Friday 30 September 2016

ጥፋት አለብኝ ብዬ ካላመንኩኝ «ወያኔ» ነኝ!

2009/1/19 ዓ.ም. (2016/9/29)

ከዲያስፖራ እየኖርኩኝ ስጋዊ ምቾቴን አጠናቅቄ ህሊናዬ እየወቀሰኝ ሀገር ቤት ያሉትን ወንድሞች እህቶቼን ታገሉ እላለሁ። ሀግሬን እወዳለሁ እላለውንጂ ያሳደገችኝ ብትሆንም ለሷ ያለኝን ሃላፊነት ከተውኩኝ ቆይቻለሁ። ክጃታለሁ ጥያታለሁም። ሆኖም ግን ሀገሬን መበደሌ አይታየኝም። ስለሌሎችን ኅጢአትና በደል እጮሀለው እንጂ። ከአይኔ ያለውን ግንድ አላየውም የሌላውን ጉድፍ ብቻ ነው የሚታዬኝ።

ምሬቴ ትንሽ በመሆኗ ምክንያት አጥሬን መግፋት መብቴ ነው እላለሁ! ገፈዋለሁ፤ ከጎረቤት ጋርም እጣላለሁ፤ መንገድንም አጠባለሁ። ለሰፈሩ ችግር እያመጣሁኝ ነው። ግን የእለት ወሬዬ ስለ ቀበሌአችን ሹማምንት የምስና ባህሪ ነው። አይኔ ውስጥ ግንድ የለም።

እውነት ነው፤ ሲያስፈልግ ጉቦ ሰጣለሁ። መብቴን ለማስከበር ብቻ ሳይሆን የማይገባኝን ለማግኘትም። ምን ይደረግ፤ የሀገራችን እውነታ ነው ብዬ እራሴን አታልላለው። ግን መሪዎቻችን እንዴት ሞራል ቢስ ናቸው ብዬ አማርራለሁ።

አንዱ የኦርቶኦክስ መሰረታዊ እምነት ሁላችንም ለሁሉም ሰው ኅጢአት በተወሰነ ደረጃ አስተዋጾ እድርገናልና ሃላፊነት አለብን የሚል ነው። ኅጢአቶቻችን የተገናኙም የተወራረሱም ናቸው። ይህንን ለማብራራት ያህል የታወቀው ሩሲያዊ ደራሲ ፊኦዶር ዶስቶኤቭስኪ በ«ካራማዞቭ ወንድማማቾች» የጻፈውን ጥቅስ እንመልከት። ታላቁ የሃይማኖት አባት ዞሲማ ልጆቻቸውን ሲመክሩ እንደዚህ አሉ፤
«አንድ ሰው በዚህ ዓለም ከሚኖሩት በሙሉ የባሰ ኅጢአተኛ እንደሆነ ሲያምን፤ በተጨማሪም ከሁሉም ሕዝብ ፊት ጥፋተኛ እንደሆነ...፤ ለዓለምም ለያንዳንዱ ሰውንም ኅጢአት እና ጥፋት እንዳለበት ስያምን ነው የ(ክርስቲያናዊ) አንድነት ድላችንን ማስመዝገብ የምንችለው..።
«ሁላችሁም ልባችሁን በደምብ አዳምጡና ለራሳችሁ ሳትሰለቹ ንስሐ ግቡ። እስከ ተጸጸታችሁ ድረስ ኅጢአታችሁ የጎላ ቢመስላችሁም አትፍሩት...።
«በጸሎታችሁ እንደዚህ አስታውሷቸው፤ «አምላካችን ሆይ የሚጸልይላቸው የሌሏቸውንም ላንተ መጸለይ የማይፈልጉትንም አድናቸው» ብላችሁ ጸልዩ። እንደዚህም ቀጥሉ «አምላኬ ሆይ እኔ ከሁሉም የባሰ ርኩስ ነኛ፤...»»
በተጨማሪ ባለፈው ጽሁፌ የጠቀስኩት በጾቪዬት እስር ቤት የተሰቃዩት አለክሻንደር ሶልዠኒትሲን ከእስር ቤት ሆነው የጻፉትን እንደገና ልጥቀስ፤

ከእስርቤታችን አልጋ የሆነው የበሰበሰው ገለባ ላይ ጋደም ብዬ ነው ለመጀመርያ ከውስጤ የበጎ መንፈስ የተሰማኝ። ቀስ በቀስ መረዳት የጀመርኩት ይህ ነው፤ ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር በሀገሮች፤ መደቦች፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም መካከል አይደለም የሚያልፈው፤ ይህ መስመር የሚያልፈው በያንዳንዱ የሰው ልብ መኻል ነው። መስመሩ እድሜአችን በሙሉ ከውስጣችን ወደፊት ወደኋላ ይላል። በክፉ የተሞሉ ልቦችም ቢያንስ ቅንጣት ያህል ጥሩነት ይኖራል፤ ከሁሉም ጥሩ ከሚባለውም ልብ ከአንድ ጥጓ ትንሽ ክፉነት ይኖራል።
«በየቦታው እየዞሩ ያሉ ክፉ ስራ የሚሰሩ ክፉ ሰዎች ቢኖሩና እነሱን ከኛ መለየትና ማጥፋት ብቻ ቢሆን ኖሮ እንዴት ቀላል ነበር? ግን ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር ከያንዳንዱ የሰው ልጅ ልብ መካከል ነው የሚያልፈውና ማን አለ ከራሱ ልብ ቁራጭ ቆርጦ ለማጥፋት ፈቃደኛ ይሆነ?»
ሶልዠኒትሲን በመታሰራቸው፤ በእስር ቤት ለደረሰባቸው በደልና ስቃይ፤ ያሰሯቸውን የዘመኑን መንግስት መሪዎች፤ የፍርድ ቤት ዳኞች፤ የደህንነት አዛዦች፤ ወዘተ ብቸኛ ጥፋተኛ አድርገው ሊቆትሩ ይችሉ ነበር። ማንናችንም ደካሞች በሳቸው ቦታ ብንሆን እንደዛ ነበር የምናስበው።

ግን እየተሰቃዩም ቢሆን ይህን ቀላሉ የውሸት መንገድን ከመከተል እውነትን መረጡ። እውነትን ፈለገው ህሊናቸውን ተጠንቅቀው መርምረው የራሳቸውም ግድፈት እንዳለ ተገነዘቡ። ከነዛ ክፉዎች እንደማይሻሉ አመኑ።

ሶልዠኒትሲን በሁለተኛ ዓለም ጦርነት ጀግና ወትደር ነበሩ። ሀገሬን እንደዚህ አገልግዬ እንዴት በማግስቱ ለማይረባ ምክንያት እታሰራለሁ ነበር በመጀመርያ ያሰቡት። ግን ህሊናቸውን ሲመረምሩ ከጦር ሜዳ የሰሩትንና ሲሰራ አይተው ዝም ያሉትን ግፍ አስታወሱ። ሀገርን በመከላከል አሳበው ህሊናቸውን እንዴት እንደሸጡ አስተዋሉ። አብረዋቸው የታሰሩትንን የመንግስት ሰለቦች ሲመለከቱም ምንም ንጹ የሚመስሉትም በተወሰነ ደረጋ ተመሳሳይ የህሊና ሽያጭ እንዳካሄዱ ተገነዘቡ።

ከዝ ቀጥሎ የበደሏቸውን ሲመለከቱ በፊት የነበራቸው እነሱ ክፉ እኔ ንጹ የሚለው አስተሳሰባቸው ውሸት እንደሆነ ገባቸው። በዳዮቻቸውም እንደራሳቸው በተለላየ አታላይና የማይረባ ምክንያት ህሊናቸውን ሽተዋል። ስንቱ ናቸው በስመ ሀገር ወዳድነት እንደ ሶልዠኒትሲን አይነቱን የሀገር ከሃዲ ብለው ያሳሰሩት። እነዚህ «እውነት አማኞች» ርዕዮት ዓለማቸውን እንደ ሃይማኖት አድረገው የሚያምኑበት ስለሱ ምንም ለማድረግ ወደኋላ አይሉም ነበር። ሶልዠኒትሲን እነሱን ሲያዩ እራሳቸውን አዩ።

የመጨረሻ ግንዛቤአቸው ንስሃ መግባት እንዳለባቸው ነበር። ንስሃ ቢገቡ በራሳቸው ብቻ ሳይሆን በባልደረቦቻቸው በሙሉ የደረሰው እንደማይደርስ ገባቸው። በሶቪዬት ህብረት የሚገኙት ሀገራት በሙሉም ሰላምና እውነታዊ መንግስት ሊያገኙ የሚችሉት በዚህ አይነት መንገድ ብቻ እንደሆነ ተገነዘቡ። ሌሎቻችንም እንደዚህ አድርገን እንድናስብ ጋበዙን።

እሺ፤ የምጨረሻ ጥቅስ ከአባ ዶሮቴዎስ፤
«አንድ ሰው በእግዚአብሔርን ፊት እራሱን በደምብ ቢመረመረ ለሚደርስበት ያለው በደል ባተግባር፤ በሃሳብ፤ በንግግር፤ በፀባይ፤ ወይም በባህሪይ ሃላፊነት እንዳለበትና ከፊል ተጠቅያቂ እንደሆነ ይገለጽለታል።»
እንዲሁም ለኢትዮጵያ ችግሮች ሁሉ፤ የፖለቲካ ችግር ተጨምሮ፤ ሁላችንም ኢትዮጵያኖች አስተዋጾ አድርገናል ሃላፊነትም አለብን ብለን ማመን አለብን። ቀጥሎ ይህን ሃላፊነት ብንወታው ችግሩ ይፈታል ብለን ማመን አለብን። አባ ዶሮቴዎስ እንዳሉት እራሳችንን ተጠንቅቀን በኢግዚአብሔር ፊት እንመርምር። ይህ ወደ ሰላምና እውነት ብጨኛው መንገድ ነው።

Monday 26 September 2016

Curbing Ethnic Nationalism via Integration and Demography

2009/1/15 (Ethiopian calendar)
2016/9/25 (European calendar)

[Note: An Amharic version of this post will appear shortly!]

In a recent post on the dangers of ethnic nationalism in Ethiopia, I explained why I agree with the idea now fashionable among followers of Ethiopian politics to establish Afaan Oromo as a federal language equal to Amharic. This policy will have two 'effects' – an integrative effect – it will help increase inter-ethnic integration – and a 'placating' effect – it will have a psychologically soothing effect on ethnic nationalists and reduce their zeal, so to speak. In this article, I'll explain that the integrative effect is the strongest and most effective and that the placating effect will be minimal. In addition, unless accompanied by other policies that advance inter-ethnic integration and policies that ensure demographics do not favour ethnic nationalism, the policy step of making Afaan Oromo a federal language, by itself, will not have much effect..

