Showing posts with label የጎሳ አገዛዝ. Show all posts
Showing posts with label የጎሳ አገዛዝ. Show all posts

Sunday, 25 March 2018

ስለ «አማራ» ያከው ውይይት

ስለ አማራ ማንነት ይሆን ወይም በሌላም አርእስት ስነወያይ ነገሮችን በጥራት እንድናይ ለመወያየት ለመከራከር ለመተቻቸት ብቻ ሳይሆን ግብ ለመምታት ከሆነ ከውይይታችን ከአስተሳሰባችን በስተ ጀርባ ዙርያውን ያለውን ሁኔታ አስተሳሰባችን መመልከት አለብን። ይህን ለማድረግ ዘንድ እስቲ እነዚህን ነጥቦች በደምብ እንመልከታቸው።

1. ሁሉም ውይይት "context" (ዐውደ ሁኔታ?) አለው። ዛሬ ያለው ሁኔታ ምንድነው? 60 ዓመት በፉት ይህ ውይይት ይኖር ነበር ቢኖርስ ምን ይመስል ነበር።

2. ለውይይቱ ምን አይነት አመለካከት ርዕዮት ዓለም እምነት ወዘተ ይዘን ነው የምንከራከረው? በጎሰኝነት ("identity") ፒለቱካ እናምናለን? ወይም የአገር ብሄርተኖች ("nationalist") ነን?

3. የምንጠቀምበት ቋንቋ ቃላቶች ምን ትርጉም አላቸው? «ጎሳ» ምንድንደው? «ህዝብ» ምንድነው? «አማራ» ምንድነው? «ማንንነት» ምንድነው?

4. የውይይታችን አላማ ምንድነው? ውይይቱን ማሸነፍ ነው? መስማማት ነው? እውነት ላይ መድረስ ነው?

5. የጠቅላላ አላማችን ምንድነው? ከአገራችን ሽኩቻ አድሎ ኢፍትሃዊነት እንዲጠፋ ሰላምና ፍትህ እንዲኖር ነው? ህወሓትን ከስልጣን ማውረድ ነው? ስልጣን መያዝ ነው? ጥሩ የሚመስለንን ሥርዓትን ማስፈን ነው?

6. ውይይታችን አቋማችን ከህዝቡ ዝንባሌ ጋር በተወሰነ ድረጃ ብቻ ቢሆንም ይሄዳል ወይ? ይህ ታላቅ ጥያቄ ነው። የ«ፌስቡክ» ብቻ ውይይት ነው? የልሂቃን ብቻ ውይይት ነው? የአዲስ አበባ ብቻ ውይይት ነው? የተማሪዎች? ወይም ከብዙኃኑ ምካከል ይህ ጉዳይ እንደ ቁም ነገር ይቆጠር ይሆን?

ሁላችንም እራሳችንን እነዚህን ጥያቄዎች ጠይቀን በአግባቡ መልሰን ነው ፍሬአማ ውይይት ሊኖርን ይሚችለው። 

እስቲ የኔን መልሶች ልስጣችሁ፤

1. ዛሬ የምዕራባዊ የማርክሲዝም የጎሳ ወይም ብሄሮች አስተሳሰብ ኢትዮጵያ ውስጥ ገብቶ በደምብ ሰክኗል። በ ኃይለ ሥላሴ ዘመን ተማሪዎቻችን ወደ ውጭ አገር ትምሕርትቤት ሄድው ያመጡት ርዕዮት ዓለም አገር ውስጥ መሰረት ጥሎ ጭርሽ ህገ መንግስታችንን በክሎታል የፖለቲካ መዋቀራችንን በይኗል። በመሀበረሰብ ደረጀ በፊት ከ«ልሂቃን» ያልወጣ አስተሳሰብ አሁን አማራ ኦሮሞ ሲዳማ ትግሬ ብዙኃኑም ያውቀዋል። ግን በትክክሉ ምንድነው የሚያውቀው? ቋንቋ ነው? «ዘር» ነው? «ቦታ» ነው? ማንነት ነው? የፖለቲካ ክፍል ነው? ብዚህ ዙርያ  የተለያዩ አመለካከቶች ቢኖሩም አብዛኞቻችን «አማራ» የሚለውን ቃል ድሮ የማንጠቀምበት ዛሬ እንጠቀምበታለን። ድሮ የፖለቲካ ትርጉም ያልነበረው ዛሬ አለው። ዛሬ ሰዎች በአማርነት ይከሰሱበታል። ይወነጀሉበታል። አንዳንዱ አማራ በመሆኔ ተጎጂ ነኝ ብሎ ያስባል። እጨቆናለሁ መብት የለኝም የሚል አለ። ባጭሩ ይህ ሁኔታ ላይ ነው ዛሬ የምንገኘው። 

