የኢሳት ተንታኞች ኤርሚያስ ለገሰ እና ሃብታሙ አያሌው አቢይ እየዋሸላቸው ኦዴፓ የክህደት ስራ ሰሩ የሚል ትርክት ጀምረዋል። ይህ ትርክት ለኢትዮጵያዊነት ኃይሉ እና ለአዲስ አበባ ህዝብ ትግል ይጠቅማል ዋይ ነው ጥያቄው?
እንደሚገባኝ ይህ ትርክት ሁለት አላማ አለው፤
፩) የአዲስ አበባ ህዝብ እና ሌላው የኢትዮጵያዊነት ጎራውን ለማስነሳት
፪) የዓቢይ መንግስት (እና ለማ እና ኦዴፓ) ላይ ጫና መፍጠር
እስቲ «ዓቢይ ከዳን» የሚለው ትርከት እነዚህን ግቦች ሊያሳካ ይችላል ወይ ብለን እንመልከት...
፩) «ጠላቶችን» በኃይል በመተቸት ህዝቡን ማነቃቃት እና ማስነሳት ኢሳት እና ሌሎች ለረዥም ዓመታት የሞከርነው ስልት ነው። አልሰራም ነው የምለው። የፖለቲካ ለውጡ የመጣው ህዝቡ የትግሬ የበላይነት እና የህወሓት ጭቆና ስለበቃው ነው። የበቃው ደግሞ «እየተቆንክ ነው» ስለተባለ አይደለም፤ የለት ኑሮው ስለሆነ ነው። ይህ የሚያሳየን የ«ለቅሶ ፖለቲካ» ማለትም ጨቋኝን መተቸት እና ስለ ጨቋኝ ማልቀስ ህዝቡን አያስነሳም። ስለዚህ አሁንም «አቢይ ከዳን» ማለት ህዝቡን አያስነሳም። ህዝቡ አሁን የሚያስፈልገው ጠላት አይደለም፤ ጠላቱን ያውቃል።
፪) የዓቢይ መንግስት ይህን አይነት ጫና አይመልስም። መንግስቱ/ኦዴፓ ጸንፈኞቹን የሚያስተናግደው አምኖበት ነው፤ ተገዶ ነው፤ ወይንም የረዥም እቅድ ስልት ይህን የወረ ጫና ምንም አይቀይረውም። በጸንፈኝነቱ አምኖበት ከሆነ ከኃይል በቀር ምንም አይመልሰውም። ተገዶ ከሆነ አሁንም ኃይል ነው አስገድዶ የሚመልሰው። ስልት ከሆነ ደግሞ አሁንም የኛን ጫና ignore ማድረግ ግድ ይሆንበታል ግቡ እስኪሳካ።
ሰልዚህ «ዓቢይ ከዳን» የሚለው ትርክት ግቦቹን አያሟላም። እርግት ለስሜታዊ ጩኸት እና እሮሮ ይመጫል። ግን ሰከን ብለን ካሰብነው ጥቅም የለውም።
አልፎ ተርፎ ጉዳት አለው። እንደተለመደው ገመደራጀት ስራችን distract ያደርገናል። ለ27 ዓመት እየጮህን ችግራችንን ህወሓት ላይ እያሳበብን መደራጀት አልቻልንም። እነ ዓቢይ መጥተው ህወሓትን አባረሩልን። አሁንም የመደራጀት አለምቻል በሽታችን ላይ ከማተኮር ፋንታ የ«አቢይ ከዳን» ትርክት ላይ ካተኮርን የትም እንቀራለን።
ሌላው ጉዳት ለፖለቲካዊ የዋህነት/ጅልነት እጃችንን መስጠት እና ትክክለኛ ግንዛቤ ማጣት ነው። የዓቢይ መንግስት የህወሓትን አገዛዝ ለመድገም ነው ከመጀመርያ የተነሳው ማለት እጅግ የተንሸዋረረ አመለካከት ነው። ፖለቲካ የalliance ጉዳይ ነው። ከማን ጋር ነው የምንጋራው እና ጥቅማችን የሚመሳሰለው የሚለውን ነገር አብጥረን ማወቅ አለብን። እና ዓቢይን ከነ ኦነግ ጋር መቀላቀል አደገኛ የዋህነት ነው።
