Friday 22 February 2019

የጅልነት ፖለቲካ

አክራሪ የኦሮሞ ብሄርተኝነት በተለያየ መንገድ ፍላጎታቸውን በአዲስ አበባ ህዝብ ላይ መጫን እንደሚፈልጉ ገልጸዋል። አቋም ከመውሰድ እና ከመናገር አልፎ በተግባር ስራቸውን ሰርተዋል። የአዲስ አበባ «ወጣቶችን» በጅምላ አስረዋል። አዲስ አበባን እናደራጅ ያሉትን አስረው አስፈራርተዋል። ከለገጣፎ አፈናቅለዋል። ወዘተ። እንዲህ በማድረግ አክራሪው ቡድን አቅታጫውን በግልጽ አስቀምቷል። የማስፈራራት ዘመቻውን ቀጥሏል።

ለነገሩ ይህ (ይቅርታ አድርጉልኝ) የጅልነት ፖለቲካ አካሄድ ነው። የሚበጃቸው የነበረው የአዲስ አበባ ህዝብን ሳያስቀይሙ ሳይነሳሱ ቀስ ብለው ውስጥ ለውስት ስራቸውን መስራት ነበር። ግን የጡንቻ አካሄድ መርጠው የአዲስ አበባ ህዝብን ያናድዳሉ እና ተነስቶ እንዲደራጀና መብቱን እንዲያስከበር ያደርጉታል።

ይህ ነው የጅልነት ፖለቲካ። ግን ምና ያመጣሉ ነው ይህን የሚያደርጉት! የአዲስ አበባ ህዝብ እና ጠቅላላ የኢትዮጵያ ብሄርተኛ ጎራው ምን ያመጣል ነው። ስለዚህ ማን ነው ጅሉ። እኛ ነን።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!