Tuesday 20 February 2018

ታሪክን አንድገም፤ ሀገርን እንገንባ

አሳፋሪና አገር አፍራሽ ታሪካችንን እንዳንደግም ነው ይህን ጽሁፍ የምጽፈው። ታሪክ እንደመዘገበው ከኢህአዴግ ውጭ ያለነው ምሁራን፤ ፖለቲከኞችና ብዙሃን በፖለቲካ ረገድ ቁም ነገር ለማድረግ እድል ባጋጠመን ቁጥር እልዳችንን አበላሽተናል። በተደጋጋሚ ጊዜ ለአገራችን የፖለቲካ መስተካከል ከኢህአዴግም ይበልጥ እንቅፋት ሆነን ተገኝተናል።  ይህን ደፍሬ መናገር የምችል ይመስለኛል።

አንዱ የድክመታችን ምክንያት ተልዕኮአችንን አለማወቃችን ወይም መርሳታችን ነው። ተልዕኮአችን የአገር ፖለቲካ ግንባታ ነው እንጂ የፖለቲካ ውድድር አይደለም። የአገር ፖለቲካ ስርዓት ግንባታ ሲባል ሁላችንም ስለ ህገ መንግስትን ማርቀቅ ነው የምናስበው። ግን ከዚህ ህገ መንግስት ማርቀቅ ስራ በፊት  የልብ ለልብ መተዋወቅ፤ በተወሰነ ደረጃ መተማመን፤ መግባባትና መስማማት ያስፈልጋል። እነዚህ ለአገር ግንባታ የፖለቲካ ድርድር ቀድሞ ሁኔታዎች ናቸውና። አለነዚህ ማንኛውም በወረቀት ያለ ህግ፤ ምንም አይነት ወርቅ የሆነ ህግ ቢሆነም፤ በስራ ሊተገበር አይችልም

ቀጥሎ በነዚህ ተመስርቶ ህገ መንግስትና ሌሎች የርዓይና የህግ ሰነዶች ይደነገጋሉ። ቅራኔ ወይም አለመግባባት ካለ በህግ መሰረት ይፈታል ህጉ ደግሞ በቂ ካልሆነ ያለው መተማንና ስምምነት ለፍትህ ይረዳል። የአገር የፖለቲካ ግንባታ ሂደት እንደዚህ ነው መሆን ያለበት።

የፖለቲካ ውድድር ደግሞ የሚጀምረው የፖለቲካ ስረዓቱ ከተዋቀረ በኋላ የሚመጣው የፖለቲከኞችና ሌሎች ለመሪነት እርስ በርስ በህጉ መሰረት መወዳደር ነው። በምእራብ «ዴሞክራሲዎች» እንደዚህ አይነቱ ውድድር በርካታ ክርክር፤ ክስ፤ ዘለፋም ወዘተ ያካትታል። የህጉን ገደብ ዳር ዳር እየነኩ ግን ሳያልፉ እነዚህን አይንቶች ባህሪዎችን ያንጸባርቃሉ። ይህ ስልጣን ለመያዝ ሊበጃቸው ይችላል ግን ምንም አይገነባም። እርግጥ መተማመንንና ውይይትን ይጎዳል ግን ከምርጫው በኋላ የደረሰውን ጉዳት ይጠግኑና የአገር ማስተዳደር ስረአቸውን ይጀምራሉ። ይህ ነው በተለምደው የምናውቀው የፖለቲካ ውድድር።

የፖለቲካ ውድድር ደግሞ የፖለቲካ ስርዓቱ ከተዋቀረ በኋላ የሚከተለው የፖለቲከኞችና ሌሎች ለመሪነት እርስ በርስ በህጉ መሰረት መወዳደር ነው። በምእራብ «ዴሞክራሲዎች» እንደዚህ አይነቱ ውድድር በርካታ ክርክር፤ ክስ፤ ዘለፋ ወዘተ ያካትታል። የህጉን ገደብ ዳር ዳር እየነኩ ግን ሳያልፉ እነዚህን አይንቶች ባህሪዎችን እያንጸባርቁ ይወዳደራሉ። ይህ ስልጣን ለመያዝ ሊበጃቸው ይችል ይሆናል ግን አገርን አይገነባም ይጎዳልም። ሰልዚህም ነው ውድድሩ ምርጫው ካለፈ አሸናፊዎቹ ውድድሩ ያደረሰውን ንዴት፤ ቂምና ጉዳት ይጠግን ዘንድ ትሸናፊዎቹንም መላው የአገሪቷን ህዝብ አንድ የሚያረግ እርቃዊ ንግግርና ተግባር የሚአደርጉት። ይህ ነው በተለምዶ የምናውቀው የፖለቲካ ውድድር።

ስለዚህ አገርን መገንባትና የፖለቲካ ውድድር የተለያዩ ባህሪያት፤ ተግባራትና ልምድ ያስፈልጋቸዋል። የአገር ግንባታ ሂደት እንደ መተማመን፤ ስምምነት፤ አንድነት፤ መግባባት፤ ህብረት፤ ቅራኔን መፍታት፤ ውይይት ወዘተ አይነቱ ባህሪያትና ልምዶች ያስፈልጉታል። የፖለቲካ ውድድር ግን ክርክር፤ ውድድር፤ ፉክክር፤ መካሰስ፤ ህግና ስረዓትን ዳር ዳሩን መጣስ፤ ወዘተ አይነቱን ልምዶች ያካትታል። በአገር ግንባታ ሂደት መካከል እነዚህን የፖለቲካ ውድድር ባህሪያትና ልምዶች ይዘን ከገባን አገርን መገንባት ሳይሆን ማፍረ ነው የምናደርገው።