2. ማንነት የሰው ተፈጥሮ ባህሪ ነው ብዬ አምናለው። በመንደር ካልሆነ በጠቅላይ ግዛት ካልሆነ በጎሳ ካልሆነ በአገር ሁላችንም አንዱ የማንነታችንን ክፍል ይህ ነው። እስቲ አንድ ምሳሌ እናስብ። አንድ ኢትዮጵያዊ አሜሪካ ለ20 ዓመት ኖሮ ዜግነት ተቀብሎ አሜሪካው ነኝ ይላል። ኢትዮጵያዊ ነኝም ይላል። ለምን ኢትዮጵያዊነቱን አይተወውም። ልም ልጆቹን የኢትዮጵያ ቋንቋ ያስተምራል ቢችልም የኢትዮጵያ ትምሕርትቤት ይልካል? ለመሆኑ አሜሪካና ኢትዮጵያ በሆነ ጉዳይ ቢቃረኑ ማንን ይሆን የሚደግፈው? ኢትዮጵያን ቢደፍግ ሌላው አሜሪካዊ ከሃዲ አይለውም ይሆን? ለሌላው አሜሪካዊ «ኢትዮጵያዊ-አመሪካዊ» ማለት ጎሳ ነው። አያችሁ የጎሳ ስሜት እንዴት የተፈጥሮ እንደሆነ። የተፈጥሮ ቢሆንም ብዙ ጎሳዎች ያሉበት አገር ውስት የጎሰኝነት ስሜት ከአገር ብሄርተኝነት ስሜት ከበለጠ የጎሳ ፉክክር ("ethnic competition") በፖለቲካ ምድር ውስጥ ያበዛና ለአገሪቷ ህልውና ለሰላም ለፍትህ አደገኛ ነው ይሚሆነው። ይህን ነው ዛሬ በኢትዮጵያ የምናየው። ይህ ምክነያት የአገር ብሄርተኛ ነኝ። ማለት ለሁላችን ሰላምና ለአገሪቷ ብልጽግና የጎሰኘት ስሜት ከአገር ስሜት በታች መሆን አለበት ብዬ ነው የማምነው። «ኢትዮጵያዊ ነኝ ቀጥሎ ኦሮሞ» ትሩ ነው። «ትግሬ ነኝ ቀጥሎ ኢትዮጵያዊ» ወደ ችግር ይመራል።

3. «ጎሳ» «ህዝብ» «ማንንነት» «አማራ» ለሁላችንም የተለያዩ ትርጉሞች አላቸው። ከላይ እንዳልኩት ለኔ የሰው ልጅ ማንነት ውስጥ አንድ የአገር ወይ ጎሳ ወይ መንደር ወዘተ ክፍል አለ። ስለዚህ ለኔ ይህ የማንነት ክፍል በ«ኢትዮጵያዊነት» ወይም «ኦሮሞነት» ወይም «ኦሮሞ-ኢትዮጵያዊነት» ወይም «ኢትዮጵያ-አማራነት» ወይም «ጎጃምነት» ወይም «አፍሪካነት» ሊሞላ ይችላል። ግን ሰውው «ጎሳ» እና «ህዝብ» እና «አገር» ሲለይ የፖለቲካ አቋምን ነው የሚገልጸው። ለምሳሌ አውሮፓ ከትናንሽ የንጉስ ግዛቶች «ጎሳዎች» ወደ አገሮች ("nation state") ሲቀየር «ጎሳ» የኋላ ቀር ነው ብለው ሰየሙ። ግን በጎስኝነት ዘመን የሚያራምዱት ጥላቻን ጦርነትን አሁን በ«አገር» ደረጃ በከፍ ያለ አቀም አራመዱት! ወደ «አማራ» የምንለው ቃል እንምጣ። የቃላቱ ትርጉም በመቶዎች ዓመታት እነደተቀየሩ ግልጽ ነው። የታሪቅ መጽሐፍቶች የድሮ አጠቃቀም ካሁኑ እንደሚለው ያሳያሉ። በቅርብ ዓመታት እራሱ ለምሳሌ ከሃረር እስከ ሸዋ መካከል «ነባር» ሙስሊም ኦሮሞዎች በቀር ሌላው «ክርስትያን» ነበር የሚባለው። ግን ነገሮች ይቀየራሉ። አሁን ከላይ እንደጠቀስኩት የማርክሲዝም ፖለቲካ ሰፍኖ ሁላችንም አማራ እንላለን ወይም ታግለን እራሳችንን እንቆጥባለን።