ስለዚህ ሰከን እንበል። ይህ ሁሉ ችግር የመታው ባለመደራጀታችን ነው። የአንድ ዓመት እድል አልፎናል። እስካሁን የኢትዮጵያዊነት ኃይሉ እና/ወይንም የአዲስ አበባ ህዝብ 100 ሚሊዮን ብር በጄት ያለው እና ሚሊዮን አባል ያለው ድርጅት መፍጠር ነበረበት። የፓርቲ አባላትን አሰልጥኖ ቢያንስ አዲስ አበባን በአንድ ለአምስት መቆጣጠር ነበረበት። በየመዋቅሩ ሰው ነአ ድር መዘርጋት ነበረበት። ይህን ሁሉ አላደርገንም። ባልማረጋችን ነው ችግሮች የቀጠሉት። አሁንም «ዓቢይ ከዳን» ብለን ማልቀስ ይህንን ግብ አያመጣም። ዋና ግባችን ላይ ብናተኩር ይሻላል።
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Showing posts with label ODP. Show all posts
Showing posts with label ODP. Show all posts
Tuesday, 12 March 2019
የሰከነ አስተያየት ስለ ዓቢይ እና ኦዴፓ
ስሜታዊ መሆን አይበጅም... ይህን የፍፁም ፈቃዱ ትክክለኛ ትንታኔ ያንብቡ።
(https://www.facebook.com/fitsum.fikadu.96/posts/2138544319567816)
ቁምነገሩ ጦርነቱን ማሸነፍ ነው
በቅድምያ በአደጋው ለተጎዳነው ሁሉ ፈጣሪ መፅናናት ይሁነን እላለሁ።አዎ እርሱው ፈጣሪ ኢትዮጵያዬን እንዲህ ካለው ሃዘን ሁሌም ይጠብቅልን እያልኩ በሰሞኑ የፖለቲካችን ፈተና ዙሪያ እንዲህ እንደሚከተለው ልል ወድጃለሁ።
የዶ/ር አብይ ቡድን ማለቴ ቲም ለማ ሃገርን አንድ ለማድረግ ከፍተኛ ትግልና ውጥረት ውስጥ ሆኖ ይታየኛል።ጁሃር (ኦነግ፣ ቄሮ) እነርሱን (ማለትም ቲም ለማን) ከኦሮሞ ህዝብ ጋር ለማጣላት ጠንክሮ እየሰራ መሆኑን አምናለሁ። እነርሱም ይህ ስለገባቸው ህውሃትን ቀስ በቀስ ድባቅ የመቱበትን ያንኑ የተለመደ ለዘብተኛ የሚመስል ግን ውስጠ ወይራ አካሄዳቸውን እየተገበሩበት ይገኛሉ። እነዚህ ብልህ መሪዎች መሬት እስከሚይዙ ድረስ ለህውሃት ተገዢና ተልመጥማጭ መስለው እንዴት አዘናግተው በጡረታ ስም ገሸሽ በማድረግ ከዚያም ጊዜ ጠብቀው እነዛኑ አይነኬ መሣይ የህውሃት መሪዎች ወደ ማሰር ውስጥ እንደገቡ ሳስብ፤ ይሄ በስሜት የሚነዳው ህዝባችን በሚፈልገው ፍጥነት ባለመሄድ ውስጥ ውጤት እንዳለ ያሳዩኛል።የእነዚህ ሰዎች አካሄድ ልክ እንደ ሺቭ ኬራ አባባል ዓይነት ነው።ማለትም፦ አሸናፊነት ማለት እያንዳንዱን የጦር ግንባር ማሸነፍ ማለት ሳይሆን ጦርነቱን ማሸነፍ ማለት ነውና።
