Friday 30 November 2018

የውጭ ሀገር ዜግነት ያለው ኢትዮጵያዊ ለፖለቲካ ስልጣን መወዳደር መቻል የለበትም


ከዚህ የኢሳት እለታዊ ውይይት የጥምር ዜግነት እና የውጭ ሀገር ዜግነት ያላቸው ኢትዮጵያዊ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ተሳታፊነት ጉዳይ ተነስቶ ነበር።

እኔ ከሲሳይ አጌና ሃሳብ ጋር እስማማለሁ። ጉዳዩ በመሰረቱ የሉዓላዊነት (sovereignty)፤ ተጠያቂነት (accountability) እና የባለ ድርሻ (stakeholder) ነው። አሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ የሆነ ሰው ለሁለቱም ሀገራት ተጠሪነት እና ተጠያቂነት አለው። የሁለቱንም ሀገራት ሉዓላዊነት የመጠበቅ ግዴታ አለበት። የሁለቱም ሀገራት ባለ ድርሻ ነው። ስለዚህ የሁለቱ ሀገራት ጥቅም፤ ሉዓላዊነት፤ «ፍላጎት»፤ የሚለያዩ ወይንም የሚቃረኑ ከሆነ ይህ አሜሪካዊ እና ኢትዮጵያዊ የሆነ ሰው ከራሳቸው ጋር ይጣላል። የየትኛውን ሀገር ሉዓላዊነት ይጠብቅ? አልፎ ተርፎ ይህ ሰው ከአሜሪካ ንብረት እና ቤተሰብ ካለው ይህን ከራስ መጣላቱን ያብሰዋል። ስለዚህ ነው የፖለቲካ መሪነት እና የመምረጥ መብት ሊኖረው አይገባም የሚባለው። አንድ ሰው የአንድ ሀገር ሉዓላዊነት ብቻ ነው (በዛሬው ዓለም) መጠበቅ የሚችለው።

ልሰ ተሳትፎ አወራን ግን የገንዘቡ ጉዳይስ? ማለትም የዲያስፖራ ኢትዮጵያዊዎች ነገ ለግንቦት ሰባት ወይንም ለኦፌኮ 10 ሚሊዮን ዶላር ሰብስበው ቢሰጡ በሀገር ሉዓላዊነት ምን ሚና ይጫወታል። በእርጥ ሉዓላዊነትን ይቀንሳል። በዚህ ምክንያት መከልከል አለበት። አብዛኞች ሀገራት የፖለቲካ ፓርቲዎች ከውጭ ሀገራት ገንዘብ ማግኘት አይችሉም የሚል ህገጋት አላቸው። ግን እንደሚታወቀው ገንዘብ፤ እንዳ ውሃ፤ መንገድ አያጣም። በሌላ ድርጅት ወይንም ንግድ ገብቶ ከዛ ያ ኢትዮጵያዊ ድርጅት ወይንም ንግድ ለፖለቲካ ፓርቲ ገንዘቡን ይለግሳል። ሆኖም መከልከሉ አሁንም አስፈላጊ ነው። ቢያንስ ግድብ ይሆናል። በፖለቲካችን ያለው የውጭ ሀገር ሚናን ይቀንሳል (minimize ያደርጋል)።

ጉዳዩን በአጭሩ እንዲህ ነው የማየው። እንደ ድሮ የዛሬውም ዓለም በሀገራት ታላቅ የአቅም ልዩነት አለ። የሀገራችንን ፖለቲካ ለውጭ ሀገር ገንዘብ እና ተሳትፎ ክፍት ካረግን በቀላሉ እንዋጣለን። የዜጎቻችን ጥቅም ከሚከበር ይልቅ የውጭ ሀገር ዜጎች፤ ድርጅቶች፤ ኩባኒያኦች እና መንግስቶች ጥቅም የሚከበርበት ፖለቲካ ይኖረናል። ሉዓላዊነታችንን አጣን ማለት ነው። ዜጎቻችን ሀገር አልባ ሆኑ ማለት ነው። ይህ እንዳይሆን በሚገባው ደረጃ አጥር እና ግድብ ማብጀት ግድ ነው።

Wednesday 21 November 2018

የትምሕርት ፍኖተ ካርታው እና ኢትዮጵያዊነት

ወደ ራሳችን የመመለስ ሂደታችን እየተጀመረ ነው። ይህን ቪዲዮ ተመልከቱ።

https://www.youtube.com/watch?v=ZxfDJ3eYcrk

አቶ ፋንታሁን የሚሉት ነገሮች ትክክል ናቸው። ሃዛቦቹን የሚገባችሁ ምሁራን ብትሳተፉ ጥሩ ይመስለኛል።

https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2017/11/the-ethiopian-intellectual-lost-and.html

Tuesday 20 November 2018

የደርግ ኢሰባዊ ድርጊቶች በአግባቡ ለህዝብ ቢገለጽ ኖሮ ታሪክ (ብሶ) እንዳይደገም ይረዳ ነበር...

በደርግ ዘመን የሚካሄዱት ኢሰባዊ ድርጊቶች እንደ ግድያ፤ እስር፤ ማሰቃየት ወዘተ ለኢትዮጵያ ህዝብ በበቂ ደረጃ በይፋ አልቀረበም። «የእርቅ እና ሰላም» እና የፍትህ ሂደት በታላቅ መድረክ ለህዝብ አልቀረበም። መቀረብ ነበረበት። ህዝቡ ከተጎጂዎች ታሪኮቸውን በደምብ መስማት ነበረበት። የጨቋኞችን የፍርድ ሂደት በደምብ መስማት ነበረበት። ይህ ሳይደረግ ቀርቶ ጉዳዩ ላይላዩን ብቻ ታይቶ ህዝቡ «የደርግ ባለስልጣኖች ታሰሩ ቀጥሎ ተፈረደባቸው» ተብሎ ጉዳዩ በዛው ተዘጋ። ለስነልቦና የሚያስፈልገው ግልጽ የሆነ የእርቅ፤ ሰላም እና ፍትህ ሂደት አልተካሄደም።

በዚህ ምክንያት ዛሬ ብዙ ሰው ስለ ደርግ፤ ነጭ ሽብር እና ቀይ ሽብር አያውቅም። የለማወቅ ብዛቱ ይገርማል፤ አዲሱ ትውልድ ብቻ ሳይሆን የደርግ ዘመነን የሚያውቁትም በአግባቡ ታሪኩን አያውቁትም። ይህ «ማህበራዊ መርሳት» አንዱ ምክንያት ይመስለኛል ኢህአዴግ የደርግን ጭቆና በባሰ ሁኔታ እንዲደግም እድል የተሰጠው።

ሰሞኑን ከአንድ ዘመዴ ጋር ስለ ቅርብ ቀናት የደህንነት፤ የፖሊስ እና የሌሎች «መርማሪዎች» እና ሥቃይ አዛዥ እና አስፈጻሚዎች መታሰር እየተወያየን ነበር። ይህ ዘመዴ በደርግ ጊዜ ታስሮ ነበር። በታሰረበት ጊዜ እሱ እና ሌሎች ላይ የደረሰባቸውን የእስር ስቃይ በትንሹ አካፈለኝ/አስታወሰኝ፤
1. ዘመዴ ብዙ ከተገረፉት አንዱ ቢሆንም የደረሰብኝ ከሌሎች ይሻላል ይላል፤ ቆሻሻ ካልሲ ከአፍ ውስጥ ወትፈው ነው ለሳምንታት የገረፉት።  
2. አሰቃዮች ሴቶችን በሲጋራ መለኮሻ ነበር «እንትናቸውን» የሚያቃጥሉት። 
3. ጥፍር መንቀል ወዘተ ተራ እና የተለመደ ነበር። 
4. አንድ የታወቀ ዘመዴ የሚያውቀው አሰቃይ ነበር። ለሊቱን በየ እስር ቤቱ እየዞረ አንዳንድ እስረኞችን መርጦ አውጥቶ በሚኪና ይወስዳቸዋል። ሜዳ ላይ ለቆ «ሩጡ» ብሎ ያዛቸው እና በካላሹ ተረከዛቸውን መሬት መሬቱን ይተኩስባቸውል። «ጨዋታው» ሲያልቅ ይገላቸዋል። ይህ አሰቃይ መጨረሻ ላይ ደርግ እራሱ አስሮት ወደ ዘመዴ ያለበት እስር ቤት ገባ። አዕምሮውን ክፉኛ ሳተ፤ ጨርቁን ጣለ።
እንደዚህ አይነት ታሪኮች ብዙ ናቸው ግን ህዝባችን በደምብ አልተነገረውም። አስቀየሚ ዝርዝሮቹ  በይፋ ይነገሩ አደለም የምለው። ላያስፈልጉ ይችላሉ። ግን ክስተቶቹ፤ ተጎጂው፤ ወንጀለኛው፤ ወዘተ በህዝብ መደረክ በሚገባው ደረጃ መቅረብ አለበት። አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ይህን አሳፋሪ ታሪካችንን ማወቅ አለበት።

ለምን የደርግ ጭካኔ ታሪክ በደምብ አይልተነገረም? እንደሚመስለኝ ኢህአዴግ እራሱ ለሰው ልጅ የሚሰጠው ዋጋ ትንሽ ስለሆነ ነው። እራሱ እንደ ደርግ ህዝብን እንደሚረግጥ ስለሚያውቅ ይመስለኛል። ስለዚህ ኢህአዴግ በደርግ ግፎች ትልቅ የፖለቲካ ትርፍ ማትረፍ ቢፈልግም የራሱ እምነቶች እና ስራዎች ይህን እድልም እንዳይጠቀም አድርጎታል።