Before going further, let me review why ethnic nationalism is dangerous for Ethiopia as a whole. First, what is ethnic nationalism? We know there are different kinds of it – soft nationalism, hard nationalism, opportunistic nationalism, ideological nationalism, etc. For our purposes here, let's define an ethnic nationalist as one who places his ethnicity ahead of his country. The type of person who says, for example, I'm Tigrean first, then Ethiopian. We all know what this means at the gut level, but let's try and spell it out with an example.

Let's say that in a given province the language of the ethnic group that is a large majority is not an official language. If members of this ethnicity campaign to have their language made the official language, it would benefit them but be a disadvantage (depending on how they take it) to those who belong to other ethnicities as they would have to learn this new language. For the province as a whole, though, the benefits are greater than the costs because a large majority have their wishes respected. Let's consider a similar example, except that the ethnic group requesting that its language be the official language is a small minority in the province. Obviously having their language be the official language would benefit the small minorty, but it would place the vast majority at a disadvantage. Yet, the minority insist. They put their ethnic demands ahead of the greater good, they put their ethnicity ahead of their province. This is what I call ethnic nationalism.

The costs of such ethnic nationalism to a nation are, again, at a gut level, quite clear. The theory is obvious as well. Christopher Clapham put it succinctly in an article just after the 2005 election – to paraphrase: When in a multi-ethnic country such as Ethiopia centrifugal forces begin to exceed centripetal forces the nation begins to pull apart. This is what is being tangibly proven in Ethiopia today, so much so that even the ethnic nationalist EPRDF is worried about it. They've always been worried about it to some extent, identifying 'narrow nationalists' as a threat to the nation. But now they're realizing that even their kind of ethnic nationalism is causing dangers that might require significant reform, such as even changing their 'front' from a group of ethnic based parties to a single non-ethnic entity! (They've seen that political oppression and ethnic identity is a dangerous mix. People are much less tolerant of a small amount of oppression that they perceive is ethnic-based than worse oppression that is not ethnic-based!)

While insisting on the dangers of ethnic nationalism to Ethiopia, I in no way deny that ethnic sentiments and identity and are part of Man's nature, or to use a modern term, a human right. As far as I am concerned, ethnic nationalism too is a human right. As such I think it is futile and even dangerous to repress ethnic identity and ethnic nationalism. If an Oromo wants Afaan Oromo to be the federal language, or if he wants Addis Ababa to be devolved into Oromia, or even if he wants to have Oromia secede from Ethiopia, he has a right to these views and to exercise them politically. Of course, like any other right, the rub lies in the extent to which these conflict with others' rights.

Again, though ethnic identity arises from Man's natural desires, it is, when it crosses the line I mentioned above, a danger to the society at large. One clearly cannot have a country where in every sphere everyone favours their own ethnic group at the expense of the country as a whole. It is for this reason that we Ethiopian nationalists must do our share to reduce ethnic nationalism in Ethiopia.

That was a long review! On to a discussion of integration as a tool to reduce ethnic nationalism and increase civic nationalism... Integration is the social and political mixing of ethnic groups so as to create new groups whose loyalty is to the mixture – the nation. We all know it as an age old formula for creating new kinship, and kinship is what we are really talking about here. The reason that Ethiopia as a nation still stands today is the result of thousands of years of integration.

In today's Ethiopia, integration promoting policies are things like promoting inter-regional migration, business, infrastructure such as transportation, etc. Assuming the ethnic-based regions stay as they are, the best way to promote migration is to have people learn languages of other regions so that they can migrate there, and so that people of the other region can also come here, so to speak. So for example if Afaan Oromo is taught in school in Amhara region and is made a priority, teachers from Oromia would have to be brought to Amhara, and they would probably settle there if properly welcomed. And of course the main goal – Amharas having learnt Afaan Oromo will find it easier to emigrate to Oromia.

At the start of the article, I mentioned making Afaan Oromo a federal language equal to Amharic. This makes sense for various reasons, including integrating the vast number of Oromo youth who for the past 25 years, thanks to ethnic nationalism, have not been taught Amharic or in fact have been taught that speaking Amharic is not a good thing. It also makes sense in the context of the Oromo being the largest or close to the largest ethnic group in Ethiopia. And as I described above, this policy will have an effective integrative effect, it will increase kinship and identity at the national level, reducing ethnic nationalism, in this case Oromo nationalism.

I will note here that I'm afraid many who advocate this policy also, mistakenly, think that the placating effect will be high. That is, they think that making Afaan Oromo a federal language will be seen as a gesture of goodwill by the Oromo public and result in a major reduction in Oromo ethnic nationalism. This, I think, is a very wrong assumption. We can see throughout the world examples of cases where concessions to ethnic nationalism had no such effect. From Canada to Spain to Belgium to Scotland etc., we see the central government making concessions to ethnic nationalists, and these concessions end up reducing only the rate of acceleration of ethnic nationalism!

In the case of Ethiopia and Oromia, there's no reason to think the same won't happen. As soon as Afaan Oromo is made a federal language, Oromo ethnic nationalists will demand that Addis Ababa be absorbed into Oromia State. Against democracy, so to speak, since the majority of Addis Ababans would not want this. This demand is driven purely by grievance and history and is exactly the type of demand that prioritizes the desires of an ethnic group over that of the population at large. And after this demand, others will follow.

However, if the central government and the governments of the other states follow policies of integration and demographic balancing in concert, then Oromo ethnic nationalism will be curbed. Again, if we look world wide, the 'success' stories of reducing ethnic nationalism involve either integration or demographics. Consider Quebec... Its geographical setting is on the edge of most of Canada, sort of like Eritrea to Ethiopia. For this and other reasons, even with official bilingualism (English and French), integration with the rest of Canada remained minimal. However, demographics did the job of burying Quebec ethnic nationalism. Like all of the West, Quebec has brought in lots of immigrants (it has tried to focus on French speaking immigrants) to augment the labour force, pay taxes, etc. These immigrants are very much anti-Quebec nationalism, and their numbers have increased so much that they have tilted the balance in Quebec. If a referendum for secession were called today, a small majority of White French Quebecers would vote to secede, but their majority would be easily overcome by the immigrant vote. Where all sorts of policies failed, the reality of demographics did the job.

So too in Ethiopia civic nationalists have to ensure that the proportion of civic nationalists to ethnic nationalists in the population does not get too low. Encouraging population growth in urban centres, which tend to be civic nationalist, is one such policy. Amhara State, being a non-ethnic nationalist state, also has to ensure that its population does not decline relative to other states in the country. And so on.


In summary, ethnic nationalism is a right which citizens must be allowed to exercise politically. However, too much ethnic nationalism, such as what we've had for the past 25 years, destabilizes the nation and is dangerous enough to result in a failed state. Therefore ethnic nationalism must be curbed, and the force that will curb it, through thoroughly democratic means, is the Ethiopian or civic nationalist constituency. The policy instruments to curb ethnic nationalism is the promotion of policies that advance inter-ethnic integration and keeping a healthy balance between the ethnic and civic nationalist constituencies.

Friday 23 September 2016

የአማራ የፖለቲካ ንቅናቄ ለኢትዮጵያ ህልውና እጅግ አስፈላጊ ነው

2009/1/12 .. (2016/9/22)

ከተለያዩ ጽሁፎች እንደጠቀስኩት ለላእፉት 25 ዓመታት የኢትዮጵያ ፖለቲካ ኢሚዛናዊ ሆኗል። በ1983 ኢህአዴግ ስልጣን ሲይዝ የኢትዮጵያ ብሄርተኛ (Ethiopian nationalist) የፖለቲካ መሪዎች ለ40 ዓመታት እርስበርስ በመፋጀት እራሳቸውን ጦራቸውንም አጥፍተው ነበር። ስለዚህ የሀገሪቷ ህገ መንግስት የተቋቋመው ሀገሪቷም የተስተዳደረችው በጎሳ ብሄርተኛ (ethnic nationalist) የሆኑ ፖለቲከኞች ነው። የፖለቲካ ኃይል በጠቅላላ በጎሳ ብሄርተኝነት እጅ ነው።

በዚህ ምክንያት በርካታ የሆነው የሀገር ብሄርተኛ ህብረተሰብ በፖለቲካ ዙርያ አልተወከለም። ለዚህ ነው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ኢሚዛናዊ ነው ማለት የሚቻለው፤ የጎሳ ብሄርተኞች ከመጠን በላይ ውክልናና ድምጽ አላቸው ርዓዮት ዓለማቸውንም ያራምዳሉ፤ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ግን አልተወከሉምም ድምጻቸውም የሚገባው ያህል አይሰማም። ይህ ሁኔታ ነው ዛሬ በኢትዮጵያ የሚታየውን ከፍተኛ ጎሰኝነትና ዘረኝነት ያመጣው።

ጎሰኝነቱ ለሀገሪቷ ህልውና እጅግ አደገኛ መሆኑ ዛሬ ግልጽ ሆኗል። ለዚህ ያለን አንዱ ከባድ መረጃ የጎሳ ብሄርተኛው ፓርቲ ኢህአዴግን ምን ያህል በሁኔታው መስጋቱ ነው። ከኢህአዴግ አመራር መካከል ጎሰኝነት በሀገሪቷ ፖለቲካ በዝቶ ለስልጣናችንም አስጊ ስለሆነ ፓርቲያችንን ወደ አንድ የሆነ በጎሳ ያልተከፋፈለ ፓርቲ (ብአዴን ህውሃት ኦህዴድ ቅርቶ ማለት ነው) እንቀይር እያሉ ይገኛሉ። ሀገሪቷን ከዚህ አደጋ ለማውጣት የኢትዮጵያ ብሄርተኛ ጎራ የፖለቲካ ድርሻውን በድፍረት (25 ዓመታት እንቅልፍ በኋላ) መውሰድ አለበት።

እሺ ማን ናቸው የኢትዮጵያ ብሄርተኞቹ? ባሁኑ ዘመን ከበየ ክልሉ ቢገኙም በርካታዎቹ ከጎሳዊ ውህደት ያለበት ስፍራዎች እንደ አዲስ አበባና ሌሎች ትላልቅ ከተማዎች ይገኛሉ። በክልል ደረጃ ደግሞ ጠቅላላው የአማራ ክልል የሀገር ብሄርተኛ ነው። ይህንን እውነታ በምርጫ 1997 ቅንጅት ያሸነፈበት ቦታዎች መረዳት እንችላለን። ለማስተዋስ ያህል ኢህአዴግና ህብረት የጎሳ ብሄርተኝነት የሚበዛበት ቦታዎችን አሸነፉ፤ ቅንጅት ደግሞ የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት የሚበዛበትን ቦታዎች አሸነፈ።

