Monday 20 December 2021

Not Yet In a Position Of Strength...

 ያለፈው ዓመት ታሪካችን መረጃዎቻችን የሚገልጹልን ነገር ይህን ነው፤ የኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ ገና ደካማ ነው እጅግ በጣም መጎልበት አለበት። በሁሉም ዘርፍ፤ ደህንነት፤ መከላከያ፤ አስተዳደር፤ ንቃተ ህሊና፤ አንድነት፤ ትብብር፤ መተማመን፤ ወዘተ። 

እያንዳንዱ መዋቅር፤ እያንዳንዱ ግለሰብ መድረስ ካለበት ደረጀ በታች ነው። አልፎ ተርፎ በርካታ ከሃዲ fifth column ዎች አሉን በተለይ «በተማረው» ክፍል። ለዚህ ነው ትንሿ ህወሓት 100 ሚሊዮን በላይ ህዝብ ያላትን ሀገር ከባድ አደጋ ላይ የጣለችው። በድክመቶቻችን ምክንያት ነው።

ባለፈው አንድ ዓመት እጥፍ ድርብ እንደተሻሻልን አልዘነጋሁም። ሁላችንም ለውጡን አይተናል። ግን ጉዞው ገና መጀመሩ ነው። ረዥም ከባድ መንገድ ይቀረናል ጠንክረን ለኛም ለአካባቢአችንም ዘላቂ ሰላም ልናመጣ የምንችልበት ቁመና ላይ እስክንደርስ።

ስለዚህ የመንግስትም የህዝብም ዋና ትኩረትና ስራ ጠንካራ ለመሆን ስራ መስራት ላይ ነው። ሁሉም ሌሎች ጉዳዮች ከዚህ ዋና ግብ በታች መሆን አለባቸው። 

Thursday 16 December 2021

የሃላፊነት ፖለቲካ

የታወቀው የመካከለኛ ምስራቅ ታሪክ ምሁር በርናርድ ልዊስ  የአረብ ፖለቲካ ባህል ድክመትን ለመተቸት እንዲህ ብሎ ነበር፤

“When people realize things are going wrong, there are two questions they can ask......One is, ‘What did we do wrong?’ and the other is, ‘Who did this to us?’ The latter leads to conspiracy theories and paranoia. The first question leads to another line of thinking: ‘How do we put it right?’”

ትርጉም፤ «ህዝብ ነገሮች እየተበላሹ እንደሆነ ሲገነዘብ ሁለት አይነት ጥያቄዎችን መጠየቅ ይችላሉ፤ አንዱ «ምን ተሳስተን ነው?» ነው፤ ሌላው ጥያቄ «ማን ነው እንደዚህ ያደረገን ነው?» የመጨረሻው አይነት ጥያቄ ወደ ሴራ፤ ፍረሃትና ጥርጣሬ ይመራል። የመጀመርያው ጥያቄ ግን «እንዴት ነው ነገሮችን የምናስተካከለው» ወደሚለው ይመራል።

የዚህ አባባል ትርጉም ባጭሩ እንዲህ ነው፤ ችግርህን ሙሉበሙሉ የጠላቴ ጥፋት ነው ካልክ ለጠላት ያጋለጡህን የራስህን ድክመቶች አታምንም አታርምም። ጠላትን በቀጥታ በማጥፋት ላይ ብቻ ታተኩራለህ፤ ካቃተህ ተስፋ ትቆርጣለህ።

ምሳሌ፤ ህወሓት ስልጣን ከያዘ ጀምሮ ተቃዋሚዎች መደራጀት ሳይችሉ፤ ገንዘብና አቅም መሰብሰብ ሳይችሉ፤ ምንም አይነት የተደራጀ የህዝብ ድጋፍ መሰብሰብ ሳይችሉ እነዚህ መሰረታዊ የህልውና ችግራቸውን ከማረም ይልቅ ያላቸውን ጊዜና አቅም ህወሓትን በመኮነን ብቻ አባከኑ። በዚህ ምክንያት ተቃዋሚዎቹ ህወሓትን ሊጎዱት አልቻልም። መጨረሻ ላይ ህወሓት የፈረሰው በራሱ ያጠመደው የጎሳ ብሄረተኝነት አደጋ ነው። 