ጁሃር በዚህም በእዛም ብሎ፤ "እኛ ከየኦሮሞ ህዝብ ጥቅምና አጀንዳ ይልቅ የምናስቀድመው የኢትዮጵያ ህዝብን አጀንዳና ጥቅም ነው" ብለው ዛሬውኑ በአደባባይ እንዲናገሩ ለማድረግ ያልወጋጋቸው ቦታ የለም። ም/ቱም ለእርሱ እንዲህ ማስባል ማለት እነርሱን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እስካሁንም በጥርጣሬ እያያቸው ካለው ከቄሮና ፅንፈኛ የኦሮሞ ብሄርተኞች ጋር ሙሉ ለሙሉ ማቆራረጥ እናም ቦታቸውን (ምርጫ ባስፈለገ ጊዜም ሆነ በአዘቦቱ ጊዜ) በኦነግ ማስቀማት ብሎም የእራሱን ርካሽ ተወዳጅነት በአክራሪ ኦሮሞ ብሄርተኞቹ መካከል ያለስጋት ማስፈን መሆኑን ስለሚያውቀው ነው።በከፍተኛ ፈተናና ጫና ውስጥ ያሉት ኢትዮጵያውያኑ ብልሆቹ መሪዎች ግን ገብቷቸዋልና፤ ቪዥናቸውን ከዳር ማድረስ እንዳለባቸው ስለሚያውቁ መረጋጋት ያለበትን በማረጋጋትና ባላንስ በመስራት ስራ ላይ ናቸው።
ኢትዮጵያውያኑ መሪዎች አዲስ አበባን ለኢትዮጵያውያን ሁሉ ብቻ በእኩል እንድትሆን እንደሚመኙ ግልፅ ማሳያው እኮ፤ መጀመሪያውኑ የኮንዶሚኒየም ዕጣ ማውጣታቸው ነው።ከዚህ በተጨማሪም አገር ሰላም ብሎ የኮንዶሚኒየም እጣ ያወጣው ደግሞ የኦዴፓ አባላቸው ማለትም ታከለ ሆኖ ሳለ ወዲያውኑ የጁሃር ጫጫታ ወደ ደም ማፋሰስ ሊሻገር መሆኑ ሲገባቸው፤ ፅንፈኞቹን ለማረጋጋትና የኦሮሞን ህዝብ ለማሳመኛ የሚሆናቸውን ጊዜ ለመግዛት የሆነ ዓይነት መግለጫ "በሌላኛው" የኦዴፖ ገፅ አውጥተው ጉዳትን ተከላክለዋል። ዳሩ ግና በስሜት የሚንቀለቀለው የህዝባችን አካል ጠረጠራቸው። እነርሱ ግን ምንተዳቸው፤ ግባቸው የብሄር ፖለቲካን ከኢትዮጵያ ምድር ለመጨረሻ ጊዜ ማጥፋት ነውና፤ ይኸው ውጥናቸው ሲሳካ ለሁሉ ምላሽ ይሆነናል በሚል ተስፋ አሁንም ዋና ስራቸው ላይ ናቸው። አዎ በብሄር ፖለቲካ ሃገራቸውን እንዲህ ቁምስቅሏን በማሳየት እያንገላታት ያለውን ኢህአዴግንም ሆነ ኦዴፓቸውን ፍርስርስ አድርገው በህብረብሄራዊ ፓርቲ መተካት ደግሞ፤ የለዘብተኛ መሳይ አካሄዳቸው የመጨረሻ ግብ በዚያውም የጁሃርም ሆነ የኦነግ አሊያም የወላጃቸው የህውሃት ወይም ደግሞ የሌሎች ዘረኛ መሰሎቻቸው ሁሉ ሃሳቦች ግብአተ መሬት እንዲሁም የኢትዮጵያዬ ትንሳዔ መሆኑ ገብቷቸዋልና፤ ለስኬቱ ትግልና ጫና ውስጥ ናቸው። እኛስ የት ነን?
