Saturday 27 April 2019

ክርስቶስ ተነስቷል!



ታላቅ አባታችን ቅዱስ ዮሃንስ አፈወርቅ ወደ 1600 ዓመት በፊት በፋሲካ የሰበከው ታዋቂ ስብከት፤
እርሱ ጽኑ የእግዚአብሔር አፍቃሪ የሆነ
ለቀረበው ያማረ ድግስ በፍሰሀ ይካፈል
እርሱ ታማኝ አገልጋይ የሆነ
ወደ ጌታው ደስታ ይግባ
እርሱ በፆም ራሱን ያደከመ
በድካም ዋጋው አሁን ሃሴት ያድርግ
እርሱ ከመጀመርያው ሰአት ጅምሮ የደከመ
ዛሬ የሚገባውን ይቀበል
እርሱ ከሦስተኛው ሰአት በኋላ የመጣ
ከድግሱ በምስጋና ይካፈል
እርሱ ከስድስተኛው ሰአት በኋላ የመጣ
አይጠራጠር ምንም አያጣምና
እርሱ እስከ ዘጠነኛው ሰአት የዘገየ
አያመንታ ይቅረብ እንጂ
እርሱም በመጨረሻው በአስራሀንደኛው ሰአት የመጣ
ምንም በዘገይም እንኳን አይፍራ
ችር ለጋሽ ጌታው የመጨረሻውን ልክ እንደመጀመርያው ይቀበላልና።
በአስራአንደኛው ሰዓት የመጣውንም ከመጀመሪያው ሰዓት ጅምሮ እንደ ደከመው እኩል ያሳረፋል።
ተግባርን ይቀበላል ምኞትንም ያፀድቃል።
ሁላችሁም ግቡ እንግዲህ፤ ወደ ጌታችን ደስታ
መጀመርያ ሆነ መጨረሻ የመጣችሁ ዋጋችሁን እኩል ተቀበሉ
ሐብታምም ሆነ ደሃ ባንድነት ዘምሩ
እናንተ የፆማችሁም ሆነ ያልፆማችሁ ባንድነት ተደሰቱ
ገበታው ሞልቷል፤ ሁሉም ይብላና ይደሰት
ፍሪዳው ሰብቷል፡ ማንም ሳይጠግብ አይሂድ።
ማንም በድህነቱ አይዘን
ሁሉን አቀፍ መንግስተ ሰማያት ተገልጧልና
ማንም ስለበደሉ አማሮ አያልዝስ
የምህረት ብርሃን ከመቃብር ተነስቷልና
ማንም ሞትን አይፍራ
የመድሀኒዓለም ሞት ነፃ አውጥቶናልና።
ሞትን በሞቱ ድል ነስቷልና
ወደ ሲዖል በመውረዱ ሲዖልን አመሰቃቅሏታል
ሲዖልን በስጋ ነፍስ አጋደደ
ይህንም ነብዩ ኢሳያስ በትንቢቱ እንዲህ ብሎ ተናግሯል፡
ሲዖልም ከምድር በታች ሲያገኝህ በመራራ ነገር ቶሞላ
በመራራ ነገር ተሞላ፤ ባዶ ተደረገና
በመራራ ነገር ተሞላ፤ ተዘበበተበትና
በመራራ ነገር ተሞላ፤ ትወገደና
በመራራ ነገር ተሞላ፤ በሰንሰለት ታሰረና።
ሲዖል ስጋን አገኘሁ ብሎ እግዚአብሔርን አጋጠመው!
ምድርን ተቀበልኩ ብሎ ከገነት ጋር ተፋጠጠ!
ሞት ሆይ መርዝህ የታል?
ሲዖል ሆይ ድልህ የታል?
ክርስቶስ ተነስቷል፤ አንድተስ ሞት ሆይ ተደምሠሃል
ክርስቶስ ተነስቷል፤ ክፉዎችህም ትጥለዋል
ክርስቶስ ተነስቷል፤ መላአክትም ተደስተዋል
ክርስቶስ ተነስቷል፤ ህይወትም ነፃ ወጥቷል
ክርስቶስ ተነስቷል፤ መቃብርም ከሙታን ፀዳ
ክርስቶስ በሞት ለመነሳቱ ላንቀላፉት መባ ሆነ።
ለርሱ ይሁን ሃይል ክብርና ምስጋና ዛሬም ዘውትርም ለዘላላሙ አሜን።

The English version:

If any be a devout lover of God,
  let him partake with gladness from this fair and radiant feast.
If any be a faithful servant,
  let him enter rejoicing into the joy of his Lord.
If any have wearied himself with fasting,
  let him now enjoy his reward.
If any have laboured from the first hour,
  let him receive today his rightful due.
If any have come after the third,
  let him celebrate the feast with thankfulness.
If any have come after the sixth,
  let him not be in doubt, for he will suffer no loss.
If any have delayed until the ninth,
  let him not hesitate but draw near.
If any have arrived only at the eleventh,
  let him not be afraid because he comes so late.
For the Master is generous and accepts the last even as the first.
He gives rest to him who comes at the eleventh hour
  in the same was as him who has laboured from the first.
He accepts the deed, and commends the intention.
Enter then, all of you, into the joy of our Lord.
First and last, receive alike your reward.
Rich and poor, dance together.
You who fasted and you who have not fasted, rejoice together.
The table is fully laden: let all enjoy it.
The calf is fatted: let none go away hungry.
Let none lament his poverty;
  for the universal Kingdom is revealed.
Let none bewail his transgressions;
  for the light of forgiveness has risen from the tomb.
Let none fear death;
  for death of the Saviour has set us free.
He has destroyed death by undergoing death.
He has despoiled hell by descending into hell.
He vexed it even as it tasted of His flesh.
Isaiah foretold this when he cried:
Hell was filled with bitterness when it met Thee face to face below;
  filled with bitterness, for it was brought to nothing;
  filled with bitterness, for it was mocked;
  filled with bitterness, for it was overthrown;
  filled with bitterness, for it was put in chains.
Hell received a body, and encountered God. It received earth, and confronted heaven.
O death, where is your sting?
O hell, where is your victory?
Christ is risen! And you, o death, are annihilated!
Christ is risen! And the evil ones are cast down!
Christ is risen! And the angels rejoice!
Christ is risen! And life is liberated!
Christ is risen! And the tomb is emptied of its dead;
for Christ having risen from the dead,
is become the first-fruits of those who have fallen asleep.
To Him be Glory and Power, now and forever, and from all ages to all ages.
Amen!

Sunday 21 April 2019

ገንቢ ውይይት ከአንዷለም አራጌ ጋር

ስዩም ተሾመ በጣም ጥሩ ቃለ ምልልሶች እያረገ ነው፤ አጠያየቁንም ወድጄዋለሁ። እንግዶቹን ከነ መልእክቶቻቸው ያከብራል። የተንዛዛ ንግግሮች እንዲያደርጉ አይፈቅድም ግን መልዕክቶቻቸውን በደምብ እንዲገልጹ ይገፋፋቸዋል። በበቂም ይሟገታቸዋል  የሚናገሩትን ለማጥራት ዘንድ።

ለማንኛውም አንድ ሁለት ነጥብ ከዚህ ውይይት... በመጀመርያ አንዱእዓለም ስለ «ሃላፊነት ፖለቲካ» (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/blog-post_30.html) አስረግጦ ተናገረ። የሀገራችን ፖለቲካዊ ይሁን ሌሎች ችግሮች በዋናኝነት የህወሓት ጥፋት ሳይሆኑ የያንዳንዶቻችን ጥፋት ናቸው። በድርጊታችን ወይንም በዝምታችን እያንዳንዶቻችን ጥፋተኛ ነን። (እኔ የምለው) አልፎ ተርፎ ህወሓትንም የወለድነው እኛው ነን (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/blog-post_21.html)። ይህን ሃላፊነት ካልወሰድን መቼም ልንድን አንችልም። ትክክለኛ መልዕክት ነው።

በሁለተኛ ደረጃ አንዱእዓለም ስለ ጎሳ ፖለቲካ ሲይወራ የጎሳ ፖለቲካ አግላይ እና ዘረኛ አድርጎ ያቀረበው መሰለኝ፡፡ እወንተ ነው፤ ብዙ ጊዜ እነኝህን ባህሪአት ይንፀባርቃል፡፡ ግን ተገቢ ጥያቄዋችም እናስሜቶች አሉት። እነዚህን ተገቢ ትያቄዎችን በመጀመርያ ካልተቀበልን መወያየት አይችልም። Don't reduce ethnic nationalism to 'racism' (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/08/blog-post_6.html)፡፡ 

<<የጎሳ አስተዳደር (ethnic federalism) ዋና ችግር የግጭት መንስኤ መሆኑ ነው፡፡ ለዚህም የ28 ዓመታት ማስረጃ አለን። የቋንቋ፤ ባህል፤ አካባቢ መስተዳደር (local autonomy) ፍላጎቶች ተገቢ ናቸው ግን ከጎሳ አስተዳደር ሌላ በሆነ አስተዳደር ነው በተገቢው እና ሰላማዊ መንገድ የሚመለሱት፡፡>> መልእክታችን ይህ መሆን ያለበት ይመስለኛል፡፡ እንጂ ዘረኝነት ነው በማለት ካተኮርን የሚጠቅም አይመስለኝም፡፡

Thursday 18 April 2019

ገንቢ ትምሕርት ክሙስታፋ ምሐመድ ዑመር

ይህንን ቪዲዮ እንድትመለከቱ በትህትና እጠይቃለሁ። ሙስጠፋ መሐመድ ዑመር (የሱማሌ ክልል ም/ርዕሰ መስተዳድር)  ታላቅ የመሪ ትህምሕርት በሚገባ ቋንቋ ነው የሰጡት።

