Tuesday 25 October 2022

የኩርፍያ ፖለቲካ

«እነ ስብሐት ነጋ ከተፈቱ ጀምሮ የአዲስ አበባ ህዝብ በዐቢይ ላይ አክሩፏል። ሮንድ ማድረርም አቆመ» ተባልኩኝ።

ይህ የፖለቲካችንን መሰረታዊ ችግር ያሚገልጽ አባባል ነው። ህዝቡ ማድረግ የነበረበት፤

1. ተቃውሞውን በሚገባው መግለጽ መንግስት እንዲሰማ እና እንዲገባው

2. እንደዚህ አይነት ነገር እንዳይደገም የመንግስት ስራተኞች፤ ህዝብ ወኪሎች፤ መሪዎችን መወትወት

ይህን ከማድረግ ፋንታ ህዝቡ ምን አደረገ፤

1. መንግስትን በሚያዳክም መልኩ እና ጠላትን በሚያጎለብት መልኩ መንግስትን ተቸ!

2. አክሩፎ እንደ ህጻን እራሱን የሚጎዳ ድርጊቶች ፈጸመ፤ ለምሳሌ አካባቢውን መጠበቅ ተወ!

ለ45 ዓመት በላይ ፖለቲካ ያቃጠለው ህዝብ እንደዚህ የፖለቲካ ደንቆሮ ይሆናል። የመንግስትን እርምጃ ለመቃወም የራሱን ጥቅም ይጎዳል! አካባቢ መጠበቅ ሮንድ ማድረግ ህዝቡን እጅግ ጠቅሟል። ደህንነትን እና አብሮነትን ጨምሯል። ህዝቡ ለዚህ መስክሯል። ስለዚህ ለራሱ ጥቅም ብሎ እነዚህን ስራዎች መቀጠል ነበረበት። ይህ ሎጂካል ነው። ግን ይህን ከማድረግ መንግስትን አክሩፍያለው ብሎ እራሱን መጉዳት ጀመረ።

ህወሓት ይሁን ሌሎች በቀላል ወሬ በህዝባችን የሚጫወቱት ለዚህ ነው። አህያ የሚሉንም ለዚህ ነው። ፖለቲካ አይገባውም። የራሱን ጥቅም አያውቅም። በቀላሉ ከምነግስት ልናፋታው እንችላለን ነው እነ ህወሓት የሚያስቡት። እንሆ ለ27 ዓመት የገዛነው ደንቆሮ ስለሆነ ነው በይፋ የሚሉት።

ሀገራችን ሰላም እንዲኖራት ይህን ነገራችንን ማሻሻል አለብን። መንግስት እያንዳንዱን የፈለግኩት ነገርን ካላደረገ ይፍረስ የሚለውን የመሃይ አስተሳሰብ እንዲጠፋ ማድረግ አለብን። ቀላል ዘመቻ አይሆንም።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!