የሚቀጥለው ጥያቄ እንዴንት ነው ይህ ከሀገር ፖለቲካ የጠፋው የሀገር ብሄርተኛ ጎራ የሚገባውን ፖለቲካዊ ድርሻ መያዝ የሚችለው። በመጀመርያ ከታች ከመላው ህብረተሰብ (grassroots) ጀምሮ የአንድነትና የአንድ አላማ መንፈስ ልያድርበት ይገባል። ይህ ለማንኛውም ስኬት ቀድመ ሁኔታ ነው! ሰውው እንደዚህ «አንድ ልብ» ሲሆን ነው የፖለቲካ እርምጃዎች መውሰድ የሚችለው። በዛሬው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሁኔታ ህብረተሰቡ ማድረግ የሚችለው እንደነዚህ አይነት ነገሮች ነው፤ በተለያዩ መዋቅሮች (የመንግስት መስሪያቤቶች፤ የሰራተኛ መሐበራት፤ የገበያ መሐበራት፤ የተቃራኒ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንደ ኢህአዴግ፤ ወዘተ) ስርጎ መግባትና መቆጣጠር፤ የእምቢተኝነት እንቅስቃሴዎች፤ ሰላማዊ ሰልፎች፤ ወዘተ።

የኢትዮጵያ ብሄርተኞች እነዚህን እርምጃዎች ማካሄድ ይችላሉ ወይ? እንደ አዲስ አበባና ሌሎች ከተማዎች የተለያዩ አይነት ሰዎች ስለሚኖሩባቸው፤ ከተማ በመሆኑ የመሐበራዊ ኑሮ ውስን ስለሆነ፤ ሰውዉ በደምብ ስለማይተዋወቅ፤ የመንግስት ደህንነት አትኩሮ ስለሚከታተላቸው፤ ወዘተ እንድዚህ አይነት ስራዎች ለማኮናሆን ከባድ ነው።

በአማራ ክልል ግን እነዚህ ችግሮች የሉም ወይም ያንሳሉ። ህዝቡ ባብዛኛው ለትውልድ የሚተዋወቅ ነው፤ አብዛኛውም ከገጠር ነው የሚኖረው። በደህንነት በኩልም መንግስት ብዙ አማራጭ የለውም። ኢህአዴግ በሀገሩ በአማራ ደህንነቶች ልቆጣጠር ካለ ይከዱታል። አንድ ልብ ማለት ይህ ነው፤ የገዛ ወንድሙንና ዘመዱን አያጠቃም። ከማጥቃት ፋንታ ለአዲስ አበባ ላሉት አዛዦቹ እያስመሰለም ቢሆን ከሀገሩ ህብረተሰብ ዘመዱ ጋር ይቆማል። ደህንነት አስፈጻሚዎቹን ከውጭ ክልሎች ላምጣ ከለ ደግሞ መንግስትን የሚያናጋ ጠባሳ የሚያመጣ የጎሳ ጦርነትን ይጋበዛል። ስለዚህ ህዝቡ ከተባበረ ከተማመነም «አንድ ልብ» ከሆነም ከሃዲዎቹም ውስን ከሆኑ የመንግስት ደህንነት ምንም ማድረግ አይችልም። በዚህ ምክንያቶች የአማራ ንቅናቄ ስኬታማ መሆን እድሉ ከፍ ያለ ነው።

የአማራ ንቅናቄ ተሳካ ማለት ደግሞ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች የፖለቲካ ኃይል በሚገባው ጨመረ ማለት ነው። ከሀገሪቷ ሁለቱ ትላልቅ ክልሎች አንዱ ከጎሳ ብሄርተኛው ኢህአዴግ እጅ ወጣ ማለት ነው። ስኬቱም እንደ አዲስ አበባ አይነቱን የኢትዮጵያ ብሄርተኛ የሚበዛበት ቦታዎች እንዲነሱ ይገፋፋል። ቅድም እንደጠቀስኩት ደግሞ ይህ የሀገር ብሄርተኛ ኃይል ሲጨምር የሀገሪቷን እሚዛናዊ የሆነውን የፖለቲካ ሁኔታ ወደ መስተካከል ይመራዋል። የጎሳ ፖለቲካ ያስፋፋውን ለሀገሪቷ አስጊ የሆኑትን ጎሰኝነትና ዘረኝነትንም እንድንቆጣጠርና እንድንቅንስ በሩን ይከፍታል። ባጭሩ ቢዝህ ምክንያት ነው የአማራ የፖለቲካ ንቅናቄ ለኢትዮጵያ ህልውና እጅግ አስፈላጊ የሆነው።

Wednesday 21 September 2016

«ወያኔ» እኛው የወለድነው ልጅ እንደሆነ አንካድ!

2009/1/11 .. (2016/9/21)

የጽሁፎቼ ሁሉ ዋና አላማ ለኢትዮጵያ ችግሮች ከኢትዮጵያዊ ብሄርተኝነት አኳያ መፍትሄ ለማጋኘት ነው። ስሜት ለማተንፈስ፤ ለመሳደብ፤ በባዶ ቤት ለመዛት ወይም ለመለመን አይደለም። መፍትሄ መፍትሄ መፍትሄ ነው አላማዬ። የአንድ ችግር መፍትሄ ለማግኘት ደግሞ ምንጩን ማወቅ ግድ ነው። ምንጩን ካወቅን መፍትሄው ይመጣል።

«ወያኔ» እኛው ሀገር ወዳድ ነን የምንለው ኢትዮጵያዊ ብሄርተኞች የወለድነው ልጅ እንደሆነ ከገባን ምን ስህተሀቶች አድርገን ልጃችን እንደዚህ እንደሆነም እነዚህንም ስህተቶች እንዴት በመአረም የኢትዮጵያ ጠክላላ የፖለቲካና መሐበራዊ ችግሮችን እንዴት መፍታት እንደምንችል እንረዳለን።

የኢትዮጵያ ዋና የፖለቲካ ችግርን በቀላሉ ማስቀመጥ ይቻላል፤ ያለው መንግስት በቂ ኢትዮጵያዊያንን አይወክልምም መላው ህብረተሰቡም በአንድ ሀገራዊ ውል (የሀገሪቷ ፖለቲካ ምን መምሰል እንዳለበት – social contract) አልተስማማምም።

ሁላችንም እንደምናውቀው ኢህአዴግ በህወሃት ትጽዕኖ የሚገዛ ድርጅት ነው። ርዓዮት ዓለሙም በጎሳ ብሄርተኝነት የተመሰረተ ነው። ከዚህ «ስዕል» ማን ነው የሚጎለው? ወይም ከሀገራችን ፖለቲካ የትኛው በርካታ ህዝብ የሚወክል ጎራ ነው የጠፋው? ኢትዮጵያዊ ብሄርተኛ ነኝ የሚለው ጎራ ነው የጠፋው። እንዴት እንደዚህ አይነት አገዛዝ በኢትዮጵያ ሊሰፍን ቻለ?! ከሌሎች ጽሁፎች እንደጠቀስኩት የኢትዮጵያ ብሄርተኞች በኃይለ ስላሴም በደርግም ዘመን የራስ ማጥፋት ዘመቻ ስላካሄዱ ነው። የኃይለ ስላሴ መንግስት እንደ መሬት ለአራሹ አይነት አስፈላጊ ለውጦች ባለማድረግና በኢትዮጵያዊነት ፋንታ ዘመናዊነትን እከተላለሁ ብሎ ሀገር አፍራሽ የሆነ የተማሪ ንቅናቄ የሚባል ትውለድ አፈራ። ደርግን ሻእብያን ህወሃያትን ኦነግን ኢህአፓ ወዘተ አፈራ። 1983 ሲደርስ እራሱን በደምብ አጥፍቶ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የገዢ ወገን በጎሳ ብሄርተኛ ብቻ ሞልቶ ቀረ። ለዚህ ነው ዛሬ ያለነው ሁኔታ የተፈጠረው እንደዚህም ነው ህወሃት ተፈጥሮ ያደገው።

ላለን ችግር ታድያ ምክንያቱ በመጀመርያ ህወሃት ነው? በፍጹም። ህወሃትም ኢህአዴግም እኛ በቀደድንላቸው ግዙፍ ቀዳዳ ባላቸው የመንፈስና የጭንቅላት አቅም የሚችሉትን እያደረጉ ነው። ከነሱ እስከ ዛሬ ያደረጉት በላይ መጠየቁ አግባብ አይደለም።

እስቲ ስሜታዊ ሳንሆን ተረጋግተን እናስበው፤ ኢህአዴግ ኢትዮጵያን እገዘዋለሁ ብሎ በፍጹም አስቦ አያውቅም። ኃይላችን ውስን ነው፤ የመኻል ሀገር መንግስቱ በርካታ ኃይልና አቅም አለው፤ ብሎ እንኳን ህወሃት ከሱ ጠንካራውም ሸአብያ ደርግን ከማሸነፍ ድርድርን በበር የሚያስበው። ህወሃት አሸንፎ ሙሉ ሀገሪቷን ሲገዙ ዱብዳ ነው የሆነባቸው።

በተፈጥሮ ትዕቢትን ይጨምራል። ኢህአዴግ ደግሞ እንደ ዳዊት ታላቁን ኃይለኛ ጎሊያድን ያሸነፈ ስለመሰለው ይበልጥ ኩራትና በራስ መተማመን አደረበት። ይህን ግብ መምታት መቻሌ ድርጊቴ በሙሉ ትክክል ነው ማለት ነው ብሎ ማሰብ ጀመረ። እራሱንም ከሌሎች ድርጅቶች በሙሉ ልዩ ጎበዝና የበላይ አድርጎ ማሰብ ጀመረ። ህወሃት በዚህ መንፈስ ነው በ1983 ስልጣን የያዘው።

ከዛ ቀጥሎ ስልጣኑን በሚያረጋግጥበት ሰሞን ተቀናቃኞቹ አንድ በአንድ ሲፈርሱ አየ። ኦነግን በቀላሉ አሸነፈ። ኢህአፓም ሌሎችም እንደዚሁ። የኢትዮጵያዊ ብሄርተኛ የፖለቲካ ጎራ ደግሞ ጭራሽ ምንም ኃይል ስላልነበረው ኢህአዴግ ምንም ማድረግ አላስፈለገውም።

በተዘዋዋሪ የኢትዮጵያዊ ብሄርተኝነት የፖለቲካ ጎራ በዛን ጊዜ ኃይል ማጣቱ ኢህአዴግን እጅግ የተሳሳተ ድምዳሜ ላይ እንዲደርስ አድርጎታል። ኃይል ስላጣ ከጥቂት የሆኑ የተማሩ ወገኖች በስተቀር ይህ ጎራ ከህብረተሰቡ ምንም ድጋፍ የለውም ብሎ ኢህአዴግ ገመተ። የቀዝቃዛ ጦርነት፤ የደርግ የኮሙኒስት አቋም፤ የኤኮኖሜው መበላሸት፤ ወዘተ እንደ ምክንያት ሳይቆጠር ደርግ መሸነፉ ኢትዮጵያ ብሄርተኝነት እንደተሸነፈም ብሀገሪቷም እንደማይፈለግ ተቆጠረ። ይህ ታልቅ ስህተት መሆኑን ኢህአዴግ በየጊዜው እየገባው ሄዷል።

ዞሮ ዞሮ ኢህአዴግ ሀገሪቷን ተቆጣጠረ። ማንም አልተፎካከረውም። ትዕቢቱም እየጨመረ ሄደ!