ሁለት ዋና ዋና ነጥቦች፤

፩) በፖለቲካ ፍፁምነት የለም። ፍፁም እውነት እና ፍፁም ውሸት የለም። ፖለቲካ እንደ ሃይማኖት አይደለም። የሁሉም ሃሳብ የተወሰነ እውነት ሊኖረው ይችላል። ስለዚህም የሌላውን ሃሳብ እና አቋም በደምብ መረዳት አለብን። እራሳችንን በሌሎች ቦታ አድርገን በርህራሄ ማሰብ አለብን። ምናልባት ልክ ሊሆኑ ይችላሉ ብለን ማሰብ አለብን። መገተር የለብንም። ለመስማማት መወያየት እና መደራደር አለብን። ይህን ተመልክቶ «ፖለቲካ ሃይማኖት አይድለም» (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/10/blog-post.html) የሚለውን ጽሁፍ ያንብቡ።

በተዘዋዋሪ በፖለቲካ ተደራድሮ ተስማምቶ መኖር ሲቻል በሃይማኖት ረገድ አይቻልም ብለው ሲአስረዱ በሃይማኖት ግን ተቻችሎ፤ ላለመስማማት ተስማምቶ አብሮ መኖር ይቻላል ብለዋል። ግን «ተቻችሎ» ብቻ ሳይሆን ተፋቅሮ መኖር ይቻላል። «ሃይማኖታዊ መቻቻል» (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/04/blog-post_3.html) የሚለውን ጽሁፍ ያንብቡ።

፪) ይህንን ተከትሎ ርዕዮት ዓለምን እንደ ፍፁም ማየት የለብንም። ርዕዮት ዓለም ሰው ስራሽ ነው እና ስህተቶች እንዳሉት ማወቅ አለብን። ርዕዮት ዓለምን እንደ ጣኦት ካመለክን ወደ እልቂት እናመራለን። አቶ ሙስታፋ ብዙዎቻችን «የምናመልከው» ዴሞክራሲም እንደ ጣኦት ከተቆጠረ ታላቅ አደጋ እንደሚያስከትል አስረዳ። በዚህ ዙርያ «ዴሞክራሲ» (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_8.html) የሚለውን ጽሁፍ ያንብቡ።

አልፎ ተርፎ በርዕዮት ዓለም ፍፁም እውነት ወይንም ፍፁም ስህተት የለም ስንል ይህን አባባል በኢትዮጵያ ነባራዊ የፖለቲካ ሁኔታ ስንተገብር አንዱ መደምደምያ የጎሳ ብሄርተኝነት ፍፁም ስህተት አይደለም የሚለው ይሆናል። እኔ የጎሳ ብሄርተኝነት በተለይ የጎሳ ፌደራሊዝም ባልወድም የጎሳ ብሄርተኝነት እና ፌደራሊዝም «ክፋት» ናቸው አራማጆቹም «ክፉ» ናቸው ማለት ተገቢ አይደለም። በነሱ ቦታ ሆኖ አስቦ ተቆቁሮ ነው ወደፊት መራመድ የሚቻለው። በዚህ ረገድ «ተረት ተረት፤ ጎሰኝነት ዘረኝነት ነው» (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/08/blog-post_6.html) የሚለው ጽሁፍ ይመልከቱ።

፫) በመጨረሻ የጎሰኝነትን አደጋ (ይህ የሀገር ብሄርተኝነትንም ሊመለከት ይችላል) «የኔ ጎሳ ሰዎች ንጹ የሌሎች ክፉ» አድርገን መቁጠር ምን ያህል ሃሰት እንደሆነ አቶ ሙስታፋ አስተማሩ። በኔም በሌላም ጎሳ ደጎች እና ክፉዎች እንዳሉ ለማንም ግልጽ ነው። ጥሩ እና ክፉን የሚለየው መስመር በጎሳዎች መካከል አይደለም የሚሄደው፤ በጎሳዎች ውስጥ ነው።

አቶ ሙስታፋ እዚህ ላይ አቆሙ፤ በሃሳቡ አልቀጠሉበትም። መሰረታዊው ነጥብ ይህ ነው፤ ጥሩን እና ክፉን የሚለየው መስመር የሚያልፈው በጎሳዎች መካከል ሳይሆን በያንዳንዶቻችን ልብ መሃል ነው። እነዚህን ሁለት ጽሁፎች ያንብቡ፤ https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/blog-post_21.html እና https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/blog-post_30.html

Tuesday 16 April 2019

በስመ አብ! አሁንም ምሁሮቻችን ይህን ስርዓት «multiculturalism» ይሉታል

ይህ ውይይት ገንቢ ይመስለኛል፤ ተመልከቱት። ግን አሁንም በርካታ ሰዎች የሚሳሳቱትን ስህተት ሰርተዋል። አሁን ያለውን multinational federalism (ይጎሳ አስተዳደር) "multiculturalism" ብለው ይጠሩታል። ይህ መሰረታዊ የቃል እና ሃሳብ አጠቃቅም ስህተት ነው።

