Showing posts with label ethnic federalism. Show all posts
Showing posts with label ethnic federalism. Show all posts

Sunday, 21 April 2019

ገንቢ ውይይት ከአንዷለም አራጌ ጋር

ስዩም ተሾመ በጣም ጥሩ ቃለ ምልልሶች እያረገ ነው፤ አጠያየቁንም ወድጄዋለሁ። እንግዶቹን ከነ መልእክቶቻቸው ያከብራል። የተንዛዛ ንግግሮች እንዲያደርጉ አይፈቅድም ግን መልዕክቶቻቸውን በደምብ እንዲገልጹ ይገፋፋቸዋል። በበቂም ይሟገታቸዋል  የሚናገሩትን ለማጥራት ዘንድ።

ለማንኛውም አንድ ሁለት ነጥብ ከዚህ ውይይት... በመጀመርያ አንዱእዓለም ስለ «ሃላፊነት ፖለቲካ» (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/blog-post_30.html) አስረግጦ ተናገረ። የሀገራችን ፖለቲካዊ ይሁን ሌሎች ችግሮች በዋናኝነት የህወሓት ጥፋት ሳይሆኑ የያንዳንዶቻችን ጥፋት ናቸው። በድርጊታችን ወይንም በዝምታችን እያንዳንዶቻችን ጥፋተኛ ነን። (እኔ የምለው) አልፎ ተርፎ ህወሓትንም የወለድነው እኛው ነን (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/blog-post_21.html)። ይህን ሃላፊነት ካልወሰድን መቼም ልንድን አንችልም። ትክክለኛ መልዕክት ነው።

በሁለተኛ ደረጃ አንዱእዓለም ስለ ጎሳ ፖለቲካ ሲይወራ የጎሳ ፖለቲካ አግላይ እና ዘረኛ አድርጎ ያቀረበው መሰለኝ፡፡ እወንተ ነው፤ ብዙ ጊዜ እነኝህን ባህሪአት ይንፀባርቃል፡፡ ግን ተገቢ ጥያቄዋችም እናስሜቶች አሉት። እነዚህን ተገቢ ትያቄዎችን በመጀመርያ ካልተቀበልን መወያየት አይችልም። Don't reduce ethnic nationalism to 'racism' (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/08/blog-post_6.html)፡፡ 

<<የጎሳ አስተዳደር (ethnic federalism) ዋና ችግር የግጭት መንስኤ መሆኑ ነው፡፡ ለዚህም የ28 ዓመታት ማስረጃ አለን። የቋንቋ፤ ባህል፤ አካባቢ መስተዳደር (local autonomy) ፍላጎቶች ተገቢ ናቸው ግን ከጎሳ አስተዳደር ሌላ በሆነ አስተዳደር ነው በተገቢው እና ሰላማዊ መንገድ የሚመለሱት፡፡>> መልእክታችን ይህ መሆን ያለበት ይመስለኛል፡፡ እንጂ ዘረኝነት ነው በማለት ካተኮርን የሚጠቅም አይመስለኝም፡፡

Saturday, 13 April 2019

A Simple Grand Bargain

Contrary to popular opinion, the ethnic crisis in Ethiopia is not so difficult to solve, assuming good faith on the part of most stakeholders. There are actually several possible solutions, and here I shall present one simple one - the Simple Grand Bargain.

Let us assume that the parties to the bargain are 'ethnic nationalists' and 'Ethiopian nationalists'. Let's begin by describing the wants of these two political groupings in the simplest terms.

The demands of ethnic nationalists are basically as follows:

1. Acknowledgement by the Ethiopian nation of past oppression
2. A new historical narrative that takes past injustices and the rest of their narrative into account
3. Have the Ethiopian nation as a society and government adequately reflect the culture and language of their ethnic groups, given that their culture and language have been repressed in the past
4. Government policies in all spheres - economic, social, educational, etc. - and at all levels - federal, regional, etc. -  that compensate for ethnic inequalities that have resulted from past injustices
5. Ethnic federalism - A political arrangement of Ethiopia being a nation of nations, where ethnic groups have similar rights to nations within a confederation, including significant sovereignty, ownership of land, etc.

Note here the special nature of 5) - ethnic federalism.

We can say that there are two kinds of ethnic nationalists in the way they look at ethnic federalism. The first group sees ethnic federalism as a means of achieving 1) through 4). This group says that 1) through 4) cannot be achieved without ethnic federalism. Or in other words, without ethnic federalism, Ethiopian nationalists will find a political way of preventing 1) through 4).

The second group sees ethnic federalism as an end in itself. Even if 1) through 4) were achieved today to their satisfaction, they see themselves as a nation and want the country's politics to reflect that.

Now, hold on to this, and let's move on to Ethiopian nationalists. The demands of Ethiopian nationalists can be summarized as follows:

1. A political arrangement based on citizenship, so that the citizen is primary unit of the nation and has an can exercise full rights anywhere without discrimination. In other words, no second class citizenship anywhere.
2. To have basically no ethnic discrimination in government structure and policy, so that no one is favoured or disfavoured based on ethnicity. Basically no affirmative action, preferential treatement, etc.

Now, before going on to discuss how these demands can be reconciled, let's look at the current state of Ethiopian politics and why there is a need for change and a new bargain.

Obviously the first and main problem is inter-ethnic conflict. The conflict is over land, over political power, and any number of other issues which always take on an ethnic dimension and are therefore exacerbated orders of magnitude. This conflict is the single and major cause of the current political crisis in Ethiopia. All political groups and observers of all stripes in Ethiopia acknowledge this, and we know this because all periodically make references to Rwanda as a worst case scenario.

So to solve this problem - the problem of inter-ethnic conflict - we add a third dimension to the bargain. The first being the demands of ethnic nationalism, the second the demands of Ethiopian nationalism, and the third is the 'demand (requirement) for peace'. The reconciliation has to take place between these three parties - ethnic nationalists, Ethiopian nationalists, 'peace' . It is of no use if the demands of any one of these parties is ignored. If ethnic nationalist and Ethiopan nationalist elites come to an agreement on paper but there is no resulting peace, it's no good. If Ethiopian nationalist demands are not addressed but there is peace, then of course eventually conflict will arise, so that's no good either. The demands of all three dimensions have to be fulfilled.

So, what is the Simple Grand Bargain that will fulfill the demands of ethnic nationalists and Ethiopian nationalists, and produce a peaceful outcome? Here it is... The solution begins by accepting the first four demands of the ethnic nationalists. Then we accept the first demand of the Ethiopian nationalists - a citizenship based constitution. We cannot accept the second demand because it may conflict with the fourth demand of the ethnic nationalists, which may include affirmative action based on ethnicity. So it looks like this:

1. Acknowledgement by the Ethiopian nation of past oppression
2. A new historical narrative that takes past injustices and the rest of the ethnic nationalist(s) narrative into account
3. Have the Ethiopian nation as a society and government adequately reflect the culture and language of all ethnic groups, given that culture and language have been repressed in the past
4. Government policies in all spheres - economic, social, educational, etc. - and at all levels - federal, regional, etc. -  that compensate for ethnic inequalities that have resulted from past injustices
5. A political arrangement based on citizenship, so that the citizen is primary unit of the nation and has an can exercise full rights anywhere without discrimination. In other words, no second class citizenship anywhere.

This arrangement fulfills nearly all the demands of ethnic nationalists, except for ethnic federalism, which as I noted above is for many just a means of achieving 1) through 4). But anyway, as I argued above, ethnic federalism is by nature a source of conflict, this has been evidenced over the past 28 years, including the past year during a time of relative freedom, so one cannot achieve any sort of peace under ethnic federalism. So as long as peace is our primary goal, only demands 1) through 4) of ethnic nationalists can be met.

As far as Ethiopian nationalists are concerned, their main demand is a citizenship-based constitution that guarantees equal citizenship rights to everyone living anywhere in Ethiopia. This Simple Grand Bargain fulfills this requirement. Yes, many Ethiopian nationalists may not agree to ethnic nationalists' demands 1) through 4), but if they get in exchange a citizenship based political arrangement, I am certain most would take it in a heartbeat.

So this is a Simple Grand Bargain. Any takers?!

Sunday, 10 March 2019

ለማ መገርሳ ልክ ነው፤ የዴሞግራፊ ለውጥ ግድ ነው

ከዚህ በፊት እንደጻፍኩት የጎሳ ብሄርተኝነትን ከፖለቲካችን ለመቀነስ እና ለማጥፋት የዴሞግራፊ ለውጦች ማምጣት ግድ ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/curbing-ethnic-nationalism-via_26.html)። ምከንያቱ ባጭሩ እንዲህ ነው...

የጎሳ ብሄርተኝነት ህዝብ ውስጥ በተለይ የኦሮሞ ህዝብ ውስጥ በደምብ እንደገባ ሁላችንም ገብቶናል። በልሂቃን ደረጃ ብቻ ሳይሆን በብዙሃን ደረጃም። ይህን ጎሰኝነት በስብከት እና ልመና ማጥፋት አይቻልም። የተም ሀገር የጎሳ ብሄርተንኘት አንዴ ከሰፈነ የሚቅንሰው ነገር ፖለቲካዊ ድርድር ሳይሆን የዴሞግራፊያዊ ለውጥ ብቻ ነው። በኢትዮጵያ የሚያስፈልገው የዴሞግራፊ ለውጥ በኦሮሞ እና ሌላው ኢትዮጵያዊ መካከል መቅላቀል እና ውህደት (integration and assimilation) ነው። ህዝቡ ተቀላቅሎ ተጋብቶ ተዋልዶ የቅይጥ ባህል እና ህዝብ መጨመር አለበት። በዚህ መንገድ የጎሳ ብሄርተኛው ጎራ እያነሰ ይሄዳል የፖለቲካ ኃይሉም ይመነምናል። ይህን የሚያስፈጽም አንድ ፖሊሲ ኦሮምኛ የህገር ሙሉ ቋንቋ ማድረግ ነው። ይህ ኦሮሞዎች ከኦሮሚያ ወደ ሌላው ኢትዮጵያ እንዲፈልሱ ይጋብዛል። ለምሳሌ ኦሮምኛ ለማስተማር ወደ አማራ ክልል ይመጣሉ። ይህ ፈልስት መቀላቀልን እና መወሃድን ያመጣል። ከላይ የጠቀስኩት ጽሁፍ ባጭሩ ይህን ነው የሚለው።

በቅርቡ ለማ መገርሳ ስለኦሮሞ ህዝብ ወደ ከተማ መፍለስ እናለበት ያሉት ነገር ከዚህ ጋር አብሮ ይሄዳል። ለምሳሌ አዲስ አበባ ዙርያ የሚኖረው ባብዛኛው ኦሮሞ ነው። አዲስ አበባ ባደገች ቁጥር በሜትሮፖሊታን ከተማው ያለው የኦሮሞ ህዝብ ቁጥር እየጨመረ መሄዱ አይቀርም። ከላይ በጻፍኩት አንጻር ይህ የኦሮሞ ህዝብ በአዲስ አበባ መብዛት አይቀሬም ብቻ ሳይሆን እንደ ጥሩ ነገር ነው መታየት ያለበት። ከተማው ህዝቡን ይቀላቅለዋል እና ያዋህደዋል። ይህ ውህደት የጎሳ ብሄርተኝነትን ይቀንሳል። ስለዚህ ኦሮሞዎችን ወደ አዲስ አበባ እና ሌሎች ከተሞች እንዲፈልሱ ያለው የኦዴፓ እቅድ ጥሩ ነው ማለት ይቻላል።

አሁን ከኛ ከኢትዮጵያ ብሄርተኞች ጎራ የሚጠበቀው ይህ እቅድ በምንፈልገው በአውንታዊ መስመር እንዲካሄድ ነው። «የጎሳ ጌቶዎች» ወይንም የአንድ ጎሳ ሰፈሮች እንዳይፈጠሩ፤ እውነታዊ ውህደት እንዲኖር፤ ሌላው ህብረተሰብ ኦሮምኛ እንዲማር፤ አድሎዋዊነት እንዳይኖር፤ ወዘተ መስራት አለብን። ሌላው ከኛ የሚጠበቀው ነገር የኦሮሞዎች መብት እና ፍላጎት በአዲስ አበባ እንደሚከበረው የሌሎች ዜጎች መብት እና ፍላጎት በኦሮሚያ እንዲከበር መሟገት እና ማስፈጸም ነው። አልፎ ተርፎ ኦሮሙማ (የኦሮሞ ባህል) በአዲስ አበባ እና መላው ኢትዮጵያ እንዲንጸባረቅ በመስማማት in exchange የጎሳ ፌደራሊዝም ሀገ መንግስቱ እንዲቀየር መሟገት እና መደራደር አለብን። ይህን ለማድረግ ታላቅ አቅም እና መደራጀት ይጠበቅብናል።

ነገሮችን ሁሉ በአውንታዊ መልኩ እንደ opportunity ማየት የአሸናፊነት ምልክት ነው። ኦዴፓ ኦሮሞን ወደ አዲስ አበባ እንዲሄድ እናበረታታለን ሲል እኛ እሰየው ብለን በሂደቱ ተሳትፈን እኛ የምንፈልገው መልክ እንዲይዝ ማድረግ አለብን። ከውጭ እያየን በፍርሃት ከማልቀስ ጉዳይ ውስጥ ገብተን መምራት ነው ያለብን።

ስለዚህ ለማ መገርሳ ልክ ነው፤ የዴሞግራፊ ለውጥ ግድ ነው። በዚህ መንገግድ ብቻ ነው መቀላቀል እና መዋሃድ የሚመጣው። በዚህ መንገድ ብቻ ነው አሁን በህብረተሰባችን የሰፈነው ጎሰኝነት ከረዥም ዓመታት በኋላ እንዲቀንስ እና እንዲጠፋ ማድረግ የሚቻለው።

Monday, 4 March 2019

የጎሳ ፌደራሊዝም ችግር አንድ ነው፤ የግጭት መንስኤ ነው!