አሁን የ«እርቅና ሰላም» ኮሚሽን ሲቋቋም ያንን የደርግንም ታሪክ እንዲያካትት እና እንዲያሰማ መደረግ ያለበት ይመስለኛል። ኮሚሽኑ የ44 ዓመታት ግፍን ያስተናግድ። እኛ ኢትዮጵያዊያን ለረዥም ዓመታት ወንጀለኞች፤ ገዳዮች፤ አሰቃዮች ወዘተ እየወለድን እያሳደግን ወደ ስልጣን እያመጣን መቆየታችንን ማየት አለብን። የዚህ ቀጥታ ሰለቦች ታሪካቸውን የመናገር እድል ማግኘት አለባቸው። ሌሎቻችን ጥፋት እና ሃላፊነታችንን በነሱ በደረሰባቸው ማየት እና ማመን አለብን።

ይህ የንስሀ ሂደት ባለፈው 27 ዓመት ብቻ ከተገደበ እራሳችንን በሚገባው እንዳንወቅስ ይረዳናል። «እነሱ ናቸው ጥፋተኞቹ» ብለን የራሳችንን ሃላፊነት እንዳናይ ያረገናል። ግን ከደርግ ጀምሮ ታሪክን ካየን ሙሉ ግንዛቤ ይኖረናል። የኛ የማህበራዊ ጉድለታችንን እንድናምን ይረዳናል። አንድ ህበረተሰብ በተደጋጋሚ ጨቃኞች ሲወልድ እራሱን ምፈተሽ አለበት።

Monday 19 November 2018

የቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ አሁንም ኋላ እንዳይቀር፤ የሙስና ማስወገድ ስራውን ያፋጥን

ወራት በፊት የሀገራችን ፖለቲካ አውንታዊ ለውጦች እያመጣ እያለ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ እራሱን በቅድምያ አላስተካከልም። ፖለቲካው ከተቀየረ በኋላ በፖለቲከኞች (እነ ጠ/ሚ አቢይ) ግፊት እና ማበረታታት ቤተ ክርስቲያን ወደ ትክክለኛ ሰላም መንገድ ገባች። የቤተ ክርስቲያናችን ሲኖዶስ ከመምራት ፋንታ ተከታይ ሆነ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/02/blog-post_15.html)። ያሳዝናል። ግን መከተሉም እራሱ ተመስገን ነው።

አሁን ደግሞ መንግስት የፍትህ እና ሰላም ስራዎች በሰፊው እየጀመረ ነው። ያለፉትን ጥፋቶች ከነ ሙስና እንዲመረመሩ እና ሰላም፤ ፍትህ እና እርቅ እንዲመጣ ሂደቶች እና መዋቅሮች እያቋቋመ ነው። በቤተ ክርስቲያናችን የሚፈፀም የነበረው ኢሰባዊነት እና ሙስና ይታወቃል። የምርመራ ስራዎች በትንሹ የተጀመሩ እንደሆነ ይታወቃል። ግን ስራው ገና ነው፤ መዋቀራዊ አልሆንም እና ለመላው ሀብረተሰብ ግልጽ እንዲሆን አልተደረገም።

አሁንም ቤተ ክርስቲያን ከመምራት ፋንታ ኋላ ቀር ሆኖ እንዳይገኝ። ሙስና እና ሌሎች ኢ-ክርስቲያናዊ ድርጊቶች ቤተ ክርስቲያኗን ማለትም ምዕመኗንም እጅግ እንደሚጎዳ በታሪክ የታወቀ ነገር ነው። የህልውና ጉዳይ ነው። ይህ ስለሆነ ቤተ ክርስቲያን አሁንም መንግስትን ቀድማ እራሷን ማጽዳት አለባት። ለመላው ሀገራችን ምሳሌ መሆን አለባት።

ስለዚህ ቤተ ክርስቲያንን ከሙስና እና ሌሎች ኃጢአቶች የማጽዳታ ዘመቻ አሁኑኑ ጠንክሮ መጀመር አለበት። ይህ ካልሆነ መንፈሳዊ ጉዳቱ እጅግ የከፋ ነው የሚሆነው።

በባንክ ዘራፊዎች ሽፍቶች ነበር ሀገራችን የተገዛው

የሃብታሙ አያሌው እና ኤርሚያስ ለገሰ ውይይትን አዳምጡት፤

https://www.youtube.com/watch?v=A78Tet3GCms

አንዱ ከሚወያዩበት ነጥቦች ስለ ኤፎርት (EFFORT) ድርጅት ነው። ሁላችንም የምናውቀው የህወሃት መንግስትን ከመቆጣጠሩ በፊት ሃብት በመዝረፍ ነበር የሚያካመቸው። የእርዳታ እህል/መድሃኔት ወዘተ በመሸጥ፤ ባንክ በመዝረፍ ወዘተ። ደምበኛ የሽፍታ ስራ። ሁላችንም የምናውቀው ታሪክ ነው። አልፎ ተርፎ የሚደንቅ ታሪክም አይደልም ህወሓት በመሰረቱ ሽፍቶች ነበሩና።

ይህን ብለን ጉዳዩ ከሌላው ዝርፊያ እና ሙስና ክስተቶች ለፍርድ መቅረብ አለባቸው ብሎ መደምደም በቂ አይደለም! ይህ የውሸት ወይንም የማይበቃ መደምደምያ ነው።

ለኔ ዋናው መደምደምያ ሀገራችን ኢትዮጵያ በጥቂት ሽፍቶች ለ27 ዓመት ተገዝቶ ነበር ነው! ይህ እውነት በመጀመርያ ደረጃ የሚያስከሥሠው እኛን ነው! እንዴት ነው በነዚህ ትንሽ ቁጥር ያላቸው ሽፍቶች የተገዛነው የሚለውን ጥያቄ መመለስ አለብን። ይህን ጥያቄ ካልመለስን ወደ ፊት ይህ መትፎ ታሪካችንን እንደግማለን።

ጣት መጠቆም ብቻ ያብቃ። እንደገና እንዳንወድቅ እራሳችን ላይ ስራ እንስራ።

Friday 16 November 2018

ብራቮ ኤርሚያስ ለገሰ!

ይህን የኤርሚያስ ለገሰ ቃለ ምልልስን እዩት!

https://www.youtube.com/watch?v=WB2enMd2Ilk&t=3990s

ሁለት ታላቅ ነገሮች ያስተምረናል፤

1) ሃላፊነት፤ ጸጸት፤ እና ንስሃ፤ ኤርሚያስ ከመጸሃፎቹ ሺያች ገንዘብ ለተለያዩ የኢህአዴግ ሰለቦች (እንደ አበበ ክንፈ ሚካኤል)መስጠቱን አውቅ ነበር (ይታወቃል)። ለምን ብሎ ሲጠየቅ የሰጠው መልስ ሃላፊነት፤ ጸጸት እና ንስሃ ምን እንደሆኑ በጥሩ መንገድ የሚያስተምር ነው።

ኤርሚያስ ለኢህአዴግ በመስራቴ ኢህአዴግ ላደረገው ኃጢአቶች ህሊናዬ ስለሚወቅሰኝ ቢያንስ እንደ አቶ አበበ አይነቱን ተጎጂዎች በመርዳት ከራሴ ጋር እታረቃለሁ እና ላደረግኩት እንደ ካሳ ይሆናል ነው። ኤርሚያስ ማንንም አላሰረም አላሰቃየምም። ግን ሃላፊነት እንዳለበት አምኖ በሚመስለው መንገድ ይቅርታ እየጠየቀ ነው። ይህ የሚያስተምረን ሁላችንም በማድረግም ባለማድረግም ከመንግስት ሩቅ ብንሆንም በኢትዮጵያ ለተደረጉት ጥፋቶች ቢያንስ የተወሰነ ሃላፊነት እንዳለብን ነው። ታላቅ ትምሕርት ነው። ሁላችንም ይህን ትምሕርት ተምረን እራሳችንን እንደ ንፁሃን ከመቁጠር እንደ ኤርሚያስ ካሳ ለመክፈል ብናስብ ጥሩ ይመስለኛል።

2) የሰው ልጅ አስተዳደግ እና ጠቅላላ የኑሮ ጉዞ ለባህሪው እና ድርጊቱ አስተዋጾ አለው። ኤርሚያስ ስለ በረከት ስምዖን እና ባልደረባው ሽመልስ ሲጠየቅ «የሰው ልጅ ከመሬት ተነስቶ ክፉ አይሆንም» ብሏል። አስተዳደግ እና ታሪካዊ ምክንያቶች አሉ አለ። ይህን ሃቅ ሁላችንም ብናውቀውም ለመፍረድ ስንቸኩል እንረሳዋለን።

ይህ ሰውን አስተዳደግ እና ታሪክ ድርጊቱ ላይ ሚና አለው ስንል ለድጊታቸው ሰበበ ለማግኘት አይደለም። ለሁለት ምክንያት ነው፤ 1) ከመፍረድ እንዲቆጥበን ነው እና 2) መሰረታዊ ችግሮችን እንድናርም ነው። ለምሳሌ ከሰፈራችን አንድ ቤተሰብ ከማህበረሰቡ አላግባብ ተገልለው ኖረው ልጃቸው የደርግ/ህወሓት ጨቃኝ አሳዳጅ እና አሳቃይ ከሆነ ብዙ ሊገርመን አይገባም። ህብረተሰባችን እንደዚህ አይነት ሰዎችን የማይወልድ አይነት እንዲሆን መስራት እንዳለብን ያስታውሰናል።