የኢትዮጵያ ህገ መንግስት በዓለም ብቸኛ እና ጸንፈኛ የሚያደርገው በጎሳ፤ በ«ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች»፤ የተመሰረተ ነው። ይህ ሌላ ሀገር የለም። የጎሳ ፖለቲካ እና የጎሳ ምብት ሌሎች ሀገራት አሉ፤ ግን የህገ መንግስታቸው መሰረት አይደለም። እንደ ካናዳ፤ ህንድ፤ ወዘተ የጎሳ ፍላጎት፤ መብት፤ ጥያቄ፤ ወዘተ፤ የባህል እና ቋንቋ ብዝሃነት፤ የማንነት ምዝያነት ወዘተ ከኢትዮጵያ በተሻለ መንገድ ያስተናግዳሉ። ግን ይህን የሚያደርጉት የባህል እና እቋንቋ ብዝሃነት የሚያስተናግድ የዜግነት ህገ መንግስት ተጠቅመው ነው እንጂ ቀጥታ የጎሳ ሀገ መንግስት ተጠቅመው አይደለም።

ልዩመንት ምንድነው? የኢትዮጵያ ባለቤቶች ጎሳዎች ናቸው። ስለዚህ እንደ ቤኒሻንጉል አይነቱ ክልል ክልሉ የተወሰኑ ብሄር ተወላጆች ንብረት ነው ብለው በህግ መደንገግ ይችላሉ። የሌላ ብሄር ተወላጅ ቤኒሻንጉል ሲኖር እንደ ሁለተኛ ዜጋ ነው። የዜግነቱ መብቶች ከቤኒሻንጉል ጎሳ መቶች በታች ነው። ይህ ዜጋ መሬትና ቤት ካለው ከቤኒሻንጉል ጎሳዎች የተከራየው ነው። ወዘተ፤ ሁለተኛ ዜጋ ነው።

በነ ህንድ አይነቱ ሀገር ክፍለ ሀገሮቹ የተከለሉት ከሞላ ጎደል ጎሳን ታስቦ ነው። ስለዚህ በያንዳንዱ ክልል ብዙ ቁጥር ያለው ጎሳ የጎሳ መብቱን ያስፈጽማል። ለምሳሌ ቋንቋውን እና ባህሉን የክልሉ ቋንቋእና ባህል ያደርጋል። ወዘተ። ግን እዛ የሚኖር የማንኛውም ጎሳ ተወላጅ ሙሉ መብት አለው! ይህ ነው ልዩነቱ። «መጤ» አይደለም። የክልሉ እኩል ባለቤት ነው።

ይህ ልዩነት ውጤቱ ምንድነው? በጎሳ ፌደራሊዝም ጎሳ ከሁሉም በላይ ስለሆነ ግጭት ይበዛዋል። ይህን በኢትዮጵያ በደምብ አይተነዋል እያየነውም ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2019/03/blog-post_4.html)። የቋንቋ እና ባህል ብዝሃነት ያለው የዜግነት ፌደራሊዝም ግን ግጭት ቢኖርም ዜግነት ከሁሉም በላይ ስለሆነ ግጭቶቹ እጅግ አነስተኛ ናቸው።

ስለዚህ እንደገና... ቁንቋችንን እናስተካከል። ይህ ህገ መንግስት multiculturalism አይደለም ያመጣው። Multinationalismን ነው ያመጣው። የትም ሀገር የሌለ ጸንፈኛ experiment ነው የሚያደርገው። ይህ ሙከራ ኢትዮጵያን የግጭቶች ምህዳር አርገዋታል። አሁን የሚያስፈልገን ወደ ለዘብተኛ መንገድ ተመልሶ ወደ የቋንቋ እና የባህል ብዝሃነት ያለው በተዘዋዋሪ የጎሳ ፋልጎቶችን የሚያስተናግድ የዜግነት አስተዳደር ነው የሚያስፈልገን።


Saturday 13 April 2019

A Simple Grand Bargain

Contrary to popular opinion, the ethnic crisis in Ethiopia is not so difficult to solve, assuming good faith on the part of most stakeholders. There are actually several possible solutions, and here I shall present one simple one - the Simple Grand Bargain.

Let us assume that the parties to the bargain are 'ethnic nationalists' and 'Ethiopian nationalists'. Let's begin by describing the wants of these two political groupings in the simplest terms.

The demands of ethnic nationalists are basically as follows:

1. Acknowledgement by the Ethiopian nation of past oppression
2. A new historical narrative that takes past injustices and the rest of their narrative into account
3. Have the Ethiopian nation as a society and government adequately reflect the culture and language of their ethnic groups, given that their culture and language have been repressed in the past
4. Government policies in all spheres - economic, social, educational, etc. - and at all levels - federal, regional, etc. -  that compensate for ethnic inequalities that have resulted from past injustices
5. Ethnic federalism - A political arrangement of Ethiopia being a nation of nations, where ethnic groups have similar rights to nations within a confederation, including significant sovereignty, ownership of land, etc.

Note here the special nature of 5) - ethnic federalism.