ዛሬ አንድ ሁለት ውይይቶች ስለ ሀገራችን «የጎሳ ፌደራሊዝም» ተመልክቼ ነበር። ውይይቶቹ ያተኮሩት በጎሳ ፌደራሊዝም እንደ ጽንሰ ሃሳብ ነው። ተናጋሪዎቹ ታሪክን እና ርዕዮት ዓለምን ፈትሸው የጎሳ ፌደራሊዝም ለሀገራችን ይበጃል ወይንም አይበጅም ብለው ተከራከሩ። Of course ውይይት/ክርክሩ የትም አልደረስም። The participants, as usual, talked right past each other።

በመጀመርያ ደረጃ አንዱ የሌላውን ፍላጎት የማይረዳበት ውይይት ውይይት አይደለም። ስለ ጎሳ ፌደራሊዝም የሉን ውይይቶች እንዲህ ናቸው። እኛ አቋማችንን እንናገራለን ሌላውም እንዲሁ አንድ ሌላው አይገባውም ውይይቱም ባለመግባባት ያልቃል።

ይህ የሚሆንበት አንዱ ምክንያት የውይይት እና ቅራኔ መፍታት ስልት በማጣት ነው። ግን አሁን ማተኮር የምፈልገው እዚህ ላይ አይደለም። ሁለተኛው ምክንያት ነው፤ ይህ ደግሞ የጎሳ እና ማንነት ጉዳይ ስሜታዊ በመሆኑ ለውይይት አይመችም። አይሆምም ማለት ይቻላል። «እኔ መጀመርያ ኦሮሞ ነኝ ቀጥሎ (ምናልትባት) ኢትዮጵያዊ» ሲል አንዱ ሌላው «እንዴት እንዲህ ትላለህ» ብሎ ሁለቱም በስሜታቸው ይመራሉ። አንዱ ሌላውም ማሳመን አይችልም።

ለዚህ ነው በጎሳ ፌደራሊዝም ጉዳይ ታሪክን እና ርዕዮት ዓለምን ፈትሸን መከራከር የትም የማያደርሰን። በጎሳ ፌደራሊዝም የሚያምን እና የጎሳ ፌደራሊዝምን የሚጠላው ሁለቱም ምክንያቶች በመሰረቱ ስሜታዊ የማንነት ናቸው። እነዚህን በርዕዮት ዓለም እና ታሪክ (in the eye of the beholder) ማስታረቅ አይቻልም።

ሁለቱን ጎራዎች ለማግባበት ወደ ሌላ level መሄድ ያስፈልጋል። ይህ ደረጃ እንዲህ ነው፤ እኔ የጎሳ ፌደራሊዝም ለኢትዮጵያ አይሆንም የምልበት ምክንያት ታሪክ እና ርዕዮት ዓለም ሳይሆን በ evidence ምክንያት ነው። የ24 ዓመት ታሪክ ከነ ያለፈው አንድ ዓመት የለውጥ ዘመን ታሪክ የሚያሳየው የጎሳ ፌደራሊዝም የግጭት መንስኤ መሆኑ ነው። የጎሳ ፌደራሊዝም በጎሳዎች መካከል በርካታ ግጭቶች እንዲኖሩ አድርጓል። ሰዎች በጎሳቸው ምክንያት የሚጎዱበት ዘመን አምጥቷል። ይህ ጉዳት ለተወሰኑ ጎሳዎች ብቻ ሳይሆን በመላው ሀገሩ ነው። ለዚህ በርካታ የ25 ዓመት evidence አለ።

ለዚህ ነው የጎሳ ፌደራሊዝም መቀየር አለበት ብለን መከራከር ያለብን። የ24 ዓመት የጭቆና እና የአንድ ዓመት የአንጻራዊ ነጻነት መረጃ የሚያሳየን የጎሳ ፌደራሊዝም ህግ እና መንፈስ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎቻችንን እንደጎዳ ነው። ሶማሌ በሶማሌነቱ፤ ኦሮሞ በኦሮሞነቱ፤ ጊዴኦ በጊዴኦነቱ፤ አማራ በአማራነቱ፤ አንዋክ በአንዋክነቱ፤ ወላይታ በወላይታነቱ፤ ስዳማ በሲዳማነቱ፤ ወዘተ ተጎድቷል። የጉዳት ፈጻሚዎቹም እንዲሁ የተለያዩ ናቸው። «ህወሓት» ወይንም የህወሓት አሽከሮች ብቻ አይደሉም ጨቋኞቹ። ህዝቡ እራሱ ይጭቋቆናል። ለዚህ በርካታ መረጃ አለን።

አንድ ታካቅ መራጀ ደግሞ የሁሉም ጎራ ፖለቲከኞች «ካልተጠነቀቅን እርስ በርስ እንፋጃለን» ማለታቸው ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/blog-post.html)! የጎሳ ፌደራልዚምን የሚደግፉትም የማይደግፉትም የጎሳ እልቂት is right around the corner ብለው ደጋግመው ይነግሩናል። ለጎሳ ፌደራሊዝም ከዚህ የባሰ indictment የለም!

ስለዚህ ለ«ዜግነት ፖለቲካ» ደጋፊዎች እና ሌሎች የዚህ የጎሳ ፖለቲካ የሚጠሉ ሰዎችን የምመክረው፤ ስሜትን በሃሳብ አትከራከሩ፤ የትም አትደርሱም። በመሰረቱ የጎሳ ፌደራሊዝም ሰውን የሚጎዳ ባይሆን ምን ችግር አለው? ምንም። የጎሳ ፌደራሊዝም ኢትዮጵያን በሰላም ቢያስተዳደር እኔ የሚጀመርያ ደጋፌው ሆን ነበር። ግን አይደለም። ሃቁ ይህ ነው። የጎሳ ፌደራሊዝም የምንጠላው የግጭት እና ጭቆና መንስኤ ስለሆነ ነው። ይህ ደግሞ በመረጃ የተመሰረተ statement ነው። ክርክራችን በታሪክ እና ርዕዮት ዓለም የተገደባ ሳይሆን ሙሉ በሙሉ መረጃ የተመሰረተ ነው። ይህ መከራከርያ መንገድ ነው አዋጪ ብዬ የማስበው።

Monday, 14 January 2019

ስለ ራያ ማንነት ውይይት፤ ዳር ዳሩን ከማለት ወደ ቁምነገሩ ካልገባን ችግሮችን አንፈታም


ይህን ስለ ራያ ማንነት ጉዳይ ቃለ ምልልስ ስመለከት ጠያቂውም እንግዶቹም ስለ ህግ አፈጻጸም እና ሂደታዊ (procedural) ጉዳዮች ከዓንድ ሰዓት በላይ ተወያይተው ዋናው መሰረታዊ የሆነው ጉዳይ ላይ ምናልባት 10 ደኪካ ነው ያዋሉት። «በግልጽ እንነጋገር ከተባለ…» ማለቱ ለምን ያስፈልጋል፤ መጀመሪያኑ በግልጽ ስለ መሰረታዊ ጉዳዩ መነጋገር ነው።

በግጭት መፍታት (conflict resolution) መሰረታዊ ችግር እንዳለ መገንዘብ፤ ከዛ ችግሩን ማወቅ፤ ከዛ ችግሩን ለመፍታት መስራት አብዛኛው ጊዜ የግድ የሆነ አስፈላጊ ሂደት ነው። አለበለዛ የችግሮቹ ውጤቶች ላይ እየተተኮረ እሳት እየተለኮሳ እሳት እያጠፋን እንቀጥላለን። መሰረታዊ ችግሩ እየተባባሰ ይሄዳል። እርግጥ የግጭቱ አካሎች ስለ መሰረታዊ ጉዳዩ ማውራት ማሰብም አይወዱ ይሆናል ግን አማራጭ የለም። ክስ ብሎ አለስልሶ ወደዛ መግባት ግድ ነውና።

የራያ መሰረታዊ ጉዳይ የራያ ማንንነት ኮሚቴ(ዎች) መቼ አመለከቱ ለማን አመለከቱ አይደለም። ይህ ሁለተኛ ጉዳይ ነው እና ብዙ የውይይት ጊዜ ሊፈጅ አይገባም። መሰረታዊ ችግር እና ጥያቄው እንደገባኝ ከሆነ እንዲህ ነው፤

1) እኛ ከትግሬ የተለየ የራያ ማንነት አለን እና አለፍላጎታችን በትግሬ ክልል ተካለልን፤
2) ሰባዊ መብታችን በትግራይ ክልላዊ መንግስት ለ27 ዓመት ትጥሷል እና ተጭቁነናል፤
3) መጀመሪያውኑ የጎሳ አስተዳደር ባይሆን ኖሮ ይህ የማንነት ጉዳያችን በዚህ መልኩ አይነሳም ኖሮ፤
4) አማራ ክልል ብንገባ መብታችን እና ሰላማችን ይከበራል እና የአምባገናን ትግራይ ክልልውስጥ መሆን አንፈልግም።

በርካታው የውይይቱ ጊዜ በነዚህ ጥያቄዎች ዙርያ መሆን ነበረበት ብዬ አስባለው። በዛሬው የፖለቲካ ሁኔታ ጥያቄዎቹ እጅግ ከባድ ናቸው እና ብዙ ውይይት ያስፈልጋቸዋል። ይህን ትቶ ስለ ደብዳቤ እና ግልባጭ ማውራት ትንሽ priority ማጣት ይመስለኛል።

Monday, 17 December 2018

ስለ ህገ መንግስት አንድ የውይይት ሃሳብ

አሁን ያለን የጎሳል አስተዳደር (ethnic federalism) የግጭት መንስኤ እንደሆነ የ27 ዓመት መረጃ አለን ብዬ ተከራክርያለሁ ከጽሁፎቼ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_89.html)። በህወሓት አገዛዝ የነበሩት የጎሳ እና የድንበር ግጭቶች ህወሓት ብቻውን ያካሄደው፤ የቀሰቀሰው፤ ያስተባበረው ብቻ አልነበሩም። ህወሓት በአስተዳደሩ ምክንያት ያሚመጡትን ችግሮች ለራሱ ጥቅም ያባብስ ነበር እና ያሉ ቅራኔዎችን ያባብስ ነበር እንጂ ችግሮችን ከሀ መፍጠር አቅም አልነበረውም። ዛሬም ለምሳሌ የሲዳማ እና ወላይታ ግጭት ስንመለከት አዎን የህወሓት እና ሌሎች ነበሮች እጅ ቢኖርበትም የጎሳ አገዛዙ መሰረታዊ መንስኤ ነው። በዚህ ምክንያት ዛሬ ያለው የጎሳ አስተዳደር ለሀገራችን ሰላም አይሆንም።

አማራጩ ምንድነው የሚለው ጥያቄ ላይ ጊዜ ብናጠፋ ጥሩ የመስለኛል። በዚህ ጉዳይ የተለያየ አቋም ያለን ኢትዮጵያዊያን ስለዚህ ገና ብዙ መነጋገር አለብን እስካሁን በቂ የተነጋገርን አይመስለኝም። ስንወያይም አብዛኛው ጊዜ የራሳችን አቋም ላይ ነው የምናተኩረው እንጂ በቂ ሌላውን አንረዳም።

ዛሬ አንድ አስተያየት ልስጥ… የጎሳ አስተዳደር ደጋፊዎች ኢትዮጵያ የብሄሮች ስብስብ ነው መሆን ያለበት ነው። የመጀመርያ ማንነታችን ጎሳችን ነው፤ ኢትዮጵያዊ ዜግነታችን ሁለተኛ ነው ነው የሚሉት። የሀገር ስሜት አለን ነው። ኦሮሞ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለች ሀገር ናት። ባለቤቷም የኦሮሞ ህዝብ ነው። ግን በታሪክ ምክንያቶች እና ዛሬ ባለው ነባራዊ ሁኔታ አብሮ መኖር ስላለብን ተገንጥለን አንኖርም ብሄሮች እርስ በርስ ውል ይኖራቸዋል ነው። እንደ ብሄር ክልል ወይንም «ትንሽ ሀገር» ከሌለን የሀገራዊ መብታችን ተወሰደ ማለት ነው። ልክ እንደ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚለው ሰው ከኬንያ ጋር በግድ ሙሉለሙሉ ተቀላቅለህ አንድ ሀገር ሁን ቢባል አይ አገርነቴን መጠበቅ እወዳለሁ እንደሚል አማራውም የብሄር ክልል ይቀር ቢባል ማንነቱ እንደተወሰደበት ይሰማዋል ነው። በአጭሩ ይህ አንዱ የጎሳ አስተዳደር ደጋፊዎች አስተሳሰብ ይመስለኛል።