(https://www.facebook.com/fitsum.fikadu.96/posts/2138544319567816)
ቁምነገሩ ጦርነቱን ማሸነፍ ነው
በቅድምያ በአደጋው ለተጎዳነው ሁሉ ፈጣሪ መፅናናት ይሁነን እላለሁ።አዎ እርሱው ፈጣሪ ኢትዮጵያዬን እንዲህ ካለው ሃዘን ሁሌም ይጠብቅልን እያልኩ በሰሞኑ የፖለቲካችን ፈተና ዙሪያ እንዲህ እንደሚከተለው ልል ወድጃለሁ።
የዶ/ር አብይ ቡድን ማለቴ ቲም ለማ ሃገርን አንድ ለማድረግ ከፍተኛ ትግልና ውጥረት ውስጥ ሆኖ ይታየኛል።ጁሃር (ኦነግ፣ ቄሮ) እነርሱን (ማለትም ቲም ለማን) ከኦሮሞ ህዝብ ጋር ለማጣላት ጠንክሮ እየሰራ መሆኑን አምናለሁ። እነርሱም ይህ ስለገባቸው ህውሃትን ቀስ በቀስ ድባቅ የመቱበትን ያንኑ የተለመደ ለዘብተኛ የሚመስል ግን ውስጠ ወይራ አካሄዳቸውን እየተገበሩበት ይገኛሉ። እነዚህ ብልህ መሪዎች መሬት እስከሚይዙ ድረስ ለህውሃት ተገዢና ተልመጥማጭ መስለው እንዴት አዘናግተው በጡረታ ስም ገሸሽ በማድረግ ከዚያም ጊዜ ጠብቀው እነዛኑ አይነኬ መሣይ የህውሃት መሪዎች ወደ ማሰር ውስጥ እንደገቡ ሳስብ፤ ይሄ በስሜት የሚነዳው ህዝባችን በሚፈልገው ፍጥነት ባለመሄድ ውስጥ ውጤት እንዳለ ያሳዩኛል።የእነዚህ ሰዎች አካሄድ ልክ እንደ ሺቭ ኬራ አባባል ዓይነት ነው።ማለትም፦ አሸናፊነት ማለት እያንዳንዱን የጦር ግንባር ማሸነፍ ማለት ሳይሆን ጦርነቱን ማሸነፍ ማለት ነውና።
ጁሃር በዚህም በእዛም ብሎ፤ "እኛ ከየኦሮሞ ህዝብ ጥቅምና አጀንዳ ይልቅ የምናስቀድመው የኢትዮጵያ ህዝብን አጀንዳና ጥቅም ነው" ብለው ዛሬውኑ በአደባባይ እንዲናገሩ ለማድረግ ያልወጋጋቸው ቦታ የለም። ም/ቱም ለእርሱ እንዲህ ማስባል ማለት እነርሱን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እስካሁንም በጥርጣሬ እያያቸው ካለው ከቄሮና ፅንፈኛ የኦሮሞ ብሄርተኞች ጋር ሙሉ ለሙሉ ማቆራረጥ እናም ቦታቸውን (ምርጫ ባስፈለገ ጊዜም ሆነ በአዘቦቱ ጊዜ) በኦነግ ማስቀማት ብሎም የእራሱን ርካሽ ተወዳጅነት በአክራሪ ኦሮሞ ብሄርተኞቹ መካከል ያለስጋት ማስፈን መሆኑን ስለሚያውቀው ነው።በከፍተኛ ፈተናና ጫና ውስጥ ያሉት ኢትዮጵያውያኑ ብልሆቹ መሪዎች ግን ገብቷቸዋልና፤ ቪዥናቸውን ከዳር ማድረስ እንዳለባቸው ስለሚያውቁ መረጋጋት ያለበትን በማረጋጋትና ባላንስ በመስራት ስራ ላይ ናቸው።
ኢትዮጵያውያኑ መሪዎች አዲስ አበባን ለኢትዮጵያውያን ሁሉ ብቻ በእኩል እንድትሆን እንደሚመኙ ግልፅ ማሳያው እኮ፤ መጀመሪያውኑ የኮንዶሚኒየም ዕጣ ማውጣታቸው ነው።ከዚህ በተጨማሪም አገር ሰላም ብሎ የኮንዶሚኒየም እጣ ያወጣው ደግሞ የኦዴፓ አባላቸው ማለትም ታከለ ሆኖ ሳለ ወዲያውኑ የጁሃር ጫጫታ ወደ ደም ማፋሰስ ሊሻገር መሆኑ ሲገባቸው፤ ፅንፈኞቹን ለማረጋጋትና የኦሮሞን ህዝብ ለማሳመኛ የሚሆናቸውን ጊዜ ለመግዛት የሆነ ዓይነት መግለጫ "በሌላኛው" የኦዴፖ ገፅ አውጥተው ጉዳትን ተከላክለዋል። ዳሩ ግና በስሜት የሚንቀለቀለው የህዝባችን አካል ጠረጠራቸው። እነርሱ ግን ምንተዳቸው፤ ግባቸው የብሄር ፖለቲካን ከኢትዮጵያ ምድር ለመጨረሻ ጊዜ ማጥፋት ነውና፤ ይኸው ውጥናቸው ሲሳካ ለሁሉ ምላሽ ይሆነናል በሚል ተስፋ አሁንም ዋና ስራቸው ላይ ናቸው። አዎ በብሄር ፖለቲካ ሃገራቸውን እንዲህ ቁምስቅሏን በማሳየት እያንገላታት ያለውን ኢህአዴግንም ሆነ ኦዴፓቸውን ፍርስርስ አድርገው በህብረብሄራዊ ፓርቲ መተካት ደግሞ፤ የለዘብተኛ መሳይ አካሄዳቸው የመጨረሻ ግብ በዚያውም የጁሃርም ሆነ የኦነግ አሊያም የወላጃቸው የህውሃት ወይም ደግሞ የሌሎች ዘረኛ መሰሎቻቸው ሁሉ ሃሳቦች ግብአተ መሬት እንዲሁም የኢትዮጵያዬ ትንሳዔ መሆኑ ገብቷቸዋልና፤ ለስኬቱ ትግልና ጫና ውስጥ ናቸው። እኛስ የት ነን?