4. ስወያይ በተቻለ ቁጥር እውነት ላይ ለመድረስ ነው የምወያየው። አዎን አንድ አንድ ጊዜ ፍተናው ያሸንፈኛልና ትቢት ተሞልቼ ማሸነፍ ፈልጋለው አቋሜ ትክክል ቢሆንም ባይሆንም። ውይም ፈርቼ ወይም ለይሉኝታ መስማማት እፈልጋለሁ ስምምነት በውሸት የተመሰረተ ቢሆንም። ግን ደካማ ወገኔን ትቻ አላማየ እውነት ነው። ባልወደውም። ለምን እውነንት? እውነት ነው ለሁሉም የሚበጀው። አላማ እውነት ነው ማለት ለታክቲክ ወይም ለጊዜያዊ ሰላም ቁስል እስኪድን ወዘተ ተብሎው ዝም አይባልም ወይም አይዋሽም ማለት አይደለም። ገን የመጨረሻ ግቡ እውነት ነው።

5. እኔ ሰላምና ፍትህ ነው የምወደው። (አድሎ ሙስና አይኖር ማለት ፍትህ ይኑር ነው።) ሰው እንዳይጎዳ። ሰው ሌላውን ጉዳ እንዳይባል መጉዳት ከመጎዳት ይበልጥ ጎጂ ነውና። ከዛ ውጭ ማን ይግዛ ምን ሥርዓት ይኖር ግድ የለኝም። እንደ ኦርቶዶክስ ክርስትያንነቴ ወደ ንጉሳዊ አገዛዝ አደላለው ከሰው ወይም ሰዎች ይልቅ እግዚአብሔር መሪ ቢሾም ይሻላል ስለሚመስለኝ። ግን ይህ ሀሳብ ለ«ዘመናዊ» ሰው አይገባውም እንተወው። ለማንኛውም ሰላም ፍቅር ፍትህን የሚያበዛ ትልና ሽኩጫን የሚያሳንስ ሥርዓት ከተባለ ከሞላ ጎደል ምን መምሰል እንዳለበት እናውቃለን። 

6. እውነቱን ለመናገር ይህ ሀአማራ ማንነት ጉዳይ ከዲያስፖራና ፌስቡክ ውች ያን ያህል ትኩረት ያለው አይመስለኝም። በኔ እይታ (በኢህአዴግም ይመስለኛል!) ያለፉት ሶስት አራት ዓመት የህዝብ ተቃውሞ በመጀመርያ ደረጃ አድሎን በተለይ የ«ትግሬ አድሎን» ተመስርቶ ነው። ይህ በአማራ ክልል የተካሄደውን ተቃውሞንም ያካትታል። መፈከሩ ትግሬ አይግዛን ነው እንጂ አማራ ይከበር አይመስለኝም። በግሌ ያየሁት የሰማሁት እንደዚህ ነው። እንደሚመስለኝ ዛሬ አማራ የምንለው ህዝብ አሁንም በጣም ወደ ኢትዮጵያዊነት ያመዝናል ከአማራነት ይልቅ። ነገ አማራ ክልል በንዚን ቢገኝ ለአማራ ክልል ብቻ ይውል የሚል ጥቂት መሰለኝ። ትግሬ ምንም አያገኝ የሚሉ ብዙ ይኖራሉ ያሳዝናል እንጂ። ጥቃት ያመታው ችግር ነው። ግን አብዛኛው አማራ በለጸገች ከማለት ኢትዮጵያ በለጸገች ነው የሚለው።

እሺ በመጨረሻ ለ«ትግሉ» ተብሎ በአማራነት መታገሉ አይሻልም ወይ የሚለው ከመምህር ሐዚም አስራት ወልደየስ ዘመን ጀምሮ ያለ ጥያቄ አለ። ያኔ አልሰራም ከላይ እንደጠቀስኩት «አማራ» የሚባለው ስሜቱ ከአማራነት ይልቅ ኢትዮጵያዊነት እጅግ ስለሚበልት። አናሳ ብሄርም ስላልሆነ። የተጭቋኝ ስሜትም ስላልነበረው። ዛሬ ሁኔታው ጠቀይሯል በተወሰነ ደረጃ ግን አሁን ስኬታማ የ«አማራ የጎሳ» ትግል ለማካሄድ የህዝቡ ሁኔታ የሚፈቅድ አይመስለኝም።