እስቲ ለዚህ አንድ የሚሆን አማራጭ መልስ እንስጥ። ከህገ መንግስቱ «ብሄር ብሄረሰቦች ህዝቦች» የሚለውን በሙሉ አውጥተን ግለሰባዊ ብቻ እናድርገው። ግን አሁን ያሉትን ክልሎች እንጠብቅ። ለክልሎች አሁን ካሉት ተጨማሪ መብቶች እንስጥ። ከዛ የኦሮሚያ «ሀገራዊ» ምስልን እንመልከት። በቋንቋ፤ ባህል፤ ማንነት፤ ወዘተ በኦሮሚያ አብዛኛው ኦሮሞ ስለሆነ የሚኖረው ፍላጎቱ እንዲሰፍን ያደርጋል። ይህ የድምጽ ብልጫ ኦሮሚያ ክልልን ከሞላ ጎደል ኦሮሚያ ሀገር ሊያደርገው ይችላል። ግን ሀገር አይባልም እና ኦሮሞ ዘር ያልሆኑ ከኦሮሞዎች እኩል መብት ይኖራቸዋል። ግን አናሳ በመሆናቸው ብዙ ተጽዕኖ አይኖራቸውም።

ለኔ ይህ አካሄድ የጎሳ አስተዳደርን መጥፎ ጎን ያስወግዳል ማለትም ሁሉ ጉዳያችን በጎሳ የተመሰረተ እንዳይሆን ያደርጋል። አንደኛ/ሁለተኛ/ሶስተኛ ዜጋ፤ መፈናቀል፤ የጎሳ ብቻ ፖለቲካ ወዘተ እንዳይኖር ያደርጋል። ግን የጎሳ ወይንም ብሄር መብት ያስከብራል። በዚህ በጎሳ መብት ማስከበር ከጎሳ አስተዳደር ብዙ ልዩነት አይኖረውም።

ይህ አንድ የመሃይም ለውይይት የቀረበ ፕሮፖዛል ነው። የጎሳ ብሄርተኞችን ፍላጎት ያሟላ ይሆን። የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ፍላጎትስ?

Wednesday, 7 November 2018

የጎሳ አስተዳደርን አደገኝነት አለመረዳት ትንሽ ግትርነት ይመስለኛል

ከዚህ ገንቢ ውይይት (https://www.youtube.com/watch?v=tVqQW7Sh_G0) ስለ ጎሳ አስተዳደር (ፌደራሊዝም) ብዙ ጊዜ የሚነሳ ነጥብ ተነስቶ ነበር። ይህም፤

«የጎሳ ፌደራሊዝም በትክክሉ አልተሞከረም። እስካሁን ዴሞክራሲ አልነበረም፤ የአምባገነናዊ ጭቆና ነበር። የህዝቡ ኤኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ጥቅምም አልተከበረም። ለዚህ ነው ፖለቲካዊ ችግሮች የሚታዩት። ዴሞክራሲ፤ የኤኮኖሚ እና ማህበራው ፍትህ ሲኖሩ የጎሳ አስተዳደር በደምብ ይሰራል።»

አንዱ ተንጣኝ ይህንን አቋም ለመግለጽ "You can't judge a philosophy by its abuse" አይነት አባባል ተናግረዋል።

መቼስ ስለ ኮምዩኒዝምም እንዲህ ማለት ይቻላል! በትክክል ቢፈጸም ገነትን ያመጣልን ነበርና።

የጎሳ አስተዳደር ችግሮች ለማንኛውም አጉል risk ወይንም የራቀ እና ጸንፍ የያዘ ፍልስፍና ማቀፍ ለማይፈልግ ሰው ግልጽ የሆነ ይመስለኛል። ምክንያቶቹ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_89.html)፤

1. ደጋግሞ እንደሚባለው የትም ሀገር የጎሳ አስተዳደር የለም። ይህ በራሱ የጎሳ አስተዳደር እጅግ ጸንፍ የያዘ አስተዳደር እንደሆነ ይገልጻል።

2. በተለያዩ ሀገራት የጎሳ አስተዳደር የሌላቸውም ግን በተለያየ በፖለቲካ ክፈተቶች ጎሰኝነት ሲሰፍን ያለው ጉዳት አይተናል። የጎሰኝነት ችግር አንዳንድ ሀገሮች እስከ የጎሳ ፓርቲዎችም መከልከል አድርሷቸዋል።

3. የ27/22 ዓመት የሀገራችን የጎሳ አስተዳደር ተለምዶ ለጎሳ አስተዳደር አደገኝነት በቂ ማስረጃ ነው። አዎን ዴሞክራሲ አልነበረም ግን የጎሳ ተኮር ግጭቶች እና ቅራኔዎች በዴሞክራሲ እጦት ማሰበብ አይቻልም። መቼም ማንም reasonable ሰው እንዲህ የሚያየው አይመስለኝም። ምንም አይነት ችግሮች በጎሳ ግጭት መልኩ እራሳቸውን የሚገልጹ ከሆኑ ጎሰኝነት ነው ችግሩ ማለት
 ነው! አልፎ ተርፎ አሁን ዴሞክራሲ እየመጣ ግጭቶቹ ቀጥለዋል ወይንም በዝተዋል!

እነዚህን ግልስ የሆን ማስረጃዎች እያለን እና ግጭቶች እየበዙ እያሉ አሁንም የጎሳ አስተዳደር experimentአችንን እንቀጥል ማለት የሰከነ አስተያየት ነው? ይቅርታ አድርጉልኝ እና አይመስለኝም።

ይህን ስል የጎሳ አስተዳደርን የሚፈልጉት ሰዎችን መሰረታዊ ጥያቄዎች ማስተናገድ አንዳለብን ይገባኛል። አማራጭ ሊኖር ይገባል። አለ ጎሳ አስተዳደር እንዴት ነው የጎሳ መብቶች (እነዚህ መብቶች አይነታቸው አከራካሪ ቢሆንም) ማስከበር የሚቻለው።

መልሱ ቀላል ነው እና እንደ ጎሳ አስተዳደር አዲስ ፈጠራ ውስጥ እንድንገባ አያስገድደንም።
ከኢትዮጵያ አስር እጥፍ በላይ የጎሳ መብቶች (ቋንቋ፤ ባህል፤ አስተዳደር) የሚያስከብሩ ሀገራት አሉ። ህንድ፤ ስዊትዘርላንድ፤ ካናዳ ወዘተ። እነዚህ ሀገራት ሁሉም ሀገ መንግስታቸውን በዜግነት ነው የመሰረቱት። የጎሳ መብቶች በክፍለ ሀገር አቀራረጽ፤ የቋንቋ ህጎች፤ ለክፍለ ሀገር የሚሰጠው የማስተዳደር መብት ወዘተ ያስከበራሉ። ግን መሰረቱ ዜግነት ነው። እነዚህን እንደ ምሳሌ ወስዶ መጠቀም ነው።

ለመዝጋት አንድ አጭር ምሳሌ ልስጥ። ዛሬ ከህገ መንግስቱ «ብሄር፤ ብሄረሰቦች እና ህዝቦች» የሚለው ጥቅስ ከህገ መንግስቱ አወጣን እንበል። የክልል ቋንቋ በክልል ህዝብ ነው የሚወሰነው እንበል። ኦሮሚኛ የፌደራል ቋንቋ አደረግን እንበል። ይህ ሁኔታ (scenario) በርካታ የጎሳ መብት ያስከብራል። ኦሮሚያ ውስጥ በድምጽ ብልጫ የክልል ቋንቋ ኦሮምኛ ሆኖ ይቀራል። ይህ ማለት የምንግስት መስሪያቤት፤ ትምሕርት ቤት ወዘተ። የኦሮሚያ ክልል አስተዳደርም በኦሮሞ ባህል እንዲሆን በድምጽ ብልጫ ይፈጸማል። ወዘተ። ይህ አንድ ምሳሌ ነው። አለ ጎሳ አስተዳደር በርካታ የጎሳ መብቶች ሊፈጸሙ ይችላሉ።

ስለዚህ ወደ ህልም፤ ጸንፍ፤ አጉል ሙከራ አንሂድ። ቀላሉን መንገድ እንውሰድ። እንደ ኮምዩኒስቶቹ ህልማችንን እስከ መቃብራችን አቅፈን አንቆይ!

Wednesday, 3 October 2018

«የዜግነት ፖለቲካ ይስፈን» ብለን እንጮሃለን ግን አልተደራጀንም!

መቼም «ከእንቁላል ውስጥ» ያሉት እነ ጠ/ሚ አብይ በሙሉ አቅማቸው ኢትዮጵያዊነትን ለማጠንከር እየጣሩ ነው። በዚህ መንገድ እንደሚቀጥሉም ይታወቃል።

አሁን በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ያለው ትልቅ ጉድለት ነገር በኢትዮጵያዊነት የምናምን ፖለቲከኛ፤ ልሂቃን እና ብዙሃን በአግባቡ አለመደራጀቱ ነው። «የዜግነት ፖለቲካ ይስፈን» ብለን እንጮሃለን ግን አልተደራጀንም!! እንኳን በሚሊዮኖች የምቆጥር በመቶ ሺዎች የሚቆጥር አባል ያለው ድርጅት የለንም። ታድያ ሌሎች የዜግነት ፖለቲካ አይሰራም ብለው እንዲያምኑ የሚያደርጋቸው እኛ ነን ማለት ነው!

እነ ግንቦት 7 ስሙ። ቶሎ ብላችሁ የዜግነት ፖለቲካ አራምዱ። አባላት እና መሪዎች በሰፊው መልምሉ። የመዋቅር መዘርጋት ስራ ካሁኑኑ ጀምሩ። ጊዜ ይፈጃል ግን ጊዜ የለንምና።

Thursday, 27 September 2018

ለምንድነው የቡራዩን ክስተት የጎሳ ማጥፋት (ethnic cleansing) ክስተት የሚባለው?

ይህን ቪዲዮ እዩት።


እንዲሁ በርካታ የቡራዩ ሰለቦች እና ምስክሮች የዘር ማጥፋት ክስተት እንደሆነ ገልጸዋል። መረጃዎቹ ቀላል ናቸው፤ ወንጀለኞቹ በአንደበታቸው ዘር እየመረጡ ነው የገደሉት እና የግድያ እና ወንጀል አየነቶቹ ማለትም ማረድ እና መድፈር የዘር ጥላቻ ያለበት የዘር ማጥፋት ዘመቻን ያመለክታሉ። ይህ ምንም ጥርጥር የሌለው እውነታ ነው።

ኦሮሞዎችም ተገድለዋል ተጎድተዋል ይባላል። ይህ የዘር ማጥፋት ክስተ መሆኑን አያስቀርም። በግርግር መሃል ይህም ተከስቶ ይሆናል። መንጋው በመጠጥም በደምም ሰክሮ ብዙ ሊያደርግ ይችላል። ግን ከመንጋ ውስጥ ዘር መርጠው እየገደሉ እንደነበሩ ሃቅ መሆኑን መሰረዝ አይቻልም።

ቅጥረኞች ናቸው ያደረጉት ይባላል። እውነት ሊሆን ይችላል። ያስኬዳልም። ቢሆንም 1) ጥላቻ የሌለባቸው ፕሮፌሽናል ቅጥረኞች የዘር ማጥፋት ምልክቶች ያሉት ግድያ እና ጭቆና ማድረግ አይችሉም! 2) «ቄሮ ነን እያላችሁ ግደሉ» ተብለው የታዘዙ ቅጥረኞች ቢሆኑ ደግሞ ኦሮሞን አይገሉም ነበር። ይልቁንስ አማራን እና ኦሮሞን ለማጣላት የተቀነጀ ሴራ በመሆኑ ከጋሞ ይልቅ አማራ ላይ ነበር የሚያተክሩት።

ስለዚህ እነዚህ ቅጥረኞች ፕሮፌሽናል ሳይሆኑ የአካባቢው ሰው እና አንዳንድ ከውጭ የሜጡ መሪዎች ናቸው። የቅጥረኛ ሴራው በአካባቢው በነበረ የጎስ ቅሬታ እሳት እና በንዚን ማቀጣጠል ነው።

ለቡራዩ ክስተት የኦሮሞ ህዝብም ይሁን ቄሮም መፈረጅ እንደሌለበት ለማንም የሰው ልጅ ግልጽ እንደሆነ እናውቃለን። አንዳንድ ክፉ አሸባሪዎች ወይንም አላዋቂ ቀንደኞች በቀር እንደዚህ አይነት ነገር አያስቡም እንኳን መናገር።

ስለዚህ ለምንድነው የቡራዩ ክስተት የዘር ማጥፋት የሚባለው? ስለነበር ነው! እውነት ስለሆነ ነው! ልክ እንደ ከሶማሌ የተፈናቀሉት ኦሮሞዎች የዘር ማጥፋት ዘመቻ ሰለቦችህ እንደነበሩት። በአዋሳ ዎላይታዎች ላይ እንደደረሰው እኩል። ጊኬኦ ላይ እንደደረሰው። አኗክ ላይ እንደደረሰው። አማራ ላይ በየቦታው እንደደረሰው። የ27 ዓመት የዘር ማጥፋት ክስተቶች ረዥም ዳታቤስ አለ። የቡራዩ ክስተት ትንሿ ናት። ልድገመው፤ ትንሿ ናት። በሶማሌ ግጭቱ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ኦሮሞዎች ነው ገቤታቸው የተባረሩት! (በነገራችን እኛ ኢትዮጵያዊነት ወዳጆች ጎፉንድሚ ለነዚህ አድርገናልን?)

