እንደሚታወቀው መሬትን የግል ማድረግ ኤኮኖሚውን ይረዳል። አሁን ደግሞ በመጠኑ የኤኮኖሚ አጣብቅኝ ውስጥ ነን። ዛሬ መሬት የግል ቢሆን መቼ እና ምን ያህል ነው ኤኮኖሚው ላይ ውጤቱ የሚታየው?
መሬት የግል ማድረግ የፖለቲካ ችግር እንዳለው ይታወቃል ስለዚህም ዛሬ priority አይደለም። ሆኖም እንደ አማራ ክልል አይነቱ ዳር ዳሩን እያለ እንደሆነ ይታወቃል። ለምሳሌ የ25 ዓመት ኪራይ (ሊስ) በህግ እንዲስተናገድ አድርጓል። ይህን የ25 ዓመት ኪራይ ወደ 1000 ዓመት ድርስ እንዲፈቀድ ቢደረግ እና ቂራዩን መሸጥ መለወጥ ቢፈቀድ de facto መሬትን የግል አደረገ ማለት ነው። ይህ በአማራ ክልል ወይንም ማንኛውም ይህን አለ ብዙ ፖለቲካዊ ችግር ማድረግ የሚችል ችግር ምን ያሀል የኤኮኖሚ ጥቅም በቅርቡ ሊያመጣለት ይችላል?
አዲስ አበባ እንዲሁ መሬት ከግለሰብ ለ1000 ዓመት መከራየት ይቻላል ኪራዩም መሸጥ መለወጥ ይቻላል ቢባል ምን ያህል ይሆን ጥቅሙ? በመፈናቀል እና መጠቀም ያለው ሚና እሳ?
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Showing posts with label land policy. Show all posts
Showing posts with label land policy. Show all posts
Saturday, 30 March 2019
Thursday, 28 March 2019
ብራቮ ሰይድ ኑሩ፤ ገበሬዎቻችን መሬት መሸጥ/መግዛት መቻል አለባቸው!
ስለዚህ የጻፍኳቸው ጽሁፎች፤ ጠቃሚ ከሆኑ...
https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2017/05/our-radical-politicians-land-to-ruler.html (English)
https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_47.html (አማርኛ)
https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_15.html
https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/blog-post_94.html
https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/12/blog-post_10.html
Monday, 4 March 2019
ተረት ተረት፤ አዲስ አበባ የኦሮሞ ገቤሬዎችን አፈናቅሏል
1. የአዲስ አበባ ህዝብ ምንም ፖለቲካዊ ውሳኔ አድርጎ አያውቅም። በኢህአዴግ (ከነ ኦህዴድ) የተገዛ ህዝብ ነበር። ስለዚህ የአዲስ አበባ ህዝብ ማንንም አላፈናቀለም። አፈናቃይ ካለ ኢህአዴግ ከነ ኦህዴድ ነው።
2. ከአዲስ አበባ የተፈናቀሉት ባብዛኛው ኦሮሞ ቢሆንም የተወሰኑ አማሮች እና የሌላ ጎሳ አባላት ነበሩ።
3. ካአዲስ አበባ ውስጥ የተፈናቀሉት ደግሞ ከሁሉም ጎሳ ነበሩ። እነዚህ የአዲስ አበባ ተፈናቃዮች ከአዲስ አበባ ዙርያ የተፈናቀሉት ገበሬዎች ይበልጥ ተበድለዋል በደልን በገንዘብ ከተረጎምነው። ከካዛንቺስ 50 ካሪሜትር ቦታው የተፈናቀለው ምናልታብት ሁለት ሶስት ሚሊዮን ብር ነው ያጣው። ከቡልቡላ የተፈናቀለው ገበሬ የዚህ ሩብም አልከሰረም።
4. ገበሬዎች እና ሌሎች «ተፈናቀሉ» ስንል መንግስት የማይመጥን ትንሽ ካሳ ሰጥቷቸው በግድ ከመሬታቸው አስነሳቸው ነው። አድግራጊው የአዲስ አበባ ህዝብ ያልመረጠው የአዲስ አበባ መንግስት ውየንም አብዛኛው ጊዜ የኦህዴድ መንግስት ነው። ገበሬውን አነስተኛ ካሳ ሰጥቶት ለኢንቬስተር በከፍተኛ ዋጋ ሽጦ ትርፉን ኪስ አስገብቷል። ለዚህ የአዲስ አበባ ህዝብ ትጠያቂ አይደለም፤ ኢህአዴግ እና ኦህዴድ ናቸው።
5. ታላቁ ግን ማንም የማያነሳው ጉዳይ የሀገራችን የመሬት ፖሊሲ ነው። መሬት የመንግስት በመሆኑ ነው ገበሬዎችም ሌሎችም የሚፈናቀሉት እና «ተፈናቀሉ» የሚባለው። አዲስ አበባ ሲሰፋ (እንደ ከተማ ይሁን እንደ metropolis) ዙርያ ያሉት ገበሬዎች ዋና ተጠቃሚ ነበር መሆን ያለባቸው፤ ይሆኑም ነበር መሬት የግል ቢሆን። አዲስ አበባ ዙርያ ያሉት ገበሬዎች ከተማው እየሰፋ ስለሄደ መሬታቸውን በእጅግ ውድ ዋጋ ሊሸጡ እና ሊጠቀሙ ይችላሉ። ቡልጋ ያለው ገበሬ የመሬቱ ዋጋ አንድ ብር በካሬ ቢሆን ይው መሬት አዲስ አበባ ዙርያ መቶ ብር ሊሆን ይችላል። በዚህ መንገድ ነው የትም ሀገር ከተማ ሲሰፋ ዙራይ ያሉት ገበሬዎች ሎተሪ እንዳሸነፉ የሚቆጠረው። ግን ኢትዮጵያ ገበሬው መረቱን መሸት ስለማይፈቀድ እና መንግስት ሲፈልግ መንጠቅ ስለሚችል ከተማ ዙርያ ያለ ገበሬ ጭራሽ ይሰጋ! ስለዚህ በዚምህ ረገድ ጥፋቱ የአዲስ አበባ ህዝብ ሳይሆን የኢህአዴግ እና ኦህዴድ የመሬት ፖሊሲ ነው። አዲስ አበባ ዙርያ ያሉ ገበሬዎች በኢህአዴግ/ኦህዴድ ምክንያት በሚሊዮኖች የሚቆጥር ብር አጥቷልና!