እውነት ነው እንደዚህ አይነቱ ትግል ያስጎመዣል። እነ ሻዕብያ ህወሓት ኦነግ እንዳረጉት ስኬታማ ትግል ማድረግ ነው። የጎሳን የተፈጥሮ የማሰባሰብ ኃይል መጠቀም ነው። ግን ሁኔታው ካልፈቀደ ህዝቡ ማንነቱ ከዚ አይነት አስተሳሰብ ጋር የማይሄድ ከሆነ አሁንም አይሳካም። ሰከን ብሎ ማሰብ ነው።

በመጨረሻ ላስታውሳችሁ የምወደው ምሳሌዎቹ ወይም "template" የሆኑት እነ ሻዕብያ ህወሓት እጅግ አናሳ ስለሆኑ ለማሸነፍ ጎሰኝነትን ግድ መጠቀም አለብን ብለው ያምኑ ነበር። ግን እስካማውቀው ኢ-ህወሓት የሆንነው ወይም «ተቃዋሚ» የሆንነው የአገሪቷ 90% ወይም 80% ወይም 70% ነን። የጎሰኝነት የፖለቲካ ኃይል መሰብሰብያ "ethnic leverage" አስፈላጊ ነው ልንል አይገባም። ትንሽ የፖልቲካ ብስለት ትብብር አብሮ መስራት መተማመን ጉዳዩን ትላንት ይጨርሰው ነበር።

Sunday, 28 January 2018

ትግሬዎች እየተጠቁ ነው?

ይህንን ታሪክ ደጋግመን አይተነዋል ብቻ ሳይሆን አሳልፈነዋል። የጎሳ ፖለቲካ በአገራችን ጎልቶ መታየት ከጀመረ ወዲህ፤ ከነጀብሃ፤ ሻብያ፤ ህወሓትና ደርግ ዘመን ጀምሮ የተደጋገመ ታሪክ ነው። በነጻነት ወይም ፍትህ ወይም «መብት» ጥያቄ ይኖራል። የሚጣሉት ጎራዎች በጥያቄው ላይ ከማተኮር ጉዳዩን ወደ ጎሳን ወይም ዘርን ያዞሩታል። ለጎሳ ጥል ምክንያት ይጠቀሙበትና የነጻነት ወይም ፍትህ ወይም መብት ጥያቄው ቀርቶ የጎሳ ውግያ ይሆናል። ጎሰኝነትን እንደ መሳርያ ይጠቀሙበታል አገርን ያጠፉበታል። (ይህን ስል በመጀመሪያ የተነሱት ጥያቄዎች መሰረተ ቢስ ነበሩ ማለቴ አይደለም ወይም በጎሳ ወይም ቋንቋ ዙርያ ችግር አልበረም አልልም። ሆኖም ጎሳ እንደ መሳርያ መጠቀም አላስፈላጊና ጎጂ ነበር፤ አሁንም ነው።)

ዛሬ በኢትዮጵያዊያን ብዙሃን በትግራይ ቅሬታ መኖሩ የማይካድ ነገር ነው። ዲያስፖራ የሚኖር ካልሆነ የትም ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖር ይህን ሃቅ በየቀኑ የሚያየውና የሚኖረው ነው። ይህ በትግሬዎች ላይ ያለው ቅሬታ ደግሞ በተቃዋሚ ወይም «ፀረ ሰላም ሃይሎች» የተቀሰቀሰ አይደለም። (ተቀዋሚዎች ምንም ለመቀስቀስ አቅሙም ትብብሩም የላቸውምና።) ከሊስትሮው እስከ ሃብታም ነጋዴው እስከ የቤት እመቤቷ እስከ ካህኑ እስከ ተማሪው ይህንን የቅሬታ ስሜት አለው። ያሳዝናል ግን ያለ ነገር ነው። የጎሳ ጉዳይ ሳይሆን የፖለቲካ ጉዳይ ነው መሆን የነበረበት፤ ሰውዉ ስለትግሬ ሲአማርር «ተውዉ፤ ገዥ መንግስቱ ሌላ ፖለቲካ ስለማይፈቅድ ብቸኛ ስልጣን ስለያዘ ነው ግፍ የበዛው» ብዬ ለማስረዳት ብሞክር ማንም አይሰማም። ሰውዉ በትግሬ በላይነት አምኖ ሌላ ነገር አይሰማም።