ይህ የሚያሳየው የጎሳ ፌደራሊዝም የግጭት ምንጭ እንደሆነ ነው። ጎሳ በፖለቲካ ሲካተት ጸንፈኝነትን እና ግጭትን ነው የሚያመጣው። ይህ ሃቅ በዓለም ዙርያም ብኢትዮጵያም ይመሰከርለታል።

አልፎ ተርፎ ሁሉም አይነት የኢትዮጵያ ፖለቲከኞች አናምንበትም ቢሉም አምነውበታል! ሁሉም ፖለቲከኞቻችን በርካታ ጊዜአቸውን የጎሳ ግጭት አሳሳቢ ነው አብሮ መኖር አለብን በመስበክ ይውላሉ! ከነ ኦሮሞ ብሄርተኛ ፖለቲከኞች! የጎሳ ግጭት የሀገራችን ዋና ፖለቲካዊ ችግር መሆኑን ከዚ በላይ የሚገልጽ የለም!

ስለዚ የጎሳ ብሄርተኝነት እና የጎሳ ፌደራሊዝም መርዝ እንደመዋት መብት ቢሆንም ይገላል!

Friday, 21 September 2018

የተረሳው ጉዳያችን፤ የመሬት ፖሊሲ ሚና በጎሳ ፖለቲካ

ከዚህ በፊት ደጋግሜ ስለ የኢትዮጵያ የመሬት ፖሊሲ ችግር ጽፍያለሁ (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_47.html)። መሬት የግል ወይንም የአካባቢ ("local community" ለምሳሌ ወረዳ) ከመሆኑ ፋንታ የመንግስት መሆኑ ለህዝባችን እጅግ ጎጂ ፖሊሲ ነው ብዬ ነው የማምነው። ለዝርዝሩ ከላይ የጠቀስኩትን ጽሁፍ አንብቡ፤ ግን በአጭሩ መሬት የመንግስት መሆኑ የፈጠረው ችግሮች እንዲህ ናቸው፤

1. ገበሬው ለ«ጎበዝ ገበሬ» የሆነው ጎረቤቱ መሬቱን ሽጦ ወደ ከተማ መሄድ ባለመቻሉ ገጠር ቀርቶ በገጠር የመውለድ መጠን (birth rate፤ በገጠር አማካኙ ከስድስት ልጅ በላይ ነው) ልጅ ወለደ። ከተማ ቢሄድ ኖሮ ሁለት ልጅ (ሁለት አማካኙ ነው ለከተማ ነዋሪ) ይወልድ ነበር። ይህ ማለት የህዝብ ቁጥርን ባልተጠበቀና በኢተፈጥሮዊ (artificial) መንገድ ንሯል። ኢተፈጥራዊ ማለት ህዝቡ ወደ ከተማ እንዳይሄድ ነፃነቱ በመገደብ የጠፈጠረ ሁኔታ ስለሆነ ነው። ከግዳጅ የመጣ ክስተት ስለሆነ ነው።

2. የገጠር ህዝብ ቁጥር ንሮ የገበሬ መሬት አንሶ ልጆች የሚወርሱት አጥተው አሁን ታላቅ የገጠር ወደ ከተማ ፍልሰት ተከስቷል። ለ40 ዓመት ቀስ በቀስ ፍልሰት ከመሆኑ ፋንታ የገጠሩ ሰው ለ40 ዓመታት ከገጠር ተጠራቅሞ አሁን ባንዴ ወደ ከተሞች እየመጣ ነው። ይህ ሁኔታ ከተሞቻችንን አስጨንቋል።

3. ገበሬዎች ቢጎብዙም ገንዘብ ቢኖራቸውም መሬት መግዛት ባለመቻላቸው የግብርና ስራውን ማስፋፋት አልቻለም። ማደግ አልተፈቀድለትም። በዚህ ምክንያት «የሰው አቅማቸው» (human capital) እንዳያድግ ተደርጓል። ለምሳሌ እንደ የግብርና የሙያ፤ የንግድ ሙያ፤ የአስተዳደር ችሎታ አይነቱን እንዳያዳብር ተደርጓል።

4. ገበሬው ሽጦ መሄድ ባላመቻሉ መሬቱን ለትውልድ እያከፋፈለ መሸንሸን ሆነበት። መሬቱ ተሸንሽኖ የያንዳንዱ ገበሬ መሬት አንሶ አንድ ቤተሰብም ማስተዳደር የማይችል ሆኗል። በዚህ ምክንያት ገበሬዎች ለድርቅ እና ርሃብ ተጋለጡ። የምግብ ዋስትና እጥረት እንዳለ ነው።

5. ጎበዝ ገበሬዎች መሬት ገዝተው መስፋፋት ባለመቻላቸው እና ደካማ ገበሬዎች ለጎበዞቹ መሸጥ ባለመቻላቸው የእርሻ ውጤት ዝቅተኛ ሆኖ ቈርቷል። ይህ ደግሞ የእህልና የምግባ ዋጋ ግሽበት አምጥቷል።

ከላይ የጠቀስኳቸው ባብዛኛው በኤኮኖሚ ዙርያ የሆኑ ነጥቦች ናቸው። ግን የመሬት ፖሊሲው ሌላ ታላቅ የፖለቲካ እና ማህበረሰባዊ ተጽዕኖ አለው።

ባጭሩ፤ የመሬት ፖሊሲው አንዱ የጎሳ አስተዳደሩ ምሶሶ ነው። መሬት የ«ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች» ነው ሲባል ለ27 ዓመት የተተረጎመው የአማራ ክልል መሬት የ«አማራ ብሄር» ነው፤ የኦሮሚያ ክልል መሬት የ«ኦሮሞ ህዝብ» ነው ወዘተ እየተባለ ነው። ትርጉሙም የህገ መንግስቱን ጽሁፍም መንፈስም የተከተለ ነው።

«መጤ» እና «ነባር» የሚሉት ጽንሰ ሃሳቦች በማህበረሰቡ በዚህ መሬት ፖሊሲ ይደገፋሉ። የ27 ዓመታት የመፈናቀል ዘመቻዎች የተካሄዱትም በዚህ ምክንያት ነው። ግን ህጉ የመሬት ባለቤትነት የግለሰብ ወይንም የቅርብ አካባቢ ሰዎች ቢያደርግ ኖሮ የ«መጤ» እና «ነባር» አስተሳሰብን ይቀንስ ነበር ነአ ቀስ በቀስ ያጠፋ ነበር። ለዚህ አስተሳሰብ የህግ ሽፋን እንዳይኖረው ያደርጋል። ተፈናቃዮች ለመብታቸው በፍርድ ቤት መታገል እንዲችሉ ያደርጋቸው ነበር።

ስለዚህ ዛሬ ያለውን ጎሰኝነትን ለመታገል እና ቀስ ብሎ ከጎሳ ፌደራሊዝም ወደ ህብረ ባህላዊ አገዛዝ ለመሄድ ይህን የመሬት ፖሊሲ መመልከትና መቀየር ጠቃሚ ይመስለኛል።

Monday, 17 September 2018

መርዝ መጠጣት መብት ቢሆንም ይገላል፤ እንዲሁም የጎሳ ብሄርተኝነት መብት ቢሆንም ህዝብን ያጠፋል

ለማንም ሰው በ«ጎሳ ብሄርተኝነት» እና የፖለቲካ ዘመዱ በ«ጎሳ አስተዳደር» ማመን መብቱ ነው። አንድ ሰው እንዲህ «ኢትዮጵያዊ አይደለሁም፤ ኦሮሞ ነኝ። ኢትዮጵያ ህዝቤን ለዓመታት ጨቁናለች ቅኝ ገዝታለችም። ማንነቴ ኦሮሞ ነው። መኖር የምፈልገው በኦሮሞ ሀገር ነው እንጂ ኢትዮጵያ አይደለም» ቢል መብቱ ነው። እንዲህ አታስብ ማለት ልክ አይደለም። ካልንም መብት ገፈናል ግጭትንም ጋብዘናል ማለት ነው (ይህንን ጥንቅቃችሁ እንድታነቡ እጠይቃለሁ http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2017/11/whats-ethnic-nationalism-again.html)።

ይህን ተከትሎ በርካታ ሰዎች እንዲህ አይነት የጎሳ ብሄርተኝነት አመለካከት ካላቸው እና የፖለቲካ ፍላጎታቸው ይህ ከሆነ ጥያቄአቸው በሰላማዊ መንገድ መስተናገድ ይኖርበታል። ለምሳሌ የአንድ ክፍለ ሀገር ወይንም ክልል 70% ህዝብ «ነፃነት» ወይንም ሌላ የፖለቲካ አስተዳደር እፈልጋለሁ ካለ በድርድር መልክ መስተናገድ አለበት። አለበለዛ መብታቸውን አላከበርንም ማለት ነው። እንዲህ አይነት አካሄድ ደግሞ ወደ ግጭት እና ጦርነት ማምራቱ የታወቀ ነው።

የጎሳ ብሀሄርተኝነት መብት ነው ብለናል። ታድያ ለምንድነው የምንቃወመው? መልሱ ቀላል ነው፤ የጎሳ ብሄርተኝነት የግጭት ምንጭ ስለሆነ ነው። በተለይ በብሶት ማንነት የተመሰረተ (grievance based identity) የጎሳ ብሄርተኝነት በ«ጭቋኝ ተጨቛኝ» አስተሳሰብ የተሞላ ስለሆነ ሁልጊዜ ግጭት ያመጣል። ተጨቁኛለሁ ጨቋኜን ማጥቃት አለብኝ ይላል። ብድር መመለስ አለብኝ ይላል። መሬቴን መመለስ አለብኝ ይላል። «መጤዎችን» ማባረር አለብኝ ይላል። ሰውን እንደ ሰው ከማየት እንደ ቡድን ያያል። የመንጋ አስተሳሰብ ይጋብዛል። ወዘተ። ታሪኩ ዓለም ዙርያ የታወቀ ነው።

የጎሳ ብሄርተኝነት ግጭት እንደሚጋብዝ የሚታወቀው በጽንሰ ሀሳብ ደረጃ ብቻ ሳይሆን በተግባር ባለፉት 27/40 ዓመት የኢትዮጵያ ታሪክ ያየነው ነው። ግጭቶቹ የህወሓት ስራ ናቸው እንጂ የጎሳ ስረዓቱ አይደለም ማለትም አይቻልም። አብዛኞቹ ግጭቶቹ ህወሓት እንደ ተጋጭ አልተሳተፈባቸውምና። ግጭቶቹ የህወሓት እጅ ቢኖርባቸውም ህወሓት በባዶ መሬት ያስነሳቸው አልነበሩም። ህወሓት የነበሩ የጎሳ ቅራኔዎችን ነበር የሚጭረው እንጂ ቅራኔዎችን ከስር አልፈጠረም። ስለዚህ ባለፉት ዓመታት ያየናቸው የጎሳ ግጭቶች የጎሳ ብሄርተኝነት እና አስተዳደር ውጤት ናቸው ማለት ይቻላል።

በቅርብ ታሪካችን እንደሚመሰክረው የፖለቲካዊ፤ ኤኮኖሚያዊ እና ማህበረሰባዊ ግጭቶች ሁሉ በ«ጎሳ ፖለቲካዊ ውድድር» ዙራይ (ethnic political competition) ነው የሚከሰቱት። ይህ ውድድር በመሬት፤ የፖለቲካ ስልጣን፤ ንብረት ክፍፍል ወዘተ ሊሆን ይችላል። «ይህ መሬት የኛ ነው»፤ «ይህ ስልጣን ለኛ ይገባል»፤ «ይህ መዓድን ውጤት ለኛ ነው መሆን ያለበት» ወዘተ እየተባለ ወደ አጉል ውድድር፤ ፉክክር እና ግጭት ይኼዳል። ይህን በተግባር አይተናል እያየንም ነው።