We can say that there are two kinds of ethnic nationalists in the way they look at ethnic federalism. The first group sees ethnic federalism as a means of achieving 1) through 4). This group says that 1) through 4) cannot be achieved without ethnic federalism. Or in other words, without ethnic federalism, Ethiopian nationalists will find a political way of preventing 1) through 4).

The second group sees ethnic federalism as an end in itself. Even if 1) through 4) were achieved today to their satisfaction, they see themselves as a nation and want the country's politics to reflect that.

Now, hold on to this, and let's move on to Ethiopian nationalists. The demands of Ethiopian nationalists can be summarized as follows:

1. A political arrangement based on citizenship, so that the citizen is primary unit of the nation and has an can exercise full rights anywhere without discrimination. In other words, no second class citizenship anywhere.
2. To have basically no ethnic discrimination in government structure and policy, so that no one is favoured or disfavoured based on ethnicity. Basically no affirmative action, preferential treatement, etc.

Now, before going on to discuss how these demands can be reconciled, let's look at the current state of Ethiopian politics and why there is a need for change and a new bargain.

Obviously the first and main problem is inter-ethnic conflict. The conflict is over land, over political power, and any number of other issues which always take on an ethnic dimension and are therefore exacerbated orders of magnitude. This conflict is the single and major cause of the current political crisis in Ethiopia. All political groups and observers of all stripes in Ethiopia acknowledge this, and we know this because all periodically make references to Rwanda as a worst case scenario.

So to solve this problem - the problem of inter-ethnic conflict - we add a third dimension to the bargain. The first being the demands of ethnic nationalism, the second the demands of Ethiopian nationalism, and the third is the 'demand (requirement) for peace'. The reconciliation has to take place between these three parties - ethnic nationalists, Ethiopian nationalists, 'peace' . It is of no use if the demands of any one of these parties is ignored. If ethnic nationalist and Ethiopan nationalist elites come to an agreement on paper but there is no resulting peace, it's no good. If Ethiopian nationalist demands are not addressed but there is peace, then of course eventually conflict will arise, so that's no good either. The demands of all three dimensions have to be fulfilled.

So, what is the Simple Grand Bargain that will fulfill the demands of ethnic nationalists and Ethiopian nationalists, and produce a peaceful outcome? Here it is... The solution begins by accepting the first four demands of the ethnic nationalists. Then we accept the first demand of the Ethiopian nationalists - a citizenship based constitution. We cannot accept the second demand because it may conflict with the fourth demand of the ethnic nationalists, which may include affirmative action based on ethnicity. So it looks like this:

1. Acknowledgement by the Ethiopian nation of past oppression
2. A new historical narrative that takes past injustices and the rest of the ethnic nationalist(s) narrative into account
3. Have the Ethiopian nation as a society and government adequately reflect the culture and language of all ethnic groups, given that culture and language have been repressed in the past
4. Government policies in all spheres - economic, social, educational, etc. - and at all levels - federal, regional, etc. -  that compensate for ethnic inequalities that have resulted from past injustices
5. A political arrangement based on citizenship, so that the citizen is primary unit of the nation and has an can exercise full rights anywhere without discrimination. In other words, no second class citizenship anywhere.

This arrangement fulfills nearly all the demands of ethnic nationalists, except for ethnic federalism, which as I noted above is for many just a means of achieving 1) through 4). But anyway, as I argued above, ethnic federalism is by nature a source of conflict, this has been evidenced over the past 28 years, including the past year during a time of relative freedom, so one cannot achieve any sort of peace under ethnic federalism. So as long as peace is our primary goal, only demands 1) through 4) of ethnic nationalists can be met.

As far as Ethiopian nationalists are concerned, their main demand is a citizenship-based constitution that guarantees equal citizenship rights to everyone living anywhere in Ethiopia. This Simple Grand Bargain fulfills this requirement. Yes, many Ethiopian nationalists may not agree to ethnic nationalists' demands 1) through 4), but if they get in exchange a citizenship based political arrangement, I am certain most would take it in a heartbeat.

So this is a Simple Grand Bargain. Any takers?!

Thursday 11 April 2019

የምኞት ፖለቲካ ሲቀጥል...

የኢሳት የኤላታዊ ተንታኞች ምኞጣጨው ጥሩ ነው፤ የጎሳ ጥላቻ በሀገራችን ያመጣው አደጋ እንዲቀረፍ ወደ ርዋንዳ መስመር ከመግባታችን በፊት። የባህል እና ቋንቋ ብዙሃነት ያለበት ግን የጎሳ አስተዳደር እና ፖለቲካ የሌለበት ሀገር ነው ምኞታቸው። ጥሩ ምኞት ነው፤ የኔም የብዙዎቻችን ነው።