ዛሬም የኢትዮጵያዊነት የፖለቲካ ጎራ ተመሳሳይ ስህተት ላይ ይመስለኛል። ችግራችን ሁሉ የህወሓት ጥፋት ነው እያለ የራሱን ችግር እንኳን ለመፍታት ለማመንም ዝግጁ አይመስለኝም። ለምንድነው ህወሓት እንደዚህ ጠንክሮ የሚቀናቀነን? ለምንድነው መጀመሪያውኑ ህወሓት ሊገዛን የቻለው? ህወሓት ከየት ነው የመጣው? እነዚህ ጥያቄዎች ጥይቀን በትክክል ብንመልስ የራሳችንን ድክመቶች አይተን አርመን ህወሓትን በተሻለ ደረጃ መግጠም እንችላለን። ግን አላደረግነውም። በራሳችን ላይ ግምገማ አላደረግንም። ስህተቶቻችንን አላመንም። አላረምንም። በዚህ ምክንያት አላስፈላጊ ዋጋ እየከፈልን ነው።

መሆን የነበረበት እራሳችንን በዚህ መንገድ መገምገም ነበር፤ 1) ማርክሲስት ሆነን እርስ በርስ በመጣላታችንና ሀገሪቷን በማድከማችን እራሳችን ነን ህወሓትን የፈጠርነው ወይንም እንዲፈጠር ሜዳውን ያዘጋጀነው፤ 2) ሀውሓት ለረጅም ዓመታት የገዛን ምክንያት እኛ ቁጥራችን እጅግ አብላጫ ቢሆንም አብሮ መስራትና መደራጀት ስላቻልን ነው፤ 3) ዛሬም የህወሓትን ጦርነት በአጭሩ መጨረስ ያልቻልንበት ምክንያት አንድ ሆነን ተማምነን ተናበን መስራት ስላልቻልን ነው።

እራሳችንን በዚህ መንገድ ከገመገምን የችግሩ መፍትሄን አገኘን ማለት ነው። የፈረንጅ ጸረ ኢትዮጵያ የሆነ እንደ ማርክሲዝም አይነት ፖለቲካዊ አስተሳሰብ ጎጂ እንደሆነ ተረድተን ከዛ አይነት አስተሳሰቦች እራሳችንን እናርቃለን። መተባበርና አንድ መሆን የግድ እንደሆነ ተረድተን ጥርጣሬ፤ መጠላለፍ፤ ምቀኝነት፤ ትእቢት ወዘተን አስወግደን በአንድነት እንሰራለን። እርስ በርስ ያሉንን ትናንሽ ልዩነቶች እንቅፋት እንዳይሆኑን ለትክክለኛው ጊዜ ና መድረክ ትተናቸው በአንድነት እንሰራለን። ለህወሓት ጥቃት ያጋለጡንን መሰረታዊ ችግሮቻችንን አርመን እንገኛለን። ይህንን ካደረግን ጠላትን በቀላሉ እናስወግዳለን።

ከንቱ መከፋፈልን ቀንሰናል፤ አሁን እናጥፋው

ሁላችንም የምናውቀው የድሮ ከንቱ መከፋፈል ባህሪአችን እየቀነሰ እያየነው ነው። የከንቱ እርስ በርስ መጣላትና መከፋፈል ባህሪአችን አደጋ ላይ እንደጣለን እና ከምድር እንድንጠፋ ጫፍ እንዳደረሰን እየገባን ነው። ህወሓትም በዚህ ምክነያት አናሳና ትንሽ ሆኖ እንደገዛን ገብቶን እያመንን ነው። 