በምንድነው ይህ የጎሳ ውድድር ከሌሎች ፖለቲካዊ ውድድሮች የሚለየው? በምን መንገድ ነው ከአካባቢ፤ ርዕዮት ዓለም፤ መደብ፤ ጥቅም ወዘተ የፖለቲካ ውድድሮች የሚለየው? ለምንድነው ጤናማ ያልሆነው? ልዩነቱ ጎሳ ከሰው ማንነት ጋር የተቆራኘ እና በቀላሉ መቀየር የማይቻል ነገር ስለሆነ ነው። አካባቢ፤ ርዕዮት ዓለም፤ መደብ፤ ጥቅም ይቀያየራሉ። ዛሬ አዲስ አበባ ነገ አምቦ መኖር ይቻላል። ዛሬ ማርክሲስት ነጋ ካፒታሊስት መሆን ይቻላል። ዛሬ ድሃ ነገ ሃብታም መሆን ይቻላል (ሳይቻል ሲቀር ደግሞ ይህም ኃይለኛ ግጭት የመጣል)። እነዚህ መስፈርቶች የሰው ልጅ ማንነት ላይ ሚና ቢኖራቸውም ሚናው መጠነኛ ነው። መቀየር ይቻላል ብዙ ጊዜም እንቀይራቸዋለን። ግን ጎሳ ወይንም ሃይማኖት የማንነት ታላቅ ክፍል ናቸው እና ባብዛኛው አይቀየሩም። ጎሳ በዚህ መልኩ ከሰው ልጅ ማንነት ጋር አጥብቆ ስለተያያዘ በጎሳ በኩል የሚመጣ ውድድር እጅግ የከረረ እና አከፋፋይ ነው የሚሆነው።

አልፎ ተርፎ የጎሳ ልዩነት እና የጎሳ ብሄርተኝነት በበዛበት ስፍራ ሁሉ ጥያቄዎች/ውድድሮች «የጎሳ መልክ» ይይዛሉ። ለምሳሌ የጎሳ ብሄርተኝነት በሌለበት ቦታ በአንድ ድርጅት እና የሰራተኛ ማህበር ግጭት ካለ ግጭቱ በኩባኒያው እና ሰራተኛ ማህበር መካከል ሆኖ ይቀራል። ምናልባት ሌሎች ቁባንያዎች ከጓድ ኩባኒያቸው ጋር ይወግኑ ይሆን እና ሌሎች የሰራተኛ ማህበራት ከጓድ ከሰራተኛ ማህበራቸው ጋር ይወግኑ ይሆናል። የከረረ ጎሰኝነት ባለበት ቦታ ግን ኩባንያውም የሰራተኛ ማህበሩም በጎሳ ይሰየማሉ እና ጎሳዎች ከኋላቸው ይሰለፋሉ። ለምሳሌ የኩባንያው ባለቤት ኦሮሞ ከሆነ ኦሮሞዎች ከሱ ጋር ይሰለፋሉ ሰራተኞቹ ደግሞ ባብዛኛው ጉራጌ ከሆኑ ጉራጌዎች ከነሱ ጋር ይሰለፋሉ። ግጭቱ ከሰራተኛ መብት አልፎ ወደ ጎሳ ግጭት ይቀየራል። ወደ ከረረ ግጭት ይገባል። ጎሰኝነት ወይንም የጎሳ ብሄርተኝነት በአንድ ሀገር ሲበዛ ይህ ነው አንዱ አደጋ እና የግጭት መብዛት መንጭ።

ግን ይህ አደጋ እንዳለ ሆኖ ከላይ እንዳልኩት አንድ ሰውን የጎሳ ማንነትህን ተው ማለት አይቻልም። መብቱ ነው ማንነቱ ነው ምንም ትክክል ባይመስለን ወይንም በሃሰት የሆነ ሃሳቦች የተመሰረተ ነው ብንልም የሌላ ሰው ማንነትን አስገድዶ መቀየር አይቻልም (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/08/blog-post_34.html)። አልፎ ተርፎ ሰውን በማንነቱ ጥንቃቄ በሌለው መንገድ ከተቸነው ይበልት እንዲከርር ነው የምናደርገው። በተለይም የጎሳ ማንነቱ በብሶት የተመሰረተ ከሆነ። ካልተጠነቀቅን አክራሪ ያልሆነውንም ወደ አክራሪነት እንገፈዋለን። ለምሳሌ «እኔ ኦሮሞ መጀመርያ ቀጥሎ ኢትዮጵያዊ ነኝ» የሚለው ኦሮሞ ማንነቱን ከተቸነው ወይንም ከተከራከርነው በማንነቴ አትምጡብኝ ብሎ ጭራሽ ኢትዮጵያዊነቱን ትቶ ወደ ኦሮሞነት ብቻ ሊያመራ ይችላል። ይህ የሚሆነው በስሜት ደረጃ ነው። «ይህ አደጋ ነው እና ኦሮሞ ብቻ ነኝ አትበል ኢትዮጵያዊ ኦሮሞ ነኝ በል» ማለት ሁኔታውን ያባብሳል ጎሰኝነቱን ይጨምራል።

ጥንቃቄ ያስፈልጋል ስንል ግን እውነት አይነገር አይደለም። ግን «ኦሮሞ አትሁን» አይነቱን አሉታዊ አስተያየት ከመሰንዘር ይልቅ በአዉንታዊው ማተኮር ነው። አዎን የጎሳ ብሄርተኝነት አደጋ እንደሆነ በግልጽ መናገር ጠቃሚ ነው። ግን ከዚህ ጋር አብሮ የጎሳ ማንነቱ እንዴት አለ ጎሳ ብሄርተኝነት (nationalism) ማስተናገድ እንደሚቻል መግለጽ ይኖርብናል። ማንነቱ በኢትዮጵያዊነት እንዲንጸባረቅ ማድረግ እንደሚቻል ማሳየት አለብን። ለምሳሌ አንድ እንደዚህ አይነት አውንታዊ ሃሳብ ኦሮምኛ ከአማርኛ እኩል የፌደራል መንግስት ቋንቋ ማድረግ ጥሩ ነው የሚለው አቋም ነው። ይህ አቋም የሚልከው መልእክት «አንተ ኦሮሞ ነህ፤ ኢትዮጵያም ኦሮሞ ናት» የሚል ነው። ማንነትህ በኢትዮጵያዊነት ተታክቷል ማለት ነው። እንዲህ አይነት አውንታዊ መርህ እና መልእክቶች ናቸው ሰው ወደ ጎሳ ብሄርተኝነት እንዳይገባ የሚረዳው ወይንም ከጎሰኝነት ወደ ኢትዮጵያዊነት እንዲያመዝን የሚያደርገው።

በሌላ በኩል ስለምናስተላልፈው መልዕክቶች መጠንቀቅ ያለብን እንዲህ ነው። ብዙ ጊዜ የጎሳ ብሄርተኝነት «ጥላቻ»፤ «ዘረኝነት»፤ «ጠባብነት»፤ «የፖለቲካ ነጋዴዎች ጭዋታ» ወዘተ ተብሎ ይሰየማል። እነዚህ በሙሉ የተወሰነ እውነታ አላቸው። ግን ሙሉ እውነታው አይደለም። በድፍኑ እንዲህ ማለቱ በርካታ ለዘብተኛ የሆኑ የጎሳ ብሄርተኞች ወይንም ገና አቋማቸውን ያልወሰኑ በመሃል የሚንሳፈፉ ሊያስቀይም እና ይበልጥ ወደ ጎሰኝነት ሊገፋቸው ይችላል። «ማንነቴ ኦሮሞ ነው ስላልኩኝ ዘረኛ ነኝ እንዴ» ብሎ ይበሳጫል። እንዳልኩት የጎሳ ማንነት በጣም ስሜታዊ ነገር ነው እና መተቸት አይወድም። ስለዚህ ስንተቸው በትክክል እና precise መንገድ መሆን አለበት። ለመልሶ ትችት የማይመች መሆን አለበት። ስለዚህ ዘረኛ አመለካከት ስንሰማ ይህን አመለካከት ዘረኛ ነው ማለት ተገቢም አስፈላጊም ነው። ወደ ኋላ ማለት እና መሸማቀቅ ጎጂ ነው። ግን በጅምላ ዘረኞች ናችሁ ካለን ሁኔታዎች ያባብሳል። በጠቅላላ የጎሳ ብሄርተኝነትን መቀነስ የምንፈልግ የማስተላልፈው ምልዕክቶአችንን ተጠንቅቀን ማርቀቅ አለብን። ልድገመው፤ የሰው ልጅ ማንነቱ ሲተችበት አይወድም።

ለማጠቃለል ያህል፤ የጎሳ ብሀኢርተኝነትን አቋም መያዝ መብት ነው። ግን የጎሳ ብሄርተኝነት እና የጎሳ ፌደራሊዝም የግጭት እና ሁከት ምንጮች ናቸው። በዚህ ምክንያት ነው የምንቃወማቸው።  በመሰረቱ ክፉ፤ ዘረኛ፤ ጠባብ ወዘተ ስለሆነ ሳይሆን የግጭት ምንች ስለሆነ ነው። ይህን በጽንሰ ሃሳብም በተግባር አይተነዋል። የጎሳ ብሄርተኝነትን ለመቀነስ ትጠንቅቀን መስራት አለብን በተለይ በምናስተላልፈው መልዕክቶቻችን ትክክለኛ እውነት ግን በጅምላ የማይፈርጅ እንዲሆኑ ማድረግ አለብን። የሰው ማንነትን አክብረን ደግሞ በኢትዮጵያዊነት ውስት ይህ ማንነት በድምብ እንዲካተት በአውንታዊ መልክ መስራት አለብን።

Tuesday, 4 September 2018

ተረት ተረት፤ በኢትዮጵያ ያለው የ«ቋንቋ ተኮር ፌደራሊዝም» ነው

በኢትዮጵያ ያለው በሀግም በህግ መንፈስ (letter and spirit of the law) የቋንቋ ተኮር ፌደራሊዝም ሳይሆን የጎሳ (ብሄር ብሄረሰቦች ህዝቦች) ፌደራሊዝም ነው። ልዩነቱ ምንድነው?

የቋንቋ ፌደራሊዝም ማለት የተለያየ የቋንቋ ተናጋሪዎች በቋንቋቸው የቋንቋ የቡድን መብት ይኖራቸዋል ማለት ነው። ለምሳሌ በኦሮሚያ የክልል ቋንቋ ኦሮምኛ ሆኖ ማንም ኦርምኛ የሚናገር ሰው በቋንቋ ችሎታው እኩ መብት አላቸው። እንደ እንግዳ ወይንም «መጤ» አይቆጠሩም። የክልሉ ቋንቋ ኦሮምኛ ነው ብሎ ሲሰየም ሁሉንም የቋንቋ ተናጋሪ ያካትተዋል። ስለዚህ የቋንቋ ፌደራሊዝም በዘር አይለይም። ማንም ቋንቋ እስከቻለ ቡድን ውስጥ አለ ማለት ነው። አግላይ አይደለም።

የጎሳ ፌደራሊዝም ግን ደም እና አጥንት የሚቆጥር ነው። በጎሳ ፌደራሊዝም ኦሮሚያ የኦሮሞ ተናጋሪ ክልል ሳይሆን የኦርሞ በደሙ ኦሮሞ የሆነ ሰው ክልል ነው። ኦሮሞ ያልሆነ ቋንቋውም ባህሉም «ኦሮሞ» ቢሆን የክልሉ ባለቤት አይደለም። ስለዚህ ይህ አሰራር በመሰረቱ አግላይ ነው። በሌላ ቋንቋ ዘረኛ ነው ማለት ይቻላል። አንድ ሰው ምንም ያህል ኦሮምኛ ቢችል በባህልም ሌላም ብዙ የተዋሃዶ ቢሆንም ኦሮሞ አይደለም ስለዚህ በኦሮሞ ክልል በዓድ ወይንም መጤ ነው።

እንደሚታዩት በሁለቱ በቋንቋ እና በጎሳ ፌደራሊዝም ታላቅ መሰረታዊ ልዩነት አለ። አንዱ ክፍት ነው ማንንም መስፈርት እስካሟለ ያቅፋል። ሌላው ግን ዝግ ነው ማንም ምንም ቢያደርግ ሊሳተፍ አይችልም። በመሰረቱ አግላይ ነው። ዘረኛ ነው የዘረኝነትን መንፈስም ተግባርም ይጋብዛል።

ለምሳሌ ጎሳ በመታወቅያ መደረጉ። እንደ የአፓርታይድ ዘመን ደቡብ አፍሪካ! ጎሳ በመታወቅያ የሚደረገው በጎሳ ለመለየት ነው። መረጃ ብቻ ሆኖ አይቀርም መለያ ይሆናል። ማለትም ዘረኝነትን ይጋብዛል። ለዚህ ነው ደቡብ አፍሪካ ይህን ስርዓት የነበረት ዘረኝነትን ለማራመድ ስለሚጠቅም። እና ምን ማለት ነው ኢትዮጵያ ይህን የዘረኝነት ስርዓት በገልበጧ?! የጎሳ ፌደራሊዝም ምን ያህል ዘረኝነትን እንደሚያራምድ እንዳሚያስፋፋ ነው የሚገልጸው። አንዴ የሀገሪቷ ዋና ህግ (ህገ መንግስቷ) ጎሰኝነትን መዋቀራዊ ካደረገች የዘረኝነት ስርዓቶች ይከተላሉ።