ለዚህ ደግሞ በርካታ ታሪካዊ ምሳሌዎች አሉን። እስቲ ወደ 15 ዓመታት ወደ ኋላ ተመልሰን የ«ተቃዋሚ» ምሁራን፤ ጋዜጠኛና ፖለቲከኞች እያደረጉ፤ እየተናገሩ፤ እየጻፉ ምን እንደነበር እናስታውስ። ስራቸውን ባጭሩ ለመግለጽ «እርስ በርስ መበላላት» ማለት ይቻላል! ተቃዋሚዎች ኢህአዴግ ከሚተቹት ይበልጥ እርስ በርስ ነበር የሚፋጁት። ጋዜጣ ላይ ቁም ነገር ሳይሆን ስድብና የመንደር ወሬ ነበር የሰፈነው። ከሞላ ጎደል ስራቸው 90% አፍራሽ 10% ገምቢ ነበር። ስለዚህም ነው ተቃዋሚው ጎራ ምርጫ '97 በግንቦት ሆኖ እሰከ የካቲት አካባቢ የትብብር መዋቅሮች ያላደራጀው! ለዚህም ነው ከምርጫው በኋላ ተቃዋሚዎች በቀላሉ የተበታተኑት። በበፊቱ ዓመታት እዱሉ እያለን ቅስ ብለን በትብብር ጉዳይ ተወያይቶ ትብብርን ከመፈጸምና ጠንካራ መሰረት የሆነ መዋቅርን ከመገንበት እንደ ምርጫ ተዋዳዳሪዎች እየተሰዳደብን ዋልን። ችግር ሲመጣ ለመቋቋም አቅሙ አልነበረንም። እርስ በርስ ተፋጅተን አለቅን። የግንባታ ስራ ያልተሰራባቸው ቅንጅትና ህብረት በቀላሉ ፈረሱ። የፖለቲካ መዋቅር ግንባታንና የፖለቲካ ውድድርን መለየት ያልቻሉትም ከፖለቲካ ወጡ። የህዝብም ትዝብት አደረባቸው።

በርካታዎቻችን በምዕራብ የሚዲያ ዜና፤ ትምህርትና ፕሮፓጋንዳ ስላደግን የነዚህ አገራት ፖለቲካ ስናይ ፖለቲካ እንደዛ መሆን እንዳለበት ይመስለናል። የናየው ደግሞ የፖለቲካ ውድድራቸውን ነው። ክርክሩን፤ ዘለፋውን፤ ስድቡን፤ ሴራውን ወዘተ። እኛም እንደነሱ ማድረግ እንወዳለን መሰለኝ። ግን ኢትዮጵያ ያለችበት ቦት፤ ለረዥም ዓመታት ያለችበት ቦታ፤ ገና የአገር ፖለቲካ ግንባታ ላይ ናት። ብዙሃኑም ልሂቃኑም የፖለቲካ መደቦቻችን እስካሁን በእምነት የተመሰረተ አገራቷን ምን መምሰል አለበት የሚል ሰፊ ስምምነት ላይ አልደረስንም። አሁንም ያለው ዋና ስራችን የህ ነው። አዎን ህገ መንግስት አለን ግን ሰፊው ርአይና ስምምነት የለንም። ነገ ኢህአዴግ ከስልጣን ቢወርድም ይህ ስምምነቱ ስለሌለ ሁከትና አብዮት ይከተላል።

በዚህ ምክንያት ሁላችንም፤ ምሁራን፤ ብዙሃን፤ ፖለቲከኛ፤ የመንግስት ሰራተኛ፤ ወዘተ ትኩረታችን ወደ አገር ግንባታ መቀየር አለበት። ይህ ማለት ከታች የተጠቀሱትን ለአገር ግንባታ አስፈላጊ የሆኑትን ብሃሪያት፤ ተግባሮችና ልምዶች ከራሳችን ጋር መዋሃድና በዚህ አስተሳሰብ ወደ ፊት መራመድ።

ስምምነት፤ አንድነት፤ መግባባት፤ ህብረት፤ መተማመን፤ በስነ ስረዓት መነጋገር፤ ውይይት፤ ቅራኔን መፍታት።

የሚቀጥለው ጊዜ አንድ ሰውን ወይም ቡድንን መዝለፍ ወይም መስደብ ካሰኘን ቆመን እናስብ። የፖለቲካ ውድድር ውስጥ አይደለንም። እንደዚህ አይነቱ ባህሪያት ታሪካችን እንደሚያረጋግጠው ሁላችንንም ጠርጎ ገደል ውስጥ ያስገባል አገራችንን ያፈርሳል። በሰላም እየተከባበርን እየተማመንን ነው መወያየት ያለብን። ይህ የሁላችንንም ጥቅም ያስከብራልና። ይህንን ብቻ ተግባራዊ ካደረግን አለ ምንም ጥርጣሬ ታላቅ አገር እንገነባለን ጠላት የምንላቸውም ምንም ሊጎዱንም አይችሉም።

