethiopianism or 2) an Ethiopia divided on ethnic lines - a nation of disparate nations. 2) is more or less what we have now, the recipe for ethnic strife and conflict. The first choice is, I think, our only choice. What is integrated and synthesized? It means reflecting as much is realistically possible and in keeping with the wants of the population everyone's identity in Ethiopianness. An obvious and often stated example of this: making the Oromo language a national language of Ethiopia, in addition to the current Amharic, integrates into Ethiopianness the use of the Oromo language. It moves it from the periphery, or from a single region, to the national level. Another example: integrating elements of the Gadaa political structure into the nation's political structure. And so on. What about other ethnic groups and their identities? What about the level of regional and local autonomy? These and several other questions can be answered via discussion and evolution. But the point is that integration and unity is the only way to peace and prosperity. A single Ethiopian identity must be cultivated, not to the exclusion of ethnic identity, but to ensure that it always supersedes ethnic identity, thereby reducing the temptation of ethnic politics and ethnic conflict.

What about the transition from ethnic based politics to this new "Ethiopian" politics? It should probably be slow since we have a generation schooled under the ERPDF's ethnic politics and we have a perhaps worse older political class schooled under Marxism and democratic socialism. The first step is to implement integrative policies such as the language policy I mentioned above. One of the goals of this policy is to increase inter-ethnic integration and increase the non-ethnicized population. After some years (or decades) of this, the proportion of non-ethnicized Ethiopians will be such that a transition to non-ethnic politics will be easy.

That is the plan. There are two hindrances that I see. First, the obvious, are the ideological and cynical ethnic politicians who would stand to lose from an abandonment of ethnic federalism. The second is the group against ethnic politics but which does not have the political savvy and empathy needed to relate to and hold discussions with ethnic federalists. The ethnic politicians we will always have with us - I don't think there is anything we can do but marginalize them. But the second group we should work on as if this group - I call it the Ethiopianist group - gets its act together, then we will have a smooth transition from today's combustible ethnic federalism to an integrated and synthesized Ethiopia.

ንቀት

እኛ ኢትዮጵያዊዎች እንደ መንናቅ የምንጠላው ነገር የለም። ከአንዳንድ ቦታዎች ንቀት እና የተደጋገመ ዝልፍያ እስከ መገዳደል ያደርሳል! መንናቅ እየጠላን ግን መናቅን እንወዳለን  አያስችለንም። ይህ ነውረኛ የንቀት ባህላችን ለበርካታ ሀገራዊ፤ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ችግሮቻችን  አስተዋጾ አድርጓል። በቀላሉ ለመከፋፈል አጋልጦናል። እርስ በርስ መናናቅን ብናቆም እነዚህ ችግሮችን ለመፍታት ይረዳናል።

«ንቅት» ስል ሰውን ወይንም ማህበረሰብን ወደ ታች አድርጎ ማየት ማለቴ ነው። «ምቀኝነት» ሌላውን በመጉዳት ራስን መጥቀም የሚቻል እንደሚመስለው ንቀትም ሌላውን ወደታች በማየት ራስን ከፍ ማድረግ ይቻላል የሚል የውሸት አስተሳሰብ አለው።

ማንን ነው የምንንቀው? ከኛ «ዝቅተኛ» ስራ የሚሰሩትን፤ (ለምሳሌ) የቤት ሰራተኞቻችንን፤ ከኛ ድሃ የሆኑትን፤ ያነሰ ትምሕርት ያላቸውን፤ አማርኛ በደምብ የማይችሉትን፤ እንግሊዘኛ በደምብ የማይችሉትን!፤ ገጠሬዎትን፤ ቀጥቃጭ፤ ቆዳ ፋቂዎች ወዘተ የሆኑትን፤ የሌላ ቋንቋ ተናጋሪዎችን ወዘተ። ዝርዝሩ ረዥም ነው!

ተናቅን የሚል ስሜት ያላቸው ከሚንቋቸው ጋር አንድነት ሳይሆን ልዩነት ይሰማቸዋል። ልዩነት ብቻ ሳይሆን ቂም እና ጥላቻ አከማችተዋል የናቋቸውን ቢበቀሉ ደስ ይላቸዋል። ይህ ማለት ህብረተሰባችን ተከፋፍሏል ነው። እርስ በርስ ጥላቻ አለው ማለት ነው። ታድያ ለረዥም ዓመታት በከፋፍሎ መገዛት ፖለቲካ ብንመራ ለምን ይገርማል። በ«ብሶት ፖለቲካ» መቆየታችን ለምን ይገርመናል? ፖለቲካችን በመጣላት የተመረዘ መሆኑን ምን ይገርማል? የፖለቲካ ውይይቶቻችን በጥይትነና በጡንቻ መካሄዳቸውን ምን ይገርማል?