ኢህአዴግ ስልጣኑን ካረጋገጠ በኋላ ህዝቡ አልፎ አልፎ መንግስት ላይ መነሳት ጀመረ። ኢህአዴግ ሁሉንም አይነት አመጽ (ለምሳሌ የ1986ና የ1993) በቀላሉ ተቆጣጠረ። ትዕቢቱ መጨመሩ ቀጠለ።

በዚህ ጊዜም አንዳንድ ተቃዋሚ ድርጅቶች ቢያንስ መንግስትን ለመተቸት ያህል ይበቁ ነበር። ግን እርስ በርስ ሲጣሉና በትንሽ ግፊት ሲፈርሱ ሲያይ የኢህአዴግ ትዕቢት ማየል ቀጠለ።

ከዛ ቀጥሎ የኤርትራ ጦርነት ተነሳ። ኢህአዴግ ይሄንንም ፈተና እንደ ድርጅት ቆስሎም ቢሆን 70,000 በላይ ወታደር ሞቶም ቢሆን አሸነፈ። የሚፈራውን ታላቅ ወንድሙን በማሸነፉ የዝቅተኛ መንፈሳቸውን አስወገዱ። ኢትዮጵያንም ለብቻው ተቆጣጠረ! ትዕቢቱም ጨመረ። እኛ ኢትዮጵያዊ ብሄርተኞች ከዳር ሆነን አጨበጨብን።

አምስት ዓመት በኋላ ኢህአዴግ የምርጫ 1997 ፈተና አጋጠመው። ፈተናው እጅግ ከባድ ቢሆንም በመጨረሻ ኢህአዴግ ያለውን የተቃዋሚ ጎር ድራሹን አጥፍቶም የሀገሪቷን ኤኮኖሚ ክፍ አድርጎ ተቃውሞን ገደለው። ለዚህ ሁሉ ድል እራሱን ለመሸለም ያህል የ2007 ምርጫን መቶ በመቶ እንዲያሸንፍ አደረገ። ትዕቢቱ ናረ!

ይህንን ታሪክ ስንመለከት እኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ህወሃትን እንደፈጠርነው፤ አጣመን እንዳሳደግነው፤ ጥሩ ምሳሌ ባለመሆናችን እንዲክደን ያደረግነው፤ እራሳችንን በማጥፋት ልቅ እንዳደረግነው ሁሉ ማመን አለብን። ኢትዮጵያ በኛ እጅ ሆና ደጋግመን ተሳሳትን አጠፋን ጨኮንንም አበላሸንም። ለእነ ህወሃት መንገዱን ጨርቅ አደረግንላቸው።

ስልጣን ከያዙም በሗል ጠፋንባቸው። እርስ በርስ ያለመተባበርም የመጠራጠርም ብሽታ ይዞን እነሱን የሚፎካከር የፖለቲካና ህዝባዊ ኃይል መዋቀር አልቻልንም። ይህም ኢህአዴግ የተሳሳተ መንገዱን እንዲቀጥል ረዳው ብቻ ሳይሆን አስገደደውምም ማለት ይቻላል። አንድ ድርጅት እራሱን ለማስተካከል ሃሳብ ብቻ ሳይሆን ተግባራው ምክንያት (incentive) ያስፈልገዋ። ኢህአዴግም የሚቀናቀነው ኃይል ፊቱ ቢቆም ኖሮ የተሻለ ሃሳብን እንዲያሰላስል ይገደድ ነበር። እኛ የኢትዮጵያዊ ብሄርተኞች ግን ይሄንን ትንሽ ግዴታችንንም አላሟላንም።


ታድያ ሀገራችን የፖለቲካ ችግር ምንጭ ዬት ነው? ከኛ ከኢትዮጵያዊ ብሄርተኞች ነው። መፍትሄውም ከኛ ነው። ኢህአዴግን መክሰስም መፍትሄ ከሱ መጠበቅም ዋጋ ዬለውም። እኛ ነን ችግሩን ያመጣነው እኛም ነን የምንፈታው። ከፈታነው በኋላ ልጆችንን «ወያኔን» ይቅርጣ እንጠይቀዋለንም።


Thursday 15 September 2016

በፈቃዳችን ነው የምንገዛው

2009/1/4 ዓ.ም. (2016/9/14)

ይህን ነጥበ በተደጋጋሚ በተለያየ መንገድ ለማስረገጥ እወዳለሁ። የዛሬው የኢህአዴግ አገዛዝን የኢትዮጵያ ህዝብ አይፈልገውም የምንለው የዚህ አባባላችንን ሙሉ ትርጓሜ ልንረዳ ይገባል። የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ኢህአዴግን የማይፈልግ ከሆነ ኢህአዴግ የአናሳ ሰዎች አገዛዝ ነው ማለት ነው። አናሳ ድጋፍ ያለው መንግስት ያለ የሌላው ፈቃደኝነት ሊገዛ አያችልም። ልድገመው፤ የአናሳ ድጋፍ ያለው መንግስት ያለ ሌላው ፈቃድ ሊገዛ አይችልም! 

ስለዚህ «የኢህአዴግ አገዛዝን የኢትዮጵያ ህዝብ አይፈልገውም» ስንል የምንገዛው በገዛ የራሳችን ፈቃደኝነት በራሳችን ጥፋት በራሳችን ድክመት ነው ማለት ነው። ሌላ ትርጉም የለውም። የችግሩ ምንጭም መፍትዬውም ከኛ ነው። ኢህአዴግ እንደ በሩ ክፍት የሆነ ቤት ያገኘ ሌባ ነው። ወደ ቤታችን ብንመለስ ሰተት ብሎ ይለቃል። ታድያ መችሄ ነው ወደ ቤታችን የምንመለሰው?

«ድጋፉ አናሳ ቢሆንም ፖሊሱ ደህንነቱ የጦር ሰራዊቱም በሙሉ ከነሱ እጅ ናቸው» ይባላል የኢህአዴግን ኃይልና ጥንካሬ ለማስረዳት። ለማስረዳት ብቻ ሳይሆን ለድክመታንንና ለሽንፈታችን ምክነያት ለመፍጠር። ኢህአዴግን ለማሸነፍ እጅግ ከባድ መሆኑን ለመግለጽ። እንዲሁም ኢህአዴግ ስልጣን በመያዙ ሃላፊነታችንን ለመሸሽ። 

ግን ለዚህ መልሱ ቀላል ነው። መሳሪያው በማን እጅ ነው? በጣም አብዛኛው ፖሊስና ጦር ሰራዊት አማራ ኦሮሞና ከትግራይ ያልሆኑ ጎሳዎች ናቸው። ይህ ማንም ያማይክደው ሀቅ ነው። የፖሊስና የጦር ስራዊቱ አመራር ብቻ ነው ባብዛናው ህወሓቶች ወይም ትግሬዎች። መሳሪያ ደግሞ በአመራር እጅ ሳይሆን በተራ ወታደሩ እጅ ነው ያለው። ስለዚህ መሳርያው በአማራና በኦሮሞ እጅ ነው ማለት ይችሃላል!

እሺ ጡንቻውን ደግሞ ትተን በመንግስት መስርያቤት አብዛኛው ማን ነው። በዚህም ረገር ትግራዩ አናሳ ነው። ለመደምደም ያህል የኢትዮጵያ ስምንት በመቶ ሆነው የትግራይ ህብረተሰብ አገሩን በሙሉ ሊያስተዳድሩት አይችሉም። ሊያስተዳድሩም ሊቆጣጠሩም ሊከታተሉም አይችሉም።

ሌሎቻችን ሃላፊነታችንን ድክመታችንን ለማምለት ምክነያት ፈልገን «ትግራይ ብቻ ሳይሆን ከሌሎቹ ጎሳዎች አደርባዮች እየረዷቸው ነው» እንላለን። ታድያ አደርባዮቹና ትግራዩ ሲደመር አብዛኛ ነው? ከሆነ ኢህአዴግ አብዛኛውን የሚወክል ጥሩ መንግስት ነው ማለት ነው! ታድያ ነው?አይደለም። በእውነቱ የአደርባዩም ቁጥር ትንሽ ነው።

ታድያ እንዴት ነው ኢህአዴግ የሚገዛው። በሌሎቻችን ፈቃድና ትብብር ነው። ትብብር ማለት እያንዳንዳችን ለዚህ አገዛዝ ያለንን አስተዋጾ ተመልክትን አምነን ከመቀየር ይልቅ «ወያኔ ሴጣን ነው» እያልን ማልቀስ ነው። ለኢህአዴግ ስልጣን ለመያዝ ያለንን ሃላፊነት ማምለጥ የኛ የተቃዋሚ ችግር ላይ ከባዱንና አስፈላጊውን ስራ መስራት እንፈልጋለን። «ወያኔ ሴጣን ነው» ብለን መዝፈን ነው የሚቀለን።

ከአብዛኛው የፖለቲካ ጎራ ደግሞ ኢትዮጵያዊ ነን ኢትዮጵያዊ ብሄርትኞች ነን የምንለው ለኢሃዴግ አገዛዝ ትልቅ ሃላፊነት አለብን። ኢህአዴግን በመጀመርያ የወለድነው እኛ ስለሆንን። በኃይለ ስላሴ ዘመን በቂ ለውጥ ባለማድረጋችን፤ የማይሆን «ፈረንጅ አምላኪ» ትውልድ ወልደን የራስ ማጥፋት ዘመቻ ማድረጋችን፤ የደርግን መንግስት ተቆጣትረን ትክክለኛ መስመር ባለማስያዛችን፤ በቀይ ሽብር እንደገና የራስ ማጥፋት ዘመቻ ማካሄዳችን፤ እነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች ናቸው ሻዕብያ ኢህአዴግና ኦነግ በ1983 የኢትዮጵያን ህልውና ብቸኛ ወሳኞች እንዲሆኑ ያደረጉት። ከዛም ለ25 ዓመት እርስ በርስ እየተጣላን ለህብረተሰቡ መጥፎ ምሳሌ እየሆንን አሳለፍን። ሃላፊነቱ ታድያ የኛ አይደለምን?