መቼስ የመንቃታችን አንዱ ምክነያት ያየነው አደጋና የጦርነት ውጤት ቢሆንም መንቃታችን ጥሩ ነው። ግን በፍጹም መዘናጋት የለብንም። የከንቱ መከፋፈል ባህሪአችን ከውስጣችን ጨርሶ እስኪጠፋ ተግተን መታገል አለብን። አማራጭ እንደሌለን ከልባችን ማመን አለብን። 

አንዱ ማድረግ ያለብን ነገር አንድነትን ዋና መግባር ማድረግ ነው። ከእውነት፤ ጽናት፤ ታማኝነት ወዘተ እኩል የሆነ መግባር መሆን አለበት። ትቢትና አውቃለሁ ባይነትን ነውር ማድረግ። ውሳኔዎችን በጋራ አድርጎ በጋራ መቀበልን ዋና መግባር ማድረግ። የክፍፍልንና እርስ በርስ መጣላትን፤ የጋራ ውሳኔን አለማክበርን ነውር ማድረግ። የህልውና ጉዳይ ነው።

Tuesday 14 December 2021

Brief Note: Ethiopian Elites and the West

Ethiopia should pursue a rational and credible foreign policy. It should rationally, not emotionally and out of revenge, re-assess its relationship with the West and engage in cooperation where interests align. But it should also credibly punish the West for what it has done. At the same time, Ethiopia should reward allies such as China who stood by it while it was under attack. Ethiopia should completely re-assess its long term geostrategic policy in light of the West's attack on it and in light of current geopolitical realities.

One of the problems Ethiopia will have as it engages in revising its foreign policy is the ideological and emotional attachment of much of its elite with the West. Before and after the Cold War, the West used its soft power, including propaganda, to capture the hearts of elites all around the world. Ethiopia was no exception. The basics of the propaganda was that the West is moral and altruistic - exceptional. It wants the best for all the world. Shocking that we believed such obviously simplistic propaganda, but we did. We developed a dangerous, irrational, emotional attachment to the West.

For the sake of peace and survival, our elite has to rid itself of this emotional irrational perception of the West. All our silly assumptions should be swept away.

Thankfully, today, most of Ethiopia has realised that the West is not any more altruistic or moral than any place else. It can be cruel and nonsensical. Its ideological Messianic complex (neocolonial impulse) can make it extremely dangerous. This realisation has to set firm roots in our psyche. For the sake of our survival and peace in our region, we should never again be so naïve.

Monday 13 December 2021

Brief Note on Ethiopia and the West: Realism and Credibility

Over the last year or so, we have all seen the West - USA, EU, and some allies - engage openly in unrelenting hybrid warfare against Ethiopia via their proxy, the TPLF rebels. They have made no attempts to hide their intentions, no attempts to equivocate or pretend to be balanced. It has been all out war. If the Ethiopian government wins the war, and it certainly looks that way today, how should Ethiopia manage its relationship with the West.

In my opinion, Ethiopia has to follow the standard geopolitical path of realism. Realism would dictate that Ethiopia has to realistically assess its interests and those of the West, and engage work together with the West where the interests coincide. Just as, for example, Russia or China work closely with the West on many matters. Ethiopia should not, out of emotion and the need for revenge, fail to rationally assess its relationship with the West.

On the other hand, and this, I think, is crucial, Ethiopia has to adhere to the other standard tenet of geopolitics, and that is credibility. The Ethiopian government must favour and reward those allies who stood by Ethiopia in its fight against the TPLF and the West, and it must punish the West for its actions. The details of how this is done are of course to be studied and will evolve, but Ethiopia has to be seen to be able to reciprocate credibly, and to follow through on its rhetoric credibly. 