እስቲ አንዳንድ ተጨባጭ የንቀት ምሳሌዎች ልስጣችሁ፤ በኃይለ ሥላሴ ዘመን ሁላችንም እንደምናውቀው ከመሳፍንቱ እና ባላባቱ መካከል ብዙዎቻችን ገበሬውን፤ ጪሰኞውን፤ ሰራተኞቻችንን ወዘተ እንንቅ ነበር እንደ በታቾቻችን እናያቸው ነበር። አዲሱ «የተማረው» መደብም ራሱ የሚንቀው ቡድን ነበር ይህም ያልተማረውን፤ ሃይማኖታዊውን ወዘተ። ይህ ንቀት ህዝባችንን ከፋፈለ የአንድነት ስሜታችንን ቀነሰ። ሀገራችንን ለኮምዩኒዝም የሚያስተምረው «ጨቋኝ ተጨቋኝ» የክፍፍል ፖለቲካ አጋለጠ። መናናቃችን ለደርግ አብዮት ታላቅ አስተዋጾ አደረገ። አብዮተኞቹ የህዝቡን የመንናቅ ብሶትን እንደ ቤንዚን ተጠቅመው ነው አብዮቱን ያራመዱት። ወዛደሮችን፤ አርሶአደሮችን፤ ሴቶችን፤ «ጭቁን ዘሮችን» ወዘተ እረደሃለሁ እበቀልሃለሁ ብለው ነው ኮምዩኒስቶቻችን የተነሱት። ተናቅን የሚሉትን በሙሉ አቅፍያለሁ እያለ ነው ደርግ የሰበከው። ግን ንቀቱ ባይኖር ብሶቱም አይኖርም ነበር አብዮቱም አይነሳም ነበር።

የኢህአዴግ ዘመንም እንዲሁ ምሳሌ ይሆነናል። ኢህአዴግ ስልጣን ስይዝ የሚናናቅ የተከፋፈለ እርስ በርስ ቂም የያዘ ህብረተሰብ ነው የጠበቀው! ይህን ህብረተሰብ ከፋፍሎ መግዛት እንደሚችል ቶሎ ተረዳ። ልክ እንደ ደርግ ግን በተሻለ ብልጠት ተንቀናል ሊሉ የሚችሉትን ቡድኖች ማፈላለግ እና ማቀፍ ጀመረ! እዚህ ላይ አንድ አስፈላጊ ነጥብ አለ። ኢህአዴግ የተጠቀመበት ክፍፍል አይነት የጎሳን ብቻ አይደለም። ሁሉንም ከላይ የጠቀስቋቸው ክፍፍሎችን፤ ሃብታም እና ድሃ፤ የተማረ ያልተማረ፤ ገበሬ ከተሜ፤ አሰሪ ሰራተኛ፤ ወንድ ሴት፤ ትልቅ ሰው ወጣት ወዘተ ተጥቅሞባቸዋል። እነዚህ ክፍፍሎች አልፈጠራቸውም ተተቀመባቸው እና አስፋፋቸው እንጂ። ስለዚህ ለኢህአዴግም አገዛዝ የንቀት ባህላችን ሙና እንደተጫዋወተ ግልጽ ነው።

ለማጠቃለል ያህል ያለፉት 60 ዓመት ፖለቲካችንን «የብሶት ፖለቲካ» ብለን መሰየም እንችላለን። ቂም እና መከፋፈል የሰፈነበት ፖለቲካ ነው። በ«ጨቋኝ ተጨቋኝ» አስተሳሰብ ተመርዟል። ስለዚህም ነው አብሮ አለመስራት፤ ውግያ፤ ጸብ፤ ቅራኔ አለመፍታት ወዘተ የሰፈነው። ንቀት እና ውጤቶቹ ብሶት እና ቂም ለዚህ ማህበረሰባዊ እና ፖለቲካዊ ችግር ትልቅ ሚና የተጫወቱ ይመስለኛል።

ከ ጠ/ሚ አብይ አህመድ ዋና መፈክሮች አንድነትን ወይንም አለመከፋፈል ነው። አንድ የሆነ ማህበረሰብ ጤነኛ ነው የተከፋፈለ ማህበረሰብ በሽተኛ ነው። የሚናናቅ ማህበረሰብ አንድ ሊሆን አይችልም ስለዚህም ይህ የ«ንቀት» ባህላችንን እንዋጋ እና እናሸንፍ!