በዚህ ምክንያት ነው ዓለም ዙርያ የትም ሀገር የጎሳ ፌደራሊዝም ውየንም የጎሳ መብት (ከሞላ ጎደል) የሌለው። ማንም ሀገር በህገ መንግስቱ «ጎሳ»፤ «ብሄር ብሄረሰብ ህዝብ» አይነቱን ጽንሰ ሀሳብ አይጠቀምም። የቋንቋ ፌደራሊዝም፤ የቋንቋ የቡድን መብቶች፤ የክልል ቡድን መብቶች በህግ ደረጃ ያሰፈኑ ሀገራት በርካታ ናቸው። ግን ማንኛውም ህጉን በጎሳ የመሰረተ የለም።

ለዚህ ይህ የኢትዮጵያ የ1985 ህገ መንግስት ጸንፍ (radical) የያዘ በዓለም ዙርያ መችሄም ታይቶ የማይታወቅ እጅግ ሃላፊነት-ቢስ ሙከራ (experiment) ነው የተባለው። የትም ሀገር ያልተደረገ እና አስፈላጊ ያልሆነ ህገ መንግስት በኢትዮጵያ አይነቱ ደካማ ሀገር መጫኑ ታላቅ ልክስክስነት እና ህጻንነት ነበር። በዚህ ነውረኛ ሙከራ ምክንያት በርካታ ዜጎቻችን ተሰቃይተዋል።

ይህ አይነት የጎሳ ፌደራሊዝም የትም ሀገር የሌለው ምክንያት አለ! ህዝብን በጎሳ መከፋፈል ወይን መብት በጎሳ መመደብ ማለት ኩፍኛ ግጭትን መጋበዝ ማለት ነው። ዓለም ዙርያ የታወቀ ነገር ነው። አንድ ምሳሌ ልስጣችሁ።

በካናዳ ኬቤክ የምትባል የፈረንሳይኛ ተናጋሪ ክፍለ ሀገር አለች (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2017/05/using-canada-to-understand-ethiopian.html)። ኬቤክ ለረዥም ዓመታት ከሌላው ካናዳ እለያየሁ እያለች ትሟገታለች ሁለት ጊዜም የመገንጠል ሬፈረንደም አካሄዳለች። ሁለቱም ጊዜ ህዝቡ ለጥቂት አንገንጠል አለ። የ ኬቤክ ቤርተኞች ግን ተጠንቅቀው የኛ ብሄርተኝነት የቋንቋ ነው እንጂ የጎሳ አይደለም ነው የሚሉት። ጎሳ አላቸው፤ 350 ዓመት በፊት ከፈረንሳይ ወደ ካናዳ የፈለሱት ፈረንሳዮች። ግን እኛ ኬቤክ ስንል ማንነታችን እንደ ቡድን መብት ይከበር ስንል በጎሳ ሳይሆን በቋንቋ ነው ብለው አስምረው ነው የሚናገሩት። በኬቤክ ማንም ፈረንሳይኛ ተናጋሪ እኩል የኬቤክ ዜጋ ነው ብለው ጠንክረው ይናገራሉ። ልምንድነው ጉዳዩን እንዲህ የሚያሰምሩበት? የቋንቋ ቡድን ክፍት ነው እና «ዘረኛ» መባል አይቻልም። ከሞሮኮ የመጣ ፈረንሳይ ተናጋሪ፤ ከኢትዮጵያ ወደ ኬቤክ የመጣ ፈረንሳይኛ የተማረ ወዘተ ሁሉም እኩል የኬቤክ ሰው ናቸው። በጎሳ ቢሆን ግን ፈረንጁ የድሮ የኬቤክ ሰው ብቻ ነው የክፍለ ሀገሩ ባለቤት የሚሆነው። ይህ ደግሞ ዘረኝነት ነው። የኬቤክ ብሄርተኞች «ዘረኞች» መባል እጅግ ስለሚፈሩ ያላቸውን መጤዎች ወደነሱ ማምጣትም ስለሚፈልጉ ሁልጊዜ የኛ ብሄርተኝነት የቋንቋ ነው ብለው ተጠንቅቀው ይገልጻሉ።

ሌሎችም በተለምዶ የሚጠቀሱት ሀገሮች እንደ ህንድ፤ ቤልጀም፤ ኤስፓኝ ወዘተ እንዲሁ ነው። የቡድን መብት በቋንቋ ወይንም በክፍለ ሀገር ነው የሚመሰረተው። ጎሳ፤ ብሄር፤ ብሄርተሰብ፤ ህዝብ ወዘተ ተጠንቅቆ ይወገዳል። ዘረኝነትን እና ግጭትን እንደሚጋበዝ የታወቀ ስለሆነ ነው። ዘረኝነትም ቢኖር ቢያንስ ዘረኛ ላለመባል ጥያቄአቸውም በቋንቋ ወይንም በክፍለ ሀገር ሽፋን ያቀርቡታል።

የዓለም ልምድ እንዲህ ሆኖ ኢህአዴግ ይህንን የሙከራ ህገ መንግስት ኢትዮጵያ ላይ መጫኑ የኛ ልሂቃን የጸንፈኝነት ዝንባሌን በደምብ ያሻያል። ትንሽ የቀለም ትምህርት ስንማር ቀንደኛ ጸንፈኛ መሆን የእውቀታችን መለክያ ይመስላችን ይሆን አላውቅም። በተማሪ ንቅናቄው ይህ በደምብ ታይቷል። በህወሓትም እንዲሁ። በኢህአፓም። ዛሬም በተለያዩ ፖለቲከኞች እናየዋለን። የችግር መፍትሄው ቀላላእና ሚዛናዊ ለዘብተኛ ፊት ለፊት እያለ ጸንፈ የያዘ ውስብስብ የሆነ መፍትሄ (ማባባሻ) ይፈለጋል። የኢትዮጵያ ህገ መንግስት ጉዳይ እንዲህ ነበር።

ዛሬ ሀገ መንግስቱ «ብሄር፤ ብሄረሰቦች፤ ህዝቦች» የሚለውን አውጥቶ የቋንቋ ፌደራሊዝም እንዲሆን አስፈላጊ ለውጦች ቢደረግ ብቻ ታላቅ መሻሻያ ይሆናል። ለነ ይህ በቂ ባይሆንም ታላቅ ታላቅ ማሻሻያ ነው የሚሆነው። ህዝባችን እና መሪዎቻችን ይህን ለማድረግ ያብቃን።

ስለዚህ ጉዳይ አንዳርጋቸው ጽጌ ያለውን ከዚህ ቪዲዮ ብትመለከቱ ጥሩ ይመስለኛል፤ https://www.youtube.com/watch?v=mCUIw2ud8EM

Tuesday, 14 August 2018

ተረት ተረት፤ «ጎሰኝነት ዘረኝነት ነው»

ይህም ከፊል እውነታ አለው። አማራ ማየት አማርኛ መስማት የሚጠሉ ጸንፈኛ ኦሮሞ ብሄርተኞች አሉ። ግን ጎሰኝነትን «ዘረኝነት» ብሎ መሰየሙ ችግሩን በትክክል አይገልጸውም ወደ መፍትሄም ለመምጣት አይረዳም። ላስረዳ…

«ዘረኝነት» የሚለው ቃል ብዙ ትርጉም ያለው፤ የተወሳሰበ፤ ኃይል ያለው ቃል ነው። የምንጠቀምበት አንድ ነገርን ወይንም ሰውን ክፉ መጥፎ ነው ብለን ለመሰየም ነው። ከክፉ ጋር ውይይት የለም ድርድር የለም። «ዘረኝነት» ብለን ሰይመን ከዚህ ሀሳብ ጋር ውይይትም ድርድርም አያስፈልግም ነው የምንለው «ዘረኛ» ስንለው። ትክክለኛ አካሄድ አይደለም።

ጎሰኝነትን እስቲ እንደዚህ ብናየው ትክክለኛ ግንዛቤ እንዲኖረን ይረዳል ጎሰኝነትን ለመቀነስ ለማጥፋትም ምን ማድረግ እንዳለብን እንድንረዳ ይረዳናል። ጎሰኝነት ገና ሲጀመር በውይይት፤ በማስረዳት እና በማስተማር ማጥፋት ይቻላል። ግን ጎሰኝነት አንድ ደረጃ ካለፈ ውይይት ከሞላ ጎደል አይሰራም።

ለምሳሌ ጎሰኛው ኦሮሞነቱ እጅግ አይሎ ኢትዮጵያዊነቱ እጅግ ከመነመነ ስለ ታሪክ እና ፖለቲካ ምን ብትሰብከው ለውጥ ሃሳቡን አይቀይርም። «ዘረኛ» ብትለውም ፋይዳ የለውም። ይህ ስወ ዘረኛ ሳይሆን ማንነቴ ሙሉ በሙሉ «ኦሮሞ» ነው ብሎ ወስኗል። ሀገሬ ኦሮሞ ነው ኢትዮጵያ አይደለም ነው የሚለው። ኢትዮጵያን ይጠላ አይጠላ አይደለም ዋናው ጉዳይ። ኦሮሞ ነኝ ማለቱ ነው። ልክ እንደ ኢትዮጵያ እና ሱዳን የተለያዩ ሀገሮች እንደሆኑ ሱዳናዊው በኢትዮጵያ ያለው መብት ውስን እንደሆነ እንዲሁም በተገላቢጦሽ ለኦሮሞ ብሄርተኛው በኦሮሚያ እና ኢትዮጵያ ያለው ልዩነት እንዲሁ ነው። ሌላ ሀገር ንኝ ነው የሚለው። ይህን የማንነት ስሜቱን ደግሞ ልንከለክለው አንችልም። «ዘረኛ» ማለቱ ዋጋ የለውም ምናልባትም ማባባስ ነው።

ታድያ ጎሰኝነት ይህ ከሆነ ምን ችግር አለው ትሉ ይሆናል? የሀገሩ ማንነት መምረጥ የሰው ልጅ «መብት» ከሆነ ምን ክፋት አለው? «ዘረኝነት» ካላልነው መጥፎነቱን እንዴት እንግለጽ? መልሱ ቀላል ነው፤ ጎሰንኘት «መብት» ቢሆንም የታላቅ ግጭት ምንጭ ነው። በአንድ ሀገር ጎሰኝነት በተለይም ጎሰኝነት እና ብሶት (grievance) አብረው ሲኖሩ ከፉ ግጭቶች ይኖራሉ። ይህ በቴኦሪ ወይንም በሌሎች ሀገራት ብቻ የሚታይ ሳይሆን ለ27 ዓመት በኢትዮጵያ የታየ ነው። ለግጭቶች ደግሞ በመንግስት አምባገንነት አናሳብብ፤ መንግስት ያልተሳተፈበት ግጭቶች ብዙ ነበሩ አሁንም አሉ። አልፎ ተርፎ መንግስት በግጭቶቹ ቢሳተፍባቸውም ባለ ክፍተት ነው እየገባ እየበጠበጠ የነበረው እንጂ የሌላ ልዩነት የመፍጠር አቅም አልነበረውም።

ስለዚህ ጎሰኝነት ወይንም የጎሳ እና ሀገር ሚዛን ከልክ በላይ ወደ ጎሳ ሲያመዝን ችግሩ ጎሰኝነት «ዝረኝነት» መሆኑ ሳይሆን የግጭት ምንጭ መሆኑ ነው። መፍትሄውም የግጭት ምንጭ ነው ብለን ጎሳን እንደ ጽንሰ ሀሳብ ከሀገሪቷ ህገ መንግስት ማውጣት እና በ«ቋንቋ እና ባህል» ጽንሰ ሀሳቦች መተካት ነው።

ተረት ተረት፤ የትግራይ ገዥ መደብ አገዛዝ እና የ«አማራ ገዥ መደብ» አገዛዝ አንድ ናቸው

«የትግራይ ገዥ መደብ አገዛዝ እና የ«አማራ ገዥ መደብ» አገዛዝ አንድ ናቸው»። ይህ ተረት ተረት (myth) በበርካታ ሰዎች ሲደጋገም ወደ እውነታ እያማራ ነው። በቅርቡ ባደረጉት ኑዛዜአቸው የቀድሞ ጠ/ሚ ታምራት ላይኔም ደግመውታል። «የአማራ ገዥ መደብ ብይ አማራ ብዙሃን እንደነገዱት ነው ህወሓት የትግራይ ገዥ መደብ በትግራይ ብዙሃን የነገዱት» ብለዋል። ይህ አስተያየት እጅግ የተሳሳተ ነው።

የሁለቱ አገዛዞች መሰረታዊ ልዩነት ይህ ነው፤ በደርግ እና በንጉሳዊው ስርዓት ጎሳ፤ ዘውግ፤ ብሄር አይነት ጽንሰ ሀሳቦች በህግ ደረጃ አልነበሩም። አገዛዙ በህግ ደረጃ ከጎሳ እና ከጎሰኝነት ውጭ ነበር። በህወሓት አገዛዝ ግን ጎሳ እና ጎሰኝነት በህግ የተደነገገ ነው። ጎሰኝነቱ በልምድ ወይንም በባህል ደረጃ ሳይሆን ህጋዊ ነው። ይህ መሰረታዊ ልዩነት ነው።