Sunday, 10 March 2019
ለማ መገርሳ ልክ ነው፤ የዴሞግራፊ ለውጥ ግድ ነው
ከዚህ በፊት እንደጻፍኩት የጎሳ ብሄርተኝነትን ከፖለቲካችን ለመቀነስ እና ለማጥፋት የዴሞግራፊ ለውጦች ማምጣት ግድ ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/curbing-ethnic-nationalism-via_26.html)። ምከንያቱ ባጭሩ እንዲህ ነው...
የጎሳ ብሄርተኝነት ህዝብ ውስጥ በተለይ የኦሮሞ ህዝብ ውስጥ በደምብ እንደገባ ሁላችንም ገብቶናል። በልሂቃን ደረጃ ብቻ ሳይሆን በብዙሃን ደረጃም። ይህን ጎሰኝነት በስብከት እና ልመና ማጥፋት አይቻልም። የተም ሀገር የጎሳ ብሄርተንኘት አንዴ ከሰፈነ የሚቅንሰው ነገር ፖለቲካዊ ድርድር ሳይሆን የዴሞግራፊያዊ ለውጥ ብቻ ነው። በኢትዮጵያ የሚያስፈልገው የዴሞግራፊ ለውጥ በኦሮሞ እና ሌላው ኢትዮጵያዊ መካከል መቅላቀል እና ውህደት (integration and assimilation) ነው። ህዝቡ ተቀላቅሎ ተጋብቶ ተዋልዶ የቅይጥ ባህል እና ህዝብ መጨመር አለበት። በዚህ መንገድ የጎሳ ብሄርተኛው ጎራ እያነሰ ይሄዳል የፖለቲካ ኃይሉም ይመነምናል። ይህን የሚያስፈጽም አንድ ፖሊሲ ኦሮምኛ የህገር ሙሉ ቋንቋ ማድረግ ነው። ይህ ኦሮሞዎች ከኦሮሚያ ወደ ሌላው ኢትዮጵያ እንዲፈልሱ ይጋብዛል። ለምሳሌ ኦሮምኛ ለማስተማር ወደ አማራ ክልል ይመጣሉ። ይህ ፈልስት መቀላቀልን እና መወሃድን ያመጣል። ከላይ የጠቀስኩት ጽሁፍ ባጭሩ ይህን ነው የሚለው።
በቅርቡ ለማ መገርሳ ስለኦሮሞ ህዝብ ወደ ከተማ መፍለስ እናለበት ያሉት ነገር ከዚህ ጋር አብሮ ይሄዳል። ለምሳሌ አዲስ አበባ ዙርያ የሚኖረው ባብዛኛው ኦሮሞ ነው። አዲስ አበባ ባደገች ቁጥር በሜትሮፖሊታን ከተማው ያለው የኦሮሞ ህዝብ ቁጥር እየጨመረ መሄዱ አይቀርም። ከላይ በጻፍኩት አንጻር ይህ የኦሮሞ ህዝብ በአዲስ አበባ መብዛት አይቀሬም ብቻ ሳይሆን እንደ ጥሩ ነገር ነው መታየት ያለበት። ከተማው ህዝቡን ይቀላቅለዋል እና ያዋህደዋል። ይህ ውህደት የጎሳ ብሄርተኝነትን ይቀንሳል። ስለዚህ ኦሮሞዎችን ወደ አዲስ አበባ እና ሌሎች ከተሞች እንዲፈልሱ ያለው የኦዴፓ እቅድ ጥሩ ነው ማለት ይቻላል።
አሁን ከኛ ከኢትዮጵያ ብሄርተኞች ጎራ የሚጠበቀው ይህ እቅድ በምንፈልገው በአውንታዊ መስመር እንዲካሄድ ነው። «የጎሳ ጌቶዎች» ወይንም የአንድ ጎሳ ሰፈሮች እንዳይፈጠሩ፤ እውነታዊ ውህደት እንዲኖር፤ ሌላው ህብረተሰብ ኦሮምኛ እንዲማር፤ አድሎዋዊነት እንዳይኖር፤ ወዘተ መስራት አለብን። ሌላው ከኛ የሚጠበቀው ነገር የኦሮሞዎች መብት እና ፍላጎት በአዲስ አበባ እንደሚከበረው የሌሎች ዜጎች መብት እና ፍላጎት በኦሮሚያ እንዲከበር መሟገት እና ማስፈጸም ነው። አልፎ ተርፎ ኦሮሙማ (የኦሮሞ ባህል) በአዲስ አበባ እና መላው ኢትዮጵያ እንዲንጸባረቅ በመስማማት in exchange የጎሳ ፌደራሊዝም ሀገ መንግስቱ እንዲቀየር መሟገት እና መደራደር አለብን። ይህን ለማድረግ ታላቅ አቅም እና መደራጀት ይጠበቅብናል።