Monday 19 February 2018

የህወሓት ትግል

ለህወሓት እራሱን መቀየር እጅግ ከባድ ስራ ነው የሚሆንበት። እንደምናውቀው ህወሓት የተመሰረተው የጽንፈኝነት በሽታ የኢትዮጵያ ምሁራንንና ፖለቲከኞችን በከባድ በሚያጠቃበት ዘመን ነበረ። ከጽንፈኝነት አልፎ ተርፎ ባህልን እና ተውፊትን የሚንቅ የምሁራን ትውልድ ነበር። ይህ  ትውልድ ነው እነ ህወሓት፤ ሻዕቢያ፤ ኢህአፓ፤ መኢሶን፤ ደርግ ወዘተ የፈጠረው። በዚህ ዘመን የተፈጠረ እና ኮሙኒዝም/አብዮታዊ ዴሞክራሲ/ጎሰኝነት አይነቶችን ርዕዮተ ዓለም እንደ ጣዖት የሚያመልክ ድርጅት መሰረታዊ ተሃድሶ ለማድረግ ከባድ ነው። ይህን በማውቅ እስካሁን ላደረጉት ትንሽም ቢሆኑ የአስተሳሰብ ለውጦች ህወሓት ሊደነቅ ይገበዋል።

ሌሎቻችን ይህ አመሰራረት ለህወሓት ምን ያህል ማነቆ እንደሆነ በቂ የሚገባን አይመስለኝም። በተማሪ ንቅናቄ ዘመን በነ ዋለልኝ መኮነን አይነቱ ተማሪና ምሁራን አመለካከት የኢትዮጵያ መሪዎች ብቻ ሳይሆኑ ኢትዮጵያ ሀገሪቷ እራሷ ጥላቻና ስር ነቅል ለውጥ ይገባት ነበር። የኢትዮጵያ ታሪክና ትውፊት በሙሉ ክፉና የተጣመመ ነውና መደምሰስ አለበት ተብሎ ነበር የሚታሰበው። ሃይማኖትም አብሮ እንደ ጠላት ይታይ ነበር። ኢትዮጵያ እንዳለ ተጥሎ ሙዚቃ፤ ጭፈራና ሙዚየሞች ብቻ ቀርተው ሌላው ባህልና ትውፊት በሁሉም ዘርፍ መጣል አለበት ነበር የነበረው አስተሳሰቡ።

ሻዕቢያና ህወሓት መካከል ደግሞ ከዚህ ሁሉ «የማንነት ጥላቻ» አልፎ የ«አማራ» ትላቻን አቀፉ። ለምን ቢባል ርዕዮተ ዓለማቸው ሁልጊዜ በጠላትነት የሚሰየም ቡድን ስለሚያስፈልገው የአማራ የግዥ መደብ ጨቋኝ ነው ተብሎ የዚህ የ«ጠላትን» ሚና ለመጫወት ምቹ ስለነበር።

እዚህ ጋር ቆም ብለን አንድ ጥያቄ መመለስ አለብን። በዛን ዘመን ከኢትዮጲያ ምሁራንና ፖለቲከኞች መካከል እንደዚህ አይነት አስተሳሰብ የሰፈነው በዓለም ዙርያ የነበረው የግራ ጸንፍ አመለካከት ብቻ ተመስርቶ ነው? በፍፁም። ሃገር ውስጥ ያለው ሁኔታ ነው ታላቁን ሚና የተጫወተው። በዛን ወቅት የነበረው የፖለቲካ አመራር ብዙሃኑ የሚያስፈልገውን የፍትሕና የሰላም መግባሮች ስላላሟላ ነው። መልካም አስተዳደር ባለመኖሩ ብሶት ተከማችቶ ነው ምሁራኑም ፖለቲከኞችም ወደዛ ወደ ሀገር አጥፊ ርዕዮተ ዓለም የገቡት።

ይህ ዋና ነጥብ ነው። ጣቶቻችንን እነህወሓት ላይ ብቻ እንዳንጠቁም ያስታውሰናል። እራሳችንን በሃሰት ከችግሩ መንጭ ነጻ አድርገን እንዳናይ ይረዳናል። ለሀገራችን ህልውና እና ትክክሉን መፍትሄ ለማግኘት «የተማሪው ንቅናቄ እና ተከታዮቹ የተፈጠሩት በራሳችን ጥፋት ነው» ብለን ማመን አለብን። እነዚህ ነገሮች ከመሬት አልተነሱም። ሁላችንም ጥፋታችንን መቀበል አለብን። ፈራጅ መሆን የለብንም። እርግት መፀፀት ነው ያለብን። በዚህ አህነት አስተሳሰብ ብቻ ነው እውነተኛው ፍትሕ እና ሰላም የሚገኘው። ሌሎችን ዝምብሎ በመኮነን ሳይሆን ሌሎችን በመረዳት እና እንደወንድማማቾች አንዱ የሌላውን ችግርና አመጣጥ በማወቅ ነው መፍትሄ ማምጣት የሚቻለው።

በዚህ ረገድ የህወሓትን እና የሻዕቢያን ታሪክን ስንመለከት እነዚህ ድርጅቶች ከተመሰረቱ ጀምሮ በተለይ የደርግ የኢትዮጵያ መንግስት ጽንፈኝነታቸውን እና በኢትዮጵያ ያላቸውን ጥላቻ እንዲጨምርና እንዲንር ነው ያደረገው። የደርግ መንግስት የነህወሓትን ጥላቻና ብሶት ደመደመላቸው። በታሪክ በጎሳና በኢትዮጵያዊነት ያላቸውን ርዕዮተ ዓለማቸውን አረጋገጠላቸው። ከዛም ይባስ ሀገሪቷን አሳልፎ ሰጣቸው!