አንድ መንግስት ጥሩ የሚሆነው እህታችን፤ ዘመዳችን፤ ጎረቤታችን፤ ወዘተ ሲመሩት ነው። ማለትም በህብረተሰቡ ክብር እና ተቀባይነት ያላቸው ሰዎች ሲመሩት ነው። በህብረተሰቡ ላይ ቂም ያላቸው ሰዎች (እንደ መለስ ዘናዊ) መንግስትን ሲመሩ መንግስቱን የቂም መወጫ ነው የሚያደርጉት። የማህበረሰባችን ዋና ስራ ቂም ያላቸውን ሰዎች አለመፍጠር ነው፤ ሁሉንም አቅፎ መያዝ።

ለማንኛውም ይህን የኤርሚያስ ቃለ ምልልስ እዩት። በጣም አስተማሪ ነው።

ስለ የዩኒቨርሲቲ ምደባ …

የታወቀ ችግር አለ…

ልጁ በ18 ዓመቱ ከወላጆቹ ቤት ለመጀመርያ ጊዜ ወጥቶ ወደ ሩቅ ሀገር ዩኒቨርሲቲ ይላካል። ከዛ ታላቅ ፈተናዎች እና አደጋዎች ይጠብቁታል። ብቸኝነት፤ ጥካት፤ ጭንቅ፤ ውጥረት፤ ስጋዊ ፈተኖች፤ ወዘተ። ዩኒቨርሲቲ እያለ በቀለ የለመደውን የቤተሰብ፤ ዘመድ እና በጠቅላላ የአካባቢ ድጋፍ የለውም። የሚደርሱበት ችግሮችን ከሞላ ጎደል ብቻውን መውጣት ይኖርበታል። አንዳንዱ ልጅ ፈተናውን ይወጠዋል አንዳንዱ ደግሞ ፈተናው ይውጠዋል።

መሰረታዊው ችግር ይህ ነው፤ «ለሰው ልጅ ከትውልድ ሀገሩ ተነቅሎ ብቻውን ሌላ ሩቅ ቦታ መሄድ ኢ-ተፈጥሮአዊ ነው»። ይህ «ስደት» ጎጊ ብቻ አይሆን «ኢ-ተፈጥሮአዊ» ነው። የሰው ልጅ በተፈጥሮ ወላጅ እና እህት ወንድሞች ብቻ ሳይሆን ዘመድ አዝማድ እና መንዳር አለው። ከነዚህ መሃል ሆኖ ነው ጤናማ ኑሮ መኖ የሚችለው።

ለዚህም ነው በሰው ልጅ ታሪክ የትውልድ ቦታን ትቶ ብቻውን ተሰዶ ሌላ ቦታ መሄድ የሌለው። ሰው ከተሰደድም 1) በታላቅ ችግር ምክንያት ነው የሚሰደደው እና 2) ብቻውን ሳይሆን ከመላ ቤተሰቡ እና መንደሩ ጋር ነው አብሮ የሚሰደደው። እንጂ የሰው ልጅ ብቻውን ቤቱን ትቶ አይሄድም።

ሁለተኛው ችግር ደግሞ ቤታቸውን ትተው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚሄዱት ገና ልጆች ናቸው። ቤተሰብ የመሰረቱ ጎልማሶች አይደሉም። ብዙዎቹ ሃላፊነትም አለመዱም። «ተማሩ እና እራሳችሁን ቻሉ» እየተባሉ ከሌላ ሃላፊነት ነፃ ሆነው ያደጉ ናቸው። እንደ ድሮ ልጆች የበሰሉ አይደሉም። ሽፋናቸው የበሰለ ይመስላል ግን ጥሬ ናቸው።

ሶስተኛ ችግር… በተፈጥሮ የሰው ልጅ ላቅማዳም ካለፈ የትወሰነ ዓመት በኋላ ቤተሰብ ይመሰርታል። እንደገና ይህ ጠፈጥሮ ነው ነአ ተፈጥሮን መታገል አጉል ነው። እነዚህ ልጆች ኃይለኛ የስጋዊ ፈተና አለባቸው። ብቻቸውን ዩኒቨርሲቲ ሲሄዱ ፈተናው ይበልጣል። ገቤተሰቦቻቸው ጋር ቢሆኑ እና በሃላፊነት እና ድጋፍ በከበቡ ይሻላል። ቢያንስ ለተወሰነ ጊዜ ፈተናውን ተቆጣጥረውት ትምሕርታቸውን ሲጨሩሱ ወደ ቤተሰብ ምስረታ መሄድ ይችላሉ።

በነዚህ ምክንያቶች ልጆችን ከቤተሰብ ነቅሎ ወደ ሩቅ ዩኒቨርሲቲዎች መላክ አይመረጥም። እነ ልጆቼ ከቤት ሆኖ ተምረው እንዲዳሩ ነው ፍላጎቴ። ይህ ትክክለኛው ተፈጥሮአዊ መንገድ ነው ብዬ አምናለሁ።

ይህን ሁሉኡ ስል የፖሊሲ አውጪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ እንደ ህዝብን ማስተዋወቅ እና ማቀላቀል መንገድ እንደሚያዩት ይገባኛል። ጥሩ አላማ ቢሆንም ጉዳቱ ከጥቅሙ የሚበልጥ ይመስለኛል። ቢያንስ አስተማሪዎችን የመመደብ እድል መስጠት ነው። እድሜአቸው ትልቅ በመሆኑ ምናልባትም ቤተሰብ ስላላቸው ከባድ ቢሆን ይሻላል።

Thursday 15 November 2018

ሁለት ተከታታይ አብዮቶች

በ1967 እና 1983 ሀገራችን በአብዮት ክፉኛ ተተረማመሰች። ለነዚህ አብዮቶች የተማሪ ንቅናቄ ይወነጀልበታል። አዎን ይህ ንቅናቄ ታላቅ ጥፋት አለበት። ግን ምንድነው የተማሪ ንቅናቄውን የፈጠረው? ይህን ግልጽ ጥያቄ በቂ አንመረምርም። በጃንሆይ ጊዜ በቂ ከባድ ችግሮች ነበሩ። በውቅቱ ባለመስተካከላቸው ነው ለአብዮት ያበቃን። ግን የጃንሆይ መንግስት ስህተቶችም ምክንያት አላቸው፤ ከዘመነ መሳፍንት ወዘተ የወረዱ ችግሮች ነበሩ።

ግንዛቤአችን በዚህ መልኩ ነው መሆን ያለበት ይመስለኛል። ጥፋትን አንድ ሰው ወይንም ቡድን ላይ መለጠፍ ህፃናዊ አስተሳሰብ ነው። እውነታው የፖለቲካ ችግሮቻችን ብዙ ምክንያቶች አላቸው። ይህን እውነታ ስንረዳ ነው ወደ ትክክለኛ መፍትሄ መሄድ የሚቻለው። በዚህም መንገድ ነው የሌሎችን ብቻ ሳይሆን የራሳችን ጥፋት አይተን መስተካከል የምንችለው።

ማን ነው የሚተርፈው?

አሉ የኢሳት ተንታኞች። በኢህአዴግ ዘመን የተከሰቱ የጭካኔ እና ሙስና ወንጀሎች ክር መተርተር ሲጀምር ማን ከኢህአዴግ እና ዙርያ ይተርፋል? ማን ያላጠፋ አለ?

ወይ ሁሉንም ማሳሰር ነው ወይንም እንደ ደቡብ አፍሪካ የእርቅ ስርዓት አቋቁሞ ፍትህ በእርቅ እንዲመጣ ማድረግ ነው ተባለ። ከነዚህ ደግሞ ሁለተኛው የእርቅ ስርዓት መንገዱ ጥሩ እና እውነት የያዘ አማራጭ ነው።

ለኔ ግን ከዚህ ሁሉ በላይ ዋናው ጓይ ይህ ነው፤ ማን ይተርፋል ብለን ስንጠይቅ ለምንድነው ስለኢህአዴግ እና ሌሎች ብቻ የምናወራው? «እኛሳ»? ጥፋት በማድረግም ባለባድረግም ነው ልንከሰስ ይገባል።

አዎን መስረቅ ጥፋት ነው። ግን የሚጎዳን አለመርዳትም እንዲሁ ጥፋት ነው። ስንቶቻችን «ብዙሃን» ባልደረቦቻችን በተለያየ መንገድ የፖለቲካ እና ማህበረሰባዊ ጥቃት ሲደርስባቸው ዝም ያልነው እና ያልረዳናቸው? ጎረቤታችን ተቸግሮ ቢያንስ «ይሄው 100ብር፤ ስለተቸገርክ ስለተጎዳህ አዝናለሁ» ያልን ስንቶቻችን ነን? እርግጥም ስንቶቻችን ነን ከጎረቤትና ባልደሮቦቻችን የከፋ ግጭት እና ቅራኔ ያለን። እርስ በርስ ተከፋፍለን ለከፋፍሎ መግዛት መንግስት እራሳችንን ያመቻቸን?!