2. ከአዲስ አበባ የተፈናቀሉት ባብዛኛው ኦሮሞ ቢሆንም የተወሰኑ አማሮች እና የሌላ ጎሳ አባላት ነበሩ።
3. ካአዲስ አበባ ውስጥ የተፈናቀሉት ደግሞ ከሁሉም ጎሳ ነበሩ። እነዚህ የአዲስ አበባ ተፈናቃዮች ከአዲስ አበባ ዙርያ የተፈናቀሉት ገበሬዎች ይበልጥ ተበድለዋል በደልን በገንዘብ ከተረጎምነው። ከካዛንቺስ 50 ካሪሜትር ቦታው የተፈናቀለው ምናልታብት ሁለት ሶስት ሚሊዮን ብር ነው ያጣው። ከቡልቡላ የተፈናቀለው ገበሬ የዚህ ሩብም አልከሰረም።
4. ገበሬዎች እና ሌሎች «ተፈናቀሉ» ስንል መንግስት የማይመጥን ትንሽ ካሳ ሰጥቷቸው በግድ ከመሬታቸው አስነሳቸው ነው። አድግራጊው የአዲስ አበባ ህዝብ ያልመረጠው የአዲስ አበባ መንግስት ውየንም አብዛኛው ጊዜ የኦህዴድ መንግስት ነው። ገበሬውን አነስተኛ ካሳ ሰጥቶት ለኢንቬስተር በከፍተኛ ዋጋ ሽጦ ትርፉን ኪስ አስገብቷል። ለዚህ የአዲስ አበባ ህዝብ ትጠያቂ አይደለም፤ ኢህአዴግ እና ኦህዴድ ናቸው።
5. ታላቁ ግን ማንም የማያነሳው ጉዳይ የሀገራችን የመሬት ፖሊሲ ነው። መሬት የመንግስት በመሆኑ ነው ገበሬዎችም ሌሎችም የሚፈናቀሉት እና «ተፈናቀሉ» የሚባለው። አዲስ አበባ ሲሰፋ (እንደ ከተማ ይሁን እንደ metropolis) ዙርያ ያሉት ገበሬዎች ዋና ተጠቃሚ ነበር መሆን ያለባቸው፤ ይሆኑም ነበር መሬት የግል ቢሆን። አዲስ አበባ ዙርያ ያሉት ገበሬዎች ከተማው እየሰፋ ስለሄደ መሬታቸውን በእጅግ ውድ ዋጋ ሊሸጡ እና ሊጠቀሙ ይችላሉ። ቡልጋ ያለው ገበሬ የመሬቱ ዋጋ አንድ ብር በካሬ ቢሆን ይው መሬት አዲስ አበባ ዙርያ መቶ ብር ሊሆን ይችላል። በዚህ መንገድ ነው የትም ሀገር ከተማ ሲሰፋ ዙራይ ያሉት ገበሬዎች ሎተሪ እንዳሸነፉ የሚቆጠረው። ግን ኢትዮጵያ ገበሬው መረቱን መሸት ስለማይፈቀድ እና መንግስት ሲፈልግ መንጠቅ ስለሚችል ከተማ ዙርያ ያለ ገበሬ ጭራሽ ይሰጋ! ስለዚህ በዚምህ ረገድ ጥፋቱ የአዲስ አበባ ህዝብ ሳይሆን የኢህአዴግ እና ኦህዴድ የመሬት ፖሊሲ ነው። አዲስ አበባ ዙርያ ያሉ ገበሬዎች በኢህአዴግ/ኦህዴድ ምክንያት በሚሊዮኖች የሚቆጥር ብር አጥቷልና!
Friday, 22 February 2019
የለገጣፎ «ህገ ወጥነት» የማን ነው?
ሰዎች ከለገጣፎ ገበሬዎች ጋር የውስጥ ውል ተፈራርመው መሬት ገዙ። የእርሻ መሬት መሸጥም መግዛትም ስለማይፈቀድ ይህ ሺያጭ ህገ ወጥ ነበር። ሆኖም ተካሄዷል።
እነዚህ አይነት ሺያጮች ሲካሄዱ የአካባቢው የኦህዴድ (ኦዴፓ) ሹማምንቶች መጀመርያ እንዳላዩ ሆኑ። ቀጥሎ የምዝበራ እድል አይተው ገቡበት። ከገበሬ እየገዙ አትርፈው መሸጥ ጀመሩ። ከገበሬዎች ገዝተው ቤት የሰሩትን ሰዎች ጉቦ ካልሰጣችሁን እናባርራችኋለን፤ መብራት ውሃ እንከለክላችኋለን ወዘተ እያሉ አስፈራሩ። በዚህ መንገድ እራሳቸውን ሃብታም አደረጉ።
የኦዴፓ ላይ ድርስ ያሉ ባለስልጣናት ይህ አይነት ነገሮች አዲስ አበባ ዙርያ እንደሚካሄድ ያውቃሉ። ለነገሩ ሁላችንም እናውቃለን።
ስለዚህ ማን ነው ህገ ወጥ?! መሬት የገዙት ሰዎች? መሬት የሸጡት ገበሬዎች? የመዘበሩ እና በጉቦ ሃብታም የሆኑት የመንግስት ሹማምንቶች? ይህ እንደሚከሰት እያወቀ ዝም ያለው የኦህዴድ አመራር?
ግልጽ ነው፤ በፈቃደኝነት የተስማሙት ሳጭ እና ገዦች በአንጻሩ ንጹህ ናቸው። ማንንም አልጎዱም። ገበሬዎቹ የራሳቸውን መሬት በፈለጉት ዋጋ ሸጡ፤ ገዦችም በተስማሙበት ዋጋ መሬት ገዙ። ይህ ሺያጭ ባይካሄድ የኦህዴድ ሹማምንቶች የገበሬዎቹን መሬት በማይገባ ትንሽ ካሳ ነጥቀው ለኢንቬስተር በውድ ዋጋ እና ጉቦ ሊዝ ያረጉት ነበር።
እነዚህ የኦህዴድ ሹማምንት እና መሪዎች ናቸው ዋና ህግ ወጦች። አዲሱ አረጋ እንዳሉት «ህግ ይከበር» ከሆነ በመጀመርያ ደረጃ የኦህዴድ ሹማምንቶች ነበር መፈተሽ እና መታሰር የነበረባቸው። ሌሎቹ፤ ገንዘብ የተቀበሉት ገበሬዎቹ እና መሬት የገዙት ሰፋሪዎቹ በለዘብተኛ መልኩ መስተናገድ ነበረባቸው።
እነዚህ አይነት ሺያጮች ሲካሄዱ የአካባቢው የኦህዴድ (ኦዴፓ) ሹማምንቶች መጀመርያ እንዳላዩ ሆኑ። ቀጥሎ የምዝበራ እድል አይተው ገቡበት። ከገበሬ እየገዙ አትርፈው መሸጥ ጀመሩ። ከገበሬዎች ገዝተው ቤት የሰሩትን ሰዎች ጉቦ ካልሰጣችሁን እናባርራችኋለን፤ መብራት ውሃ እንከለክላችኋለን ወዘተ እያሉ አስፈራሩ። በዚህ መንገድ እራሳቸውን ሃብታም አደረጉ።
የኦዴፓ ላይ ድርስ ያሉ ባለስልጣናት ይህ አይነት ነገሮች አዲስ አበባ ዙርያ እንደሚካሄድ ያውቃሉ። ለነገሩ ሁላችንም እናውቃለን።
ስለዚህ ማን ነው ህገ ወጥ?! መሬት የገዙት ሰዎች? መሬት የሸጡት ገበሬዎች? የመዘበሩ እና በጉቦ ሃብታም የሆኑት የመንግስት ሹማምንቶች? ይህ እንደሚከሰት እያወቀ ዝም ያለው የኦህዴድ አመራር?