ሃላፊነት ወስደን ምን እናድርግ። ሁሉም በበኩሉ ማድረግ የሚችለው አለ። ሆኖም ሁሉ ስራችን መፈከር መሆን ያለበት «ክፉ አታድርግ» ነው። ይህ ማለት አብዛኞቻችን በመሃበራዊ ኑሮው ክፉ ነገር ከማድረግ ብንቆጠብ፤ ከጎረቤቶቹ ጋር ተፋቅረን ብንኖር፤ ከስራ ባልደረቦቹ ጋር ብንግባባ፤ ለስራተኞቻችን ደግ ብንሆን፤ የተቸገሩትን በደምብ ብንረዳ፤ ወዘተ ለውጥ ወድያው ይመጣል። ኢህአዴግም ምንም ሊከላከለው አይችልም።

ዛሬ እነዚህ አይነት አዝማሚያ እያየን ነው። በአማራ ክልል ለምሳሌ አመራሩም ፖሊሱም ወታደሩም ክፉ ነገር አላደርግም የራሴን ህዝብ አልገልም አልጎዳምም ስላለ ነው የእምቢተኝነት ንቅናቄው እዚ የደረሰው። የብአዴን አመራር ፖሊስና ወታደር በመቅጣት ብቻ ሳይሆን በተለያየ መንገድ ህዝቤን እረዳለሁ፤ በትክክል አስተዳድራለሁ፤ አልጎዳም፤ ወዘተ ካለ ኢህአዴግ ከሌሎች ክልሎች አስተዳዳሪ ፖሊስና ወታደር ወደ አማራ አምጥቶ ለመቆጣጠር ቅንጣት አቅሙ የለውም። (አለው ካልን አናሳ መሆኑን አጣን ማለት ነው!) ለጊዜው ለማስፈራራት ያህል የብዙ ሰው መግደልና ማሰር አቅም አለው እያደረገውም ነው ግን ከተወሰና ደረጃ ማለፍ አይችልም። 

ኢህአዴግም በፖለቲካ የበሰለ ስልሆነ ይህን በደምብ ይገባዋልና በዚህ ማስፈራራትና ጭቆና ነገሩን ካላበረድኩኝ መቆጣጠር አልችልም ብሎ ያምናል። በተዘዋዋሪ ዛሬም የሚካሄደው ማስፈራራት የአማራ ከሃዲዎች ባይኖሩበት ሊካሄድ አይችልም ነበር። (ከሃዲዎቹንም እኛ ነን የወለድናቸው። ቁጥራቸው በርካታ ከሆኑ በአማራ ክልል በኛ መሃል ችግር አለ ማለት ነው የከሃዲ ፋብሪካ ሆነናል ማለት ነው! ከሃዲዎቹ ላይ ከማተኮር የሚፈጠሩበትን ምክንያት አጣርቶ ማስተካከል ነው ያለብን።)

ለአማራ ህዝብ ምክሬ እንደዚህ ነው። እርስ በርሳችሁ ሰላም፤ አንድነት፤ መታማመንና ፍቅር አዳብሩ። መሃበራዊ ኑሮአችሁ ያማረ ይሁን። የቀበለ አስተዳደርን በጥሩ ሁኔታ አስፈጽሙ። ካህናት የህዝቡን የህሊና ንቃትን አዳብሩ በስብከት ሳይሆን ይበልጥ ምሳሌ በመሆን። ውስጣችሁ ያሉትን ቅራኔ ያለባቸውን ቡድኖች እንደ የተለያዩ አናሳ ጎሳዎች በጥበብና በፍቅር ያዙም የጥፋት አካል እንዳይሆኑ ተንከባከቧቸው! በማህላችሁ ያሉትን የተጎዱ ስራ ያጡ ማደርያ ያጡ ወዘተን ተንከባከቧቸው። ሰላማዊ ሁኑ፤ የሰው ቤት ማቃጠል ንብረትንም ማውደም ይቅር። ይህ የህሊናም የፖለቲካም ጉዳት ብቻ ነው የሚያመጣው። ከፍተኛ አስተዳደር ቦታ ላይ ያላችሁ በትክክል አለ ሙስና አለጥፋት አለክፋት አስተዳድሩ። ፖሊስና ወታደሮች መትፎ ነገር አታድርጉ። ሄዳችሁ እሰሩ የሚል አለአግባባ የሆነ ትዛዝ ብታገኙ እምቢ ከማለት ሰውየውን አጣን ብላችሁ ተመለሱ! ወዘተ።

እንደዚህ አይነት እርምጃዎች ሁሉም ህብረተሰብ ማድረግ ይችላል በቀላሉም መንግስትን ይለውጣል። እግዚአብሔር ከኛ ጋር ይሁን ያጠፋውንም ይቅር ይበለን ለፈተናም ካኑ ወድያ እንዳንገዛ ብርታቱ ይስጠን።

Wednesday 14 September 2016

ከጎረቤቱ ጋር የተጣላ «ወያኔ» ነው!

2009/1/4 ዓ.ም. (2016/9/14)

የጎረቤታሞቾ ልጆች ይጣላሉ። አንዱ ሌላውን የትምህርት ቤት መጸሐፌን ሰረቀ ብሎ ይከሰዋል። ወሬው ወደ ወላጅ ጆሮ ይደርሳል። የተከሳሹ ቤተሰብ እንዴት ልጃቸው ልጃችንን ሌባ ይላል ብለው ጎረቤቶቻቸውን ይቀየማሉ። በዚህ ተነስቶ የሁለቱ ጎረቤታሞቾ ግንኙነት መበላሸት ይጀምራል። ሐሜትና ክስ መመላለስ ይጀምራሉ። በተዘዋዋሪም በቀጥታም መሰዳደብ ይጀምራሉ። አንዱ ሌላውን እንደ «ጠላት» ይቆጥራል። ጓደኞቻቸውም ይወግናሉ።

አብዮቱ ከነበልባል ወደ እሳት እየተፋፋመ ነው። አንዱ ቤተሰብ የጠላት ጎረቤታቸውን ልጅ ኢህአፓ ነው እያሉ ማስወራት ይጀምራሉ። ልጁ ታስሮ ይወሰዳል ይሰቃያል ይገደላልም። ታሪክ ልጁን የደርግ ሰለባ አድርጎ ይመዘግበዋል። እውነቱ ግን የጎረቤት ሰለባ መሆኑ ነው። ደርግ መሳርያ ብቻ ነበር።

በትምህርት ቤቱ ሰራተኞች መካከል ምንጩ የተረሳ የቆየ ጸብ አለ። ሰራተኞቹ ለሁለት ተከፍለዋል፤ ዋናው አስተዳዳሪው አንድ ወገን ይዟል፤ ምክትል አስተዳዳሪው ሌላውን ወገን ይዟል። ጦርነት አይደለም፤ ትምህርት ቤቱ ይሰራል ልጆቹም ይማራሉ። ግን ውስጥ ለውስጥ ችግር አለ፤ ትምህርት ቤቱ በሐሜትና ሹክሹክታ መንፈስ ተይዟል።

ኢህአዴግ ስልጣን በቅርብ ይዞ ለአብዮታዊ ዴሞክራሲ እንቅፋት ለሆኑትን «ነፍጠኖች» ከመንግስት ስራ እያባረረ ነው። ምክትል አስተዳዳሪው የሱ «ጠላት» ጎራ የሆኑትን በውሸት ትምክህተኞች ነፍጠኞች ብሎ ለመንግስት ይጠቁማቸዋል ከሰራም ይባረራሉ። ኢህአዴግ አባረራቸው ተብሎ ታሪክ የሚዘግበዋል። ግን ይህን ጉዳት ያደረሱባቸው ባልደረቦቻቸው ናቸው። ኢህአዴግ መሳርያ ብቻ ነበር።

ትምህርት አይሆነውም የሚባል ልጅ ከሰፈራችን አለ። ቤተሰቡም ዘመዶቹም ትምህርት ቤቱም ካህኑም አይረዱትምም አይረዱትም። ጭራሽ ይለቅፉታል ይሰድቡታል ይተቹታል። ልጁ እያደገ ሲሄድ ብሶትና ምሬት ያለው ከራሱ ጋር የተጣላ የዝቅተኝነት ስሜት ያለው ጎረምሳ ይሆናል።

ከምርጫ 97 በኋላ ሰላማዊ ሰልፎች እየተካሄዱ እያለ ፌዴራል ፖሊስ እየዞሩ ህዝብን እያሰሩ ነው። ይህንን ብሶት የተሞላው ልጅ ከሰፈርህ የሰልፉን አስተባባሪዎች የሆኑትን ጠቁምልን በቋሚነትም ጠቋሚያችን ሁንልን ብለው ይጠይቁታል። ልጁ ተስማምቶ በርካታ የሰፈር ልጆችን ይጠቁማል። እስረኞቹም ቤተሰቦቻቸውም ይሰቃያላኡ። የታሰሩት የተሰቃዩት ታሪክ ሲመዘገብ እንደ ኢህአዴግ ሰለቦች ይመዘግባቸዋል። ግን ጠቋሚው ባይጠቁማቸው ምንም አይደርስባቸውም ነበር። ልጁ አሁንም የሰፈሩ «ጠቋሚ» ትብሎ ይታወቃል።

ምርጫ 97 ሊደርስ አቅራብያ አቋማቸው ተመሳሳይ የሆኑት የተቃዋሚ ፓርቲዎች አንድ ግንባር ፈጥረው እራሳቸውን «ቅንጅት» ብለው ሰይመው ምርጫውን ይወዳደራሉ። አሸንፉም። መንግስት ግን አላሸነፋችሁም አመጽም ማስነሳት ሞክራችኋል ብሎ ያስራቸዋል። ከዓመት በላይ ታስረው ከእስር ቤት ሲወጡ ባመረረ የእርስ በርስ ጥል ይለከፋሉ። በጸባቸው ምክንያት የነፃነት ንቅናቄውንም እንዲፈርስ ያደርጋሉ። እርስ በርስ ቢጣሉም የነፃነት ትግሉን ብያከሽፉትም «ውያኔ» በድሎናል ብለው ያለቅሳሉ።