የፖለቲካ እና ማህበራዊ ጥፋቶች የማህበሩ ማለትንም የእያንዳንዶቻችን ነው። No man is an island። ጥፋታችንን አምነን ወደ ንስሃ ከገባን ብቻ ነው እርፍት እይሚኖረን። እንጂ ዎንጀሎችን አስረን ሰላም ይመጣል ማለት ታሪክን አለማወቅ እና እራስን ማታለል ነው።

ታዋቂው ሩሲያዊ የፖለቲካ እስረኛ እንዳሉት፤
«ከእስርቤታችን አልጋ የሆነው የበሰበሰው ገለባ ላይ ጋደም ብዬ ነው ለመጀመርያ ከውስጤ የበጎ መንፈስ የተሰማኝ። ቀስ በቀስ መረዳት የጀመርኩት ይህ ነው፤ ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር በሀገሮች፤ መደቦች፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም መካከል አይደለም የሚያልፈው፤ ይህ መስመር የሚያልፈው በያንዳንዱ የሰው ልብ መኻል ነው። መስመሩ እድሜአችን በሙሉ ከውስጣችን ወደፊት ወደኋላ ይላል። በክፉ የተሞሉ ልቦችም ቢያንስ ቅንጣት ያህል ጥሩነት ይኖራል፤ ከሁሉም ጥሩ ከሚባለውም ልብ ከአንድ ጥጓ ትንሽ ክፉነት ይኖራል።
በየቦታው እየዞሩ ያሉ ክፉ ስራ የሚሰሩ ክፉ ሰዎች ቢኖሩና እነሱን ከኛ መለየትና ማጥፋት ብቻ ቢሆን ኖሮ እንዴት ቀላል ነበር? ግን ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር ከያንዳንዱ የሰው ልጅ ልብ መካከል ነው የሚያልፈውና ማን አለ ከራሱ ልብ ቁራጭ ቆርጦ ለማጥፋት ፈቃደኛ ይሆነ?»
https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/blog-post_30.html

Tuesday 13 November 2018

ወግ እና ማንነት ሲናቅ ግብረ ገብ ይጠፋል

በደርግ ዘመን የተደረገውን ማሰቃየት (torture) ይታወቃል። በወያኔም ዘመን እንዲሁ መቀጠሉን ሁላችንም እናውቃለን መንግስት አምኖ የፍትህ እርምጃዎች መውሰዱ ታላቅ እርምጃ ቢሆንም።

ለምንድነው ይህ የተከሰተው የሚለውን ጥያቄ በተለያየ መንገድ መመለስ ይቻላል። አንዱ መልስ የራስን ባህል፤ ወግ፤ እና ታሪክን ንቆ እና ትቶ የሌላ የበአድ መንገድ መከተል ነው።

ኃይለ ሥላሴ (የሚመጣውን ችግር በደምን ሳይረዱ?) ራሱን የሚጠላ ፈረንጅ አምላኪ ልሂቃን ትውልድ ከፈጠሩ በፊት ዛሬ የምንሰማው አንየንት የግብረ ገብ ጥሰት እና ማሰቃየት አልነበረም። ሰው ወህኒ ቤት ይታሰራል፤ ግዞት ይላካል፤ ማናልባትም ይገደላል። እነዚህ ነገሮች በአግባብም አለአግባብም ይደረጉ ነበር። ግን «ባህላዊ» ናቸው ማለት ይቻላል፤ ለመቶዎች/ሺዎች ዓመታት የሚደረጉ ነገሮች ነበሩ።

ዘመናዊው ትውልድ ግን የበአድ ባህሪዎችን አመጣብን። በፍፁም የማይታሰቡ አስተሳሰቦች አመጣ። በፍፁም የማይደረጉቶች አመጣ። እራሱን፤ ማንነቱን፤ ኢትዮጵያዊነቱን ሳተ። ወደ ኢ-ኢትዮጵያዊነት ሙሉ በሙሉ ገባ። ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ ድርጊቶች ፈጸመ። ለዚህም ነው ዛሬም ቢሆን ኢትዮጵያዊያን ስለነዚህ ድርጊቶች ሲሰማ እጅግ እሚደነግጠው።

ይህን ስል በባህላችን ችግሮች የሉም ማለቴ እንዳልሆነ መቼም ሁላችሁም ትገነዘባላችሁ! ሆኖም ችግሮችን ቀርፎ ማውጣት እና ጥሩ ነገሮችን ይዞ መጓዝ ነው እንጂ ሁሉንም አራግፎ ወደ ሌላ መንገድ መሄድ አደጋ ነው። ይህን አደጋ በተለያየ መንገዶች አይተነዋል እያየነውም ነው።

ይህ የማሰቃየት ታሪካችን እንዳይደገም አንዱ መፍትሄ ወደ ወጋችን፤ ወደራሳችን መመለስ ነው።

Thursday 8 November 2018

ለአቶ ፋንታሁን ዋቄ ዝቅ ብዬ እጅ እነሳለሁ!

ይህንን የአቶ ፋንታሁን ዋቄ ንግግርን ጠንቅቃችሁ እንድታዳምጡ እጠይቃችኋለሁ፤

https://www.youtube.com/watch?v=S_OSDSUo_ds

ባህል እና ወግ ለሰው ልጅ መሰረት መሆኑን በአጭር እና ግልጽ መንገድ አስረድተዋል። ባህል እና ወግን አጥብቆ የያዘ መቼም መንገድ እንደማይስት ያስረዳል። ጠንቅቃችሁ አዳምጡት!

በ1960ዎቹ ታዋቂው አሜሪካዊ መምህር ዶናልድ ለቪን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ያስተምሩ ነበር። መምህር ዶናልድ ተማሪዎቻቸው እና አዲስ አበባን የሚንሸራሸሩት ልሂቃን ወደ «ፈረንጅ» እና ዘመናዊነት አምልኮ ሲጠመዱ አዩ። የህን በማየት ኢቲዮጵያዊያንን እንዲህ ብለው አስጠነቀቁ፤

"The vitality of a people springs from feeling at home in its culture and from a sense of kinship with its past. The negation of all those sentiments acquired in childhood leaves man adrift, a prey to random images and destructive impulses…"

Wednesday 7 November 2018

የጎሳ አስተዳደርን አደገኝነት አለመረዳት ትንሽ ግትርነት ይመስለኛል

ከዚህ ገንቢ ውይይት (https://www.youtube.com/watch?v=tVqQW7Sh_G0) ስለ ጎሳ አስተዳደር (ፌደራሊዝም) ብዙ ጊዜ የሚነሳ ነጥብ ተነስቶ ነበር። ይህም፤

«የጎሳ ፌደራሊዝም በትክክሉ አልተሞከረም። እስካሁን ዴሞክራሲ አልነበረም፤ የአምባገነናዊ ጭቆና ነበር። የህዝቡ ኤኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ጥቅምም አልተከበረም። ለዚህ ነው ፖለቲካዊ ችግሮች የሚታዩት። ዴሞክራሲ፤ የኤኮኖሚ እና ማህበራው ፍትህ ሲኖሩ የጎሳ አስተዳደር በደምብ ይሰራል።»

አንዱ ተንጣኝ ይህንን አቋም ለመግለጽ "You can't judge a philosophy by its abuse" አይነት አባባል ተናግረዋል።

መቼስ ስለ ኮምዩኒዝምም እንዲህ ማለት ይቻላል! በትክክል ቢፈጸም ገነትን ያመጣልን ነበርና።

የጎሳ አስተዳደር ችግሮች ለማንኛውም አጉል risk ወይንም የራቀ እና ጸንፍ የያዘ ፍልስፍና ማቀፍ ለማይፈልግ ሰው ግልጽ የሆነ ይመስለኛል። ምክንያቶቹ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_89.html)፤

1. ደጋግሞ እንደሚባለው የትም ሀገር የጎሳ አስተዳደር የለም። ይህ በራሱ የጎሳ አስተዳደር እጅግ ጸንፍ የያዘ አስተዳደር እንደሆነ ይገልጻል።

2. በተለያዩ ሀገራት የጎሳ አስተዳደር የሌላቸውም ግን በተለያየ በፖለቲካ ክፈተቶች ጎሰኝነት ሲሰፍን ያለው ጉዳት አይተናል። የጎሰኝነት ችግር አንዳንድ ሀገሮች እስከ የጎሳ ፓርቲዎችም መከልከል አድርሷቸዋል።

3. የ27/22 ዓመት የሀገራችን የጎሳ አስተዳደር ተለምዶ ለጎሳ አስተዳደር አደገኝነት በቂ ማስረጃ ነው። አዎን ዴሞክራሲ አልነበረም ግን የጎሳ ተኮር ግጭቶች እና ቅራኔዎች በዴሞክራሲ እጦት ማሰበብ አይቻልም። መቼም ማንም reasonable ሰው እንዲህ የሚያየው አይመስለኝም። ምንም አይነት ችግሮች በጎሳ ግጭት መልኩ እራሳቸውን የሚገልጹ ከሆኑ ጎሰኝነት ነው ችግሩ ማለት
 ነው! አልፎ ተርፎ አሁን ዴሞክራሲ እየመጣ ግጭቶቹ ቀጥለዋል ወይንም በዝተዋል!