ግልጽ ነው፤ በፈቃደኝነት የተስማሙት ሳጭ እና ገዦች በአንጻሩ ንጹህ ናቸው። ማንንም አልጎዱም። ገበሬዎቹ የራሳቸውን መሬት በፈለጉት ዋጋ ሸጡ፤ ገዦችም በተስማሙበት ዋጋ መሬት ገዙ። ይህ ሺያጭ ባይካሄድ የኦህዴድ ሹማምንቶች የገበሬዎቹን መሬት በማይገባ ትንሽ ካሳ ነጥቀው ለኢንቬስተር በውድ ዋጋ እና ጉቦ ሊዝ ያረጉት ነበር።
እነዚህ የኦህዴድ ሹማምንት እና መሪዎች ናቸው ዋና ህግ ወጦች። አዲሱ አረጋ እንዳሉት «ህግ ይከበር» ከሆነ በመጀመርያ ደረጃ የኦህዴድ ሹማምንቶች ነበር መፈተሽ እና መታሰር የነበረባቸው። ሌሎቹ፤ ገንዘብ የተቀበሉት ገበሬዎቹ እና መሬት የገዙት ሰፋሪዎቹ በለዘብተኛ መልኩ መስተናገድ ነበረባቸው።
Monday, 10 December 2018
አዴፓ እና የመሬት ይዞታ ፖሊሲ
አቶ ንጉሱ ጥላሁን በዚህ ቃለምልልስ ዛሬ ያለው የመሬት ፖሊሲ አንዱ «ምሶሶአችን» ነው ብለዋል።
ይህን እሳቸውም ድርጅታቸውም ሌሎች አቋሞቻቸውን እንደፈተሹት እንዲፈትሹ እጠይቃለሁ። መሬት የግል ይሁን ይሉ አልልም የፖለቲካ ሁኔታው ለዛ አይነት ድምዳሜ ዛሬ የሚመች አይሆንምና። ግን አቋሙ ምሶሶ ነው አይበሉ። እየፈተሹት እየተዉት ይሄዱ።
የአማራ ገበሬ እራሱን ማሻሻል ያልቻለው እና ዝቅተኛ እስረኛ ሆኖ የቀረው ከጎረቤቱ መሬት ገዝቶ መስፋፋት እና በራሱ ላይ ኢንቬስት ማረግ ባለመቻሉ ነው። በተጨማሪ መሬት የመንግስት ይሁን የሚለው ፖሊሲ ጸንፈኛ የሆነ ዓለም ዙርያ ከአንድ ሁለት ሀገር በቀር የማይታይ ፖሊሲ ነው። አዴፓ ለዘብ ያለውን መካከለኛ መንገድ በዚህም ጉዳይ እንዲከተል እጠይቃለሁ።
https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_47.html
https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/blog-post_94.html
Tuesday, 2 October 2018
መሬት የግል ቢሆን ባለሃብት ይገዘዋል የሚባለው ሃሰት ነው
መሬት የግል መሆን አለበት ሲባል እንዱ በተለምዶ የሚሰነዘረው ተቃውሞ ገበሬዎች አግባብ ባልሆነ ርካሽ ዋጋ መሬታቸውን ይሸጣሉ እና ባለሃብት ብቻ መሬቱን ይገዛሉ። መሬት በሙሉ የባለሃብት ይሆናል ወደ «ፍዩዳል» ዘመን ከነችግሩ እንመለሳለን።
ይህ እጅግ የተሳሳተ አመለካከት ለመሆኑ ተጨባጭ መረጃ አለ። ላለፉት በርካታ ዓመታት መንግስት በሊዝ (የ55 ዓመት ሊዝ ለምሳሌ) በርካታ ትላልቅ መሬቶች ማከራየት ሞክሯል። በየክልሉ መርጥ የሆኑ ህዝብ ያለበትም የሌለበትም ለእርሻ አመቺ የሆኑ ቦታዎች ለሊዝ ኪራይ ቀርበዋል። ዋጋቸውም እጅግ ረካሽ ነበር። ለምሳሌ በጋምቤላ በዓመት 100,000 ብር አካባቢ ለመቶዎች ዬክታር ይከራያል።
ይህም ሆኖ ጥቂት ባለ ሃብቶች እና ኩባኒያዎች ናቸው ወደ እርሻ የገቡት። የቁጥር ሰነድ በእጄ የለኝም ግን ሊገን ይችላል። ግን አሁንም የሊዝ ቦታ በርካሽ ዋጋ መኖሩ የእርሻ መሬቱ ብዙ ፈላጊ እንዳልነበረው ያሳያል።
ዛሬ ባለሃብቶች በርካሽ ዋጋ ምርጥ የእርሻ መሬት ሊዝ ማድረግ ያልፈለጉ ከግል ገበሬዎች የደከመ የተበጣጠሰ መሬት ይገዛል ብለን ማሰብ አንችልም። ገበሬው መሬትን መሸጥ ቢችልም አብዛኛው ጊዜ ባለሃብት አይገዛውም።
የሚገዛው ጎረቤቱ ነው የሚሆነው። ዛሬ በየአመቱ በእኩል የሚከራየው ጎረቤት ገበሬ ከምከራይ ልግዛ ብሎ ይጠይቃል። የጎበዝ ገበሬው ይዞታ ይሰፋል የመሬት ጠቅላላ ምርቱም ይጨምራል። ጎበዝ ገበሬው በዚህ መንገድ እየተስፋፋ ታዳጊ ገበሬ ይሆናል። ይህ የሃገራችንን ጠቅላላ ምርት ይጨምራል።
(http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_47.html)
ይህ እጅግ የተሳሳተ አመለካከት ለመሆኑ ተጨባጭ መረጃ አለ። ላለፉት በርካታ ዓመታት መንግስት በሊዝ (የ55 ዓመት ሊዝ ለምሳሌ) በርካታ ትላልቅ መሬቶች ማከራየት ሞክሯል። በየክልሉ መርጥ የሆኑ ህዝብ ያለበትም የሌለበትም ለእርሻ አመቺ የሆኑ ቦታዎች ለሊዝ ኪራይ ቀርበዋል። ዋጋቸውም እጅግ ረካሽ ነበር። ለምሳሌ በጋምቤላ በዓመት 100,000 ብር አካባቢ ለመቶዎች ዬክታር ይከራያል።
ይህም ሆኖ ጥቂት ባለ ሃብቶች እና ኩባኒያዎች ናቸው ወደ እርሻ የገቡት። የቁጥር ሰነድ በእጄ የለኝም ግን ሊገን ይችላል። ግን አሁንም የሊዝ ቦታ በርካሽ ዋጋ መኖሩ የእርሻ መሬቱ ብዙ ፈላጊ እንዳልነበረው ያሳያል።
ዛሬ ባለሃብቶች በርካሽ ዋጋ ምርጥ የእርሻ መሬት ሊዝ ማድረግ ያልፈለጉ ከግል ገበሬዎች የደከመ የተበጣጠሰ መሬት ይገዛል ብለን ማሰብ አንችልም። ገበሬው መሬትን መሸጥ ቢችልም አብዛኛው ጊዜ ባለሃብት አይገዛውም።
የሚገዛው ጎረቤቱ ነው የሚሆነው። ዛሬ በየአመቱ በእኩል የሚከራየው ጎረቤት ገበሬ ከምከራይ ልግዛ ብሎ ይጠይቃል። የጎበዝ ገበሬው ይዞታ ይሰፋል የመሬት ጠቅላላ ምርቱም ይጨምራል። ጎበዝ ገበሬው በዚህ መንገድ እየተስፋፋ ታዳጊ ገበሬ ይሆናል። ይህ የሃገራችንን ጠቅላላ ምርት ይጨምራል።
(http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_47.html)
የአዲስ አበባ ተፈናቃዎች
የኛ የአዲስ አበባዎች አንዱ (ከብዙ) ድክመቶቻችን በዚህ ቪዲዮ ይገለጻል፤
https://www.youtube.com/watch?v=fhKBwe1wF2Y
ይህ ድክመት ከመሬታቸው የተፈናቀሉት ወንድሞች እይቶቻችን ጎረቤቶቻችንን ዞር ብለን አለማየት ነው። በመቶ ሺዎች «የብሎኬት ካሳ» ተሰጥተው ከቤታቸው ወደ ዳር ከተማ ባዶ የሆነ 70 ካራሜትር ተባርረዋል።
ሰፈር ከነ ማህበራዊ ኑሮ ተበታትነዋል። አብዮተኛ እርምጃ ተወስዶባቸዋል ማለት ይቻላል። ይህ ለተፈናቃዮች ብቻ ሳይሆን ለመላው የአዲስ አበባ ህዝብ ምን ያህል ጎጂ እንደሆነ ይታወቃል። "Social capital" ከሰረ፤ መተባበር ጠፋ፤ መተዋወቅ ጠፋ፤ መደጋገፍ ጠፋ፤ ማህበራዊ ግብረ ገብ ጠፋ፤ ኢ-ማህበራዊነት በዛ፤ ወንጀል በዛ ወዘተ።
አንዱ ለችግሩ መፍትሄ የመሬት ፖሊሲውን መቀየር ነው።
1. ካሁን ወድያ መንግስት መሬት መውሰድ የሚችለው ለመንግስት ጥቅም እንደ መብራት፤ ውሃ፤ መንገድ ወዘተ ይሁን። ካሳውም የ«ብሎኬት ዋጋ» ሳይሆን የመሬቱ ከነቤቱ የገበያ ዋጋ መሆን አለበት።