ነገሮችን ሁሉ በአውንታዊ መልኩ እንደ opportunity ማየት የአሸናፊነት ምልክት ነው። ኦዴፓ ኦሮሞን ወደ አዲስ አበባ እንዲሄድ እናበረታታለን ሲል እኛ እሰየው ብለን በሂደቱ ተሳትፈን እኛ የምንፈልገው መልክ እንዲይዝ ማድረግ አለብን። ከውጭ እያየን በፍርሃት ከማልቀስ ጉዳይ ውስጥ ገብተን መምራት ነው ያለብን።
ስለዚህ ለማ መገርሳ ልክ ነው፤ የዴሞግራፊ ለውጥ ግድ ነው። በዚህ መንገግድ ብቻ ነው መቀላቀል እና መዋሃድ የሚመጣው። በዚህ መንገድ ብቻ ነው አሁን በህብረተሰባችን የሰፈነው ጎሰኝነት ከረዥም ዓመታት በኋላ እንዲቀንስ እና እንዲጠፋ ማድረግ የሚቻለው።
የጎሳ ብሄርተኝነት ህዝብ ውስጥ በተለይ የኦሮሞ ህዝብ ውስጥ በደምብ እንደገባ ሁላችንም ገብቶናል። በልሂቃን ደረጃ ብቻ ሳይሆን በብዙሃን ደረጃም። ይህን ጎሰኝነት በስብከት እና ልመና ማጥፋት አይቻልም። የተም ሀገር የጎሳ ብሄርተንኘት አንዴ ከሰፈነ የሚቅንሰው ነገር ፖለቲካዊ ድርድር ሳይሆን የዴሞግራፊያዊ ለውጥ ብቻ ነው። በኢትዮጵያ የሚያስፈልገው የዴሞግራፊ ለውጥ በኦሮሞ እና ሌላው ኢትዮጵያዊ መካከል መቅላቀል እና ውህደት (integration and assimilation) ነው። ህዝቡ ተቀላቅሎ ተጋብቶ ተዋልዶ የቅይጥ ባህል እና ህዝብ መጨመር አለበት። በዚህ መንገድ የጎሳ ብሄርተኛው ጎራ እያነሰ ይሄዳል የፖለቲካ ኃይሉም ይመነምናል። ይህን የሚያስፈጽም አንድ ፖሊሲ ኦሮምኛ የህገር ሙሉ ቋንቋ ማድረግ ነው። ይህ ኦሮሞዎች ከኦሮሚያ ወደ ሌላው ኢትዮጵያ እንዲፈልሱ ይጋብዛል። ለምሳሌ ኦሮምኛ ለማስተማር ወደ አማራ ክልል ይመጣሉ። ይህ ፈልስት መቀላቀልን እና መወሃድን ያመጣል። ከላይ የጠቀስኩት ጽሁፍ ባጭሩ ይህን ነው የሚለው።
በቅርቡ ለማ መገርሳ ስለኦሮሞ ህዝብ ወደ ከተማ መፍለስ እናለበት ያሉት ነገር ከዚህ ጋር አብሮ ይሄዳል። ለምሳሌ አዲስ አበባ ዙርያ የሚኖረው ባብዛኛው ኦሮሞ ነው። አዲስ አበባ ባደገች ቁጥር በሜትሮፖሊታን ከተማው ያለው የኦሮሞ ህዝብ ቁጥር እየጨመረ መሄዱ አይቀርም። ከላይ በጻፍኩት አንጻር ይህ የኦሮሞ ህዝብ በአዲስ አበባ መብዛት አይቀሬም ብቻ ሳይሆን እንደ ጥሩ ነገር ነው መታየት ያለበት። ከተማው ህዝቡን ይቀላቅለዋል እና ያዋህደዋል። ይህ ውህደት የጎሳ ብሄርተኝነትን ይቀንሳል። ስለዚህ ኦሮሞዎችን ወደ አዲስ አበባ እና ሌሎች ከተሞች እንዲፈልሱ ያለው የኦዴፓ እቅድ ጥሩ ነው ማለት ይቻላል።