እነዚህን ግልስ የሆን ማስረጃዎች እያለን እና ግጭቶች እየበዙ እያሉ አሁንም የጎሳ አስተዳደር experimentአችንን እንቀጥል ማለት የሰከነ አስተያየት ነው? ይቅርታ አድርጉልኝ እና አይመስለኝም።

ይህን ስል የጎሳ አስተዳደርን የሚፈልጉት ሰዎችን መሰረታዊ ጥያቄዎች ማስተናገድ አንዳለብን ይገባኛል። አማራጭ ሊኖር ይገባል። አለ ጎሳ አስተዳደር እንዴት ነው የጎሳ መብቶች (እነዚህ መብቶች አይነታቸው አከራካሪ ቢሆንም) ማስከበር የሚቻለው።

መልሱ ቀላል ነው እና እንደ ጎሳ አስተዳደር አዲስ ፈጠራ ውስጥ እንድንገባ አያስገድደንም።
ከኢትዮጵያ አስር እጥፍ በላይ የጎሳ መብቶች (ቋንቋ፤ ባህል፤ አስተዳደር) የሚያስከብሩ ሀገራት አሉ። ህንድ፤ ስዊትዘርላንድ፤ ካናዳ ወዘተ። እነዚህ ሀገራት ሁሉም ሀገ መንግስታቸውን በዜግነት ነው የመሰረቱት። የጎሳ መብቶች በክፍለ ሀገር አቀራረጽ፤ የቋንቋ ህጎች፤ ለክፍለ ሀገር የሚሰጠው የማስተዳደር መብት ወዘተ ያስከበራሉ። ግን መሰረቱ ዜግነት ነው። እነዚህን እንደ ምሳሌ ወስዶ መጠቀም ነው።

ለመዝጋት አንድ አጭር ምሳሌ ልስጥ። ዛሬ ከህገ መንግስቱ «ብሄር፤ ብሄረሰቦች እና ህዝቦች» የሚለው ጥቅስ ከህገ መንግስቱ አወጣን እንበል። የክልል ቋንቋ በክልል ህዝብ ነው የሚወሰነው እንበል። ኦሮሚኛ የፌደራል ቋንቋ አደረግን እንበል። ይህ ሁኔታ (scenario) በርካታ የጎሳ መብት ያስከብራል። ኦሮሚያ ውስጥ በድምጽ ብልጫ የክልል ቋንቋ ኦሮምኛ ሆኖ ይቀራል። ይህ ማለት የምንግስት መስሪያቤት፤ ትምሕርት ቤት ወዘተ። የኦሮሚያ ክልል አስተዳደርም በኦሮሞ ባህል እንዲሆን በድምጽ ብልጫ ይፈጸማል። ወዘተ። ይህ አንድ ምሳሌ ነው። አለ ጎሳ አስተዳደር በርካታ የጎሳ መብቶች ሊፈጸሙ ይችላሉ።

ስለዚህ ወደ ህልም፤ ጸንፍ፤ አጉል ሙከራ አንሂድ። ቀላሉን መንገድ እንውሰድ። እንደ ኮምዩኒስቶቹ ህልማችንን እስከ መቃብራችን አቅፈን አንቆይ!

Tuesday 6 November 2018

ዲያቆን ዳኒኤል ክብረት ስለ ውጭ ሀገር ጳጳሳት የጻፈውን ለመማርያ እንጠቀም…

(UPDATE) ዛሬ ጥቅምት 21 ይህን ሰማን፤ ከ16 «ውጭ ሀገር ካልተመደብን» አሉ ከተባሉት ጳጳሳት ሁለቱ፤ አቡነ ዮሃንስ እና አቡነ ሚካኤል፤ ሀገር ውስጥ እንሰራለን ብለው ተመድበዋል! ስለዚህ እስካሁን ከ20 ጳጳሳት አራቱ ሀገር ውስጥ፤ ያውም አንዱ ጅጅጋ፤ ለመስራት ተዘጋጅተዋል። ሌሎችም ሊቀጥሉ ይችሉ ይሆናል።

ዲያቆን ዳኒኤል ክብረት በቅርብ ጊዜ ጽሁፉ እንዲህ ይላል፤
«ባለፉት ሦስት ወራት አያሌ ፖለቲከኞች ወደ ኢትዮጵያ በመግባት በሀገር ውስጥ ባለው ፖለቲካ ለመሳተፍ እየተንቀሳቀሱ ነው፡፡ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች እየተዘዋወሩም ድጋፍ እየሰበሰቡ ነው፡፡ በተቃራኒው ደግሞ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጳጳሳት ፖለቲከኞቹ የለቀቋቸውን አሜሪካ፣ አውሮፓና አውስትራልያ ለማጥለቅለቅ ወደ ውጭ እያቀኑ ነው፡፡ 
በተለይም ከውጭ የመጡት ብጹአን አባቶች ኢትዮጵያ ውስጥ የመመደብ ፍላጎት ፈጽሞ የላቸውም፡፡ በዚህ ረገድ ከ18 ጳጳሳት ሁለት ብቻ ናቸው የተገኙት፡፡ ሌሎቹ ግን በአሜሪካና በአውሮፓ ካልመደባችሁን እንገነጠላለን ብለው የሚያስፈራሩ ሆነዋል፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ መለመንና ማግባባት ሲያቅተው ጳጳሳቱን የደብር አስተዳዳሪዎች አድርጎ እስከ መመደብ ደርሷል፡፡
…»
ጽሁፉ ይቀጥላል። የጽሁፉ ዋና ነጥብ ይህ ነው፤ ለስደተኛው ሲኖዶስ የሚያገለግሉ የነበሩት ጳጳሳት ኢትዮጵያ ውስጥ መመደብ እና መስራት አይፈልጉም።»

የዲያቆን ዳኒኤል ጽሁፍ እንደኚህ አይነት በርካታ ጥያቄዎች ያስከትላል፤

1. እውነትም 16ኡም ጳጳሳት ውጭ ሀገር ካልተሾምን «እንገነጠላለን» ነው ያሉት ወይንም አንዳንዶቹ በነበርንበት ውጭ መመለስ እንወዳለን ነው ያሉት? «ይህ ቢደረግልኝ ነው የምፈልገው» እና «ይህን ካልተደረገልኝ እገነጠላለሁ» የተለያዩ አቋሞች ናቸው።

2. 16ኡም ሁኔታቸውም አቋማቸው እና ሁኔታቸው አንድ ነው? ልምሳሌ አንዳንዶቹ እውነትም አሳሳቢ የጤንነት ችግር እያላቸው ነው ሀገር ውስጥ መስራት አንችልም የሚሉት? ወይንም ከምዕመናኖቻቸው ጋር ያላቸውን ትሥስር ምክንያት መልቀቅ አልፈለጉ ይሆን? ወይንም ሀገር ውስጥ ለመስራት በቂ ብቃት እና ችሎታ የለኝም ብለው በልባቸው የሚያስቡ ይሆናል (አንዳንዱ በቀላሉ ስለተሾሙ)? አንዳንዶቹ ሀገር ውስጥ ለመስራትና ለመኖር መንፈሳዊ ፍርሃት ይኖራቸው ይሆን?

3. ቅዱስ ሲኖዶስ 16ኡም ጳጳሳት ሀገር ውስጥ እንዲሰሩ ይፈልግ ይሆን? ወይንም አንዳንዶቹን ብቻ ነው ኢትዮጵያ ውስጥ ሊመድባቸው ያሰበው?

4. ይህን ተከትሎ እነዚህ 16ኡ ሁሉም ኢትዮጵያ ውስጥ ቢመደቡ ቤተ ክርስቲያንን ይጠቅሟት ይሆን?

እነዚህ ጥያቄዎች እስከተረዳሁት ድረስ በዲያቆን ዳኒኤል ጽሁፍ አልተመለሱም። ታድያ እነዚህ መሰረታዊ ጥያቄዎች ሳይመለሱ እንዴት ነው በ16 ሰው ላይ (የጅምላ) ክስ ማቅረብ የሚቻለው?

ለኔ ይህ ጽሁፍ ለቅራኔ መፍታት (conflict resolution) እና የቅራኔ መፍታት እጦት ጥሩ ትምሕርት ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_21.html)።

ማንኛውም ጹፍ፤ ንግግር፤ ውይይት ወይንም ተግባር ግብ አለው። በተለይ እንደ ዲያቆን ዳኒኤል አይነቱ ታዋቂ እና ባለስልጣን የሆነ ሰው መልዕክት በአንደበትም በጽሁፍም ሲያስተላልፍ ይህን ግብ ጠንቅቆ አስቦ ነው ማድረግ ያለበት።

የዚህ የዲያቆን ዳኔኤል ጽሁፍ ግቡ ምንድነው? እኔ እንደሚመስለኝ 1) ህዝብን የነዚህ ጳጳሳትን ራስ ወዳድነት ወይንም ብቃት ማጣትን ለማሳየት እና 2) ጳጳሳቱን ለመገሠጽ። እነዚህ ግቦች ተገቢ ናቸው ብንልም የዲያኮን ዳኒኤል ጽሁፍ እነዚህን ግቦች ከማሳካት ይልቅ እንዳይሳኩ ያረጋል። እስቲ ጉዳዩን እንመርምረው…

ይህ ጽሁፍ ህዝብን ስለጳጳሳቱ ችግር አያሳውቅም። ለምን?