2. መሬት ለግል ጉዳይ እንደ ኢንቬስትሜንት ከተፈለገ ኢንቬስተሩ በግል ከመሬት ባለቤቶቹ መሬቱን ተደራድሮ ይግዛ። መንግስት ጣልቃ አይግባ። ገዥ እና ሻጭ ከተስማሙ ሁለቱም ደስተኛ ይሆናሉ። ኢንቬስተሩ የገበያ ዋጋ ስለከፈለ በመሬቱ አይቀልድም አዋጪ ነገር ላይ ያውለዋል። ሻጩም ተበድያለሁ አይልም በራሴ የወሰንኩትን አገኘሁኝ ብሎ ያምናል።
የሚጠቀም ሶስተኛ ወገኖችም አሉ። መላው የአዲስ አበባ ህዝብ ከመፈናቀል የሚያመጣው ጠቅላላ ህምሞች ይተርፋል። የመንግስት ሰራተኞችም ከሙስና ፈተና ይድናሉ። ማፈናቀል ወይንም የመሬት ፖሊሲው በጠቅላላ ካድሬዎች በረካሽ አፈናቅለው በውድ ለኢንቬስተር በመስጠት ሙስና የጋበዘ ስርዓት ነበር። ፖሊሲው ከተቀየረ ሁላችንም ከዚህ ሁሉ እንተርፋለን።
https://www.youtube.com/watch?v=fhKBwe1wF2Y
ይህ ድክመት ከመሬታቸው የተፈናቀሉት ወንድሞች እይቶቻችን ጎረቤቶቻችንን ዞር ብለን አለማየት ነው። በመቶ ሺዎች «የብሎኬት ካሳ» ተሰጥተው ከቤታቸው ወደ ዳር ከተማ ባዶ የሆነ 70 ካራሜትር ተባርረዋል።
ሰፈር ከነ ማህበራዊ ኑሮ ተበታትነዋል። አብዮተኛ እርምጃ ተወስዶባቸዋል ማለት ይቻላል። ይህ ለተፈናቃዮች ብቻ ሳይሆን ለመላው የአዲስ አበባ ህዝብ ምን ያህል ጎጂ እንደሆነ ይታወቃል። "Social capital" ከሰረ፤ መተባበር ጠፋ፤ መተዋወቅ ጠፋ፤ መደጋገፍ ጠፋ፤ ማህበራዊ ግብረ ገብ ጠፋ፤ ኢ-ማህበራዊነት በዛ፤ ወንጀል በዛ ወዘተ።
አንዱ ለችግሩ መፍትሄ የመሬት ፖሊሲውን መቀየር ነው።
1. ካሁን ወድያ መንግስት መሬት መውሰድ የሚችለው ለመንግስት ጥቅም እንደ መብራት፤ ውሃ፤ መንገድ ወዘተ ይሁን። ካሳውም የ«ብሎኬት ዋጋ» ሳይሆን የመሬቱ ከነቤቱ የገበያ ዋጋ መሆን አለበት።
2. መሬት ለግል ጉዳይ እንደ ኢንቬስትሜንት ከተፈለገ ኢንቬስተሩ በግል ከመሬት ባለቤቶቹ መሬቱን ተደራድሮ ይግዛ። መንግስት ጣልቃ አይግባ። ገዥ እና ሻጭ ከተስማሙ ሁለቱም ደስተኛ ይሆናሉ። ኢንቬስተሩ የገበያ ዋጋ ስለከፈለ በመሬቱ አይቀልድም አዋጪ ነገር ላይ ያውለዋል። ሻጩም ተበድያለሁ አይልም በራሴ የወሰንኩትን አገኘሁኝ ብሎ ያምናል።
የሚጠቀም ሶስተኛ ወገኖችም አሉ። መላው የአዲስ አበባ ህዝብ ከመፈናቀል የሚያመጣው ጠቅላላ ህምሞች ይተርፋል። የመንግስት ሰራተኞችም ከሙስና ፈተና ይድናሉ። ማፈናቀል ወይንም የመሬት ፖሊሲው በጠቅላላ ካድሬዎች በረካሽ አፈናቅለው በውድ ለኢንቬስተር በመስጠት ሙስና የጋበዘ ስርዓት ነበር። ፖሊሲው ከተቀየረ ሁላችንም ከዚህ ሁሉ እንተርፋለን።
Friday, 21 September 2018
የተረሳው ጉዳያችን፤ የመሬት ፖሊሲ ሚና በጎሳ ፖለቲካ
ከዚህ በፊት ደጋግሜ ስለ የኢትዮጵያ የመሬት ፖሊሲ ችግር ጽፍያለሁ (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_47.html)። መሬት የግል ወይንም የአካባቢ ("local community" ለምሳሌ ወረዳ) ከመሆኑ ፋንታ የመንግስት መሆኑ ለህዝባችን እጅግ ጎጂ ፖሊሲ ነው ብዬ ነው የማምነው። ለዝርዝሩ ከላይ የጠቀስኩትን ጽሁፍ አንብቡ፤ ግን በአጭሩ መሬት የመንግስት መሆኑ የፈጠረው ችግሮች እንዲህ ናቸው፤
1. ገበሬው ለ«ጎበዝ ገበሬ» የሆነው ጎረቤቱ መሬቱን ሽጦ ወደ ከተማ መሄድ ባለመቻሉ ገጠር ቀርቶ በገጠር የመውለድ መጠን (birth rate፤ በገጠር አማካኙ ከስድስት ልጅ በላይ ነው) ልጅ ወለደ። ከተማ ቢሄድ ኖሮ ሁለት ልጅ (ሁለት አማካኙ ነው ለከተማ ነዋሪ) ይወልድ ነበር። ይህ ማለት የህዝብ ቁጥርን ባልተጠበቀና በኢተፈጥሮዊ (artificial) መንገድ ንሯል። ኢተፈጥራዊ ማለት ህዝቡ ወደ ከተማ እንዳይሄድ ነፃነቱ በመገደብ የጠፈጠረ ሁኔታ ስለሆነ ነው። ከግዳጅ የመጣ ክስተት ስለሆነ ነው።
2. የገጠር ህዝብ ቁጥር ንሮ የገበሬ መሬት አንሶ ልጆች የሚወርሱት አጥተው አሁን ታላቅ የገጠር ወደ ከተማ ፍልሰት ተከስቷል። ለ40 ዓመት ቀስ በቀስ ፍልሰት ከመሆኑ ፋንታ የገጠሩ ሰው ለ40 ዓመታት ከገጠር ተጠራቅሞ አሁን ባንዴ ወደ ከተሞች እየመጣ ነው። ይህ ሁኔታ ከተሞቻችንን አስጨንቋል።
3. ገበሬዎች ቢጎብዙም ገንዘብ ቢኖራቸውም መሬት መግዛት ባለመቻላቸው የግብርና ስራውን ማስፋፋት አልቻለም። ማደግ አልተፈቀድለትም። በዚህ ምክንያት «የሰው አቅማቸው» (human capital) እንዳያድግ ተደርጓል። ለምሳሌ እንደ የግብርና የሙያ፤ የንግድ ሙያ፤ የአስተዳደር ችሎታ አይነቱን እንዳያዳብር ተደርጓል።
4. ገበሬው ሽጦ መሄድ ባላመቻሉ መሬቱን ለትውልድ እያከፋፈለ መሸንሸን ሆነበት። መሬቱ ተሸንሽኖ የያንዳንዱ ገበሬ መሬት አንሶ አንድ ቤተሰብም ማስተዳደር የማይችል ሆኗል። በዚህ ምክንያት ገበሬዎች ለድርቅ እና ርሃብ ተጋለጡ። የምግብ ዋስትና እጥረት እንዳለ ነው።
5. ጎበዝ ገበሬዎች መሬት ገዝተው መስፋፋት ባለመቻላቸው እና ደካማ ገበሬዎች ለጎበዞቹ መሸጥ ባለመቻላቸው የእርሻ ውጤት ዝቅተኛ ሆኖ ቈርቷል። ይህ ደግሞ የእህልና የምግባ ዋጋ ግሽበት አምጥቷል።
ከላይ የጠቀስኳቸው ባብዛኛው በኤኮኖሚ ዙርያ የሆኑ ነጥቦች ናቸው። ግን የመሬት ፖሊሲው ሌላ ታላቅ የፖለቲካ እና ማህበረሰባዊ ተጽዕኖ አለው።
ባጭሩ፤ የመሬት ፖሊሲው አንዱ የጎሳ አስተዳደሩ ምሶሶ ነው። መሬት የ«ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች» ነው ሲባል ለ27 ዓመት የተተረጎመው የአማራ ክልል መሬት የ«አማራ ብሄር» ነው፤ የኦሮሚያ ክልል መሬት የ«ኦሮሞ ህዝብ» ነው ወዘተ እየተባለ ነው። ትርጉሙም የህገ መንግስቱን ጽሁፍም መንፈስም የተከተለ ነው።
«መጤ» እና «ነባር» የሚሉት ጽንሰ ሃሳቦች በማህበረሰቡ በዚህ መሬት ፖሊሲ ይደገፋሉ። የ27 ዓመታት የመፈናቀል ዘመቻዎች የተካሄዱትም በዚህ ምክንያት ነው። ግን ህጉ የመሬት ባለቤትነት የግለሰብ ወይንም የቅርብ አካባቢ ሰዎች ቢያደርግ ኖሮ የ«መጤ» እና «ነባር» አስተሳሰብን ይቀንስ ነበር ነአ ቀስ በቀስ ያጠፋ ነበር። ለዚህ አስተሳሰብ የህግ ሽፋን እንዳይኖረው ያደርጋል። ተፈናቃዮች ለመብታቸው በፍርድ ቤት መታገል እንዲችሉ ያደርጋቸው ነበር።
