Sunday 21 April 2019

ገንቢ ውይይት ከአንዷለም አራጌ ጋር

ስዩም ተሾመ በጣም ጥሩ ቃለ ምልልሶች እያረገ ነው፤ አጠያየቁንም ወድጄዋለሁ። እንግዶቹን ከነ መልእክቶቻቸው ያከብራል። የተንዛዛ ንግግሮች እንዲያደርጉ አይፈቅድም ግን መልዕክቶቻቸውን በደምብ እንዲገልጹ ይገፋፋቸዋል። በበቂም ይሟገታቸዋል  የሚናገሩትን ለማጥራት ዘንድ።

ለማንኛውም አንድ ሁለት ነጥብ ከዚህ ውይይት... በመጀመርያ አንዱእዓለም ስለ «ሃላፊነት ፖለቲካ» (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/blog-post_30.html) አስረግጦ ተናገረ። የሀገራችን ፖለቲካዊ ይሁን ሌሎች ችግሮች በዋናኝነት የህወሓት ጥፋት ሳይሆኑ የያንዳንዶቻችን ጥፋት ናቸው። በድርጊታችን ወይንም በዝምታችን እያንዳንዶቻችን ጥፋተኛ ነን። (እኔ የምለው) አልፎ ተርፎ ህወሓትንም የወለድነው እኛው ነን (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/blog-post_21.html)። ይህን ሃላፊነት ካልወሰድን መቼም ልንድን አንችልም። ትክክለኛ መልዕክት ነው።

በሁለተኛ ደረጃ አንዱእዓለም ስለ ጎሳ ፖለቲካ ሲይወራ የጎሳ ፖለቲካ አግላይ እና ዘረኛ አድርጎ ያቀረበው መሰለኝ፡፡ እወንተ ነው፤ ብዙ ጊዜ እነኝህን ባህሪአት ይንፀባርቃል፡፡ ግን ተገቢ ጥያቄዋችም እናስሜቶች አሉት። እነዚህን ተገቢ ትያቄዎችን በመጀመርያ ካልተቀበልን መወያየት አይችልም። Don't reduce ethnic nationalism to 'racism' (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/08/blog-post_6.html)፡፡ 

<<የጎሳ አስተዳደር (ethnic federalism) ዋና ችግር የግጭት መንስኤ መሆኑ ነው፡፡ ለዚህም የ28 ዓመታት ማስረጃ አለን። የቋንቋ፤ ባህል፤ አካባቢ መስተዳደር (local autonomy) ፍላጎቶች ተገቢ ናቸው ግን ከጎሳ አስተዳደር ሌላ በሆነ አስተዳደር ነው በተገቢው እና ሰላማዊ መንገድ የሚመለሱት፡፡>> መልእክታችን ይህ መሆን ያለበት ይመስለኛል፡፡ እንጂ ዘረኝነት ነው በማለት ካተኮርን የሚጠቅም አይመስለኝም፡፡

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!