1) ጽሁፉ የተመሰረተበት ማስረጃ ሙሉ እውነት አይደለም። እንሆ 18 ጳጳሳት ሀገር ውስጥ መሾም አይፈልጉም ተብሎ ነበር ዛሬውኑ 16 ሆነ። ቁጥሩ አሁንም ሊቀንስ ይችላል።

2) ጸሃፌው ዲያቆን ማስረጃ ቢኖሮውም ከጽሁፉ አላቀረበውም። ክሱ ታላቅ ነው ማስረጃው ታናሽ። ስለዚህ አንባቢው በጥርጣሬ ነው የሚያነበው። ከላይ ያነሳኋቸውን ጥያቄዎች ያነሳል። በዚህ ጥርጣሬ መካከል አንባቢው እነዚህ ጳጳሳት እንዲህ አድርገዋል የሚባለውን ለማመን ያስቸግረዋል።

ጽሁፉ ሁለተኛውን የጳጳሳቱን መገሠጽ አላማውንም አያስፈጽምም። ለምን?

1) በሀሰት የተከሰሱት ጳጳሳት፤ ማለትም ሀገር ውስጥ አንሰራም ያላሉት፤ አይመለከታቸውም። ባይመለከታቸውም አብሮ በመከሰሳቸው ዲያቆኑ ላይ ቅሬታ እንዲኖራቸው ያደርጋል።

2) ጽሁፉ ለተገቢ ምክንያት ሀገር ውስጥ መስራት አንፈልግም ያሉትም ዲያቆን አኒኤል ላይ ቅሬታ እንዲኖራቸው ያደርጋል። የሚያሳስባቸው የጤንነት ችግር አላቸው፤ ህዝባቸውን መትወ አይፈልጉም፤ ሀገር ውስጥ ለመስራት ይፈራሉ ወዘተ ምክንያት ይኖራቸዋል። ዲያቆን ዳኒኤል ሳይጠይቃቸው ሳያነጋግራቸው በደፈናው እንዲህ በመፍረዱ ደስተኛ አይሆኑም። የሱን ተግሣጽ አይቀበሉም።

ስለዚህ የዲያቆን ዳኒኤል ጽሁፍ ሁለቱንም ግቦች አይመተም። ይልቁንስ ቅሬታ ያሰፍናል። ጳጳሳቱ ቅር ይላቸዋል። በርካታ አንባቢ ጽሁፉ የጅምላ ያለማስረጃ ክስ በመሆኑ ቅር ይለዋል። ሌሎች አንባቢዎች ደግሞ ጽሁፉን ቢያምኑት ደግሞ የሀሰት ወይንም ያልተሟላ ክስን አመኑ ማለት ነው እና  እንዲፈርዱ ወይንም ፈራጅ እንዲሆኑ አደረጋቸው። የጽሁፉ መጨረሻ ውጤት አያምርም።

እንዲህ የሆነበት ምክንያት ጽሁፉ መሰረታዊ የአወያየት ስህተቶች ስላሉት ነው። ለምሳሌ፤

1) መፍረድ፤ ማለት ድርጊትን ከመቃውም አድራጊውን መቃወም እና መወንጀል። ልምሳሌ «ጳጳሳት አለ ጥሩ ምክንያት ሀገር ውስጥ መስራት አልፈልግም ማለት ተገቢ አይመስለኝም» ማለት ጥሩ ነው። «እንደዚህ ያሉ ጳጳሳት ካሉ ምክንያታቸው በደምብ ቢታይ ጥሩ ነው» ማለት ተገቢ ነው። ግን «ጳጳሳቱ ምቾት ለምደው ሀገር ውስጥ መስራት አይፈልጉም» ማለት ድርጊትን ሳይሆን ሰው ላይ (ያውም አለማስረጃ) መፍረድ ነው።

2) ማስረጃ አለመስጠት፤ አወያየት እምኔታ ያስፈልገዋል። አንዱ የአምኔታ መስፈርት ማስረጃ ነው። ማስረጃ ከሌለ ጥርጣሬን ነው የሚጋብዘው። ጽሁፉ ጥርጣሬን ያንጸባርቃል።

3) የጅምላ ፍርድ፤ ምናልባት አንዳንዱ ጳጳሳት (ልባቸውን ከፍተን አይተን) መጠን የለሽ ራስ ወዳድ ሆነው ሌሎቹ ግን አይደሉም ክሱም አይመለከታቸውም። ግን አብረው ተፈርጀዋል። የጅምላ ፍርድ የውውት፤ መስማማት፤ እውነት ላይ መድረስ፤ መተማመን ወዘተ ገዳይ ነው።

4) ሀሜት፤ ሰውን ቀጥታ ከመተቸት በተዘዋዋሪ ወይንም በብዙሃን መደረክ መተቸት እንደ ሀሜት ነው። የሚተቸው ሰውን ትችቱን በጥሞና ለመቀበል ይከብደዋል። ተዋረድኩኝ ይላል። ውየንም በሃሰት ተከሰስኩኝ ይላል። በጥሞና ከመቀበል ይልቅ ጥላቻ ያድርበታል።

5) ለሰው አለመቆርቆር፤ በሰው ቦታ ሆኖ ማሰብ የክርስትና ተዕልኮ ነው። ጳጳሱ እውነት እጅግ የሚያማቸው ሆኖ በኢትዮጵያ ህክምና የሚፈሩ ቢሆንስ? በነሱ ቦታ ብንሆን ምን እናደርግ ይሆን? «መነኩሴ ኖት» ማለት ቀላል ነው ግን ተገቢ አይደለም። ለሰው አለመቆርቆር ማለት መወያየት አለመቻል ነው።

6) ስም ማጥፋት፤ የጽሁፉ መንፈስ የስም ማጥፋት መንፈስ አለው ይመስላል። ልምን እንዲህ እላለሁ? እንደገና የጅምላ ፍርድ ያለው እና ግልጽ ማስረጃ የሌለው በመሆኑ ነው።

በነዚህ ምክንያቶች ጽሁፉ ችህግርን ከመፍታት ቅራኔን ያመጣል ወይንም ቅራኔን ያጎለብታል ማለት ይቻላል። እኔ እንደዚህ ነው የሚመስለኝ።

በተጨማሪ ዲያቆን ዳኒኤል የቁጣ መግሥጽ አጻጻፋቸውን ለማስረዳት በመሃበራዊ ሚዲያ ምን አሉ፤ «ጳውሎስ ያን የጻፈው ለእኛ ትምህርት እንዲሆን ነው። ይህም እንደዚሁ»።

የቅዱሳን አባቶቻችን ትምሕርት ከገባኝ «አትፍረዱ» አንዱ ዋና ትእዛዛችን ነው። ቅዱስ ጳውሎስ በቁጣ እየፈረዱ ስለጻፉ እኛም እንደዛ ማድረግ አለብን ማለት አይደለም! የተናጋሪው ማንነት ወሳኝ ነው። ቅዱስ ጳውሎስ የበቃ እረኛ፤ ለእግዚአብሔር እጅግ የቀረበ ሃዋሪያ በመሆኑ ለምዕመናን የሚሰጠው «መድሃኒት» ተገቢው ነው። የምዕመናን ልብን ያውቃል። ምን እንደሚያስፈልገን ያውቃል። ይህ ከቅድስና የሚመጣ ጸጋ ነው። ለዚህ ነው የቅዱሳን አባቶቻችን አንዳንዴ በኃይለኛ ቋንቋ የተናገሩት። ለዚህ ነው እንደ ዮሃንስ አፈወርቅ አይነቱ ህዝብን በጅምላ የገሠጸው። በኢግዚአብሔር ያላቸው ቅርበት ምክንያት እውነትን ይዘው ነው የሚናገሩት በትክክል የሚያስፈልገንን መልዕክት ነው የሚሰጡን። ግን ሌሎቻችን ይህ ደረጃ ላይ ስላልሆንን «አትፍረዱ» የሚለውን ትዛዝ አጥብቀን ይዘን ነው መራመድ ያለብን። እኛ ቅዱስ ጳውሎስ አይደለንም። ዮሃንስ አፈወርቅ አይደለንም። በአነስተኛ የመንፈሳዊ ደረጃችን እንደነሱ እናድርግ ካልን እንሳሳታለን። ወደ መፍረድ፤ ግብዝነት እና ትዕቢት እንድንሄድ ይፈትነናል። አልፎ ተርፎ ቅራኔን ያበዛል።

ይህን ሁሉ ስጽፍ ልብ ካላችሁ የዲያቆን ዳኒኤል ማንነትን አልተቸሁም። ስለ ጻፈው ብቻ ነው የጻፍኩት። ይህ አጻጻፍ ወይንም አነጋገር ገምቢ አይደለም እና ቅራኔ ያንጸባረቃል ነው ያልኩት።

አንድ የሊሂቃን ንስሃ፤ ዶ/ር ታደሰ ወልዴ

ይህንን ቪዲዮ ብትመለከቱ ጥሩ ይመስለኛል።

https://youtu.be/qSPFi8xsbBo?t=1696

ረዥም ከአንድ ሰአት በላይ የሚወስድ ቢሆንም ከላይ ባስቀመትኩት ሊንክ ጀምሮ ብታዩት ስለ ንስሃ ታላቅ ትምሕርት በተለይም ታላቅ ምሳሌ ታያችሁ።