ስለዚህ ዛሬ ያለውን ጎሰኝነትን ለመታገል እና ቀስ ብሎ ከጎሳ ፌደራሊዝም ወደ ህብረ ባህላዊ አገዛዝ ለመሄድ ይህን የመሬት ፖሊሲ መመልከትና መቀየር ጠቃሚ ይመስለኛል።
1. ገበሬው ለ«ጎበዝ ገበሬ» የሆነው ጎረቤቱ መሬቱን ሽጦ ወደ ከተማ መሄድ ባለመቻሉ ገጠር ቀርቶ በገጠር የመውለድ መጠን (birth rate፤ በገጠር አማካኙ ከስድስት ልጅ በላይ ነው) ልጅ ወለደ። ከተማ ቢሄድ ኖሮ ሁለት ልጅ (ሁለት አማካኙ ነው ለከተማ ነዋሪ) ይወልድ ነበር። ይህ ማለት የህዝብ ቁጥርን ባልተጠበቀና በኢተፈጥሮዊ (artificial) መንገድ ንሯል። ኢተፈጥራዊ ማለት ህዝቡ ወደ ከተማ እንዳይሄድ ነፃነቱ በመገደብ የጠፈጠረ ሁኔታ ስለሆነ ነው። ከግዳጅ የመጣ ክስተት ስለሆነ ነው።
2. የገጠር ህዝብ ቁጥር ንሮ የገበሬ መሬት አንሶ ልጆች የሚወርሱት አጥተው አሁን ታላቅ የገጠር ወደ ከተማ ፍልሰት ተከስቷል። ለ40 ዓመት ቀስ በቀስ ፍልሰት ከመሆኑ ፋንታ የገጠሩ ሰው ለ40 ዓመታት ከገጠር ተጠራቅሞ አሁን ባንዴ ወደ ከተሞች እየመጣ ነው። ይህ ሁኔታ ከተሞቻችንን አስጨንቋል።
3. ገበሬዎች ቢጎብዙም ገንዘብ ቢኖራቸውም መሬት መግዛት ባለመቻላቸው የግብርና ስራውን ማስፋፋት አልቻለም። ማደግ አልተፈቀድለትም። በዚህ ምክንያት «የሰው አቅማቸው» (human capital) እንዳያድግ ተደርጓል። ለምሳሌ እንደ የግብርና የሙያ፤ የንግድ ሙያ፤ የአስተዳደር ችሎታ አይነቱን እንዳያዳብር ተደርጓል።
4. ገበሬው ሽጦ መሄድ ባላመቻሉ መሬቱን ለትውልድ እያከፋፈለ መሸንሸን ሆነበት። መሬቱ ተሸንሽኖ የያንዳንዱ ገበሬ መሬት አንሶ አንድ ቤተሰብም ማስተዳደር የማይችል ሆኗል። በዚህ ምክንያት ገበሬዎች ለድርቅ እና ርሃብ ተጋለጡ። የምግብ ዋስትና እጥረት እንዳለ ነው።
5. ጎበዝ ገበሬዎች መሬት ገዝተው መስፋፋት ባለመቻላቸው እና ደካማ ገበሬዎች ለጎበዞቹ መሸጥ ባለመቻላቸው የእርሻ ውጤት ዝቅተኛ ሆኖ ቈርቷል። ይህ ደግሞ የእህልና የምግባ ዋጋ ግሽበት አምጥቷል።
ከላይ የጠቀስኳቸው ባብዛኛው በኤኮኖሚ ዙርያ የሆኑ ነጥቦች ናቸው። ግን የመሬት ፖሊሲው ሌላ ታላቅ የፖለቲካ እና ማህበረሰባዊ ተጽዕኖ አለው።
ባጭሩ፤ የመሬት ፖሊሲው አንዱ የጎሳ አስተዳደሩ ምሶሶ ነው። መሬት የ«ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች» ነው ሲባል ለ27 ዓመት የተተረጎመው የአማራ ክልል መሬት የ«አማራ ብሄር» ነው፤ የኦሮሚያ ክልል መሬት የ«ኦሮሞ ህዝብ» ነው ወዘተ እየተባለ ነው። ትርጉሙም የህገ መንግስቱን ጽሁፍም መንፈስም የተከተለ ነው።
«መጤ» እና «ነባር» የሚሉት ጽንሰ ሃሳቦች በማህበረሰቡ በዚህ መሬት ፖሊሲ ይደገፋሉ። የ27 ዓመታት የመፈናቀል ዘመቻዎች የተካሄዱትም በዚህ ምክንያት ነው። ግን ህጉ የመሬት ባለቤትነት የግለሰብ ወይንም የቅርብ አካባቢ ሰዎች ቢያደርግ ኖሮ የ«መጤ» እና «ነባር» አስተሳሰብን ይቀንስ ነበር ነአ ቀስ በቀስ ያጠፋ ነበር። ለዚህ አስተሳሰብ የህግ ሽፋን እንዳይኖረው ያደርጋል። ተፈናቃዮች ለመብታቸው በፍርድ ቤት መታገል እንዲችሉ ያደርጋቸው ነበር።
ስለዚህ ዛሬ ያለውን ጎሰኝነትን ለመታገል እና ቀስ ብሎ ከጎሳ ፌደራሊዝም ወደ ህብረ ባህላዊ አገዛዝ ለመሄድ ይህን የመሬት ፖሊሲ መመልከትና መቀየር ጠቃሚ ይመስለኛል።
Tuesday, 14 August 2018
ተረት ተረት፤ አዲስ አበባ የሰፋችው ኦሮሞ ገበሬን በማፈናቀል ነው
እንደ አብዛኛው ውሸት «አዲስ አበባ የሰፋችው ኦሮሞ ገበሬን በማፈናቀል ነው» የሚለው የተወሰነ እውነታ አለው። አዎን በኢህአዴግ አገዛዝ በአዲስ አበባ ዙርያ ያሉ ገበሬዎች ለመሬታቸው ከሚገባው እጅግ ዝቅተኛ የሆነ ካሳ ተከፍሏቸው በግዴታ ከመሬታቸው ተባረዋል። ግን ይህ ሙሉ ታሪኩ አይደለም።
እንደሚታወቀው በሀገራችን መሬት የመንግስት ነው የሚል አሳዛኝ ህግ ነው ያለው። ይህ ህግ ሲተገበር ስናይ መንግስት ባሰኘው ጊዜ የከተማም ይሁን የገጠር መሬት ከነዋሪዎች ይወስዳል። ሲወስድ ደግሞ የሚከፍለው ካሳ የ«ገበያ» ዋጋ ሳይሆን መንግስት እራሱ የሚተምነው እጅግ አናሳ ካሳ ነው። ልምሳሌ አዲስ አበባ ውስጥ ለ«ልማት» ተብሎ መሬትን መንግስት ሲወስድ የሚከፍለው ካሳ የቤትና የጊቢው አብሮ ዋጋ ሳይሆን የቤቱ (የግንቡ) ዋጋ ብቻ ነው። ለምሳሌ 100 ካሬ ላይ ቤት አለኝ ከሸጥኩት 500,000 ብር ያመጣል እንበል። መንግስት ሊወስደው ከፈለገ ግን የቤቱ ግምብ ዋጋ ብቻ እራሱ (ሶስተኛ ወገን ሳይሆን) ገምቶ ምናልባት 50,000 ብር ከፍሎኝ በግድ ይወስደዋል። በገጥር ደግሞ እንደ ክልሉ እና ዞኑ ቢለያይም አንድ ምሳሌ ልስጣችሁ። መንግስት ከገበሬ መሬቱን ሲወስድ የሶስት ዓመት ገቢውን ለካሳ ይከፍለዋል። ገጠር መሬት መሸጥ ባይኖርም የዚህ መሬት ዋጋ ከዚህ በላይ እንደሚሆን መገመት ይቻላል። የሶስት ዓመት ገቢ ሳይሆን ቢያንስ የአስር ነው መታሰብ የነበረበት።
ከዚም አልፎ ተርፎ ይግባኝ የለም። መንግስት አንዴ ትፈናቀላላችሁ ካለ ይህን ውሳኔ መታገል አይቻልም። ከመሬት ንትቅያው በስተጀርባ ያለው የገንዘብ እና የፖለቲካ ኃይል እጅግ ከባድ ነው። የኢህአዴግ ባለሟሎች አሉ፤ ኢነቬስተር ዩኖራል፤ ጉቦኛ መንግስት ሰራተኛው አለ፤ ባለ ስልጣን አለ። ባለ መሬቱ ከነዚህ ጋር መጋፋት አይችልም እና ተዛዙ ሲመጣ እሺ ጌታዬ ብሎ መንግስት የሚሰጠውን ካሳ ተቀብሎ መሄድ ነው።
ይህ ሁኔታ ያለው በመላው ሀገሪቷ ነው በአዲስ አበባ ብቻ አይደለም። ከመሬታቸው አለ አግባብ የሚፈናቀሉት ኦሮሞ ብቻ ሳይሆኑ ሌሎች ሁሉ ናቸው። ገበሬዎች ብቻ ሳይሆን ከተሜዎችም ናቸው። አዲስ አበባን ከመሬታቸው የሚፈናቀሉትን ካየን ከአዲስ አበባ ዙርያ ካሉት ገበሬዎች ይልቅ የከተማው ተፈናቃይ ነው ይበልጥ መፈናቀል የሚጎዳው። ለምን? አራት ኪሎ 100 ካሬ ላይ የሚኖር ቤቱን ከነ ጊቢው ቢሸጠው አንድ ሚሊዮን ያገኝበት ነበር 50,000 ተሰጥቶ ይባረራል። ገበሬው ግን ሰፋ ያለ መሬት ቢኖረውም ከከተማ ሩቅ በመሆኑ ዋጋው ያን ያህል ውድ አይደለም በሚሰጠው ካሳ እና በመሬቱ እውነተኛ ዋጋ ያለው ልዩነት እንደ ከተማው መሬት አይሆንም። ስለዚህ አዲስ አበባ እና ዙርያ ሁሉም በመንግስት ከመሬታቸው የተፈናቀሉ ቢጎዱም በአማካይነት የከተማው ከገበሬው ይበልጥ ተጎድቷል።