Monday 20 September 2021

ምእራቡ ለምን ኢትዮጵያን ኢትዮጵያዊያንን ትንቃለች

የምእራቡ/ አሜሪካ ለኢትዮጵያ ያላቸው አቋም እንደዚህ ፅንፍ የያዛ የሆነው አንዱ መክነያት ለኢትዮጵያ በተለይም ለኢትዮጵያዊነት የፖለቲካ ጎራው ያለቸው መጠን የለሽ ንቀት ነው። ኢትዮጵያ/ ኢትዮጵያዊነት ምንም አቅም የለውም፣ በጣታችን ገፋ ካርግነው ይፈራርሳል የሚል ድምዳሜ ላይ ከደረሱ ቆይተዋል። ይህ ድምዳሜ ላይ የደረሱበት ምክነያቶቹ ባጭሩ ይህን ይመስላሉ፤ 

1. በ1983 የደርግ ጦር ባንዴ መቅለጡ፣ 
2. ህዝቡ ህወሓትን ከሞላ ጎደል በበቂ ሁኔታ አለማታገሉ፣
3. የኢትዮጵያዊነት ጎራው ፖለቲከኖች እርስ በርስ ሲፋጁ ለ30+ ዓመት አቅመ ቢስ ሆነው ሲቆዩ፣ 
4. 8%ን "የወከለው" ህወሓት ሀገሩን በቀላሉ ሲገዛ፣ 
5. የህወሓትና የሻብያ ዲያስፖራ የፖለቲካ ተሳትፎ የኛን በአስር እጥፍ በልጦ ሲገኝ። ለምሳሌ ሲጠየቁ ባንድ ቀን 20 ሚሊዮን ሲያዋጡ የኛ ዲያስፖራ ደግሞ በ27 ዓመት ጠቅላላ ሶስት ሚሊድንም ያላዋጣና ሳይደራጅ መቅረቱ፣
6. "በቅኝ ግዛት ያልወደቀችው ኢትዮጵያ" የስንዴና ስኮላርሺፕ ለማኝ ሆና ስትቀር፣
7. ዛሬም አንዳንድ ኢትዮጵያዊ ነን ባዮች መንግስትን ለማዳከም ይጥራሉ።

ምእራባውያን ይህን ሁሉ አይተው ነው ኢትዮጵያም (አማራውም) ደካማ አቅመ ቢስ ናቸው ብለው የደመደሙት።

በተጨማሪ የምእራቡ የኢትዮጵያ " አዋቂዎች" በኢትዮጵያ (ለነሱ አማራ) ባህል ጠንካራና አስፋሪ ቋንቋ ነው የሚሰራው ብለው በለብለብ ጥናቶቻቸው ደምድመዋል። ለዚህም ነው የአሜሪካ መንግስት መግለጫዎች ባልሰለጠነና ተራ ቋንቋ የተጻፉት።

መእራቡ ኢትዮጵያን እንደሚንቅ ማውቁ ምን ይጠቅመናል? እውነታንና የራስን ሰህተቶችን የላወቀ ስህተቶቹን ይደግማል፣ ችግር ውስጥ ይገባል፣ ሊጠፋም ይችላል። ከላ የተጠቀሱት የተናቅንበት ምክነያቶች ሁሉ እኛ ኢትዮጵያዊያን በራሳችን ላይ የመጣናቸው ችግሮች ናቸው። ከ1968-83 እርስ በርስ ሰንፋጀ እራሳችንን አጠፋንና በሩን ለጠላቶች ከፈትን። እና ህወሓትን ከተራ ሸፈታ ወደ ሀገር ገዥነት አጎለበትን። እኛ ነን ይህን የደረገ ነው፤ ባንከፋፈል ኖሮ የትም አይደርሱም ነበር። ወነኛው መማር ያለብ ትምሕርት ካሁን በሗላ የመከፋፈል ባህሪአችን መጥፋት አለበት። የህልውና ጉዳይ እንደሆነ መረዳት አለብን።

ሁለተኛ መማር ያለን ትምህርት ምን ያህል እራሳችን እንደጎዳንና ገና ጉድጓድ ውስጥ መሆናትን ነው። በጣም ብዙ የዓመታት ስራ እንዳለብን ማወቅ አለብን። ስራው ብዙ ስለሆነም ትእግስት እንደሚያስፈልግን አምነን መንግስትንም እራሳችንንም  መታገስ አለብን።