መንግስትንም ያስጨነቀው ይህ ነው። ከመሪ ወይም ተቃዋሚ መደብ ሳይሆን የብዙሃኑ የህዝቡ ብሶት እንደሆነ ስለሚያውቅ ነው መንግስት ለውጥ ለህልውናው ግድ እንደሆነ አምኖ እርስ በርሱ የሚወያየው።

በዚህ ሁኔታ ትግሬዎች አለ አግባብ ተጥቅተዋል ገና ሊጠቁም ይችላሉ። ጥያቄ የለውም። (እዚህ መጥቀስ የምፈልገው ግን እድሜ ለብዙሃኑ ታሪካዊ ዝንባሌ ጎሰኝነት እንደ የ27 ዓመታት የኢህአዴግ ፕሮፓጋንዳ ያህል አያጠቃውም። ሆኖም ያለውም መጠን ችግር ነው።) ግን ይህ ፍግ መቆም አለበት፤ ትግሬ መጠቃት የለበትም ብሎ መጮህ ምን ዋጋ አለው? ማን ይሰማናል? ከላይ እንደጠቀስኩት ህዝቡ ትግሬዎች አንደኛ ዜጋ ናቸው ሌሎቻችን ሁለተኛ ዜጋ ነን ብሎ ደምድሟል። አይደለም የፖለቲካ ጉዳይ ነው፤ አማራ ክልል ጭቋኙ አማራ ነው ኦሮሚያ ጮቋኙ ኦሮሞ ነው ብንል አልሰሙንም አሁንም አይሰሙንም።

ስለዚህ መፍትሄው ከተቃዋሚ ወይም «ኢሳት» ወዘተ እጅ አይደለም። መፍትሄው ከመንግስት ብቻ ነው መምጣት የሚችለው። መንግስት ዙሪያ ያለነው በሙሉ ሃይላችን መንግስት የሚያስፈልገውን ለውጦች እንዲያመጣ መግፋት አለብን። በተለይ ለተጋሩ መጠቃት ዋናው መፍትሄ የመንግስት የጎሰኝነት አቋምና ፕሮፓጋንዳውን መቀየር ነው። በህዝቡ ልብ የ26 ዓመታት የጎሳ ስሜት በመሸርሸር ነው ያሉትን ቅሬቴዎች ከጎሳ ወደ ፖለቲካ መቀየር የሚቻለው።

አንድ ነገር መርሳት የለብንም። ይህንን ትጠንቅቃችሁ እንድታነቡ ብትህትና እጠይቃለሁ። የኢህአዴግ አቋም፤ በእርግጥ አብዛኛው የተማሪዎች የፖለቲካ ንቅናቄ አቋም፤ የኢትዮጵያ የፖለቲካ መሃበራዊና ኤኮኖሚ ቅሬታዎችና ችግሮች በጎሳ የተመሰረቱ ናቸው ነው። ይህ ነው የኢህአዴግ አቋም። ጭቆና አለ? የጎሳ ችግር ነው። እኩልነት የለም? የጎሳ ችግር ነው፡ ድህነት አለ? የጎሳ ችግር ነው። የጎሳውን ችግር ከፈታን ሁሉም ይፈታል። ታድያ ዛሬ ህዝቡ ችግራችን በሙሉ በትግሬ የበላይነት ምክንያት ነው ካለ በትክክል የኢህአዴግን አቋም ነው የሚያንጸባርቀው ማለት አይደለምን?! የጎሳ ፖለቲካ እንዴት አደገኛ እንደሆነው አያችሁ። ትግሬዎች ደግሞ መልሳቸው የምንጠቃው በኢህአዴግ ብቸኛ ስልጣን በመያዝ ሳይሆን በትሬነታችን ነው ብለው ይመልሳሉ። ምን ይደረግ፤ ችግሩን ወደ ጎሳ በማውረድ አብሮ ገደል መግባት ነው።