በ1950 አብዛኛው ኤርትራዊ ኢትዮጵያን ይወዱ ነበር ኢትዮጵያዊ ነን ይሉ ነበር። 40 ዓመት በኋላ ኢትዮጵያን ይጠሉ ነበር ኢትዮጵያዊም አይደለንም አሉ። እጅግ ያሳዝናል። የሀገራችን የፖለቲካ ችግር መጠኑን ምን ያህል እንደነበረ አሁንም እንደሆነ በደምብ ያሳየናል።

ህወሓት ስልጣን ከያዘ ጀምሮ የሚያምንበት እና እንደ የስልጣን ስልት የሚጠቀምበትን ጎሰኝነትን አራግቧል። በህግ ደረጃ ብቻ ሳይሆን በማሕበረሰቡ ፕሮፓጋንዳ በመንዛት። ህወሓት ለነባር ኢትዮጵያ ያለውን ጥላቻ በተግባር አሳይቷል። ለምሳሌ «ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ይድከም»፤ «ኢትዮጵያዊነት ይድከም» የህወሓት እና ደጋፊዎቹ መፈከር ነበሩ። ትንሽ ቢያሰቡበት ኖሮ ግን ይህ አቋማቸው ለሚወክሉት የትግራይ ህዝብ እጅግ ጎጂ እንደሆነ ይገነዘቡት ነበር! አብዛኛው ትግሬ ኦርቶዶክስ ነው። ትክክል ቢሆንም ባይሆንም የጽንፈኛ ሙስሊም አካሄድ ያሳስባቸዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ ደግሞ ጎሰኝነት ከሰፈነ በኢትዮጵያ ተጠቃሚ የሆኑት ትንናሽ ብሄሮች እንደ ትግሬና ጉራጌ ነው በመጀመርያ የሚጎዱት። እንደ ኦሮሚያ አይነቱ ትልቅ ብሄር ጎሰኝነትን ቢያራምድም የሚከተሉትን ጉዳቶችን በመጠኑም ቢሆን በግዙፍነቱ ምክንያት ሊቋቋማቸው ይችል ይሆናል። ትግራይ ግን የጎሰኝነትን እልቂት ልትቋቋም አትችልም። በነዚህ ምንክንያቶች የትግራይ ጥቅም የነበረው አሁንም የሆነው በጎሳ ያልተከፋፈለች አንድ ፈደራላዊ ኢትዮጵያ ነው። ግን ህወሓት ይህን እውነታ ትቶ የሚወክለውን ህዝብ የሚጎዳው አቋምን አራመደ።

ይህ የህወሓት ቅዠት (ወይም schizophrenia)በኃይለ ሥላሴ ዘመን የነበረው የኢትዮጵያ ፖለቲካ አለመስተካከል ምን ያህል ጉዳት እንዳመጣ ያሳየናል። የተለያዩ ጎራዎች ለመብትና ለጥቅማቸው ከመታገል ፋንታ በሚጎዳቸው እና ጥማቸውን በሚሽር መንገድ እንዲ ሄዱ አረገ! ህወሓት ለዚህ ሁሉ ዓመት ህዝቧን ለሚጠቅም አንድነት ከመቆም ፋንታ ህዝቧን ለሚጎዳ ጎሰኝነት ቆመች! ከጎሰኞች ጋር አብሮ አጨበጨበች። ምክር አልሰማ (https://www.youtube.com/watch?v=WaDzzD8uCYU&t=9s) አለች። አሁን ጉዳቱን እያየች እያለ እንዴት የ40 ዓመት እምነቷን ትቀየር?!

ከባድ ነው። ቅድም እንዳልኩት እስካሁን መግዛታቸውም አሁን ለውጥ ለማድረግ ማሰባቸውን ይደነቃል። ከተነከሩበት ርዕዮተ ዓለም መውጣት ከባድ ነው። ይህ ነው የህወሃት ትግል። የኛ ትግል ደግሞ አይዟችሁ እያልን ሳንፈርድባቸው እራሳችንን ደግሞ እያጠነከርን መሄድ ነው።

Friday 16 February 2018

ይሄ ነው ራዕይ!

በያንዳንዷን ጥቃቅን ነጥብ ባልጋራም አቶ አቢይ አህመድ በዛሬው ኢትዮጵያ እንደዚህ አይነት ወርቅ የሆነ አመለካከት፤ ሃሳብና እቅድ ማርቀቅ መቻላቸው እጅግ ያስደንቃል!

በተለይ ስለውህደት ለሰላምና ፍቅር አስፈላጊነት ያሉትን በደንብብ ያዳምጡ። በተለይ በተለይ ስለቋንቋ በውህደት ያለው ሚና!

የአብይ አህመድ ራዕይ!

ብራቮ!