ግን «ጠ/ሚ አቢይ፤ ጎሰኞቹን በአዋጅ አግታቸው፤ የመንግስት መዋቅርን በሹመት ተቆጣጠር፤ የክልል ጦሮችን በአዋጅ ህገ ወጥ አድርግ፤ ወዘተ» በማለት ይህ ምኞት ሊፈጸም አይችልም። የሀገራችን የፖለቲካ ነባራዊ ሁኔታ ይህን አይፈቅድም። የጎሳ ብሄርተኛ ጎራው የ«ፖለቲካ ኃይል» አለው። ይህ ጎራ የተዋቀረ እና የተቀነባበረ ኃይል፤ በመንግስት መዋቅሮች የተሰገሰገ ኃይል፤ የገንዘብ ኃይል፤ ወዘተ ኃይል አለው። ጠ/ሚ ዓቢይ የእለታዊ ተንታኞች የሰቡትን እርምጃዎች ልውሰድ ካለ የጎሳ ብሄርተኛው ጎራ ቀውስ ያስነሳል። ጠ/ሚ ዓቢይ እንደዚህ አይነት እርምጃዎች ከመውሰዳቸው በፊት በስልት እና ዘዴ የጎሳ ብሄርተኛውን ኃይል ማድከም አለበት። አለበለዛ ነባራዊ ሁኔታን የማይመጥን እርምጃ ይሆናል እና ሁኔታውን ያባብሳል።

የጎሳ ብሄርተኛ ጎራውን ከማድከም እና ማከፋፈል አልፎ ሌላ ዋና እርምጃ ያስፈልጋል፤ ይህ የ«መሃል ፖለቲካው» ወይንም የዜግነት ፖለቲካ ጎራው እጥፍ ድርብ መጠንከር አለበት። ይህ ጎራ መዋቅር፤ ቅንብር፤ የገንዘብ፤ የመንግስት መዋቅር ከውስጥ በኔትወርክ መአስር ኃይል ሊኖረው ይገባል። የዜግነት ፖለቲካ ጎራው እንደዚህ አይነት «የፖለቲካ ኃይል» ሲኖረው የጎሳ ፖለቲካን ለመቀነስ የሚወሰዱ እርምጃዎች ሲወሰዱ የጎሳ ብሄርተኞች የሚነሳውን ሁከቶች መቋቋም ይቻላል። የጠ/ሚ ዓቢይ መንግስት በጎሳ ብሄርተኞች ሲጫን የዜግነት ጎራው ይደፍገዋል። ቀደም ተከተሉ እንዲህ ነው መሆን ያለበት።

ግን አሁን የዜግነት ፖለቲካ ጎራው ገና በቂ አልተደራጀም። ለዚህ ነው የጠ/ሚ ዓቢይ መንግስት አሁንም ከባድ ሁኔታ ውስጥ ያለው። ለዚህ ነው «ከባድ እርምጃ ውሰድ» የሚለው ሃሳብ አጉል ምኞት የሆነው። መጀመርያ የዜግነት ፖለቲካ ጎራው ማለትም «መሃሉ» ጠንክሮ መገኝነት አለበት የጎሳ ብሄርተኞቹን ጫና ለመቋቋም።

ስለዚህ የእለታዊ ተንጣኞች በሙሉ ኃይላቸው ይህ የዜግነት ፖለቲካ ጎራ መደራጀት እና መጠንከር ዋና ተልዕኮአቸው ማድረግ አለባቸው። ለሀገራችን ሰላም ቀድመ ሁኔታ ነው። ማለት ይህ ካልሆነ ምንም አይነት የፖለቲካ መሻሻል ሊመጣ አይችልም።

Wednesday 10 April 2019

"Make A Wish" Politics

RE: Ethiopia: A Country On The Brink (http://www.ethioreference.com/archives/17240), by Dawit Woldegiorgis.

With respect - and Dawit Woldegiorgis and I are on the same side of course - I cannot fathom how anyone with the least knowledge of politics can consider a transitional government without an opposition to speak of. For me, Ato Dawit's article is a continuation of 27 years of those opposing the TPLF complaining and discussing wild ideas without presenting a viable alternative. Viable.

Today, the only opposition with any real power are the ethnic nationalists (e.g. Qerro). The Ethiopianist opposition has no strong organization and little power. It has little ability to influence, exert soft or hard power, raise funds, mobilize masses, mobilize the elite, enforce its will within government institutions, etc. This weakness of the Ethiopianist political segment is, by the way, the main source of our political problems. PM Abiy Ahmed has to be careful in handling the ethnic nationalists, but he has no Ethiopianist organization to buttress him from the other side. Yes, G7, Addis Ababa,  and others are working on creating strong Ethiopianist organizations, but we are still a long way off. Maybe some months or a year from now, things will be different. But for now, the ethnicists have the upper hand - by far.

A transitional government by definition has to reflect political power, otherwise it cannot govern and enforce its edicts. If for example the EPRDF decides to create a transitional government with equal representation from the ethnic nationalists and the Ethiopianists, the ethnic nationalists can throw a fit and create real, tangible problems, from street riots to using their influence within current government structures to sabotage the transitional government. The Ethiopianist opposition, on the other hand, has no tangible way in which to express it's displeasure. It has no tangible way to project its power. Maybe more articles from the likes of Dawit and me is all it can do. Maybe a street protest that will easily be quashed, as we have little power inside government institutions to prevent this.