በመጨረሻ ማን ነበር እነዚህን ገበሬዎች የሚያፈናቅለው ብለን ከጠየቅን የኦሮሚያ የኦህዴድ ቀበሌ እና ውረዳ ሰራተኞች እና የነሱ አዛዦች ናቸው። ለምሳሌ ባለ ሃብት ወይንም የአዲስ አበባ መንግስት በኢህአዴግ ድጋፍ መጥተው የለገጣፎን ባለስልጣኖች መሬት እንፈልጋለን ይላሉ። እነዚህ የኦህዴድ ባለ ስልጣኖች አላማቸው ትንሽ ካሳ ለገበሬው ሰጥቶ በትልቅ ዋጋ ለአዲስ አበባ ወይንም ለባለ ሃብት መስጠት እና በመካከል ከዋጋ ልዩነቱ ጉቦ መብላት ነው። አዲስ አበባ ውስጥም ይህ ነበር አሰራሩ። በጠቅላላ ላለፉ 27 ዓመት መሬት ለመንግስት ሹማምንት ታላቅ የጉቦ የገቢ ምንጭ እና ለኢህአዴግ ታላቅ የካድሬ መያዣ መንገድ ነበር። ስለዚህ አዲስ አበባ ሳይሆን የራሱ የኦህዴድ ካድሬ ነው አዲስ አበባ ዙርያ ያለውን ኦሮሞ ገበሬ አለ አግባብ ያፈናቀለው። አዲስ አበባ ናት ያፈናቀለቻቸው ማለት ሃሰት ነው።
ሙሉ እውነታው ይህ ነው፤ አዲስ አበባ ዙርያ ሳይሆን አዲስ አበባ ውስጥም ሀገር ዙርያም በየቀኑ ዜጎቻችን ከመሬታቸው አለ አግባብ እና አለ በቂ ካሳ ይፈናቀላሉ። የሚፈናቀሉት ደግሞ ኦሮሞዎች ብቻ ሳይሆኑ ሁሉም ነው። ችግሩ በአዲስ አበባ እና በኦሮሚያ መካከል ሳይሆን የመሬት የመንግስት ነው የሚለው ፖሊሲ (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_47.html) ነው። መሬት የግል ቢሆን እነዚህ ገበሬዎች በነፃነት በሚያስደስታቸው ዋጋ መሬታቸውን ሽጠው ነበር።
እንደሚታወቀው በሀገራችን መሬት የመንግስት ነው የሚል አሳዛኝ ህግ ነው ያለው። ይህ ህግ ሲተገበር ስናይ መንግስት ባሰኘው ጊዜ የከተማም ይሁን የገጠር መሬት ከነዋሪዎች ይወስዳል። ሲወስድ ደግሞ የሚከፍለው ካሳ የ«ገበያ» ዋጋ ሳይሆን መንግስት እራሱ የሚተምነው እጅግ አናሳ ካሳ ነው። ልምሳሌ አዲስ አበባ ውስጥ ለ«ልማት» ተብሎ መሬትን መንግስት ሲወስድ የሚከፍለው ካሳ የቤትና የጊቢው አብሮ ዋጋ ሳይሆን የቤቱ (የግንቡ) ዋጋ ብቻ ነው። ለምሳሌ 100 ካሬ ላይ ቤት አለኝ ከሸጥኩት 500,000 ብር ያመጣል እንበል። መንግስት ሊወስደው ከፈለገ ግን የቤቱ ግምብ ዋጋ ብቻ እራሱ (ሶስተኛ ወገን ሳይሆን) ገምቶ ምናልባት 50,000 ብር ከፍሎኝ በግድ ይወስደዋል። በገጥር ደግሞ እንደ ክልሉ እና ዞኑ ቢለያይም አንድ ምሳሌ ልስጣችሁ። መንግስት ከገበሬ መሬቱን ሲወስድ የሶስት ዓመት ገቢውን ለካሳ ይከፍለዋል። ገጠር መሬት መሸጥ ባይኖርም የዚህ መሬት ዋጋ ከዚህ በላይ እንደሚሆን መገመት ይቻላል። የሶስት ዓመት ገቢ ሳይሆን ቢያንስ የአስር ነው መታሰብ የነበረበት።
ከዚም አልፎ ተርፎ ይግባኝ የለም። መንግስት አንዴ ትፈናቀላላችሁ ካለ ይህን ውሳኔ መታገል አይቻልም። ከመሬት ንትቅያው በስተጀርባ ያለው የገንዘብ እና የፖለቲካ ኃይል እጅግ ከባድ ነው። የኢህአዴግ ባለሟሎች አሉ፤ ኢነቬስተር ዩኖራል፤ ጉቦኛ መንግስት ሰራተኛው አለ፤ ባለ ስልጣን አለ። ባለ መሬቱ ከነዚህ ጋር መጋፋት አይችልም እና ተዛዙ ሲመጣ እሺ ጌታዬ ብሎ መንግስት የሚሰጠውን ካሳ ተቀብሎ መሄድ ነው።
ይህ ሁኔታ ያለው በመላው ሀገሪቷ ነው በአዲስ አበባ ብቻ አይደለም። ከመሬታቸው አለ አግባብ የሚፈናቀሉት ኦሮሞ ብቻ ሳይሆኑ ሌሎች ሁሉ ናቸው። ገበሬዎች ብቻ ሳይሆን ከተሜዎችም ናቸው። አዲስ አበባን ከመሬታቸው የሚፈናቀሉትን ካየን ከአዲስ አበባ ዙርያ ካሉት ገበሬዎች ይልቅ የከተማው ተፈናቃይ ነው ይበልጥ መፈናቀል የሚጎዳው። ለምን? አራት ኪሎ 100 ካሬ ላይ የሚኖር ቤቱን ከነ ጊቢው ቢሸጠው አንድ ሚሊዮን ያገኝበት ነበር 50,000 ተሰጥቶ ይባረራል። ገበሬው ግን ሰፋ ያለ መሬት ቢኖረውም ከከተማ ሩቅ በመሆኑ ዋጋው ያን ያህል ውድ አይደለም በሚሰጠው ካሳ እና በመሬቱ እውነተኛ ዋጋ ያለው ልዩነት እንደ ከተማው መሬት አይሆንም። ስለዚህ አዲስ አበባ እና ዙርያ ሁሉም በመንግስት ከመሬታቸው የተፈናቀሉ ቢጎዱም በአማካይነት የከተማው ከገበሬው ይበልጥ ተጎድቷል።
በመጨረሻ ማን ነበር እነዚህን ገበሬዎች የሚያፈናቅለው ብለን ከጠየቅን የኦሮሚያ የኦህዴድ ቀበሌ እና ውረዳ ሰራተኞች እና የነሱ አዛዦች ናቸው። ለምሳሌ ባለ ሃብት ወይንም የአዲስ አበባ መንግስት በኢህአዴግ ድጋፍ መጥተው የለገጣፎን ባለስልጣኖች መሬት እንፈልጋለን ይላሉ። እነዚህ የኦህዴድ ባለ ስልጣኖች አላማቸው ትንሽ ካሳ ለገበሬው ሰጥቶ በትልቅ ዋጋ ለአዲስ አበባ ወይንም ለባለ ሃብት መስጠት እና በመካከል ከዋጋ ልዩነቱ ጉቦ መብላት ነው። አዲስ አበባ ውስጥም ይህ ነበር አሰራሩ። በጠቅላላ ላለፉ 27 ዓመት መሬት ለመንግስት ሹማምንት ታላቅ የጉቦ የገቢ ምንጭ እና ለኢህአዴግ ታላቅ የካድሬ መያዣ መንገድ ነበር። ስለዚህ አዲስ አበባ ሳይሆን የራሱ የኦህዴድ ካድሬ ነው አዲስ አበባ ዙርያ ያለውን ኦሮሞ ገበሬ አለ አግባብ ያፈናቀለው። አዲስ አበባ ናት ያፈናቀለቻቸው ማለት ሃሰት ነው።
ሙሉ እውነታው ይህ ነው፤ አዲስ አበባ ዙርያ ሳይሆን አዲስ አበባ ውስጥም ሀገር ዙርያም በየቀኑ ዜጎቻችን ከመሬታቸው አለ አግባብ እና አለ በቂ ካሳ ይፈናቀላሉ። የሚፈናቀሉት ደግሞ ኦሮሞዎች ብቻ ሳይሆኑ ሁሉም ነው። ችግሩ በአዲስ አበባ እና በኦሮሚያ መካከል ሳይሆን የመሬት የመንግስት ነው የሚለው ፖሊሲ (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_47.html) ነው። መሬት የግል ቢሆን እነዚህ ገበሬዎች በነፃነት በሚያስደስታቸው ዋጋ መሬታቸውን ሽጠው ነበር።
Saturday, 6 May 2017
Our Radical Politicians - Land to the Ruler!