ስለዚህ ብእራችንንና ድምጻችንን አቅመ ቢስ የሆኑት ትቃዋሚና «አክቲቪስት» ላይ ከማባክን መንግስት አቋሙን እንዲቀይር ብለን እናሳምነው። መንግስት የሃሳብ እርዳታ ያስፈልገዋል። የ40 ዓመት ጣኦት የሆነ ርዕዮተ ዓለሙን መቀየር እጅግ ከባድ ነውና መንገዱም በጥንቃቄ የተአሰበበትና የታቀደ መሆን አለበት።

በትግሬ በትግሬነቱ የሚደርስበት ጭቆና ይውደም! የሚያወድመው ግን የኢህአዴግ የውስጥ ለውጥ ነው።

Tuesday, 4 October 2016

Ethnic federalism kills Meles' developmental state

2009/1/23 (Ethiopian calendar)
2016/10/3 (European calendar)

[Note: An Amharic version of this post will appear sometime!]


In a nutshell, the EPRDF's deal or social contract with the Ethiopian population over the past 15 years or so has been as follows: I will give you development and growth. In exchange, you will not challenge my political power and you will ignore the fact that my membership will have certain economic and other privileges that the rest of you will not have.

This is what a 'developmental state' led by a 'vanguard party' basically is. The classic example is China. We all know that the Chinese people, in aggregate, have prospering for years. People have been getting richer, there's more education, better health care, better infrastructure, etc. Again, this is in aggregate – large sections of the population have suffered for this and continue to suffer, but let's set that aside for the moment. As far as Ethiopians are concerned, when they see China, they see prosperity.

Now, the only political party in China – the Communist Party – has no political competition, which means there is little accountability. Party members can enrich themselves through corruption and other means and the population can do nothing about it because it cannot get rid of the party – that's part of the deal. Now, if this corruption threatens economic development and therefore threatens the Communist Party's deal with the people, which would then lead to revolt and overthrow of the party, then there's a crackdown on corruption. So as we all have seen, every so often, the party campaigns against corruption, arrests a few thousand party members and cronies, and then when it all dies down forgets about it for a while. Corruption goes up again.

Now, why isn't this working in Ethiopia? Development is taking place, economic growth is pretty good, the big projects such as the Nile Dam are still going strong. So why the unrest? Why the revolt?

The answer is ethnic federalism. You see, in China, there is more or less only one ethnicity. The population resents the privileges of the members of the Communist Party. People resent that party members are rich, have preferential treatment in everything, including the legal system, jobs, contracts, etc. However, the resentment is what we might call class resentment. The upper class is the Communist Party and the lower class the rest of the population. The upper class makes sure the lower class does quite well – not as well as the upper class but well enough to keep politically quiet.

In Ethiopia not only do we have many ethnicities, but ethnicity is part of the government! The vanguard party EPRDF is composed of ethnic parties, and the most powerful party as everyone knows and perceives is the TPLF. Just as in China, the population resents the privileges of the members of the EPRDF and their relatives and cronies. But this resentment is much greater and politically dangerous than in China because the resentment is not just class resentment, but ethnic resentment, and ethnic resentment is extremely dangerous.

As I have written before, people are far more tolerant of oppression by their own ethnic group or no ethnic group than by another ethnic group, or by what they perceive to be another ethnic group. When it comes to political oppression, ethnic feelings are strong. This is why the combination of developmental state and ethnic federalism is not working in Ethiopia.

By the way, this understanding of ethnicity as a strong political force is precisely the basis of of ethnic federalism! We need ethnic federalism, ethnic group rights above all else, etc., because ethnicity is the basis our polity, is what Meles and the EPRDF said when creating the constitution. If we do not give ethnicity this primacy, then there will be an ethnic revolt, they said. What irony then, that the ethnic division they laid in place for this reason is precisely that which is is proving their downfall.

Now, how can the EPRDF get out of this quagmire. The band aid solution is to try and severely clamp down on corruption, which it has tried to do repeatedly. But how can the EPRDF do that given the nature of the vanguard party / developmental state model, since party privilege and corruption is an unavoidable consequence of it? The other option is to do something about ethnic federalism. Of course the EPRDF can't touch the constitution, but as we have heard there is a proposal within the party to change it from a multi-ethnic front to a single non-ethnic party, thereby reducing the ethnic glare, so to speak, from the population. But this will alienate the EPRDF's more fervent ethnic nationalists, but at the same time it won't attract civic nationalists. This might have been a good option 20 years ago, but now it's too little too late.


In a later article, I will discuss what I think is a better solution for the EPRDF.