ጨቋኝና ተጨቋኝ

እንደተረዳሁት ባለፈው ባወጣው መግለጫ ኦህዴድ የኢትዮጵያ መሰረታዊ የጭቆና ታሪክ የ«መደብ ጭቆና» ነበር እንጂ የ«ብሄር ጭቆና» አልነበረም ብሏል። ለዚህ አቋማቸው ኦህዴድን አደንቃለው አመሰግናለውም። ከረዥም ዓመታት የተሳሳተ እምነታቸው መቀየር ከባድ ነውና ጥንካሬና ህሊና ይጠይቃል። ዛሬ በሃገራችን ያለውን ከፍተኛና ኢ-ጤናማ የጎሳ ውጥረትንም ተገንዝበው የተሳሳተ ርእዮተ ዓለማቸውን ገምግመው ሃሳባቸውን ቀይረው ይህንን በይፋ ማውጣታቸው ትልቅ ነገር ነው። ደግሞ ከሌሎች አጋር ፓርቲዎቻቸው ቀድመው ይህን ማድረጋቸውም ሊደነቅላቸው ይገባል። እነ ለማ መገርሳ ለኢትዮጵያዊነት ታላቅ አስተዋጾ እያደረጉ ነው።

ሆኖም ይህ ዜና በሃገራችን መሰረታዊ የሆነ አሳዛኝ አስተሳሰብ አሁንም እንዳለ ይገልጻል? «ጨቋኝ» እና «ተጨቋኝ» እራሱ የተሳሳተ ቋንቋ ነው። ጽንሰ ሃሳብ የመጣው ከውሸትና ኢባህላዊ የሆነ የምእራባዊ የኮምዩኒስት አስተሳሰብ የመነጨ ነው። እስቲ አንድ እርምጃ ወደ ኋላ ተመልሰን ለምንድነው የሰው ታሪክ በ«ጨቋኝና ተጨቋኝ» የሚለው አስተሳሰብ መወሰን ያለበት? እንደዚህ አይነቱ አስተሳሰብ በሃሳብም ደረጃ በተግባርም ግጭት፤ ቅሬታ፤ ቂም፤ ጦርነት፤ ግድያ፤ አብዮት ወዘተ የሚያስገድድ ነው። አንድነት፤ ፍቅር፤ ይቅርታ፤ ትህትና፤ መስማማት ወዘተ የሚቃረን አስተሳሰብ ነው።

አልፎ ተርፎ ማን ግለሰብም ህብረተሰብም ፍፁም ንፁሃን ፍፁም ጥፋተኛ የሆነ የለም። እያንዳዳችን ጨቁነናል ተጭቁነናል፤ በድለናል ተበድለናል፤ ወደናል ተወደናል፤ ተስማምተናል ተጣልተናል፤ ተሳስተናል ስታታችንን አምነን ይቅርታ ጠይቀናል፤ ቂም ይዘናል ይቅርታን ተቀብለናል። በዚህ ዓለም እኔ ነኝ ንጹ ተጨቋኝ የሚል የራሱን ጥፋት ስለማይመለከት ወደ ከባድ ጥፋጡስት ይገባል ሰፊ በደልም ይፈጽማል።

በዚህ ጉዳይ ታላቅ የሩሲያ ደራሲ አለክሳንደር ሶልዠኒትሲን ያሉትን በደምብ ሊገባን ይገባል፤
ከእስርቤታችን አልጋ የሆነው የበሰበሰው ገለባ ላይ ጋደም ብዬ ነው ለመጀመርያ ከውስጤ የበጎ መንፈስ የተሰማኝ። ቀስ በቀስ መረዳት የጀመርኩት ይህ ነው፤ ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር በሀገሮች፤ መደቦች፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም መካከል አይደለም የሚያልፈው፤ ይህ መስመር የሚያልፈው በያንዳንዱ የሰው ልብ መኻል ነው። መስመሩ እድሜአችን በሙሉ ከውስጣችን ወደፊት ወደኋላ ይላል። በክፉ የተሞሉ ልቦችም ቢያንስ ቅንጣት ያህል ጥሩነት ይኖራል፤ ከሁሉም ጥሩ ከሚባለውም ልብ ከአንድ ጥጓ ትንሽ ክፉነት ይኖራል።
በየቦታው እየዞሩ ያሉ ክፉ ስራ የሚሰሩ ክፉ ሰዎች ቢኖሩና እነሱን ከኛ መለየትና ማጥፋት ብቻ ቢሆን ኖሮ እንዴት ቀላል ነበር? ግን ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር ከያንዳንዱ የሰው ልጅ ልብ መካከል ነው የሚያልፈውና ማን አለ ከራሱ ልብ ቁራጭ ቆርጦ ለማጥፋት ፈቃደኛ ይሆነ?
ሶልዘኒትሲን ኮምዩኒስት የነበሩ ወታደር የነበሩ ስታሊን ለዓመታት በሞት እስር ቤት (ጉላግ) ያሰራቸው ከሩሲያ ወደ ኦርቶዶክስ ሃይማኖታቸው የተመለሱ የሩሲያ ጀግና ነበሩ። ተጨቋኝ ነኝ ማለት የሚገባቸው ነበሩ። ለሃገረቸው ጦርነት ተዋግተው በማግስቱ የታሰሩ ናቸው። አለምንም ጥርጥር ተጨቋኝ ነኝ ማለት የሚገባቸው ነበር። ግን እስር ቤት የሌሎችን ሳይሆን የራሳቸውን ኃጢያት እንዲገለጽላቸው አደረገ! የሰው ልጅ እውነተኛ ባሕርይ እንዲረዱ አደረገ። የሰው ልጅ ችግርም እንዴት መቅረፍ እንደሚቻል ገባቸው። በጦርነት፤ በማስወገድ፤ በማባረር፤ በመወገን ሳይሆን በንስሃ፤ በመስማማት፤ በመከባበር፤ በመቻቻል ነው።

ይህ ሩሲያዊ ሶልዠኒትሲን የዘመኑን «ጭቋኝና ተጨቋኝ» አስተሳሰብን ትተው የእውነትን ባህላዊ የኢትዮጵያዊ አስተሳሰብ ነው የገለጹት። ሩሲያዊው ኦርቶዶክስ ባህላችንን ያስታውሱን። ለምንናውም የኢትዮጵያ ባህል፤ ማንኛውም ሃይማኖት፤ ይህ የ«ጨቋኝና ተጨቋኝ» ርእዮተ ዓለም በአድ ነው። በአድ ነው። ሚስኪኖቹ የጃንሆይ ተመሪዎች ወደ ሃገራችን ከምእራብ ሃገራት ያመጡት መርዝ ነው። መርዙን እናውጣው። ወደ እራሳችን እንመለስ።

Thursday 15 February 2018

ቤተ ክርስቲያን መቅደም አለባት!