This is, by the way, the reason why Ethiopianists and the Amhara, who at the time were all Ethiopianists, were not represented in the transitional government of 1991. We had no real power! In the face of being excluded, we could do nothing except, again complain and write articles. Dawit Woldegiorgis, who was around at that time, ought to remember this well.

Both Ato Dawit's proposals - that Abiy resign and be replaced by someone who will not acquiesce to ethnic nationalists, and that Abiy form a transitional government - assume the existence of an Ethiopianist political segment with real power. Such an Ethiopianist organization does not exist. This is reality. So all the focus should be on strengthening Ethiopianist political institutions. Parties, civic organizations, etc. We need money, people, influence, people within government structures, etc. When this work is completed, then any option, a transitional government or Abiy himself, will have a good outcome.

Tuesday 2 April 2019

የጎሳ ፖለቲካ በዋናነት ስሜታዊ ስለሆነ ለመቀልበስ ታላቅ ስልታማነት ይጠይዎል

ጉዳዩ የሀሳብ ሳይሆን የሰሜት ሰለሆነ logic ውስን ሚና ነው የሚጮወተው። ከባድ ስልት የሚጠይቀው ለዚህ ነው። When Quebecers were voting on whether to secede from Canada, polls showed that after secession, most expected that they would retain their Canadian passports and all other benefits of Canadian citizenship while at the same time having their own separate country! Ethnic nationalist politicians sell their audience a bill of goods and their audience, raptured with emotion, swallow it whole. That's why enormous tact is required in the struggle against ethnic nationalism and for multiculturalism. Appealing to logic and self-interest alone will not do it. A multi-pronged approach is needed.

Monday 1 April 2019

የህፃንነት ፖለቲካ

ላለፉ 50 ዓመታት፤ ከደርግ አቢዮት ጀምሮ የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ጎራው በህፃንነት የፖለቲካ አስትሳሰብ ተለክፏል። ተመልከቱ...

በአንድ በኩል ኃይል ያለው የጎሰኛ ጎራ አለ። ኃይል ማለት ኃይለ ቃል አይደለም አንዳንዶች ሁለቱ አንድ ይመስላቸዋልና። «ከተሳደብኩኝ ተሟገትኩኝ» ብሎ የሚያስብ አለ እንጂ። ኃይል ማለት ጎሰኛው በየ መንግስት መዋቅሩ ተሰግስጓል። ገንዘብ አለው። ሚዲያ አለው። መዋቅሮች አለው። ጦር አለው። አካላዊ እና ንብረታዊ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል። ፍላጎቱን በተለያየ መንገዶች ሊያስፈጽም ይችላል። መንግስት ውስጥ የተሰገሰገው በዛ አቅሙ ይጠቀማል። ጦር ያለው በሱ ይጠቀማል። ሚዲያው እንዲሁ። «ኃይል» ማለት ይህ ነው። ጎሰኛው ተጨባጭ (tangible) ኃይል አለው።

የኢትዮጵያ ብሄርተኛ ወይን አንድነት ጎራው ይህ ነው የሚባል ተጨባጭ ኃይል የለውም። መንግስት መስሪያቤት ውስጥ ያለው ቁጥሩ ትንሽ ነው መንግስት የኢህአዴግ ስለሆነ። ጦር የለውም። ሚዲያው ደካማ ነው። ምንም መዋቅር የለውም። ገና እየተደራጁ ያሉ እነ ግንቦት 7 እና ባልደራስ ነው ያሉት። ሌላ ነገር የለም። ሰለዚህ ይህ ጎራ ፍላጎቱን ለማስፈጸም አቅም የለውም። የራሱን መከላከልም አቅም የለውም። መዋቅር እና ኔትወርክ አልዘረጋም። ከሞላ ጎደል ኃይሉ እጅግ አነስተኛ ነው። አልፎ ተርፎ ይህ ጎራ ዋናው hobbyው እርስ በርስ መጠላለፍ እና መጣላት ነው።

ይህ እንደሆን እነ ጠ/ሚ ዓቢይ የሚፈሩት ማንን ነው፤ ጎሰኛውን ነው የኢትዮጵያ ብሄርተኛው? ጎሰኛውን ነው። ገጀራን ዝም ብለው ባልደራስን የሚተቹት ለምንድነው? ባለ ገጀራው ኃይል አለው ባልደራስ የለውም። ግልጽ ነው።

በዚህ ሁኔታ ጠ/ሚ ዓቢይ ላይ መውረድ ምን ዋጋ አለው?! ቢፈልግም ገጀራውን ዝም ብሎ መደምሰስ አይችልም። በዘዴ መሆን አለበት፤ ጊዜ ይፈጃል። እያሳሳቀ ነው ሊያጠፋው የሚችለው። አንዳንዶች እንደሚሉት ከባለ ገጀሮቹ አንዱ ከሆነ ጠ/ሚ ዓቢይ መነጫነጫችን ዋጋ የለውም ማለት ነው።