በኃይለ ሥላሴ መንግስት ማንኛውም ግለሰብ በጎሳ ምክንያት ከመንግስታዊ ስልጣን እና ሹመት አይከለከልም ነበር። አይከለከልም ብቻ ሳይሆን ጎሳው ጭራሽ እንደ ጉዳይ አይነሳም፤ በህግ እና ስረዓት ደረጃ ጎሳ የሚባል ጸንሰ ሀሳብ የለም። በዚህም ምክንያት በኃይለ ሥላሴ መንግስት በርካታ ከተለያዩ ጎሳ የሆኑ ባለ ስልጣኖች ነበሩ።

ሆኖም የአስተዳደር ቋንቋው አማርኛ ነበር። ይህ ከጅማ ለተወለደው ኦሮሞ መሰናከል ነበር። የገዥ ስረዓቱ ንጉሳዊ ነበር። ይህ ከኮንሶ የተወለዱት ባዕዳዊ ስረዓት ነበር። በነዚህ አይነት ምክንያቶች አማራ ያልሆኑ ወደ ስልጣን ለመቅረብ ከአማራ ይልቅ ይከብዳቸው ነበር ማለት ይቻል ይሆናል። አማራ ቋንቋውን በማወቅ ከሌላው ይበልጥ እድል ነበረው ማለት ይቻላል። እንዲሁም የአዲስ አበባ ተወላጅ ይበልጥ እድል ነበረው ማለት ይቻላል። በዚህ ደረጃ በተለያዩ የጎሳ ተወላጆች የስልጣን እና ሹመት እድል ልዩነት መኖሩን መካድ አይቻልም። ግን ይህ ልዩነት የታሪክ አጋጣሚ ነው እንጂ በህግ የተደነገገ አልነበረም። ስለዚህ አማራ ያልሆነው ቢከብደውም ወደ ስልጣን መምጣት ይችል ነበር። አድሎ ነበር ግን አድሎው ህጋዊ አልነበረም ስለዚህ ሊቀለበስ የሚችል አድሎ ነበር።

የህወሓት አገዛዝ ግን መሰረቱ ጎሰኝነት ነበር። ህወሓት የትግራይ ድርጅት ለትግራይ ህዝብ ነው። አማራው በአማራነቱ ቦታ የለውም። ቋንቋ ባለመቻሉ ወይንም የፖለቲካ ባህሉን ባለማወቁ ሳይሆን በአማራነቱ ምክንያት ስልጣን ሊይዝ አይችልም። በህወሓት ዘመን አድሎ መቀልበስ የማይችል የጎሳ የደም አድሎ ነበር።

ይህን የ«ትግራይ ገዥ መደብ» እና የ«አማራ ገዥ መደብ» አገዛዝ ልዩነት ስንመለከት አንድ ትልቅ ትምሕርት እንማራለን። ይህ ስለ የጎሳ አገዛዝ አደገኝነት ነው። ጎሳ የትውልድ የደም ጉዳይ ስለሆነ በመሰረቱ ህዝብን የሚለይ እና አድሎ (discrimination) የሚያመጣ ነው። በዚህ ምክንያት ነው የጎሳ አገዛዝ የግጭት (conflict) ፋብሪካ የሚሆነው።

የጎሳ መብቶችን ለማስተናገድ የጎሳ አስተዳደርን ከመጠቀም ወይንም የጎሳ መብቶች በህግ ከማወጅ የቋንቋ እና የባህል መብቶችን ማደንገድ ይሻላል። ቋንቋ እና ባህል ማንም መማር መቀየር የሚችለው ስለሆነ መሰረታዊ አድሎ የላቸውም። በዚህ ምክንያት በአድሎ የተነሳ የተጨቋኝ ስሜቶችን አያዳብርም ስለዚህ ግጭትን አያበዛም።

ይህን ተመስርተን ነው የኢትዮጵያ ህገ መንግስት ጸንፈኛ ነው የምንለው። ዓለም ዙርያ ሀገራት የቋንቋ እና ባህል መብቶችን በህጋቸው ያስተናግዳሉ። የጎሳ መብቶችን በዚህ መንገድ ያስተናግዳሉ። ግን የትም ሀገር ጎሳን በህጋቸው አያስተናግዱም። በጎሳ እና በቋንቋና ባህል ያለውን ልዩነት በግጭት መጋበዝ አኳያ በድምብ የታወቀ ስለሆነ ነው እንዲህ የሆነው። ግን ኢትዮጵያ ብቸኛዋ ጎሳን በህግዋ ውስጥ ያካተተች ናት። ለሀገራችን ህልውና ይህን መቀየሩ አስፈላጊ ነው።

Wednesday, 11 July 2018

Towards an Integrated Ethiopia

Decades ago we used to be presented with a stark choice between a "unitary" state speaking Amharic, assimilating all other ethnic groups, and with nearly everything controlled by the central government, and approximately 85 separate nations, one for each of our ethnic groups! And unfortunately all debate revolved around these caricatures, and we never got anywhere.

Today, thankfully things have changed. We have, fortunately or unfortunately, data from 27 years of the radical experiment called ethnic federalism, where as much as was realistically possible, regions were drawn along ethnic lines and ethnicity ("nations, nationalities, and peoples") became the foundation of the Ethiopian state. I would say that these 27 years have shown us conclusively that this formula is one of ethnic strife, conflict, war, ethnic competition, ethnic-motivated mass dislocations, etc.

Some would say that what we have had is fake or bastardized ethnic federalism in which the TPLF ruled as a dictatorship and never really implemented the constitution in practice. This is certainly true to some extent, but enough was implemented to see the results. Ethnic based regions were created, ethnic based identity cards were encouraged in many regions, and there was some degree of self rule in the regions. Moreover, most of the ethnic conflicts throughout Ethiopia have not been related to TPLF dominance. Instead, they have been occurring between non-Tigrean ethnic groups. Take for example Amharas and other "non-locals" being evicted from various regions, or being hunted down and murdered in the name of retribution for historical injustices. Or conflicts between Gedeo and Guji, or Oromo and Somali, or Qemant and Amhara, or Agew and Amhara, etc. There are plenty of examples. It is clear that the placement of ethnicity at the centre of political life resulted in conflict and ethnic political competition, which is always a recipe for disaster. Despite the fact that the ethnic federalism experiment was not perfectly tried out, we have seen enough to know that it cannot work for Ethiopia.

As I say this, I have to add that the even EPRDF itself recognized a couple of years ago that this was the case. The main catalyst for this recognition was that the ethnic hatred inculcated by ethnic federalism started to target Tigreans more and more. The combination of ethnic federalism and the EPRDF's beloved developmental state was proving untenable. The public's resentment against the ruling class, as represented by the EPRDF, was not only based on politics and class, but on ethnicity - on anti-Tigrean sentiment. The resentment became virulent, and the EPRDF knew that things could not continue as is without full blown ethnic war. Hence the beginning of the opening of the EPRDF, and in particular the TPLF, to changes that eventually brought about Prime Minister Abiy Ahmed and his team to power.

So I think today it is clear that the ethnic federalism formula as we have it, even if implemented 'perfectly', is not a good solution for Ethiopia because it brings about conflict. Not because it is inherently unjust, but because we have evidence that it does not work and it results in concrete strife and misery. Why has it not worked? A few reasons... First, there is in many parts of Ethiopia ethnic resentment and historical baggage. Ethnic-based governance only exacerbates this. Second, a significant portion of our incapable political elite wish to use ethnic competition as a way to political power and have no qualms about encouraging ethnic conflict. Third, there has been over hundreds or thousands of years significant integration and even assimilation in Ethiopia, resulting in a large constituency not interested in ethnicity, but nevertheless persecuted by ethnic politics for historical grievance reasons and for not signing on to the ethnic ideology. For these and other reasons, and given the evidence we have, the current ethnic federalism formula should, in time, be abandoned.

Abandoned for what? For many of us, the choice today is between 1) an integrated and synthesized Ethiopianism or 2) an Ethiopia divided on ethnic lines - a nation of disparate nations. 2) is more or less what we have now, the recipe for ethnic strife and conflict. The first choice is, I think, our only choice. What is integrated and synthesized? It means reflecting as much is realistically possible and in keeping with the wants of the population everyone's identity in Ethiopianness. An obvious and often stated example of this: making the Oromo language a national language of Ethiopia, in addition to the current Amharic, integrates into Ethiopianness the use of the Oromo language. It moves it from the periphery, or from a single region, to the national level. Another example: integrating elements of the Gadaa political structure into the nation's political structure. And so on. What about other ethnic groups and their identities? What about the level of regional and local autonomy? These and several other questions can be answered via discussion and evolution. But the point is that integration and unity is the only way to peace and prosperity. A single Ethiopian identity must be cultivated, not to the exclusion of ethnic identity, but to ensure that it always supersedes ethnic identity, thereby reducing the temptation of ethnic politics and ethnic conflict.

What about the transition from ethnic based politics to this new "Ethiopian" politics? It should probably be slow since we have a generation schooled under the ERPDF's ethnic politics and we have a perhaps worse older political class schooled under Marxism and democratic socialism. The first step is to implement integrative policies such as the language policy I mentioned above. One of the goals of this policy is to increase inter-ethnic integration and increase the non-ethnicized population. After some years (or decades) of this, the proportion of non-ethnicized Ethiopians will be such that a transition to non-ethnic politics will be easy.

That is the plan. There are two hindrances that I see. First, the obvious, are the ideological and cynical ethnic politicians who would stand to lose from an abandonment of ethnic federalism. The second is the group against ethnic politics but which does not have the political savvy and empathy needed to relate to and hold discussions with ethnic federalists. The ethnic politicians we will always have with us - I don't think there is anything we can do but marginalize them. But the second group we should work on as if this group - I call it the Ethiopianist group - gets its act together, then we will have a smooth transition from today's combustible ethnic federalism to an integrated and synthesized Ethiopia.

Thursday, 11 May 2017

Using Canada To Understand Ethiopian Ethnic Federalism Today

I am fortunate to have acquired a somewhat intimate knowledge of Canadian politics and have found that, unlike US politics for example, Canadian politics holds wonderful parallels and lessons for Ethiopia in the area of federalism and ethnic federalism. So in this article I will briefly describe the history and nature of Canadian politics and how it can help us understand the Ethiopian political reality today, especially concerning ethnic federalism.

Here’s the (very) brief history… Canada was settled by English and French colonists beginning in the 1600’s. Soonafter, the English and French began warring for control of Canada (and North America as a whole), and around 1770, the English won decisively. However, in order to avoid problems with the large French population that had already settled in what is today known as the province of Quebec, the English government allowed the French to use their own language, worship in their own religion (Catholic), and to keep their own system of law (civil law). Over the following decades and centuries, the English continued to grant Quebec various such levels of autonomy and self-governance, both official and unofficial. For example, Quebec had its own legislature and French and both provincial and federal government services were provided in French and English. Unofficially, almost every second Canadian Prime Minister from 1867 (the official formation of Canada) onwards was French.

Nevertheless, despite such increasing levels of autonomy and recognition of language rights (note that it was always refered to as ‘language’, not ‘ethnic’ rights), ethnic nationalism in the French province of Quebec did not go away. The idea that Quebec was different from the rest of Canada, to the extent that it should secede and be a different country, actually grew over the decades despite increasing political and economic fortunes. So much so that in the late 1960’s and early 1970’s, there was a small armed resistance advocating for the separation of Quebec. This was followed by increasing support for even more autonomy and even secession among both the Quebec population and its French elite.

This resulted in two referendums on secession. In the first referendum of 1980, the ‘yes’ side – the secession side - lost by a significant margin. But, the fact that it was held at all and that it gained 40% support scared enough people that the federal government took even further steps to give Quebec more autonomy, to increase the prominence of French throughout the country, and to unofficially increase the amount of money Quebec got from the federal government. Yet, despite this, a second referendum was held 1995, strategically at a time when the economy was in recession and people were angry. This referendum was again won by the ‘no’ side, but by only one percentage point 50.5% to 49.5%! Significantly, 60% of native French speakers voted for secession, but almost 100% of English and other language speakers voted against secession. Thus, despite being a small minority, non-French speakers were the decisive voters in the referendum.

Today, there is little interest in secession in Quebec – or to put it more accurately, it seems impossible for the 40% of Quebec who still support secession to get enough support from the rest of the population to win a referendum.

What are the lessons to learn from this Canadian example for Ethiopia?

Modernization, rather than reducing ethnic nationalism, can actually increase it. As Quebec modernized, became less religious, more affluent, etc. support for ethnic nationalism, manifested in reduction in English and other (non-French) language rights, secession from Canada, etc. actually increased! Modernization and increased ethnic nationalism go hand in hand.

Canada over the centuries embarked on various policies aimed at accommodating and satisfying the demands of French Quebecers such as the granting of extensive language rights, allowing the suppression of English and other languages in Quebec, making French an official language of the entire country despite only a tiny French population outside Quebec, transfering large amounts of federal money to Quebec despite the wealth of Quebec, etc. The political calculation was that if the demands of French Quebecers were met, they would be less likely to manifest their ethnic nationalism in ways that would cause dramatic damage the rest of Canada, such as secession. This shows that ethnic nationalism cannot be defeated by a stick – it requires plenty of carrot.