አንድ የመጨረሳ ነጥብ ፍቀዱልኝ። ንቀት «አንተ የማትወደውን ለባለእንጀራህ አታድርግ» ስለሚሽር መጥፎ ስነ መግባር መሆኑ ሁላችንም ይገባናል። መንናቅ ስለማንፈልግ መናቅ የለብንም ነው። ግን ይህ ሙሉው ታሪክ አይደለም። ንቀት ኢተፈጥሮ ነው። የሰው ልጅ በእግዚአብሔር አምሳል ስለተፈጠረ ሰውን መናቅ ማለት የሚወደን ፈጣሪአችን እግዚአብሔርን መናቅ ነው። እንደዚህ ስንመለከተው ንቀት እጅግ ከባድ ማጣት ነው።

Tuesday 10 July 2018

የብሄር ጥያቄ ዛሬ

ዛሬ የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ሁኔታ ተገለባብጦ ቢሆንም አሁንም «የብሄር ብሄረሰብ ጥያቄ» ዋና ጉዳያችን ነው። በዚህ ዙርያ ያሉት ጥያቄዎች ናቸው ዋና የሀገራችን የክፍፍል እና የግጭት ምንጭ። ይህ አሳዛኝ ሁኔታ በዋናነት የተፈጠረው በጎሳ ብሄርተኞች ሚና ሳይሆን በሀገር ብሄርተኛ ጎራው ነው። እኛ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ብሄርተኞች ደጋግመን በሰራናቸው ስህተቶች እና ሀገራችንን በሚገባው ማስተዳደእር ስላልቻልን ነው የብሄር ጥያቄው እንደዚህ የሰፈነው። ለምሳሌ ያህል ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ በማያሻማ አገላለጽ አስቀምጠውታል፤ ኢህአዴግ ደርግን አላሸነፍም፤ ደርግ እራሱን አሸነፈ እንጂ። እኛ የሀገር ብሄርተኞች አድሃሪ፤ ተራማጅ፤ ኢህአፓ፤ ምኤሶን ወዘተ እየተባባልን አሳፋሪው ደርግን ፈጠርን ደርግ ሀገሪቷን አጥፍቶ ለኢህአዴግ፤ ኦነግ እና ሻዕብያ ስልጣን አስረከበ።

ለምንድነው ይህ ነጥብ ላይ የማተኩረው? ለምንድነው ለኢትዮጵያ የፖለቲካ ችግሮች እንደ ኢህአዴግ አይነቱ የጎሳ ብሄርተኞችን ጥፋተኛ ከማድረግ የአንድነቱን ጎራ የሀገር ብሄርተኞችን ጥፋተኛ የማደርገው?

1. ሁለት አይነት ሰዎች አሉ። አንዱ ችግር ሲደርስበት ማንነው ይህን ያመጣብኝ ብሎ የሚአማርር
ሌላውን አድራጊ እራሱን ሰለባ በማድረግ እራሱን አቅሜ ቢስ ያደርጋል። ሌላው ሰው ምን አድርጌ ነው ይህ የደረሰብኝ ብሎ እራሱን በመገምገም እና ሃላፊነት በመውሰድ እራሱን አቅም እንዲኖረው ችግሩን መፍታት እንዲችል የሚያደርግ ነው። እኔ በአንድነት የማምን የሀገር ብሄርትኛ ነኝ እና ጥፋቴን ማምን ሃላፊነቴን መቀበል እፈልጋለሁ። ጣቴን በሌሎች ላይ በማተቆር የራሴን ጥፋቶች መካድ አልፈልግም። በተጨማሪ ሃላፊነት በመውሰዴ የችግሩ ምንጭ እኔ ነኝ በማለት የመፍትሄው ምንጭም እኔው ነኝ ማለት ነው። መፍትሄውን ከሌላ ሰው አልጠብቅም። ይህ ተመልካች ሳይሆን አስፈጻሚ ያደርገኛል። ይህ አቅሜን ከመመንመን ያጎለብተዋል።