አምባገናናዊ መንግስት በካላሉ ካስቀመጥነው «አምባገነን» የሚባለው የአብዛኛው የህዝብ ድጋፍ ስለሌለው ነውና የራሱን ፍላጎት ህዝቡ ላይ ስለሚጭንባቸው ነው። አብዛኛውን ቢወክልማ ምን «አምባገነን» ያስብለዋል። ኢህአዴግ አምባገነናዊ ነው ካልን የትንሽ ሰው ቁጥር ድጋፍ ነው ያለው ማለት ነው። የትንሽ የሰው ቁጥር ድጋፍ ያለው መንግስት ደግሞ አብዛኛ የሆነውን ህብረተሰብ መግዛት የሚችለው ይህ ህዝብ እርስ በርስ ለመከፋፈልና ለመገዛት ፈቃደኛ ከሆነ ብቻ ነው! «ፈቃደኛ» የሚለውን ቃል የተጠቀምኩት አውቄ ነው። ምክንያቱም አንድ ህብረተሰብ «ተከፋፈል» ትብሎ መታዘዝ አይቻልም። እራሱ ነው ልከፋፈል ውይም አልከፋፈል ብሎ የሚወስነውና።

ይህ መከፋፈል ነው ኢህአዴግን እስካሁን በስልጣን ላይ ያቆየው። ስለዚህ የኢህአዴግ ኢትዮጵያን እስካሁን መግዛት ሃላፊነቱን መሸከም ያለበት በገዛው ፈቃድ የተከፋፈለው የአገሪቷ ህብረተሰቡ ነው። 

ከላይ ያስቀመጥኳቸው ምሳሌ ታሪኮች ይን ይገልጻሉ። እርስ በርስ ሲጣላ ሲጠላ ሲቃረን የዋለ ህዝብ እንዲህ ይላል «ለጎረቤቴ ወይም ለወንድሜ ያለኝ ጥላቻ ለአምባገነኑና ለአምባገነኑ ጭካኔ ካለኝ ጥላቻ ይበልጣል፤ አምበገነኑ ይግዛኝ!» ታድያ የፖለቲካ ችግር ምንጭና ሃላፊነት ዬት ነው? ከ«ዎያኔ» ነው ወይስ ከኛ ኢትዮጵያ ህዝብ ነው?። ከኛ እንደሆነ ግልጽ የሆነ ይመስለኛል። የችግሩ መንጭም እኛው ነን፤ ሃላፊነቱም የኛው ነው፤ መፍትሄውም ከኛው ነው።

የታወቁት የሶቪዬት (የሩሲያ) ጸሃፊ አሌክሳንደር ሶልዠኒትሲን ለረጅም ዓመታት በ«ጉላግ» ከሚባለው የሶቪዬት «የሞት» እስር ቤቶች በፖለቲካ ምክንያት ታስረው ነበር። የሶቪዬት የኮምዩኒስት አምባገነናዊ መንግስት እስከ 20 ሚሊዮን ሰዎች (ከ160 ሚሊዮን የህዝብ ቁጥር) ወደነዚህ የጉልበት ስራ የስቃይና የሞት እስርቤቶች ልኮ ነበር።

ሶልዠኒትሲን ጀግና የሆኑ ሀገራቸውን ያገለገሉ ወታደር ነበሩ። ቢሆንም መንግስቱና በተለይ ሹማምንቱን ወቀስክ ተብለው ታሰሩ። ከእስር ቤት ሆነው እንደማንኛውም የህሊና እስረኛ «ለምን ታስረርኩኝ» «ምን አይነት ጭካኞች ናቸው» የሚሉትን ሃሳቦች ያንሸራሽሩ ነበር። ግን ከእስር ቤት ሆነው ስለ እስራ ዘመናቸው ሲመዘግቡ ከታች የተጠቀሰውን ታላቅ ሃሳብ ተገለጸላቸው፤ በታወቀው «የጉላግ አርኪፔላጎ» መጸሃፍ ሳፉት (ትርጉም የኔ ነው)፤

ከእስርቤታችን አልጋ የሆነው የበሰበሰው ገለባ ላይ ጋደም ብዬ ነው ለመጀመርያ ከውስጤ የበጎ መንፈስ የተሰማኝ። እውነቱን ቀስ በቀስ እንደዚህ እንደሆነ መረዳት ጀመርኩኝ፤ ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር የሚያልፈው በሀገሮች፤ በመደቦች፤ በፖለቲካ ፓርቲዎችም መካከል አይደለም፤ ይህ መስመር የሚያልፈው በያንዳንዱ የሰው ልብ መኻል ነው። መስመሩ እድሜአችን በሙሉ ከውስጣችን መለስ ከለስ ይላል። በክፉ የተሞሉ ልቦችም ቢያንስ ቅንጣት ያህል ጥሩነት ይኖራቸዋል፤ ከሁሉም ጥሩ ከሚባለውም ልብ ከአንድ ጥጓ ትንሽ ክፋት ይኖራታል።

በየቦታው እየዞሩ ያሉ ክፉ ስራ የሚሰሩ ክፉ ሰዎች ቢኖሩና እነሱን ከኛ መለየትና ማጥፋት ብቻ ቢሆን ኖሮ እንዴት ቀላል ይሆን ነበር! ግን ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር ከያንዳንዱ የሰው ልጅ ልብ መካከል ነው የሚያልፈውና ማን አለ ከራሱ ልብ ቁራጭ ቆርጦ ለማስወጣት ፈቃደኛ ይሆነ?

በዚህ አባባላቸው ሶልዠኒትሲን የሚሉት የአምባገነናዊ ስረዓት የገዢና የመሪ ውጤት ሳይሆን የያንዳንዱ ሰው ድክመትና ጠፋት ውጤት ነው። ይህ አስተማሪ አባባል የዛሬውን የኢትዮጵያ ፖልቲካ ሁነታ በደምብ ይገልጻል።

ቅድም እንዳልኩት ኢህአዴግ አናሳ ድጋፍ ነው ያለው። በተጨማሪ ከለሎች አምባገነናዊ ስረዓት አናሳነቱ የተለየ ነው። ለምሳሌ የሶቪዬት መንግስት አናሳ ድጋፍ ቢኖረውም ይህ ደጋፍ በጎሳ የተመሰረተ አልነበረም። ስለዚህ የሶቪዬት ህዝብ ተጨቆኛለሁ ሲል በራሴ ወገን በሶቪዬቶች ነው የተጭቆንኩት ብሎ ነበር የሚያስበው። የኢህአዴግ አገዛዝ ግን አናሳ ብቻ ሳይሆን በጎሳ የተመሰረተ ነው። ህገ መንግስቱም አስተምረውም እንደዚህ ነው። ህዝቡም እንደዚህ ነው የሚመለከተው። የሰው ልጅ ባህሪ ደግሞ በራሱ ወገን ቢገደል ይሻለዋል በሌላ ወገን ወይም ጎሳ ከሚጨቆን! ስለዚህ የኢህአዴግ የጎሳ አገዛዝ ከሌላው አማገነናዊ ስረዓት ይበልጥ ህዝብ ቅራኔና አመጽ የተጋለጠ መሆን ነበረበት።

ይህን አመዛዝነን ከተረዳን ለኢህአዴግ በስልጣን መቆየት እኛ ኢትዮጵያዊያን ዋና ምክንያት መሆናችንን ይገባናል። አንድነት ያለው ህብረተሰብ ብንሆን እርስ በርስ ብንስማማ ብንተሳሰብ ብንፋቀር ኢህአዴግ ድሮ ወድቆ ነበር። በተጨማሪ ማለት የምንችለው ኢህአዴግ በኃይል ሊገዛን አይችልም በኃይል ገዝቶንም አያውቅም! በኛ እርዳታ፤ ትብብርና ፈቃድ ነው እየገዛን ያለው። የኛ ጥፋትና ሃጥያት ነው የኢህአዴግ አገዛዝ ምሶሶ። ስለዚህም ኢህአዴግን የፈጠርነው የምናቆመውም እኛ ከሆንን የምናፈርሰውም የምናጠፋውም እኛው ነን የምንሆነው። ውግያና ተመሳሳይ ቀውጥ አያስፈልግም፤ ከጎረቤቴ ጋር አልጣላም ማለት ብቻውን በቂ ነው። እንደዚህ ካረግን የኢህአዴግ ይፈርሳል። እርግጠኛ ነኝ በርካታ የኢህአዴግ አባላትም ያንን ሸክማቸውን የሚያወርዱበትን ቀን በጉጉት የጠብቁታል!

Thursday 8 September 2016

ሙባረክና መለስ

2008/13/2 ዓ.ም. (2016/9/7)

ስልጣን ላይ በነበሩበት ግዜ ፕሬዘዳንት ሆስኒ ሙባረክ ከሃይማኖት ጋር ያልተያያዙ (“secular/liberal”) የግብጽ የዴሞክራሲ ተቀናቃኞችንና ደጋፊዎቻቸውን ለማስፈራራትም ለመተንኮስም «እኔ ከስልጣን ብወርድ የሙስሊም አክራሪዎቹ ይገዟችኋል፤ የምትጠሉትን የሙስሊም ሃይማኖት አገዛዝ የሸሪያ ህግንም ይጭኑባችኋል» ይሏቸው ነበር። ከዛ ደግሞ ወደ ሙስሊም ወንድማማቾች የሚባሉት ትንሽ «ከረር» ያሉ የሙስሊም ፖለቲካ ፓርቲና ደጋፊዎቹ ፕሬዘዳንት ሆስኒ ዞር ብለው «እኔ ባልገዛ ኖሮ እነዚህ ሃይማኖታችሁን የማያከብሩ፤ ሃይማኖት የሌላቸውና ክርስቲያኖች ይገዟችሁ ነበር» ይሏቸው ነበር! ሁለቱም ሙባረክን የሚጠሉትና ዴሞክራሲ እንፈልጋለን ባይ የሆኑት ከሃይማኖት ውጭ ዴሞክራሲ ተቀናቃኞችና የሙስሊም ወንድማማቾች ተፈራርተው አንዱ ሌላው ስልጣን እንዳይዝ ብለው ሙባረክ በስልጣን ላይ እንዲቆይ ፈቀዱ።

ሆኖም ግን አንድ ቀን ሁለቱ የዴሞክራሲ ተቀናቃኝ ጎራዎች በአምባገነኑ ሙባረክ መገዛት በቃን አሉ። ፕሬዘዳንት ሆስኒ ሙባረክን ከስልጣን ለማውረድ ተባበሩ። የሁለቱ ድጋፍ ተደምሮ የሙባረክ መንግስት ከነበረው ድጋፍ እጅግ ከፍተኛ ስለነበር በ2011 እ.ኤ.አ. ወደ 1000 አካባቢ ሰው በሞተለት «የአረብ ፀደይ» ተብሎ በተሰየመው ዓብዮት የሙባረክን መንግስት ገለበጡ። የምዕራብ ዓለም ሚዲያዎች በሙሉ አጨበጨቡ።