However, all over the above policies may have slowed the pace of increasing ethnic nationalism, but did not stop it. The results of the 1995 referendum, which almost initiated a process of secession or at least more separated federal arrangement, shows that accommodating ethnic nationalism, though helpful for some time, will not at the end stop the movement.

Ethnic nationalism does not fundamentally mean secession. It is the desire of a certain group for special rights above the rights of the rest of the population, in recognition that this group is a nation, or a pseudo-nation. For hardline ethnic nationalists, this recognition can only be realized within a politically separate nation. For ‘softer’ nationalists, having asymmetric rights within one nation is enough. Having more autonomy than other provinces, having a French-only province, having the federal language use French equal to English, etc. is enough for them to express their nationhood. The common theme however is that it has to have special rights as a group, even though these rights impinge upon the rights of other citizens.

An immigrant to Quebec cannot send his child to English school. English has not official status as a language in Quebec. Anyone in Quebec who does not speak French is de facto a second class citizen. More so than someone who does not speak English and lives in the English parts of Canada. ‘Native’ Quebecers – those who trace their ancestry to the original French Quebecers – are a privileged class in Quebec, even more so that ‘native’ English are in the rest of Canada. These are the practical consequences of ethnic nationalism – asymmetric rights and privilege that impinge on others’ rights.

Quebec nationalists go out of their way to emphasize that theirs is not an ‘ethnic’ nationalism, but a geographic (Quebec) or language-based (French) nationalism. The reason is that ethnic nationalism is seen within Canadian politics as a whole as primitive and potentially discriminatory. Thus when after the failed 1995 referendum one of the leaders of the Quebec separatist movement (truthfully) said that they lost the vote because of English speakers and immigrants, he was roundly denounced by his own side. What he said was true but not the perception of Quebec separatism that separatists wanted to portray. They wanted to portray their side as open to all, especially immigrants, with the common goal of having an independent Quebec. Ethnic nationalism is in a mature political arena seen as too divisive and dangerous by all sides.

Ethnic nationalism is politically costly. Since its inception, Canada has an extraordinary amount of its political energy on this issue. This energy could have been better spend on the myriad of other matters, such as the economy, trade, government organization, etc. that are everyday political issues in any other nation. The cost has been not only to Canada as a whole, but particularly to Quebec. In Quebec, most issues are sign primarily or at least secondarily through ethnic nationalist implications. Even political parties are organized around this issue, instead of around other ideology or interest groups.

Ethnic nationalist is economically costly. Canada spends significant amounts of money implementing the asymmetrical rights and privileges to Quebec that I mentioned above. The Quebec economy, too, has long been held hostage to the ethnic nationalist movement’s desire to use the economy first and foremost as a tool to promote its ethnic nationalist agenda.

Ethnic nationalism can only be significantly weaked through demographics, including integration and assimilation with the rest of the population. As I said above, though accommodation is often necessary and helpful, at the end of the day, it will only slow the tide of ethnic nationalism, not stop it. If it were not for the changing demographics in Quebec resulting from increasing numbers of immigrants, today Quebec might be a separate country or a very separate province in Canada. Immigrants and their children have increased the population of those whose mother tongue is not French to over 20%, and This group is not only not part of Quebec nationalism, but against it. Whereas accommodation could not defeat ethnic nationalism, demographics has done the job. For now.

These lessons are, as far as I am concerned, very much applicable to today’s Ethiopia. For me, Quebec mirrors Oromia. Oromia, notwithstanding the policies of the EPRDF, is today the one and major Ethiopian state where ethnic nationalism has a significant political impact. Yes, there is ethnic nationalism in other states, but where it is strongest and has to be dealt with ‘specially’ is in Oromia. Oromia, because of history and EPRDF policies, is Ethiopia’s asymmetric state – the one that requires special political attention, the one that is most costly, and the one for whom policies of accommodation, but more importantly integration and assimilation have to  be especially targeted. I will address how I think this should be done in another article.

Tuesday, 4 October 2016

Ethnic federalism kills Meles' developmental state

2009/1/23 (Ethiopian calendar)
2016/10/3 (European calendar)

[Note: An Amharic version of this post will appear sometime!]


In a nutshell, the EPRDF's deal or social contract with the Ethiopian population over the past 15 years or so has been as follows: I will give you development and growth. In exchange, you will not challenge my political power and you will ignore the fact that my membership will have certain economic and other privileges that the rest of you will not have.

This is what a 'developmental state' led by a 'vanguard party' basically is. The classic example is China. We all know that the Chinese people, in aggregate, have prospering for years. People have been getting richer, there's more education, better health care, better infrastructure, etc. Again, this is in aggregate – large sections of the population have suffered for this and continue to suffer, but let's set that aside for the moment. As far as Ethiopians are concerned, when they see China, they see prosperity.

Now, the only political party in China – the Communist Party – has no political competition, which means there is little accountability. Party members can enrich themselves through corruption and other means and the population can do nothing about it because it cannot get rid of the party – that's part of the deal. Now, if this corruption threatens economic development and therefore threatens the Communist Party's deal with the people, which would then lead to revolt and overthrow of the party, then there's a crackdown on corruption. So as we all have seen, every so often, the party campaigns against corruption, arrests a few thousand party members and cronies, and then when it all dies down forgets about it for a while. Corruption goes up again.

Now, why isn't this working in Ethiopia? Development is taking place, economic growth is pretty good, the big projects such as the Nile Dam are still going strong. So why the unrest? Why the revolt?

The answer is ethnic federalism. You see, in China, there is more or less only one ethnicity. The population resents the privileges of the members of the Communist Party. People resent that party members are rich, have preferential treatment in everything, including the legal system, jobs, contracts, etc. However, the resentment is what we might call class resentment. The upper class is the Communist Party and the lower class the rest of the population. The upper class makes sure the lower class does quite well – not as well as the upper class but well enough to keep politically quiet.

In Ethiopia not only do we have many ethnicities, but ethnicity is part of the government! The vanguard party EPRDF is composed of ethnic parties, and the most powerful party as everyone knows and perceives is the TPLF. Just as in China, the population resents the privileges of the members of the EPRDF and their relatives and cronies. But this resentment is much greater and politically dangerous than in China because the resentment is not just class resentment, but ethnic resentment, and ethnic resentment is extremely dangerous.

As I have written before, people are far more tolerant of oppression by their own ethnic group or no ethnic group than by another ethnic group, or by what they perceive to be another ethnic group. When it comes to political oppression, ethnic feelings are strong. This is why the combination of developmental state and ethnic federalism is not working in Ethiopia.

By the way, this understanding of ethnicity as a strong political force is precisely the basis of of ethnic federalism! We need ethnic federalism, ethnic group rights above all else, etc., because ethnicity is the basis our polity, is what Meles and the EPRDF said when creating the constitution. If we do not give ethnicity this primacy, then there will be an ethnic revolt, they said. What irony then, that the ethnic division they laid in place for this reason is precisely that which is is proving their downfall.

Now, how can the EPRDF get out of this quagmire. The band aid solution is to try and severely clamp down on corruption, which it has tried to do repeatedly. But how can the EPRDF do that given the nature of the vanguard party / developmental state model, since party privilege and corruption is an unavoidable consequence of it? The other option is to do something about ethnic federalism. Of course the EPRDF can't touch the constitution, but as we have heard there is a proposal within the party to change it from a multi-ethnic front to a single non-ethnic party, thereby reducing the ethnic glare, so to speak, from the population. But this will alienate the EPRDF's more fervent ethnic nationalists, but at the same time it won't attract civic nationalists. This might have been a good option 20 years ago, but now it's too little too late.


In a later article, I will discuss what I think is a better solution for the EPRDF.

Where the TPLF went wrong

2009/1/23 (Ethiopian calendar)
2016/10/3 (European calendar)

[Note: An Amharic version of this post will appear sometime!]


A lot has been written about this over the past 25 years, but it doesn't hurt repeating, especially given today's political circumstances in Ethiopia. The TPLF's biggest historical mistake was interpreting its coming to power in 1991 as a full mandate from the vast majority of Ethiopians and assuming it meant a complete rejection of everything that preceded it. This mistaken assumption involved a typically modern Ethiopian exercise in black and white or zero sum thinking.

Basically, this is how the thought process worked... The Haile Selassie government fell, not because it failed to make some sensible reforms, but because it failed to make all the radical changes demanded of it by the students movement. The fall of the Dergue government had nothing to do with the Cold War, a failed Communist economy, or the war with Somalia, but because Ethiopia was a prison of nationalities that had to be liberated. The rise of the TPLF had nothing to do with the end of the Cold War and a bankrupt regime, but because the TPLF and its ethnic ideology best represented the interests of a majority of Ethiopians. The TPLF blinded itself to obvious facts in a bid to convince itself of its monopoly on truth and ability to rule Ethiopia.

Thus, after gaining power, the TPLF, in the form of the EPRDF, began a ruling style that involved continually trying to do the radical and the impossible, its hubris deluding it into believing that it was special enough to do anything politically.

This mindset is what emboldened the EPRDF to saddle Ethiopia (and itself) with perhaps the most radical ethnic based constitution in world history. With a little more maturity, it would have realized that this constitution was not only unpopular and fundamentally at odds with the interests of a large section of the population, but so radical, untested, and risky that there was a good chance it would in the future make governing impossible. For everyone except the EPRDF and other ethnic nationalists, it was clear that a more moderate constitution would have easily satisfied all constituencies, including ethnic nationalists and made governing far easier for the EPRDF.

Building on the constitution, the EPRDF embarked on an ethnic policy that can only be described as playing with fire. It engaged in policies (such as official identification by ethnicity) and rhetoric ('reactionaries' and 'narrow nationalists') that emphasized differences among Ethiopians and diminished commonalities. It thought that it could promote ethnic nationalism and at the same time control ethnic strife, knowing full well that its ethnic political base, Tigray, was composed of a small minority! An impossibly delicate formula if there ever was one. However, thanks to various factors, especially the sad state of the Ethiopian nationalist elite, the EPRDF has managed so far to survive on this knife's edge.

But the fundamentals remain wrong, and this explains today's smoldering dissent. It's a political reality that a people can tolerate far more oppression from their own ethnic group or in a non-ethnic context than they can from another ethnic group. The TPLF knows this quite well, having leveraged the political tool of ethnicity to its fullest during its liberation struggle. Yet, the EPRDF continued a policy of promoting ethnic nationalism while real power and perception of real power, remained in the hands of the TPLF. This has inevitably resulted in widespread resentment against the TPLF and Tigray. This was all predictable from the beginning; there have been ever increasing signs of it in the past two decades, yet hubris has prevented the EPRDF from changing course.

Note that this policy from the beginning was the antithesis of what is best for Tigray. A small minority can flourish in a multi-ethnic society, but not in a society where ethnic division and tension dominate, since the minority is dependent on migration and integration to prosper. The region of Tigray, like all the small ethnicities in Ethiopia, would do best in a country that is more united than divided. Yet, the ideology of the TPLF (and its big brother EPLF) was so ingrained that they basically ignored this danger and continued promoting ethnically divisive policies.

To be fair, the EPRDF did eventually realize the seriousness of the problem. Part of the reasons for the full mobilization of party resources towards the developmental state project ('lemat', for the masses) that begin during the mid part Prime Minister Meles' tenure was to mitigate ethnic division. The rhetoric of economic development was ramped up as a political tool to promote civic nationalism – to give all parts of the country something in common to unite around – and counter the obvious damage of ethnic nationalism. But of course the economy cannot by itself bring down ethnic boundaries and increase civic nationalism. Inter-ethnic integration, which the EPRDF's constitution essentially prevents, is the only way to do so.

The above is just a small list of the radical and reckless policies of the EPRDF over the past 25 years, which aros a consequence of the circumstances around its rise to power, including the absence of an opposing elite power to act as a moderating influence. Now, what does this history teach us about what is happening today? What is happening today?

Well, we continue to hear from hardline EPRDF leaders the same old rhetoric about reactionaries and narrow nationalists – the same old hubris. But there are moderates in the EPRDF and TPLF who have long ago come to realize the folly in their fundamental assumptions. These moderates and hardliners are discussing behind closed doors how to address the current revolt. The moderates are right and sensible, of course, but what has always handicapped them is external leverage. They need a strong Ethiopian nationalist movement and elite, the opposing elite power which I mentioned above, with power on the ground, that they can count on as a foil for the hardliners. They need a political partner on the other side, in other words, so that they can say to the hardliners, “Look, you've tried it your way, and now there is an opposition that your hardline policies cannot dislodge. It's time for you to step aside and let us negotiate a new system of governance.”

Unfortunately, this Ethiopian nationalist movement is not yet there. The soft and hard ethnic nationalists in Oromia who are against TPLF domination have been doing their part for years, but not the Ethiopian nationalists. Now we have the uprisings in Amhara Region, and this is a huge step in the right direction, but there is no organization yet. It is important that these uprisings soon coalesce into a tangible political movement so that it can work with the moderates in EPRDF to find a way out if its quagmire. Failing this, we have to count on the EPRDF reforming by itself. It's a tall order for any organization, especially on with the historical baggage of the TPLF.