2. እውነት ነው፤ እኛ የሀገር ብሄርተኞች ነን የኢትጵያ የፖለቲካዊ ችግሮች ያመጣነው። በጃንሆይ አገዛዝ ሀገሪቷን በተቆጣጠርን ጊዜ አስፈላጊ ለውጦች ባለማድረግ የመደብ እና የጎሳ ጥያቄዎችን አስነሳን። የሀገሩን ትውፊት የሚንቅ የተማሪ እንቅስቃሴን ወለድን። ደርግ የኃይለ ሥላሴን መንግስት አልገለበጠም የኃይለ ሥላሴ መንግስት ነው አስፈላጊ ለውጦች ባለማድረግ እራሱን ለአብዮት ያጋለተው። አብዮቱን የአንድነት ጎራውን ለሁለት ለ«አድሃሪ» እና «ተራማጅ» ከፋፈከው ተራማጁ አድሃሪውን አጠፋ። ከዛ ደግሞ ተራማጆቹ እርስ በርስ ተጨራረሱ። አልፎ ተርፎ ደርግ በ«ኢትዮጵያ ብሄርተኝነት» ስም «ነግዶ» ህዝብን ጭቆነ እና ለሀገር ብሄርተኝነት መጥፎ ስም ሰጠ። ይህ መጥፎ ስም የጎሳ ብሄርተኞችን እንቅስቃሴን አበረታታ። ደርግ ሲወድቅ የሀገር ብሄርተኝነት ጎራ እራሱን አጥፍቶ አልቋል። የጎሳ ብሄርተኞቹ ሙሉ በሙሉ ስልጣን ተቆጣጠሩ። በኃይለ ሥላሴ ምንም አቅም ያልነበርው የጎሳ ብሄርትኝነት አሁን ሀገራችንን ገዝቶ ኤርትራን አስገነጠለ። ይህ በአጭሩ እኛ የሀገር ብሄርተኞች ዛሬ ያለብንን የጎሰኝነት ችግር እንዴት እንዳመጣን ይገልጻል።

3. አሁንም ዋናው የሚያሳስበኝ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ጎራ የሀገር ብሄርተኛው ነው። በህዝብ ደረጃ ይህ ጎራ ቢንገዳገድም ደህና ነው። እንደ አብይ አህመድ አይነቱን መሪዎች እየወለደ ነው። ገን በልሂቃን (elite) ደረጃ ችግር እንዳለ ነው። አንድ ሆነን ሀገራችንን ማዳን እንችላለን ወይንም እንዳለፉት 50 ዓመት እርስ በርስ ተከፋፍለን እንደገና የጎሳ ብሄርተኝነት እንዲሰፍን እናደርጋለን? ዋና ጥያቄ ነው። የቅርብ ታሪካችን ጥሩ አይደለም። ይሄው ለኢህአዴግ የ27 ዓመት አገዛዝ አንድ ጠንካራ የፖለቲካ ድርጅት ሀገር ውስጥም ውጭም ማቋቋም አልቻልንም። አሁንስ አንድ ሆነን ከ«ለማ ቡድን» ጋር እየሰራን ሀገራችንን ማዳን እንችላከን? ወይንስ እንደልማዳችን እንከፋፈላለን እና ሀገራችንን ለቀውስ እና ግጭት የሚፈጥረው ጎሰኝነት እንደገና አሳልፈን እንሰአለን? ቁም ነገር ከማድረግ አቅሙ አለን ትያቄ የለውም። ግን ፍላጎቱ አለን ወይ ነው ጥያቄው።

በነዚህ ምክንያቶች ነው በዚህ ወቅት ከሁሉም የፖለቲካ ጎራዎች የሀገር ብሄርተኛ ጎራው የሚያሳስበኝ። እንደ ህወሓት ምናልባትም ኦፌኮ አይነቱ የጎሳ ብሄርተኞች ምንም አያሳስቡኝም። የታወቁ ናቸው በልመና ልንቀይራቸው አንችልም። በስልት፤ በዘዴ እና በውይይት ከነሱ ጋር እንደራደራለን። ግን ለመደራደር እና ውጤታማ ለመሆን የአንድነት ጎራው አንድ እና ጠንካራ መሆን አለበት። ድርድር የሚሳካው እራስን መጀመርያ እራስን ጎልብቶ ነው አለበለዛ ደካማ ከሆንን አይሳካልንም። እርግጠኛ ነኝ የአንድነት ጎራው አንደና ተንካራ ከሆንን በነዚህ ድርድሮች እርግጥ ውጤታማ እንሆናለን የጎሳ ብሄርተኞችን በጥሩ መልክ እንይዛቸዋለን። ግን ከተከፋፈልን የበፊቱ 60 ዓመት ችግሮችን እንቀጥላለን።