Teshome Guebremariam, the recently departed former legal advisor to Emperor Haile Selassie’s government, once said something to the effect of ‘we said “land for the tiller,” but we ended up with land for the ruler (the government)’. Land to the tiller – a policy of giving tenant farmers land title to the land they rent from large landowners – although a morally, politically, and technically difficult policy, seemed a reasonable and moderate response to the land exploitation situation during the Emperor’s time. Land to the ruler – transferring ownership of all land to the government – nationalizing all land – was a radical and extreme response. Unfortunately, our political elite at the time chose the radical and extreme response. Indeed, at critical junctures during Ethiopia’s modern history, our political elite, especially ‘Haile Selassie’s children’ – those educated from the 1950’s onwards – have too often taken radical and extreme political decisions which have resulted in long term disaster for the nation. This has resulted in repeated disasters and unanticipated and unintended consequences for the nation.
In this article, let us consider that fateful decision to nationalize land, a decision that the Ethiopian people have paid for and continue to pay for dearly. In brief, this policy has resulted in:
1. Artificially high national population and birth rate
2. The recent explosion of rural-urban migration that is chocking our cities
3. Low levels of human capital in rural areas, particularly in the area of farming expertise
4. Low agricultural productivity
5. Extremely high food prices and inflation
6. Food insecurity
How did all this come about? First, the nationalization of land, which included forbidding farmers to sell and buy land, essentially imprisoned our rural population. It meant farmers and their families could no longer move to the city. Let me explain by an example – an example farmer – call him ‘Amde’. In 1975, Amde had seven hectares of land – quite a decent sized holding. If Amde wanted to move to the city, he would need some money – some ‘start-up money’ – to live on until he settled down, found a source of income, etc. Normally, this money would come from selling all or even part of his land – his biggest asset. After all, most Ethiopian farmers in the past and today do not have other assets of significant value. However, thanks to the nationalization of land, the farmer was no longer allowed to sell or trade his land, or even mortgage it. Moreover, if he moved to the city, he most cases he would forego all rights to his piece of land! So not only could he not sell his land for money to live on in the city, but if he moved to the city and then for some reason changed his mind after some time and wanted to return to the farm, he could not do so – his farm would have been taken. Knowing this, farmers in general did not move to the city in numbers that they otherwise would have done. Indeed, the statistics show (I discuss this below) that there was minimal rural to urban migration from 1975 until very recently.
So, what was life like for Amde on the farm? Well, like all rural dwellers, he had many children, let’s say seven children (6.5 was the rural average birth rate around 2007 – keep in mind the Addis Ababa average was 2.2 – a big difference). As his children grew older, he divided his seven hectares into seven pieces – his children got one hectare each. And then his children too had seven children each. His land started getting crowded. As the years went by, country-wide, the average plot size of farmers started approaching one hectare and rural areas started getting congested.