አሁን ከኛ ከኢትዮጵያ ብሄርተኞች ጎራ የሚጠበቀው ይህ እቅድ በምንፈልገው በአውንታዊ መስመር እንዲካሄድ ነው። «የጎሳ ጌቶዎች» ወይንም የአንድ ጎሳ ሰፈሮች እንዳይፈጠሩ፤ እውነታዊ ውህደት እንዲኖር፤ ሌላው ህብረተሰብ ኦሮምኛ እንዲማር፤ አድሎዋዊነት እንዳይኖር፤ ወዘተ መስራት አለብን። ሌላው ከኛ የሚጠበቀው ነገር የኦሮሞዎች መብት እና ፍላጎት በአዲስ አበባ እንደሚከበረው የሌሎች ዜጎች መብት እና ፍላጎት በኦሮሚያ እንዲከበር መሟገት እና ማስፈጸም ነው። አልፎ ተርፎ ኦሮሙማ (የኦሮሞ ባህል) በአዲስ አበባ እና መላው ኢትዮጵያ እንዲንጸባረቅ በመስማማት in exchange የጎሳ ፌደራሊዝም ሀገ መንግስቱ እንዲቀየር መሟገት እና መደራደር አለብን። ይህን ለማድረግ ታላቅ አቅም እና መደራጀት ይጠበቅብናል።
ነገሮችን ሁሉ በአውንታዊ መልኩ እንደ opportunity ማየት የአሸናፊነት ምልክት ነው። ኦዴፓ ኦሮሞን ወደ አዲስ አበባ እንዲሄድ እናበረታታለን ሲል እኛ እሰየው ብለን በሂደቱ ተሳትፈን እኛ የምንፈልገው መልክ እንዲይዝ ማድረግ አለብን። ከውጭ እያየን በፍርሃት ከማልቀስ ጉዳይ ውስጥ ገብተን መምራት ነው ያለብን።
ስለዚህ ለማ መገርሳ ልክ ነው፤ የዴሞግራፊ ለውጥ ግድ ነው። በዚህ መንገግድ ብቻ ነው መቀላቀል እና መዋሃድ የሚመጣው። በዚህ መንገድ ብቻ ነው አሁን በህብረተሰባችን የሰፈነው ጎሰኝነት ከረዥም ዓመታት በኋላ እንዲቀንስ እና እንዲጠፋ ማድረግ የሚቻለው።
Friday, 22 February 2019
የለገጣፎ «ህገ ወጥነት» የማን ነው?
ሰዎች ከለገጣፎ ገበሬዎች ጋር የውስጥ ውል ተፈራርመው መሬት ገዙ። የእርሻ መሬት መሸጥም መግዛትም ስለማይፈቀድ ይህ ሺያጭ ህገ ወጥ ነበር። ሆኖም ተካሄዷል።
እነዚህ አይነት ሺያጮች ሲካሄዱ የአካባቢው የኦህዴድ (ኦዴፓ) ሹማምንቶች መጀመርያ እንዳላዩ ሆኑ። ቀጥሎ የምዝበራ እድል አይተው ገቡበት። ከገበሬ እየገዙ አትርፈው መሸጥ ጀመሩ። ከገበሬዎች ገዝተው ቤት የሰሩትን ሰዎች ጉቦ ካልሰጣችሁን እናባርራችኋለን፤ መብራት ውሃ እንከለክላችኋለን ወዘተ እያሉ አስፈራሩ። በዚህ መንገድ እራሳቸውን ሃብታም አደረጉ።
የኦዴፓ ላይ ድርስ ያሉ ባለስልጣናት ይህ አይነት ነገሮች አዲስ አበባ ዙርያ እንደሚካሄድ ያውቃሉ። ለነገሩ ሁላችንም እናውቃለን።
ስለዚህ ማን ነው ህገ ወጥ?! መሬት የገዙት ሰዎች? መሬት የሸጡት ገበሬዎች? የመዘበሩ እና በጉቦ ሃብታም የሆኑት የመንግስት ሹማምንቶች? ይህ እንደሚከሰት እያወቀ ዝም ያለው የኦህዴድ አመራር?