ከትላንት ወድያ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ዙርያ ያልጠበቅናቸው መልካም አሳቢዎች እንደ ለማ መገርሳና አቢይ አህመድ ብቅ ማለት ጀመሩ። ትላንትና መንግስት ለረዥም ዓመታት የሚለመነውን ነገር አደረገ፤ ያለጥፋት የታሰሩትንና የተሰቃዩትን በርካታ እስረኞችን ፈታ። ዛሬ ደግሞ ጠቅላይ ሚኒስቴራችን ኃይለማርያም ደሳለኝ በፈቃደኝነታቸው ስልጣናቸውን ከቀቁ። መልካ ለውጦች ይታያሉ፤ እግዚአብሔር መጨረሻውን ያሳምርልን።

ግን ከፖለቲካው ቤተ ክርስቲያናችን መቅደም አልነበረበትም? (ይህን ስል እኔም እንደ አንድ ምእመናን እራሴን እየወቀስኩኝ ነው።) የኛ ለማ መገርሳዎች፤ በትህትና አለመፍረድ፤ በፍቅርና በምሳሌ፤ የሚናገሩት የት አሉ? እርግጥ አሉ፤ ግን በሌሎቻችን ተከበው ድምጻቸው በአግባቡ አይሰማም። እስረኞችንን መቼ ነው የምንፈታው? በርካታ እስረኞች አሉን፤ ፍቅር፤ ሃላፊነት፤ እርቅ፤ ትህትና፤ ሰላም። እነዚህንንሁሉ አስረን ቁጭ ብለናል። መቼ ነው የምንፈታቸው? ደግሞ መቼ ነው ሃላፊነት ወስደን እራሳችንን ህዝብ ፊት ዝቅ የምናደርገው። እንዲህ የሚያደርጉ አሉ ግን በኔ አይነቱ ተከበው አይታዩም። እንቅፋትም ሆነናቸዋል።

ቤተ ክርስቲያናችን እንደ አቡነ ጴጥሮስ መምራት መጀመር አለባት። በፖለቲካው መመራት ወይም መቀደም እፍረት ነው። አሁን ከቤተ ክርስቲያን እርቅ በፊት በሃገራችን ፖለቲካ እርቅ ቢመጣ ታላቅ እፍረት አይደለም? ከዛ በሗላ መጀመሪያውኑ ፖለቲካ ነው ያስቸገረን ብለን ልናሳብብ ነው? እነ ቅዱስ ጴጥሮስ በሮሜ ፖለቲካ እየተሰውዉ ደፍሮ ያላሉትን ልንል ነው?! ይህ ቢሆን እጅግ አሳሳዛኝ ነው።

ስለዚህ እንምራ! በሃገር ውስጥና በውጭ ያሉት ስይኖዶስ መካከል ፈጥነን እርቅ እናምጣ። ለኢትዮጵያ ህዝብ ምሳሌ እንሁን። ፈተናው ብዙ ነው። ገና እየበዛ ይሄዳል። ግን እግዚአብሔር ሁልጊዜ በሁሉም ቦታ ከኛ ጋር ነው። ይህን ካመንን ለፍቅር እንድፈር፤ አንፍራ!

Wednesday 7 February 2018

ሞኙ ህብረተሰብ

ከአባ ቲኾን (ሼቭኩኖቭ) መጸሃፍ Everyday Saints፤ «ሞኙ ህብረተሰብ»። ትርጓሜው የኔ አይደለም።
ሞኙ ህብረተሰብ

በአንድች ሰነፍና የተኛች ይቢዛንቲየም ከተማ: የጥሩውን እና የሽማግሌውን ጳጳስ ምክር ተቃውሞ እና ልመና ትንሽ እንኳን ሳይፈሩ የከተማው ሰዎች በሚሰሩት ግብረ ገብ መጣስና ህግ ማፍረስ ሀፍረተ ቢሶች ሆነዋል። እንደውም በጳጳሱ ላይ ሳቁበት በዕኩይ ስራቸውም ገፉት።

በመጨረሻም ሽማግሌው ጳጳስ ሞተ እና አዲስ ጳጳስ ተሾመላቸው። አዲሱ ተሿሚም የከተማው ሰዎች እስኪደነቁ እና እስኪያዝኑ ድረስ  ስርዓት የሌለው በቅንጦት የሚኖር ጉቦኛ ሆነ እና ደጉን እና ሟቹን ጳጳስ እንዲናፍቁ አደረጋቸው ።

በተደጋጋሚ የሚፈጽመውን ጉቦኝነት ማዋረድ ድብደባ እና ከሁሉበላይ ደግሞ ማመን ያቃታቸው ለከት የሌለው ረብሻ መቋቋም ባለመቻላቸው በአንድነት ሆነው ወደ እግዚአብሔር «ጌታ ሆይ እንደዚህ አይነት ጭራቅ ለምን ላክህብን?» በማለት ጮሁ።