አቶ ታደሰ ወልዴ፤ ታላቅ የኦክስፎርድ መምህር፤ ለኛ ሁሉ ንስሃ ለመግባት ምሳሌ በመሆኖ እግዚአብሔር ይስጦት።

Sunday 4 November 2018

ጠ/ሚ አቢይ፤ መሬትን የግል በማድረግ የኤኮኖሚ ድል ያገኛሉ

እነ ጠ/ሚ አቢይ የለውጥ ሂደታቸውን ለማረጋጋት፤ አቅም ለመገንባት እና ጥሩ መሰረት ለመገንባት ኤኮኖሚይ እንዲጠነክርላቸው ይፈልጋሉ። ይህን ለማድረግም ብዙ እርምጃዎች እየወሰዱ እናያለን።

አንድ ያልወሰዱት እርምጃ መሬትን የግል ማድረግ ነው። ወይንም ህገ መንግስቱን ሳይቀይሩ በተዘዋዋሪ መንገድ ከተማም ገጠርም መሬት መሸጥ መለወጥ ማድረግ ነው። ልምሻሌ አማራ ክልል እንደተደረገው የረዥም ዓመት ግለሰብ ለግለሰብ ሊዝ (አማራ ክልል 25 ዓመት) መፍቀድ እና ማበረታቻ ህጎች ማርቀቅ ነው። ለምሳሌ 25 ዓመቱ 199 ዓመት ከሆነ de facto ሺያጭ ማለት ነው።

መቼስ ዛሬ መሬት መሸጥ መለወጥ ቢቻል ለኤኮኖሚውም ለማህበረሰብ ጤንነትም ታላቅ ድል እንደሚሆን ማስረዳት አያስፈልገኝም! ምርትን ይጨምራል፤ የገበሬ አቅምን (human capital) ይጨምራል፤ ሙስናን ይቀንሳል፤ የመሬት ዋስትናን (ማለትም የአዕምሮ ረፍት) ይጨምራል፤ መሬት በሚገባው ደረጃ ጥቅም እንዲውል ያደርጋል ወዘተ። ለዝርዝሩ እነዚህን ጽሁፎች  ተመልከቱ፤

፩፤ https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_47.html
፪፤ https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/blog-post_94.html

በመጨረሻ የጎሳ ብሄርተኝነት ፖለቲካ ይህን እርምጃ ለመውሰድ የሚያግድ ከሆነ የጎሳ ብሄርተኝነት የማይበዛበት ቦታዎች እንደ አዲስ አበባ፤ አማራ፤ ደቡብ፤ ሌሎችም ይህን ፖሊሲ ማካሄድ ነው። ጥናቱ ቶሎ ይጀመር። ድሉ ብዙ ነው የሚሆነው።

ጥብቅ ማህበራዊ ኑሮ ለሰው ልጅ ተፈጥሮው ነው

ስለ ብቸኛ (individualist) እና ማህበራዊ (collective) ማህበረሰብ ወይንም ባህል ብዙ ተተንትኗል። የቃላቶቹ ትርጉም በጣም ጥብቅ ባይሆንም ከሞላ ጎደል ግልጽ ነው። እነ አሜሪካ እና አውሮፓ የብቸኛ ማህበረሰብ ባህል አላቸው። በርካታው ሶስተኛ ዓለም የማህበራዊ ባህል ነው ያለው። የብቸኛ ኑሮ የግል መብትና ራስን በራስ መቻል ላይ ነው የሚያተሩረው። የማህበራዊ ኑሮ የሰው ልጅ ይበልጥ ለማህበረሰቡ ህገጋት እንዲገዛ ያደርጋል እና መደጋገፍ እንዲኖር ያደርጋል። ወዘተ።

አብዛኛው ጊዜ ስለ ብቸኛ እና ማህበራዊ ባህሎች ሲተነተን ባህሪአቸው፤ ጥቅም እና ጉዳታቸው፤ በፖለቲካ እና ኤኮኖሚ ያላቸው ተፅዕኖ ወዘተ ነው የሚጠቀሰው። ሰው እንደ ርዕዮት ዓለሙ ወይንም እንደ ግል ምኞቱ ይህ ከይህ ይሻላል ይላል። የአስተሳሰብ እና ፍላጎት ጉዳይ ነው የሚደረገው። ግን በዚች ዓለም ዘመናዊነት ሁሉንም መግዛቱ ስለማይቀር በርካታ ተንታኞች ሁሉ ቦታ የብቸኛ ኑሮ እንደሚሰፍን ያምናሉ።

ግን ጥንታዊው ክርስትና እነዚህን ብቸኛ እና ማህበራዊ የምንላቸውን አኳኋን እንደ እኩል አማራጭ አያቆጥራቸውም። ክርስትና የሚለው የማህበራዊ አኗኗር የሰው ልጅ ተፈጥሮ ነው (ontological)። የሰው ልጅ ህይወት ከባለንጀራው ጋር የተቆራኘ ነው። እርስ በርስ አንድነት አለን። ከኢግዚአብሔር አንድነት (communion) አለን። በዘር፤ በትውልድ፤ በሀገር፤ ከቤተሰብ ወዘተ የወረስነው ሁሉ እራሳችን በራሳችን በምኞት እና ፍላጎት ከምንወስነው ይልቅ እጅግ ግዙፍ ነው።

ዛሬ እንደ በርካታ የሶስተኛ ዓለም ሀገራት በኢትዮጵያም የብቸኛ ኑሮ በ«ዘመናዊነት» እና «ልማት» በኩል አድርጎ እየመጣ ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/04/blog-post_13.html)። በተለይ በአዲስ አበባ እና በተወሰነ ደረጃ በትናንሽ ከተሞች ህብረተሰቡ ይህ የብቸኛ ኑሮ ተዕፅኖ እየተሰማው ነው። ሰው አይጠያየቅም፤ አይተዋወቅም፤ አይደራረስም፤ ልጆቹንም በደምብ አያገኝም፤ ባለመተዋወቅ ምክንያት ወንጀል ይበዛል፤ ፍቅር የለም፤ ከሰው ይልቅ ገንዘብ ወዳድ ሆኗል፤ ለባለንጀራው ግድ የለውም፤ አዛውንቶች አይጦሩም፤ ወዘተረፈ ደጋግሞ ሲባል ሁላችንም እንሰማለን። ጥሩ ነገር እንዳልሆነ እናውቃለን ግን እንደ መዓበል መቶብን በትክክል ምን እንደሆነም ችግሩን ለመቅረፍ ምን ማድረግ እንዳለብን አናውቅም።

በዚህ አጭር ጽሁፍ ማለት የምፈልገው «ይህን ችግር አንንቀው» ነው። ወጋችንን ብቻ ሳይሆን እንደ ሰው ልጅ ማንነታችንንም የሚያጠፋ ነገር ነው። በ«ሰለጠነው ዓለም» የብቸኛ ኑሮ ያመጣውን ልባዊ ቀውስ እያየን ነው። ኪስ ሙሉ ደስታ (እውነታዊ ደስታ) የለም። የሰው ልጅ ለብቸኝነት አልተፈጠረምና። ጠ/ሚ አቢይ ይህንን በተወሰነ ደረጃ እንደ ገባቸው አመልክተዋል። ግን እሳቸውም ሁላችንም ጠልቀን እንመርምረው። በታቻለ ሁኔታ በግል ኑሮዋችንም በመንግስት ፖሊሲም የብቸኝነት ኑሮ እንዳይሰፍን እንስራ። የህልውና ጉዳይ ነውና።

Friday 2 November 2018

When Miracles Ceased

ኢትዮጵያዊያን የምዕራብ ዓለም ወይንም የ«ፈረንጅ» ዓለም ከመሰረቱ ምን እንደሆነ ለማወቅ የመምህር ስቲፋኖስ ፍሪማን (Father Stephen Freeman) ጽሁፎችን ማንበብ ነው። ምዕራባዊ በመሆናቸው የምዕራብ ዓለም ስህተትን አበጥረው ያውቁታል። የምስራቅ ኦርቶዶክስ ካህን በመሆናቸው ናቸው እና የጥንታዊ እምነታችንን ይዘው ነው የሚያስተምሩት። አንብቧቸው!

https://blogs.ancientfaith.com/glory2godforallthings/2018/10/13/when-miracles-ceased/

Thursday 1 November 2018

ህዝባችንን «ኤክስፖርት» ማድረግ የዝቅተኝነትን መንፈስ (inferiority complex) ያዳብራል

https://addisstandard.com/news-ethiopia-overseas-employment-in-new-push-to-send-professionals-graduates-to-gulf-states/?fbclid=IwAR0AFtxLsaFDY9uxzWD8wa6Y7x27mYPh0_PpVOSpBbkOyFvxiEvoQ7e8NsE

መቼስ የዚህ የሰው ኃይል ኤክስፖርት ማድረግ ያለውን የማይጠበቁ ውጤቶችን (unintended consequences) እንደተገነዘቡ ተስፋ አየኝ። የህዝብ ተስፋውን በሀገር ሳይሆን በውጭ ማድረግ በነ ፊሊፒንስ እና ኬራላ ህዝቦች ያደረሰው የስነ ልቦና እና የራስ መተማመን ችግር መገንዘብ ይቻላል። እንደዚህ አይነቱ ነገር ህዝብን ወደ ራስን መጥላት እና የዝቅተኝነት መንፈስ ሊመራ ይችላል። የራሱን ሀገር እንዲንቅ ያደርጋል። መቼስ ይህ አይነት ፖሊሲ ለምን ለፖለቲከኞች እንደሚያስጎመዥ ይታወቃል። ችግርን ያስተነፍሳል። ግን ችግሩ ደግሞ የረዥም ጊዜ ተፀዕኖ ነው ያሚኖረው።

Ethiopia's Distorted Political Landscape

I believe that, today, the main hurdle facing Prime Minister Abiy Ahmed et al as they work on solving Ethiopia's various political problems is the imbalance between the ethnic nationalist and civic nationalist (Ethiopianist) elites. This imbalance has resulted in a distorted political landscape, a distortion which if left uncorrected, will continue to obstruct any possible progress.