Monday 9 July 2018

«ይቅር እንባባል»

ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ የእውንተኛ የይቅርታ ሰባኪ መሆናቸውን ሁላችንንም አይተናል። ለበደሉንን ሁሉ ይቅርታ በማድረግ በሰላም እና ፍቅር አብረን መኖር እንደምንችልም እንዳለብንም እያሳመኑን ነው። በዚህ ምክንያት ፖሊሱን፤ መርማሪውን፤ ፍርድ ቤቱን፤ ካድሬውን፤ ሰአላዩን፤ ጎረቤቴን፤ ወያኔን፤ ኦነግን፤ ሻዕብያን፤ ነፍጠኛውን፤ ጠባቡን ወዘተ በደሉን የምንለውን ሁሉ ይቅር ለማለት እራሳችንን እያሳመንን ነው። የበደሉን የመሰለንን ይቅር እንድንል በማሳመናቸው ጠ/ሚ አብይ ታላቅ ስራ ነው የሰሩት።

ሆኖም ጠ/ሚ አብይ እኮ ማንንም ይቅር አላሉም። ይቅርታ ነው የጠየቁት! ንስሃ ነው የገቡት! እባካችሁን እንደ መንግስት ላደረግነው እንደ መንግስት አካል ላደረግኹት ይቅር በሉን በሉኝ ነው ያሉት። ከይቅር ማለት አልፎ ይህንን ንስሃ መግባት እና ይቅርታን መጠየቅን ነው በመጀመርያ ደረጃ ከአብይ አህመድ መማር ያለብን!

ንስሃ መግባት እና ይቅርታ መጠየቅ ለሁላችንም የሰው ልጅ እጅግ ከባድ ነገር ነው። የማንፈልገው የምንሸሸው ነገር ነው። ጥፋታችንን ማመን ቁስላችንን በተለይም ህፈራትችንን በደምብ እንድንመለከት ስለሚያደርገን አንፈልገውም። ግን ለጤናማ እና እውነተኛ ኑሮ ግድ ነው። 

አንዳንዶቻችሁ እንደ አንድ ግለሰብ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ዙርያ ምን ኃጢአት አለብኝ ትሉ ይሆናል። 
ጥሩ ጥያቄ ነው። ብዙ ጊዜ የኛ «ትናንሽ» ኃጢአቶች ታላቅ ጉዳት እንደሚፈጽሙ አይታየንም እንደናየውም አንፈልግም። ስለዚህም አንዳንዴ ንስሃ ለመግባት እና ይቅርታ ለመጠየቅ ትንሽ ግፊት ያስፈልጋል። እስቲ እኔ ልሞክር። የአብይ አህመድን ምሳሌ ተከትዬ እስቲ እንደ አንድ በአንድነት የሚያምን የኢትዮጵያ ብሄርተኛ ንሰሃ ልግባ ለነዚህ የፖለቲካ ኃጢአቶቼ ይቅርታ ልጠይቅ፤

1. በጃንሆይ ዘመን ልጆቼን ወደ ውጭ ሀገር ትምሕርትቤት ልኬ እራሳቸውን እንዲንቁ የምዕራባዊ አስተሳሰብ ከነ ኮምዩኒዝም ይዘው ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ እና እንዲበጠብጡ በማድርጌ ይቅር በሉኝ

2. ልጆቼን እትዮጵያዊ እንዲሆኑ ፈንታ ታሪካቸውን እንዳያውቁ ፈረንጅ እንዲያመልኩ የራሳቸውን ወግ እና ትውፊት እንዲጠሉ በማድረጌ ይቅርታ

3. አለአግባብ የወረስኩትን መሬት ለጪሰኞች መልሼ በሚቀረኝ (ሰፊ) መሬት ተደላድዬ ከመኖር በመስገበገቤ ይቅርታ

4. ሰራተኛዬን፤ ጎረቤቴን፤ እንደኔ ያህል ያልተማረውን፤ «ያልሰለጠነውን»፤ ገበሬውን ወዘተ ስለ ናቅኩኝ ይቅር በሉኝ

5. የፖለቲካ ለውጥ በጊዜው ባለማምጣቴ አቢዮትን እና የሁከት እና ግድያ ዘመን ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት ለተጫወትኩት ሚና ይቅርታ