እንዴት እንደሚጸለይም አያውቁም ሰለነበር ዝም ብለው ጮሁ። ከብዙ ጩኸት በኋላ ጌታ ለአንዱ የከተማው አባት ተገልጾ «ከእሱ የከፋ ለማግኘት ሞከርኩ ነገር ግን ለማግኘት አልቻልኩም» አለው።

Thursday 1 February 2018

ትህትና

አባ ቲኾን በጻፉት መጸሃፍ "Everyday Saints" አባ ቲኾን አንድ ታላቅና ጀግና መኖክሲት፤ በሶቪዬት መንግስት ደጋግመው የታሰሩ የሆኑ፤ ስለ ገዳም ኑሮ ሲጠይቋቸው እኚህ መኖክሲት እንደዚህ አልዋቸው፤ «ዋናውና መጀመርያው ነገር ይህ ነው፤ ማንንም ላይ አትፍረድ»

አለመፍረድ ማለት አለመኮነን ነው። ይህ መፍረድ ድርጊትን ወይም አቋምን ጥሩ ነው ወይ መትፎ ነው ማለት አይደለም። እንደዚህ አይነት ፍርድ ተገቢም አስፈላጊም ነው። አትፍረዱ ማለት አትኮንኑ፤ ሰውን ከድርጊቱ ጋር አታቆራኙ። ሰውየው እራሱ መጥፎ ነው፤ ሃጥያተኛ ነው፤ እኔ ከሱ እሻላለሁ፤ እሱ ወደ ገሃንም ይገባል አይነቱ ነው አትበሉ አታስቡ የምንባለው። ስለዚህ ለክርስቲያን በድርጊት መፍረድ ተገቢ ነው ግን በሰው ማንነት መፍረድ ትክክል አይደለም።

በሰው መፍረድ ኢክርስቲያናዊ የሆነው አንዱ ምክነያት መፍረድ ወደ ተዕቢት ስለሚመራ ነው። ተዕቢት ደግሞ የመጀመርያውና ዋናው እግዚአብሔርን ያጣንበት ምክንያት ነው። አዳምና ሄዋን በትዕቢታቸው ምክንያት መልአክት ለመሆን አስበው ነው እጸ በለሱን የበሉትና። ስለዝህ እንደ ክርስቲያን ከትእቢት ርቀን ወደ ተቃራኒው ትህትና ነው መጠጋት ያለብን።

አዎን ትህትና አንድ ክርስቲያን ከሚፈልገው ዋና ጥሩ ባህርይ ነው። «ትህትናና ፍርሃ እግዚአብሔር ከሁሉ መልክአ ምግባር በላይ ናቸው» ትብሏል። ትህትና የሰው ልጅን ዋና ተልኮ፤ ማለት ወደ እግዚአብሔር መቅረብ፤ ለማሟላት ግድ ነው። እራሱን እንዲገመግም፤ ከፈተናና ሴጣን እንዲርቅ፤ ሌሎችን ላይ ከመጠቆም እራሱን ላይ መጠቆም። እነዚህ በሙሉ ትህትና ይጠይቃሉ።

እንደዚህ ሆኖ ማንም ሰው፤ በተለይ መሪ፤ ትህትናን ሲያንጸባርቅ ደስ ይለኛል። እራሱን ወይም ወገኑን የማያሞገስ፤ እራሱን አጥፊና ሃላፊ የሚያደርግ፤ እራሱን ጥልቆ የሚገመግም፤ ሌሎችን በፍርድ ሳይሆን በመቆርቆር አይን የሚያይ ሰው ደስ ይለኛል። ይህ ባህሪዎች ለራሱም ለዙርያው ላሉትም እጅግ ይበጃል።

እኔ አቶ ለማ መገርሳን አላውቋቸውም ግን ያዳማጥኳቸው ንግግሮቻቸው በትህትና የተሞሉ በመሆናቸው ተደስጭያለው። በዚህ ረድፍ ለሁላችንም ታላቅ ምሳሌ መሆናቸው ነው ከሁሉም በላይ ያስደሰተኝ።

ከአቶ ለማ ሌሎችን በሰሞኑ አይቻለሁ። ብአዴን በደብረ ብርሃን የጠራው የምሁራን ስብሰባ ላይ አንድ ወጣት ምህሩን በጥህትና እጅግ እጅግ አስደሰተኝ። እኛ ምሁራን ባንኖር ገበሬው (ብዙሃኑ) በሰላም አብሮ ይኖር ነበርና እኛ ነን ችግሩ። ለችግሩ መፍትሄ እናገኝለታለን ከማለት መጀመርያ እራሳችንን እንፈትሽ ብሎ ታላቅና አስደናቂ ንግግር አቀረበ። እንደዚህ አይነቱ የምላስ ሳይሆን የመንፈስ ጀግና ነው ሁላችንም የሚያስፈልገን።

ሁላችንም በሌላ ላይ ከመጠቆም፤ ችግርሮቻችንን ብሌላ ከማሳበበ፤ መፍትሄም ከሌሎች ነው የሚመጣው ብለን ከምናሰብ፤ እራሳችንን ወድቅ (disempower) ከማድረግ፤ ውስጣችንን መርምረን ሌሎች ላይ ሳንፈርድ ብንራመድ ለሁላችንም መልካም እንሆን ነበር።

እግዚአብሔር ትህትና ይስጠን። ከትዕቢት ፈተና ያርቀን። የእርስበርስ ሰላም እንድሽ ይርዳን።

Short Memories!