ግልጽ ነው፤ በፈቃደኝነት የተስማሙት ሳጭ እና ገዦች በአንጻሩ ንጹህ ናቸው። ማንንም አልጎዱም። ገበሬዎቹ የራሳቸውን መሬት በፈለጉት ዋጋ ሸጡ፤ ገዦችም በተስማሙበት ዋጋ መሬት ገዙ። ይህ ሺያጭ ባይካሄድ የኦህዴድ ሹማምንቶች የገበሬዎቹን መሬት በማይገባ ትንሽ ካሳ ነጥቀው ለኢንቬስተር በውድ ዋጋ እና ጉቦ ሊዝ ያረጉት ነበር።
እነዚህ የኦህዴድ ሹማምንት እና መሪዎች ናቸው ዋና ህግ ወጦች። አዲሱ አረጋ እንዳሉት «ህግ ይከበር» ከሆነ በመጀመርያ ደረጃ የኦህዴድ ሹማምንቶች ነበር መፈተሽ እና መታሰር የነበረባቸው። ሌሎቹ፤ ገንዘብ የተቀበሉት ገበሬዎቹ እና መሬት የገዙት ሰፋሪዎቹ በለዘብተኛ መልኩ መስተናገድ ነበረባቸው።
እነዚህ አይነት ሺያጮች ሲካሄዱ የአካባቢው የኦህዴድ (ኦዴፓ) ሹማምንቶች መጀመርያ እንዳላዩ ሆኑ። ቀጥሎ የምዝበራ እድል አይተው ገቡበት። ከገበሬ እየገዙ አትርፈው መሸጥ ጀመሩ። ከገበሬዎች ገዝተው ቤት የሰሩትን ሰዎች ጉቦ ካልሰጣችሁን እናባርራችኋለን፤ መብራት ውሃ እንከለክላችኋለን ወዘተ እያሉ አስፈራሩ። በዚህ መንገድ እራሳቸውን ሃብታም አደረጉ።
የኦዴፓ ላይ ድርስ ያሉ ባለስልጣናት ይህ አይነት ነገሮች አዲስ አበባ ዙርያ እንደሚካሄድ ያውቃሉ። ለነገሩ ሁላችንም እናውቃለን።
ስለዚህ ማን ነው ህገ ወጥ?! መሬት የገዙት ሰዎች? መሬት የሸጡት ገበሬዎች? የመዘበሩ እና በጉቦ ሃብታም የሆኑት የመንግስት ሹማምንቶች? ይህ እንደሚከሰት እያወቀ ዝም ያለው የኦህዴድ አመራር?
ግልጽ ነው፤ በፈቃደኝነት የተስማሙት ሳጭ እና ገዦች በአንጻሩ ንጹህ ናቸው። ማንንም አልጎዱም። ገበሬዎቹ የራሳቸውን መሬት በፈለጉት ዋጋ ሸጡ፤ ገዦችም በተስማሙበት ዋጋ መሬት ገዙ። ይህ ሺያጭ ባይካሄድ የኦህዴድ ሹማምንቶች የገበሬዎቹን መሬት በማይገባ ትንሽ ካሳ ነጥቀው ለኢንቬስተር በውድ ዋጋ እና ጉቦ ሊዝ ያረጉት ነበር።
እነዚህ የኦህዴድ ሹማምንት እና መሪዎች ናቸው ዋና ህግ ወጦች። አዲሱ አረጋ እንዳሉት «ህግ ይከበር» ከሆነ በመጀመርያ ደረጃ የኦህዴድ ሹማምንቶች ነበር መፈተሽ እና መታሰር የነበረባቸው። ሌሎቹ፤ ገንዘብ የተቀበሉት ገበሬዎቹ እና መሬት የገዙት ሰፋሪዎቹ በለዘብተኛ መልኩ መስተናገድ ነበረባቸው።
Subscribe to:
Posts (Atom)