መፍትሄው አንድ ብቸኛው ነው፤ የአንድነት ኃይሉ «ኃይል» ማጠራቀም አለበት። ከባለ ገጀራው እጥፍ ኃይል ከሌላው ዋጋ የለውም። ይህን ኃይል እስኪያጠራቅም ደግሞ ወደ ጸብ መግባት የለበትም፤ ይህ ቀላል የፖለቲካ ስልት ነው። አንገት ደፍቶ ሁሉንም እንደ አጋር አስመስሎ የኃይል ማጠራቅም ስራውን መስራት አለበት። እንጂ ገና ምንም ኃይል ሳይኖረው ሌሎችን አምበረግጋለሁ ማለት እራስን መጥለፍ ማለት ነው።

ስለዚህ ጠ/ሚ ዓቢይ ላይ የምትወርዱበት፤ ጩሀታችሁ ዋጋ የልውም፤ ጭራሽ ዋጋ ያስከፍላል። እኛ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ተጨባጭ ኃይል እስኪኖረን እሱ ላይ መጮህ፤ እርስ በርስ ጸጉር መሰንጠቅ ዋጋ የለውም። መጀመርያ ተደራጅተን መዋቅሮች እና ኔትዎርኮች ዘርግተን ከዛ ብኋላ ወደ ሙግት።

(ለምን «ባለ ገጀራ» የሚለውን አሉታዊ አነጋገር ተጠቀምኩኝ? የዚህ ጽሁፍ audience የጎሳ ብሄርተኞች ላይ ኃይለ ቃል የሚጠቀሙ የአንድነት ሰዎች ናቸው። ለአንባቢው የሚመች ቃላቶችን ተጠቀምኩኝ። እነ ለማ መገርሳ ለርዥም ዓመታት «ኦነግ በሽፋን» የሆነውን የኦህዴድ ካድሬዎችን ሲያነጋግሩም እንዲሁ ብትረዷቸው ጥሩ ይመስለኛል።)

የቅንጅት ታሪክ ሊደገም ነው?

ታሪኩን ለማታስታውሱ ወጣቶች፤ የቅንጅት «ፓርቲ» አመራሮች ከእስር ቤት ከወጡ በኋላ ኃይለኛ የእርስ በርስ የፖለቲካ ጦርነት አካሄዱ። ዋና አቋሞቻቸው አንድ ነበር፤ የኢህአዴግ/ህወሓት አምባገነን አገዛዝን ማስቆም እና «ዴሞክራሲ» እና የዜግነት ፖለቲካን ማምጣት። እንደዚህ አይነት ግዙፍ እና ዋና ጉዳዮች ላይ የሚጋሩ ቢሆንም ሁለቱ የቅንጅት ወገኖች አብሮ ለመስራት አልፈለጉም፤ መጨራረስን መረጡ። ጥላቸው እየከረረ ሲሄድ እርስ በርስ ያላቸው ጥላቻ ለኢህአዴግ ካላቸው ጥላቻ በልጦ ተገኘ! የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት እና ዴሞክራሲ ትግል እንደገና ፈራረሰ ተበታተነም (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_21.html)።

ዛሬም ይህን ታሪክ ካልደገምን እያልን ይመስላል። የኢትዮጵያ ብሄርተኛ ነኝ፤ የዜግነት ፖለቲካ ደጋፊ ነኝ፤ ዴሞክራሲን እደግፋለሁ፤ ጎሰኝነት ይውደም፤ የምን ሆነን እነዚህ የጋራ ፍላጎት እና ጥቅማችን አብሮ በመስራት ከማስከበር ፋንታ በትናንሽ የሚለያዩን ጉዳዮች እንፋለማለን!! የጉድ ጉድ ነው። ይህ ሁሉ የምንጋራው ዋና ነገሮች እያሉ እንጣላለን። ምን ማለት ነው?

ለምሳሌ ግንቦት 7ን መሳደብ። አዴፓን መሳደብ። የእስክንር ነጋን ንቅናቄ ማጥላላት። ምን ማለት ነው? በሰለጠነ ፖለቲካ እነዚህ ሁሉ ጠንካራ አጋሮች መሆን ይኖርባቸው ነበር። ትናንሽ የታክቲች እና ስትራቴጂ ልዩነቶች አላቸው። በመነጋገር እና መናበብ እርስ በርስ መጠቃቀም እና መደጋገር ይችላሉ። ለነገሩ የበሰለ አብንም እንዲሁ የዜግነት ፖለቲካ ነው የምፈልገው ሰለሚል። ግን የለም። 100% ካልተስማማን ወይንም የግል ጸብ ካለን ከምንተባበር ኦነግ ቢያሸንፍ ይሻላል ነው አመለካከታችን።

የቅንጅት እርስ በርስ ጦርነት እንደ ባቡር ግጭት ለረዥም ጊዜ እንደሚከሰት እያየን ምንም ማረግ ሳንችል የተከሰተ እልቂት ነበር። አሁንም ይህ ባቡር ይተየኛል፤ የግጭት ጉዞውን ጀምሯል።