6. አድሃሪ፤ ኢህአፓ፤ መኢሶን፤ ደርግ፤ ሻዕብያ፤ ወያኔ ወዘተ እያልኩኝ «ግደሏቸው» በማለቴ ይቅርታ

7. ከሰው ልጅ ይልቅ የፖለቲካ ጦርነት ይበልጣል እያልኩኝ በጦርነት የሚሞቱትን እንደ ምንም ባለመቁጠሬ ታላቅ ይቅርታ

8. ሻዕብያ፤ ወያኔ እና ኦነግ ስልጣን ሲይዙ ወደ ስልጣን የገቡበት ምክንያት በኔ ጥፋት ባዶ የፖለቲካ ሜዳ ስላገኙ ነው ብዬ ባለማመኔ ይቅርታ

9. ኢትዮጵያን በሽብር፤ በጦርነት እና መጥፎ አስተዳደር እጅግ የማይመች ሀገር እንድትሆን  በማድረጌ የኤርትራ ህዝብን ወደ መገንጠል በመገፋፋቴ ይቅርታ አድርጉልኝ

10. ለትግራይ ህዝብ እንዲሁም ፖለቲካውን በአግባብ ማስተናገድ ባለመቻሌ ወደ ትውፊትና ሃይማኖታችሁን የሚጠላው ህወሓት እንድትሸገሸጉ በማድረጌ ይቅርታ

11. ለ27 ዓመት ለችግራችን ያለኝን አስተዋጾ በመካድ ለመፍትሄው ያለኝን ሃላፊነት በመካድ ቁም ነገር ሳላደርግ ለሁሉ ችግሬ እንደህጻን «ወያኔ ነው» ብዬ በማልቀሴ ይቅርታ

ይህን የንስሃ መግባት እና ይቅርታን መጠየቅንም አንብባችሁ እኔ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ዙርያ ምንም ይቅርታ የምልበት ነገር የለም የምትሉ ትኖራላችሁ። ከጎረ ቤቱ ጋር የተጣላ በተዟዋሪ የፖለቲካ ኃጢአት ፈጽሟል ማለት እንደሆነ አናውቅምን (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/blog-post_14.html)? እስካሁን ያሉን የፖለቲካ ችግሮቻችን ከማህበረሰባዊ ክፍፍል የመነጩ ናቸው። ስለ ህወሓት የምንለው «ከፋፍሎ ገዛን» አይደለምን? ታድያ ከጎረቤታችን ጋር የተጣላን፤ ሰውን የናቅን፤ ሰው ላይ የፈረድን፤ ባለንጀራችንን ያልደገፍን ሁሉ ኃጢአተንኛ መሆናችንን ማመን ያለብን ይመስለኛል። «ህዝብ (አንዳንዴ) የሚገባውን መንግስት ያገኛል» ይባላል።

አዎን ይቅርታን መጠየቅ ከባድ ነው። ሁላችንም ኃጢአተኞች እንደሆንን ልባችን ያውቃል። ግን ይህን ማመኑ የሚያገልጠውን ህፍረት እና ቁስል እንፈረዋለን። ስለዚህ ኃጢአቶቻችንን  ለመሸፈን እንወዳለን። ይህንን በማወቅ ነው ቅዱስ ጳውሎስ ሲያስተምርን ዘንድ እራሱን «የኃጢአተኞች ዋና» ብሎ የሰየመው። ታድያ ሃዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ማለት ከቻለ እኛ እጅግ ኃጢአተኞች የሆንነው ምን እንበል?

ንስሃ መግባት ነፃ ያወጣል ከአቅመ ቢስነት ወደ አቅም መጎልበት ያሻግራል። ሰው ላይ ጣትን መጠቆም ሽንፈት እና እራስን አቅመ ቢስ ማድረግ ማለት ነው። የኢትዮጵያ ችግሮች የራሴ ናቸው መፍትሄውም ከራሴ መጅመር አለበት ብዬ አምናለሁ። ይህንን ነው ጠቅላይ ሚኒስቴ አብይ ሊያስተምሩን የፈለጉት።