የሙባረክ መንግስት ከወረደ በኋላ አዲሲቷ ግብጽ ምን መምሰል አለባት በሚለው ጉዳይ በርካታ ፓርቲዎች ተወያዩ ተስማሙና  አገሪቷንም ለነፃ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ አበቋት። ምርጫውን የሙስሊም ወንድማማቾች ፓርቲ በትንሽ ልዩነት አሸነፈ። የቀሩት የፓርላማ መቀምጫዎች በሌሎቹ በበርካታ የዴሞክራሲ ተቀነቃኝ ፓርቲዎች ተያዙ።

ልክ የሙልሲም ወንድማማቾች ስልጣን ከያዘ በኋላ ችግሮች መታየት ጀመሩ። በመጀመርያው ሌሎቹ ፓርቲዎች የሙስሊም ወንድማማቾች ከሃምሳ በመቶ በላይ ድምጽ አገኝቶ ሙሉ ስልጣን ማግኘቱን ቅር ብሏቸው ነበር። ከዛም ቀጥሎ የሙስሊም ወንድማማቾች መሪ መሃመድ ሞርሲ የፓርቲያቸውን ኃይል የሚያጠነክርና ቀስ ብሎ የሸሪያ ህግ ለማምጣት የሚያመቹ እርምጃዎች መውሰድ ጀመረ። እርግጥ አላማቸው የሸሪያ ህግ ላይሆን ይችል ነበር፤ ነገር ግን የሌሎቹ የፖሊቲካ ፓርቲዎች ጠንካራ ጥርጣሬ ይህ ነበር። በተጨማሪም የሙስሊም ወንድማማቾች ቀስ በቀስ ስልጣኑን እየጨመረ እራሱን ሰዎች በየቦታው እየሾመ የሌሎችን ስልጣን እየሸረሸረ ነበር።

በግብጽ ከሃይማኖት ነጻ የሆኑት ፓርቲዎችና እንደ የሙስሊም ወንድማማቾች አይነት የሃይማኖት ፓርቲዎች መካከል ያለው ጥርጣሬና ጥላቻ እንደገና መታየት ተጀመረ። ሙባረክን ለመጣል ብቻ ነበር የተስማሙት እንጂ ከዛ በኋላ ለሚመጣው የግብጽ የፖሊቲካ ሁኔታ ከልባቸው አልነበረም የተስማሙት። የዓመታት ጥርጣሬና አለመስማማታቸውን አላስወገዱም ነበር። በአንድ አገር በሰላምና ሁሉንም በሚያስማማ ህግ ስር አብሮ ለመኖር አልተስማሙም ነበር። ትንሽ አለመግባባት ሲመጣ ወዲያው ወደ ድሮው ጥርጣሬና ጥላቻቸው ተመለሱ።

የዚህ ታሪክ የመጨረሻው ክፍል እጅግ አሳዛኝና አሳፋሪ ነው። አስተማሪም ነው። ከሃይማኖት ነጻ የሆኑት ፓርቲዎች ሁለተኛ አቢዮት አስነሱ። ሙባረክን በስልጣን ላይ ያቆየውን ኃይል የግብጽ ጦር ሰራዊትን የሞርሲን መንግስት እንዲገለብጡ ለመኑ! የሞርሲ መንግስት በዴሞክራሲ ከሚገዘን አምባገነኑ ጦር ሰራዊት ይግዛን አሉ! ይህም የመንግስት ግልበጣ ተካሄደና ይባስ ብሎ ሞርሲና በርካታ ባልደረቦቹ ታሰሩ፤ የሞት ፍርድም ተፈረደባቸው!

ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዘናዊም በስልጣን ላይ በነበሩበት ዘመን ህወሓት ወክለው ደጋግመው አማራውን «እኛ ከስልጣን ብንወርድ ኦሮሞ ብሄርተኛው ያርዳችኋል»፤ ኦሮሞውን ደግሞ «እኛ ከስልጣን ብንወርድ ነፍጠኛው አማራ መሬታችሁን ይነጥቅና ባርያ ያደርጋችኋል» እያሉ ይዘፍኑ ነበር። ሁለታችሁ አትስማሙም ልትስማሙም ስለማትችሉ እኛ ህወሓት መግዛት አለብን ይሉ ነበር። ዛሬም በርካታ የህወሓት አክራሪዎች በዚህ አስተሳሰብ እንደተመረዙ ያሉ አሉ።

ሆኖም ይህ የህወሓት ዘፈን የተወሰነ እውነታ እንዳለው እኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ማመን አለብን። ችግራችንን ለመፍታት ችግራችንን ማመን አለብን። በአማራና ኦሮሞ ፖለቲከኞች መካከል ብቻ ሳይሆን በስመ ኢትዮጵያ የሚንቀሳቀሱ ፖሊቲከኞች መካከል እጅግ ከባድና አሳፋሪ ቅራኔ፤ ሽኩቻ፤ አለመተማመንና አለመስማማት አለ። ባለፉት የተወሰኑ ዓመታት ግን እነዚህ ቅራኔዎች እየቀነሱ ሄደዋል። ይህ መሻሻልና ለውጥ አስፈላጊና ለሁላችንም ህልውና ግዴታ ነው።

አንድ ምሳሌ ልስጥ፦ በዛሬ በአማራ ክልል ያለው ንቅናቄ ምክንያት ኢህአዴግ ኦሮምኛን የአዲስ አባባ ቋንቋ አደርጋለሁ ብሎ ጭምጭምታ እያሰማ ነው። ይህ የተለመደው የኢህአዴግ ዘፈን አማራንና ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚሉትን የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን «ኦሮሞ ሊገዛችሁ ነው» በማለት ለማስፈራራት ነው! ህዝቡ ግን ይህ ማስፈራሪያ አሁን አይሰራም፤ ኦሮምኛን ጭራሽ የኢትዮጵያ ሁለተኛ ብሔራዊ ቋንቋ አድርጉት እያለ ነው። ኢህአዴግ ምን ይበጀው ይሆን!

ይህ ምናልባት ህልም ሊሆን ይችላል፤ ነገር ግን ይህ ህልም በተግባር እንዲውል የኢትዮጵያ ብሄርተኛ ነን የምንለው ወገን ታላቅ ሃላፊነት አለብን። የኛ የፖለቲካ ጎራ በመጀመሪያ እርስ በርሳችን አንድ ሆነን ሽኩቻን አስወግደን ጠንካራ ሆነን ከዛም በዚህ ጉዳይ ላይ መስራት አለበን፤ ከኦሮሞ ፖለቲካ ወገን ጋር በደምብ ስምምነት ላይ ባስቸኳይ መድረስ አለብን። እንደ ግብጽ አገር በመጨረሻ ደቂቃ እንስማማ ማለት ውድቀትን መጋበዝ ይሆናልና።



Monday 5 September 2016

የጎሳ ብሄርተኝነትን እንዴት እንቀንስ?

2008/13/1 ዓ.ም. (2016/9/5)

በመጀመርያ እኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ስለ ጎሳ ብሄርተኝነትና የጎሳ ስሜት ወይም የማንነት (ethnic identity) ስሜት በደምብ መረዳት አለብን። የጎሳ ስሜት የተፈጥሮ ጉዳይ እንዶሆነ ማመን አለብን። የሰው ልጅ ቤተሰቡን እንደሚወድ፤ መንደሩን እንደሚወድ፤ ጎሳውን ይወዳል። አንዳንዱ ጎሳውና ሀገሩ አንድ ስለሆነ ለጎሳውና ለሀገሩ ያለው ሲሜት አንድ ነው። አንዳንዱ ደግሞ ከብዙ ጎሳ ያለበት ሀገር ስለሚኖር ጎሳውና ሀገሩን ለይቶ ለሁለቱ የተለያየ ስሜት ይኖረዋል።

የጎሳ ስሜት ተፈጥሮ እንደመሆኑ ለመረዳት አይናችንን ከኢትዮጵያ ዞር አድርገን ዓለም ዙርያ ያሉትን ሀገሮችን እንመልከት። በታዳጊም በበለጸጉም፤ በምዕራባዊም በሌላውም፤ በአዲሱም በጥንታዊውም ሀገሮች የጎሳ ስሜት ሲንጸባረቅ እናያለን። ታሪካዊ ውይም ወቅታዊ ብሶቶች ቢኖርም ባይኖርም፤ የኤኮኖሚ ጥቅም ጉዳይ ቢኖርም ባይኖርም፤ ወዘተ የጎሳና የማንነት ስሜት አለ። ከዚህ ትንታኔ በዓለም ዙሪያ ያሉትን ምሳሌዎች አልደረድርም። ግን ይህ የጎሳ ጉዳይ ዓለም ዙሪያ መገኘቱ የሰው ልጅና ማኅበራዊ ውነታ እንደሆነ ያሳያል።

ታድያ ተፈጥሮ ከሆነ ምንድንነው የጎሳ ወይም የማንነት ስሜት ችግር።? ችግሩ የሚመጣው አንድ ሰው ጎሳውን ከሀገሩ (ወይም ከመላው የሀገሩ ህዝብ) ይበልጥ ሲወድና ሲያስቀድም ነው። በመጀመሪያ ትግራይ ነኝ ቅጥሎ ኢትዮጵያዊ» አይነቱ አባባል።) ይህ ሰው ከጎሳውን መውደድና በጎሳው መኩራት አልፎ ወደ የጎሳ ብሄርተኝነት (ethnic nationalism) ተሻግሯል ማለት ነው። እንደዚህ አይነቱ አስተሳሰብ ችግር እንደሆነ ለማስረዳት አንድ ምሳሌ ልስጥ፡ «የጎሳዬ ቋንቋ የአካባቢዬ የአስተዳደር፤ ትምህርት፤ ፖሊቲካ፤ ወዘተ ቋንቋ ይሁን» የሚለውን አቋም እንመልከተው። ጎሳው በአካባቢው የህዝብ ቁጥር በጣም አባዛኛ ከሆነ አቋሙ ትክክል ነው ማለት ይቻላል። ጥቂት ሰው ነው አለፍላጎቱ ይህን ቋንቋ መማር የሚኖርበት። ህዝቡ ባብዛኛው ተጠቃሚ ስለሚሆን ሀገርን የሚጎዳ አቋም አይደለም። በአንጻራዊው ደግሞ ይህ ጎሳ ከአካባቢው እጅግ አናሳ ነው እነበል። ይህ ማለት ለጥቂት ሰው ፍላጎት ተብሎ በርካታ ህዝብ በሌላው ቋንቋ በግድ ሊስተዳደር ነው። የዚህ ጎሳ ሕብረተሰብ «ምንም ይሁን ማንም ይጎዳ የኛ የጎሳ ፍላጎት ነው መቅደም ያለበት» የሚል ከሆነ ጎሳውን ከሀገሩ አስቀድመዋል። የጎሳ ብሄርተኝነት ማለት ይሄ ነው።