Some of us seem surprised at comments by a certain political commentator, Muluwerq Kidanemariam, that given the current political atmosphere, Tigray Region might find it necessary to invoke article 39 of the constitution and exit Ethiopia. But given the history of the TPLF, such comments are nothing unusual and nothing to be alarmed about.

It seems that many have forgotten, or were too young to remember, the TPLF and EPRDF of the 1990's, particularly until the 2000 Ethio-Eritrean War. This was the peak of ethnic nationalism and anti-Ethiopian nationalist rhetoric in Ethiopia, sponsored and encouraged by the TPLF and EPRDF. TPLF supporters, arm in arm with their EPLF comrades, gleefully lorded it over us 'chauvinists'. It was de rigueur for EPRDF members and supporters to identify with their ethnicity first, and Ethiopia second, and reluctantly at that. Often us naïve and shell-shocked Ethiopian nationalists would during the course of a discussion ask a TPLF or OPDO/OLF supporter if they consider themselves Ethiopian, and the defiant answer would be that they are Tigrean or Oromo first, and then Ethiopian (maybe)!


EPRDF officials and supporters would often say that if by some improbable tragedy the TPLF/EPRDF would fall from power and the 'chauvinists' replace them, they would promptly exit Ethiopia. Their 'Ethiopianness' hung on a thread. This was the tone of Ethiopian politics during the 1990's, and this is merely what Ato Muluwerq has repeated in his interview. Nothing new!

During the Ethio-Eritrean war, things changed a little. The departure of EPLF officials and supporters from Ethiopian political circles resulted in a lowering of anti-Ethiopianism in Addis Ababa. In addition, the war effort required the EPRDF to mobilize a good degree of patriotism - Ethiopian patriotism - all around Ethiopia, even in Oromia, the region that the EPRDF claimed was most victimized by Ethiopian nationalism. The EPRDF were very pragmatic - they did what they needed to do to achieve their goal which was, via war, saving face over the EPLF. So pragmatic were they that they recruited former military officers of their arch-enemy Dergue into the Ethiopian military for the fight!

After the war, and leading up to the 2005 elections, the EPRDF began to shift from fervent anti-Ethiopian nationalism to a little more centrist position. Its anti-chauvinist rhetoric began to be accompanied by anti-'narrow nationalist' rhetoric. Eventually, driven by a more flexible Meles Zenawi, the EPRDF even tried the open 2005 elections, leaving itself vulnerable to the feared and hated chauvinist political forces. When the course of the elections did not go as planned, Meles reverted to form and raised the specter of anti-Tigrayan violence and even talked about genocide! Again, this is what we are seeing now - again, many TPLF supporters are interpreting the threat to the monopoly that the TPLF/EPRDF has on political power as an anti-Tigrayan pogrom!

After crushing the 2005 anti-government movement - with indispensable help from the opposition I might add - the ERPDF moved quickly to an agenda of political monopoly through economic growth - the China/East Asia 'developmental state' model. In the Ethiopian context, the EPRDF named this model 'lmatawi mengst'. The EPRDF figured that a focus on development would make the people forget about politics and, just as importantly, ethnicity. The developmental state was a bargain with the Ethiopian people - high economic growth in exchange for monopoly political power - and it was a great success for the EPRDF. Far more successful than it would have ever imagined. Any political opposition was squashed with impunity, but we, the masses, generally acquiesced, was we were to busy making money - or trying to.

During this time, the EPRDF continued moving slowly away from ethnic nationalism. The rhetoric about Tigrawi-first, Ethiopian-second became a distant memory. Instead, members and supporters of the EPRDF began to portray themselves as being 'more Ethiopian' than their opponents, including the 'chauvinists'! The term 'chauvinist' itself became passé in EPRDF circles, and was replaced by terrorists and anti-Ethiopians! What a change from the old days!

However, with time, the developmental state began to display its own problems. As elsewhere, for example China, the masses began to express intense dissatisfaction with the corruption of the ruling party and the resulting lack of civic and economic justice. This is a significant problem in and of itself. But in Ethiopia, it has been increased orders of magnitude because of ethnic nationalism. Because of ethnic nationalism, this dissatisfaction is expressed not just in civic terms, but ethnic terms, and as we all know, any conflict is greatly increased if ethnicity becomes a factor.

So now, the TPLF and its supporters see themselves faced with an existential crisis, and they don't seem to have anyone to help them figure out an innovative solution. So they retreat into old theories and clichés of their childhood, such as what Ato Muluwerq talks about in his interview.

This is not surprising, neither should it be alarming. But it is folly to expect the TPLF, a small partner in the EPRDF, to continue to manufacture solutions - good or bad - to Ethiopian political problems. Inevitably, they will reach a state of exhaustion - they might even be there now. Their never ending yearning for Meles, who had a way of assessing and finding a way out of problems, shows this. They should be relieved of this huge burden that we have saddled them with for decades. By 'we', I mean the general political opposition, especially those who consider ourselves Ethiopian nationalists. It is we who have failed the nation, and even though we have severely debilitated ourselves, we have no choice but to somehow grow up and do our fair share.

So let us not worry about the Ato Muluwerq's of this world. They are at their wits end, and for this I don't blame them. It us up to us to find a way out of this quagmire.