What exactly is this distortion? Today, ethnic nationalist elite power and institutional power adequately reflects the level of support for ethnic nationalism among the masses. On the other hand, civic nationalist elite power and institutional power greatly under represents the level of support for civic nationalism among the masses. In simple terms, let us assume half the general population supports civic nationalism and the other half ethnic nationalism. The problem is that 80% of the political elite, in terms of political parties, power, organized influence, and institutional power, is composed of ethnic nationalists. The civic nationalist elite is running at 20%. That is, our political elite is overwhelmingly dominated by ethnic nationalists, while the general population is at worst evenly split between ethnic nationalism and civic nationalism. This political distortion is, in my opinion, the overarching problem in Ethiopian politics that continues to prevent any kind of reality-based, serious negotiations among our political elites.

While the ethnic nationalist elite hopes to use this disproportionate leverage that it has gained from over 27 years of domination to its advantage, the civic nationalist elite are too weak to respond constructively. The under represented civic nationalist masses absolutely refuse to give in to any kind of ethnic nationalist agenda. We have an impasse. Unless the 'elite distortion' is corrected, the impasse will continue and we will never be able to take solid steps towards a robust and long lasting political settlement.

Now, obviously, many would question my premise that there still is today in Ethiopian massive support for civic nationalism. Many would say that no, there is not much support for civic nationalism today in Ethiopia, and the weakness of its elite properly reflects this low support. Well, let me address this briefly. Since we do not have any polls in Ethiopia, we have to take various indicators as evidence when we make our arguments. Let us look at these indicators.

First, there is a good argument to be made that there are reasons for the weakness of the civic nationalist elite that have nothing to do with dwindling support for civic nationalism among the general population. Over the past fifty plus years, the civic nationalist elite has suffered from tremendous internal conflict - two endogenous revolutions and upheavals - the 1974 revolution and the Red Terror - and then one exogenous revolution, the 1991 revolution. The end effect of all of this was more or less the ousting of civic nationalist elites from Ethiopian political space.

Another external factor that weakened the elite was the rise of Marxism, which not only divided the Ethiopianist elite and infected it with a culture of self-mutilation, but also weakened the country with poor political and economic policies. This weakened not only the country as a whole, but also the elite, as it resulted in the masses becoming alienated from the leadership. And then add to this another factor - the fall of Marxism (Soviet Union), an event which led to the sudden and ungraceful collapse of the Dergue. And to all of this we can add another, underappreciated factor - a political culture of nearly devoid of conflict resolution. All of these factors contributed to a massive implosion of the civic nationalist elite, an implosion which had little to do with its constituency among the masses. The elite collapsed while its constituency remained more or less intact.

The subsequent 27 years of ethnic nationalist rule by the TPLF, with its sustained anti-civic nationalism propaganda and policies, can be said to have increased overall support for ethnic nationalism among the population. Again, we have no polls, but there is enough anecdotal evidence to make this argument. However, there is also evidence that this increase in ethnic nationalism is often over-estimated. Take, for example, what we can take away from the case of the 2005 elections. The civic nationalist Kinijit won an easy majority of the national vote in this election, and Kinijit together with the Hibret, a coalition of soft ethnic nationalists, won 70% of the total vote (before the rigging started). This result was quite unexpected at the time, and one reason why it was unexpected was that few thought that there remained so much support for civic nationalism. The results of the vote showed that even after 14 years (1991-2005) of TPLF propaganda against civic nationalism, civic nationalism was alive and strong.

Today, after 13 years after the 2005 election, there is more anecdotal evidence of the decline of civic nationalism support; for example, the increase in heretofore unheard of Amhara nationalism. But on the other hand, we have seen overwhelming support nation-wide for Prime Minister Abiy Ahmed and Oromia President Lemma Megersa, a large part of the support obviously stemming from their Ethiopianist rhetoric and positions. This outpouring of support for PM Abiy et al clearly shows that civic nationalism, among the masses at least, is alive and well in Ethiopia. So yes, all in all, I think it is safe to say that today, at least half of the Ethiopian population firmly support civic nationalism.

But how is this population represented among the political elite and in political and governmental institutions? The civic nationalist populace today has basically two elite representatives - Ginbot 7, and a part of the EPRDF, that represented by Abiy Ahmed, Team Lemma, et al. I argue that this representation is quite inadequate given the level of civic nationalist support among the masses.

Let us start with the EPRDF... The EPRDF was a full fledged ethnic nationalist coalition that is now being transformed from within towards civic nationalism. But transforming this decades old institution will deep rooted tentacles will take time. Ethnic nationalists are, obviously, resisting that transformation with full force. As a result, the EPRDF is yet to make a solid connection with the civic nationalist masses. Instead, it remains focused on this internal battle, the battle we are all familiar with, the battle that Abiy Ahmed and his team is currently engaged in. Now, to ensure that civic nationalism wins this battle, civic nationalists have to do two things. The first is to capture the EPRDF from within by changing minds, and the second is to capture it by, where possible joining the various EPRDF parties and basically outnumbering the ethnic nationalists and changing the power balance. As of yet, this process still at its beginning stages. So the EPRDF today cannot be said in anyway fully represent the civic nationalist population. There is a long way to go.

Ginbot 7, a brave and valiant party, basically the only civic nationalist party of any consequence, remains too small both in terms of membership and resources, to adequately represent the Ethiopianist masses. A clear illustration of this gap between the capacity of Ginbot 7 and the support for civic nationalism is the situation of Addis Ababa, where the vast majority of the city clearly supports civic nationalism, and yet there is not a single group, including Ginbot 7, which has harnessed this support into an organized and powerful political or civic force. Hence we have an Addis Ababa populace that, because it has no organized representation, feels powerless in the face of what it thinks is encirclement by ethnic nationalism. Easily over 80% of Addis Ababa's population of about five million are firm supporters of civic nationalism. How is it that such a large and resourceful population feels powerless? Because it is not organized - it is insufficiently represented among elites and institutions. Not because it is outnumbered, not because it is a minority, and not because it lacks in raw resources and capacity, but because it is unorganized, unrepresented, and incapable of mobilizing its resources. This example of Addis Ababa clearly illustrates the lack of capacity of Ginbot 7 has today.

Let us look, on the other hand, at the ethnic nationalist end of the scale. Clearly, the ethnic nationalist population has been well represented by its elites for the past 27 years. During this period, the ruling party has been ethnic nationalist, and all institutions, including the educational institutions, have been captured by ethnic nationalists in terms of numbers, propaganda, and policy. Even though today, the EPRDF is reforming towards civic nationalism, the institutional attachment to ethnic nationalism remains. Even today, ethnic nationalists in the party still hold significant power especially in Oromia and among the lower ranks. Given the size and nature of the EPRDF, it will take a long time for it to shed ethnic nationalism and then to connect with the civic nationalist population. Apart from the EPRDF, ethnic nationalist opposition parties, especially Oromo ones, are relatively well organized from top to bottom. In general, I don't think anyone would claim that the ethnic nationalist population lacks for elite representation in any way.

So there we have it, a relatively strong ethnic nationalist elite and a relatively weak civic nationalist elite. And at the same time, the division among the population at large between ethnic nationalism and civic nationalism is at most 50-50. A distorted political reality. Half the population is well represented but the other half is not.

How does this situation prevent Ethiopian politics from proceeding to a reasonable settlement? Well, given the distorted reality, elite negotiation between a strong ethnic nationalist elite and weak civic nationalist elite will result in the ethnic nationalists having the disproportionate upper hand and gaining disproportionate rewards. The result is a disgruntled and fearful civic nationalist populace whose wishes have been ignored. This populace may in the short term acquiesce, but in the long term it will either rebel or itself become ethnic nationalist, increasing the level of ethnicism in the country. In both cases the result will be catastrophic conflict.

So basically, either the civic nationalist elite organizes into a capable force or the country spirals into conflict and chaos. Yes, this is an existential issue.

Unfortunately, the task of empowering the civic nationalist elite is not an easy one. Civic nationalism cannot rely on ethnic fervor to mobilize itself as ethnic nationalists can. Instead, it will be tough slogging. Perhaps it is the knowledge that this work is tough and difficult that has led many civic nationalist elite members - including political parties and media - to simply avoid facing it, and rather spend their time raising the decibels against ethnic nationalists. Of course, avoiding the necessary tough work is no solution. What must be done must be done, as painful and hard as it must be.

From now on, the one and only priority of civic nationalists must be to strengthen the elite. Time and resources on 'opposition' activities, such as analysing, commentating on, and criticizing others' political activities and events should be minimized. Instead, all energy should be directed towards strengthening existing institutions such as Ginbot 7, creating additional political and civic institutions, mobilizing the civic nationalist population, and capturing the EPRDF.

A last word... A precondition to empowerment of the civic nationalist elite is a certain unity of thought and direction heretofore unseen among them. The culture of conflict mismanagement illustrated, for example, by the Kinijit conflict of 2005-2008, the various party conflicts of the last few years (Andinet, Medrek, etc.), the EDU internal conflicts during and after the Dergue, etc. must be ended!