እንደዚህም ሆኖ የጎሳ ብሄርተኝነትን ስንቃወም መጠንቀቅ አለብን። በመጀመሪያ የጎሳ ብሄርተኛ የሆኑት ፖለቲከኞች የነሱን አቋም የሚቃዎሙትን እንደ ፖለቲካ መሳርያ በቀላሉ መጠቀም ይችላሉ። የጎሳ ብሄተኝነት ብዙ ግዜ ሆድ የባሰው ስልሆነ «የኛን አቋም የሚቃዎሙት የጎሳችን ጠላቶች ናቸው፤ መብቶቻችንንም እንዲከበር የማይፈልጉ ናቸው» ብለው በማናፈስ በቀላሉ የተከታዮቻቸውን ቁትር ይጭምራሉ። በሁልተኛ ደረጃ የጎሳ ብሄርተኛን አቋም መቀየር ከባድ ነው። ከጎሳ ብሄርተኝነት የተቀየሩ ሰዎች ጥቂትና በጣም የሚደነቁ ናቸው። እነሱም የተቀየሩት በክርክርና ብሙግት ሳይሆን ትህትና፤ ንፁህ ልብና ለዘብተኛ አቋም ያላቸው ሰዎች ስላጋጠሟቸውና እንደነዚህ አይነት ሰዎች እንደ ወንድሞቻቸው ማየት የህሊና ግዴታ ስለሆነባቸው ነው።

የጎሳ ብሄርተኝነትና ጎሳን ከሀገር ማስቀደም ምን ችግር አለው የሚሉ አሉ። የጎሳ ብሄርተኝነት ለሀገር ህዝብ ያለውን ጉዳት ባጭሩ ለማስረዳት ስለኢትዮጵያ ትንታኔ የሚሰጡ ምሁር ክሪስቶፈር ካላፓም አንድ ግዜ የጻፉትን ገላች አባባል ልጥቀስ፡ «በአንድ ሀገር የሚያራርቁና የሚያለያዩ ኃይሎች ከሚያገናኙና የሚያዋህዱ ኃይሎች ካየሉ ለሀገር ህልውና አስጊ ይሆናል» (ትርጉሙ የኔ ነው)። እያንዳንዱ ጎሳ በጎሳ ብሄርተኝነት ላይ ካቶከረ ሀገሩ ሀገር መሆኑን ቀርቶ የቅራኔ፤ ሹክሹክታና ጦርነት ስፍራ ይሆናል። ሁሉም ለራሱ ብቻ ስለሚያስብና ስለሚታገል። ለዚህ ነው የጎሳ ብሄርተኝነት ሀገርን እጅግ የሚጎዳው።

የዛረው የኢትዮጵያን ሕገ መንግሥትን የመሰረተውና ላለፉት 25 ዓመታት ሀገሪቱን የመራው ኢህአዴግ ይህ የጎሳ ብሄርተኝነትን ጉዳት አልገባውም። ለነገሩ አባዛኛው የኢህአዴግ አባላት የጎሳ ብሄርተኞች ስለነበሩ አይፈረድባቸውም። (በሌላ ጽሁፍ እንደተቀስኩት የኢትዮጵያ ብሄርትኛ ነኝ የሚለው እርስ በርሱ ተፋጅቶ 1983 .. ሲደርስ የፖለቲካ ሜዳው በጎሳ ብሄርተኞች ብቻ ቁጥጥር ስር ወድቆ ነበር። ጥፋቱም መፍትሄውም ከእኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች እንደሆነ አንርሳ ለማለት ነው።) «የጎሳ መብት» ብለው የሰየሙት ሃሳብ በተግባር ላይ ሲውል ሁሉ ጎሳዎች የሀገር ባለቤትነት ስለሚሰማቸው የሀገር ፍቅር ያድርባቸዋል ብለው ሰበኩ። ነገር ግን ሕገ መንግስቱም አስተዳደሩም የመንግስት መፈክሮችም ይጎሳ ብሄርተኝነት እንዲጥነክርና እንዲያከር ነው ያበረታታው! የመንግስት ድርጊቶች በሙሉ የህዝብ መለያየቱ፤ የጎሳ ውድድርና ቅራኔዎች እንዲሰፉ ነው ያደረገው። የዚህ አካሄድ ውጤት እጅግ ጎጂ መሆኑን ከኢህአዴግ ዓመራር ውስጥ ያሉም በርካታ አባላት ተገንዝበውትም መፍትሄ እየፈለጉለት ነው (ለስልጣናቸው አስጊ እንደሆነ ስለተረዱ)። ይህን ግንዛቤያቸውን የሚያሳየው ዓስር ዓመት በፊት የተጀመረው «ልማት» የሚለው መፈክር ነው። ይህ መፈክርና ቀጣይ መርህዎች የተፈጠሩበት አንድ ምክንያት የጎሳ ክፍፍል በአደገኛ ደረጃ እያየለ ስለሆነ ሀገሩን አንድ የሚያረግ ህብረ ጎሳዊ የሆነ መፈክር ያስፈልጋል ተብሎ ነው። ኤኮኖሚው ቢያድግም ልማትም ቢስፋፋም የጎሳ ብሄርተኝነቱ ጭራሽ እየሰፋ መሄዱ ለሁሉም ተመልካች ግልፅ ነውና ለዚህም ነው አንዳንድ ይኢህአዴግ ክፍሎችን ያሳሰባቸው።

የጎሳ ብሄርትኝነት በሀገራችን ምንም በዝቶ ቢሆንም መፍትሄ አለው። ዋናው መፍትሄ የሕዝባዊ «ውህደት» (integration) የሚያራምዱ መርህዎችን ማካሄድ ነው። ኢትዮጵያ እስካሁንም እንድ ሀገር ሆና ያለችው በታሪኳ የውህደት አጋጣሚዎች ነው። ጎሳዎችዋ በተለያየ መንገድ ስለተቀላቀሉ የተቀላቀለው ኃይል ሀገሪቱን አንድ አድረጎ ይዟታል። የሃማኖት፤ የመልክዓ ምድር፤ የግሳ (በፍልሰት)፤ ወዘታ ውህደቶች ናቸው ኢትዮጵያን አንድ ሀገር ያረጓትና እነዚህም ናቸው እስካሁን የጠበቋት።

ማንኛውም የመንግስት መርህ ከፖለቲካ እውነታ ጋር ካልተያያዘ አይሰራምም ጎጂም ይሆናል! ዛሬ እድሜ ለ25 ዓመታት በመንግሥት ደረጃ የጎሳ ብሄርተኝነትን መስፋፋት የኢትዮጵያ ጎሳዎች ከድሮ ይልቅ ተራርቀዋል። ለምሳሌ በኦሮሚያ ክልል የአማርኛ ትምህርት ባብዛኛው ስለማይሰጥ ብዙ ኦሮሞ ወጣቶች አማርኛ ሳይችሉ ትምህርት ቤት ይጨርሱና ከሌላ ክልል መማርም መስራትም ያቅታቸዋል። ይህ በገዛ ሀገራቸው መወሰናቸው ደግሞ ካላቸው ይበልጥ ጎሰኝነት እንዲሰማቸው ያደርጋል። የዚህ መፍትሄ ኦሮምኛን እንደ አማርኛ የኢትዮጵያ የሀገሩ ቋንቋ ማድረግ ነው። ከዚህም አልፎ ተርፎ ሌሎች ክልሎች፤ በተለይ የጎሳ ብሄርተኝነት ጠላት የሆነው የአማራ ክልል፤ በተቻለ ቁጥር በትምህርት ደረጃ ኦሮምኛ እንዲያቀርብና ተማሪዎቹ በደምብ አድርገው እንዲማሩት ማድረግ ነው። ይህ መርህ እርግት ወጪ ይኖረዋል ግን ጥቅሙ መለካት የማይቻል ነው። ኦሮምኛ በመስፋፋቱ የሚመጣው የስነ ልቦና ለውጥና በአማራና ኦሮምያ መካከል የፍልሰት ጭማሬ ሁለት የዚህ መርህ ውጤቶች ይሆናሉ። በዚህ አካሄድ የጎሳ ብሄርተኝነት እጅግ ይቀንሳል።

ከዚህ አያይዤ ማለት የምወደው በጎሳ ብሄርተኝነት የማይታማው ጎሳ አማራ ስለሆነ ይህን ጉዳይ ለመፍታት ከሌላው ጎሳ ይበልጥ ሀላፊነት አለበት። (ላለፉት 25-45 ዓመት ለመተኛቱም መካስ አለበት!) ስለዚህም በሀገር ደረጃ ኦሮምኛ ለማስፋፋት ሁኔታዎች ባይመቹም የአማራ ክልል ብቻውን በትምህርት ቤት ደረጃ የኦሮምኛ ትምህርት እንዲካሄድ እንደ ዋና እቅድ ማድረግ አለበት። ይህ ተግባር ለምላው ሀገሪቱ ታላቅ አስተዋሶ ይኖሮዋል።

ሶስት ሌሎች ውህደትን የሚጨምሩና የጎሳ ብሄርተኝነትን የሚገድቡ መርህዎች ጠቅሼ በሌላ ጽሁፍ አብራራቸዋለሁ። እነዚህ 1) በክልሎች መካከል ፍልሰት፤ 2) እንደ ትላልቅ ከተማዎች፤ አማራ ክልል፤ ወዘተ ውህደትና የሀገር ብሄርተኝነት የሚበዛባቸው ቦታውችን ኤኮኖሚ ማዳበር ሰውው ወደነዚህ ቦታዎች እንዲ ፈልስ፡ 3) የሀገሩን የሰው ቁጥር አከፋፈል (demography) ሚዛን እንዳይዛነፍ መጠንቀቅ። ለምሳሌ የሀገር ብሄርተኝነት የሚበዛባቸው ቦታዎች እንደ አዲስ አበባ በህዝብ አለመውለድ ምክንያት የህዝብ ቁጥሩ ከሌላው ዓንጻር እንዳይቀንስ መጠንቀቅ።

በመጭረሻ ማስረገት የመፈልገው ነጥብ ያለፈው የ25 ዓመት ኢሚዛናዊ የሆነ የኢህአዴግ የጎሳ ብሄርተኝነት አካሄድ በኢትዮጵያ በርካታ ጉዳት ቢያመጣም ማስተካከል ይቻላል። ሙሉ ሀላፊነቱ ግን የኛ የሀገር ብሄርተኞች ነው።