Wednesday 30 June 2021

የቶክስ ማቆም ውሳኔውና የጎሳ ብሔርተኝነት አደጋ

ስሜታዊና በፖለቲካ ያልበሰልን ስለሆንን የትግራይ ህዝብ ከህወሓት ጋር ወግኗል እንላለን። ይህ አመለካከት እጅግ simplistic ነው። በሕብረ ብሔሪዊ ሀገራት የህዝቡ ታማኝነት ከፊል ለሀገሩ ከፍል ለጎሳው/ብሔሩ ነው። ሀገሪቷ ጤናማ (ሰላማዊ) የምትሆነው የህዝቡ ታማኝነት ከጎሳው ይልቅ ወደ ሀገሩ ቢያደላ ነው። ለምን ሲባል የሀገርና የጎሳ ፍላጎትና ጥቅም አልፎ አልፎ ሊለያዩ ይችላሉ። ጎበዝ ፖለቲካኞች ካሉ እነዚህን ልዩነቶች የሳንሳሉና ወደ ሁሉንም የሚጠቅም መንገድ ያመራሉ። ምንም ቢጥሩ ግን አለመስማማት አይቀርም። ስለዚህ ህዝቡ ከጎሳው ይልቅ ሀገሩን የሚያስቀድም ከሆነ፤ ማለት የጎሳ ብሔርተኝነት ስሜት እናሳ ከሆነ፤ በጎሰና በሀገር ያሉት ልዩነቶች በቀላሉ ይፋታሉ። ካልሆነ ግን ሀገሪቷ የግጭት ስፍራ ትሆናለች።

አሁን በትግራይ የምናየው ይህ ነው። ለ57 አመት ለትገራይ ህዝብ የተሰበክለት የጎሳ ብሔርተኝነት ዋጋ እያስከፈለ ነው። ከ 57 አመት በፊት የትግራይ ህዝብ የጎሳ ብሔርተኝነት ስሜት አልነበረውም ማለት አይደለም። ግን ስሜቱ በየጊዜው እየጨመረ ሄደና አሁን ከመጠን በላይ ትግራዊ ጎሳውን ከሀገሩ በደምብ የስቀድማል።

የጎስንነት ስሜት ተቀያያሪ ነው። 69 ዓመት በፊት ኤርትራዊያን ከኢትዮጵያ ጋር እንቀላቀል አሉ። 41 ዓመት በሗላ ከ90% በላይ እንገንጠል አሉ! ፖለቲካ፤ ኤኮኖሚ፤ ግጭት ወዘተ የሰውን ስሜት ይቀይራል። የጎስኝነት ስሜቹን መመለሱ ቀላል አይደለም። ብዙ ጊዜ አይቻልም። 

ሰባት ወር በፊት መንግስት አብዛኛው የትግራይ ህዝብ ልብ የት እንደሆነ መገመት ብቻ ነበር የሚችለው። የጎሳ ብሔርተኝነት ስሜቱ ምን ደረጃ ላይ ነው? ሰላም፤ ፍትህና የኤኮኖሚ እርዳታ ከሰጠነው የሀገሩ ስሜት ከጎሰኝነቱ እንዲያይል ማድረግ ይቻላል ወይ? መሞከሩ ነው የሚያዋጣው ብሎ ወስነ መንግስት። ሞክረና አልቻለም። ወደ ሁለተኛው አማራጭ ዞረ። ብዙ ሰዎች፣ ቤተሰቦች፣ መንዶሮች ዋጋ ይከፈላሉ ልክ እንደ የኤርትራ መገንጠል።

በዚህ ምክንያት በሕብረ ብሔራዊ ሀገራት የጎሳ ብሔርተኝነት እንዳይበዛ መንግስት ሁልጊዜ መጠንቀቅ አለበት። ያለውን የገንዘብ፣ የፖሊሲ፣ የኃይል አቅም በሙሉ ተጠቅም የጎሳ ስሜትና ፍላጎት እንዲከበርና ሀገራዊነት እዲያይል መደረግ አለበት።