Note that at the time of the 1975 land proclamation, about 85% of Ethiopia’s population, about 28 million people, lived in rural areas. In 2015, 40 years later, about 80% of Ethiopia’s population, or about 80 million people, lived in rural areas! In 40 years, the rural share of the population changed only 5%, but given the naturally high rural birth rates, the absolute rural population skyrocketed. Why? Because for 40 years, farmers, not being allowed to sell their land, did not move to urban areas. If the natural, controlled, and steady rural to urban migration that has occurred and continues everywhere around the world were allowed to happen in Ethiopia, then perhaps by 2015 the percentage of population rural areas would have fallen to 70% or lower. This would have meant more people in urban areas where the birth rate is low, and less people in rural areas where the birth rate is high, and this would have resulted in the overall population in Ethiopia being somewhat lower as well. However, because this natural rural-urban migration was artificially restricted in Ethiopia, the population of the rural ‘prison’ grew and grew, in 40 years from 28 million to 80 million. So this continued high rural-urban population ratio is a major cause of the artificially high national population today.
So what happened to Amde’s family? Recall that his children have one hectare each and seven children each. They cannot divide that one hectare into seven pieces for each of their children – the resulting plots would be too small to sustain a household. So they leave their land to only one of their children, with the remaining six children, having received a high school education thanks to the massive increase in rural public education, forced to try and make their living in the city. This is what is happening today in Ethiopia. The inevitable land deficit that we all expected by that the government ignored is now occurring. Today, millions of farmers have only enough land for one child to inherit – the rest of their children are all migrating to the city.
Hence the explosion in rural to urban migration we see today. Plot sizes have shrunk so much so as to be unsustainable. Most rural children are no longer inheriting land from their parents the plot sizes are too small to be divided. And, even though food prices are extremely high and there has never been a better time to be a farmer, if you have enough land, young people are flooding into urban areas. What we are seeing today is 40 years’ worth of pent up, accumulated, and multiplied rural-urban migration happening virtually at once. And this great rural-urban migration explosion is just starting.
But there’s more to this story – let’s go back to Amde. Amde was not a very productive farmer – he was just did not have the skills nor the desire to farm but farmed only to make a living. But his neighour Gemechu was an excellent farmer who made the most of his plot of land and wished to expand. He was, like any other business person, eager to expand is operations, could not. But, given the government land policy, he could not buy land. Amde would have been willing to sell his land to him and Gemechu would have bought it – they would have agreed on a price, but this was not allowed. So the best Gemechu could do was rent land from Amde on a seasonal basis. Gemechu wished to dig a well, plant trees, and make other long term investments, but he could not since the land was only his for a season and he could not know what would happen in the long term. He also dreamed of a time when he could buy other neighbours’ plots and expand to a level where he could learn mechanized farming, learn about growing fruit seedlings, etc. But his dreams never materialized.
Note that Gemechu was producing 20 quintals of teff per hectare, while the not very productive Amde was producing 10. If Gemechu had bought Amde’s seven hectares and planted teff, the seven hectares would have gone from producing 70 quintals to 140 quintals. Overall agricultural productivity would have increased significantly. Gemechu, with his increased income and taking advantage of economies of scale, would have gone on to greater agricultural exploits. Amde would have been able to buy cheaper teff.
What happened to Gemechu was a travesty that the government(s) of Ethiopia brought on the country’s farmers. By not allowing farmers to be entrepreneurial and to expand, the government stifled farmers’ human capital. This has had not only an economic but also psychological, political, and social impact on farmers. Unlike those in all other commercial sectors, farmers uniquely were restricted from freedom in their business – they were not allowed to expand. As a result, they were indirectly restricted from improving their agricultural skills and education and essentially forced to remain as they were, and to give up hope. Imagine if a mechanic was by law prevented from having a garage bigger than a one-car garage. He would not come close to achieving his potential. If a professor were told that he could never look for another job and he could never conduct research on anything but one subject, he too would never achieve his potential. In fact, he soon stop trying and just mindlessly do his job. Same for farmers. The system made it communism for the farmers, capitalism for the rest.
To add insult to injury, successive governments and NGO’s continued to regard farmers as almost daft – as ignorant and incapable and in need of all forms of paternalism and assistance. It is true that the agricultural sector – that farmers – have not been able to increase their human capital – their knowledge and capacity – but this was and is only because they have been restricted from being able to expand their business. In true communist fashion, the governments’ plan was to hold the most important factor – land – constant, and increase inputs such as improved seeds, fertilizer, agricultural education, etc., with the hope that this would result in greater productivity. Of course it has not worked.
Today, in Ethiopia, agricultural productivity per unit of land is low. Food prices are some of the highest in developing countries. Milk, eggs, butter, meat, and honey are more expensive in Ethiopia than in many Western countries! The agricultural sector has been unable respond to the even the high demand and high prices in today’s Ethiopia that should have resulted in greater investment and productivity. Hence the food inflation – the leading source of inflation in the country – something the government continues to battle.
Back to Amde… The once a decade drought arrived and Amde’s children suffered a tiny harvest. In the old days, when Amde had his seven hectares, he was able to withstand drought because the grain he harvested from his seven hectares was enough for more than one year. But today, Amde’s children have one hectare each with which to provide for their families, and the harvest from one hectare is barely enough for one year. So with this drought, Amde’s children’s families end up all receiving food aid for a year.
So there we have it: An artificially high national population and birth rate, an explosion of rural-urban migration that is chocking our cities, low agricultural human capital in rural areas, low agricultural productivity, high food prices and inflation, and food insecurity. All consequences of the radical land proclamation of 1975. This is one example of the dangers and risks of radical and untried policies being implemented by desperate and immature new political elites. Today’s rulers would do well to learn from this and reconsider the other radical and immoderate policy that is haunting Ethiopia – ethnic federalism.
In this article, let us consider that fateful decision to nationalize land, a decision that the Ethiopian people have paid for and continue to pay for dearly. In brief, this policy has resulted in:
1. Artificially high national population and birth rate
2. The recent explosion of rural-urban migration that is chocking our cities
3. Low levels of human capital in rural areas, particularly in the area of farming expertise
4. Low agricultural productivity
5. Extremely high food prices and inflation
6. Food insecurity
How did all this come about? First, the nationalization of land, which included forbidding farmers to sell and buy land, essentially imprisoned our rural population. It meant farmers and their families could no longer move to the city. Let me explain by an example – an example farmer – call him ‘Amde’. In 1975, Amde had seven hectares of land – quite a decent sized holding. If Amde wanted to move to the city, he would need some money – some ‘start-up money’ – to live on until he settled down, found a source of income, etc. Normally, this money would come from selling all or even part of his land – his biggest asset. After all, most Ethiopian farmers in the past and today do not have other assets of significant value. However, thanks to the nationalization of land, the farmer was no longer allowed to sell or trade his land, or even mortgage it. Moreover, if he moved to the city, he most cases he would forego all rights to his piece of land! So not only could he not sell his land for money to live on in the city, but if he moved to the city and then for some reason changed his mind after some time and wanted to return to the farm, he could not do so – his farm would have been taken. Knowing this, farmers in general did not move to the city in numbers that they otherwise would have done. Indeed, the statistics show (I discuss this below) that there was minimal rural to urban migration from 1975 until very recently.
So, what was life like for Amde on the farm? Well, like all rural dwellers, he had many children, let’s say seven children (6.5 was the rural average birth rate around 2007 – keep in mind the Addis Ababa average was 2.2 – a big difference). As his children grew older, he divided his seven hectares into seven pieces – his children got one hectare each. And then his children too had seven children each. His land started getting crowded. As the years went by, country-wide, the average plot size of farmers started approaching one hectare and rural areas started getting congested.
Note that at the time of the 1975 land proclamation, about 85% of Ethiopia’s population, about 28 million people, lived in rural areas. In 2015, 40 years later, about 80% of Ethiopia’s population, or about 80 million people, lived in rural areas! In 40 years, the rural share of the population changed only 5%, but given the naturally high rural birth rates, the absolute rural population skyrocketed. Why? Because for 40 years, farmers, not being allowed to sell their land, did not move to urban areas. If the natural, controlled, and steady rural to urban migration that has occurred and continues everywhere around the world were allowed to happen in Ethiopia, then perhaps by 2015 the percentage of population rural areas would have fallen to 70% or lower. This would have meant more people in urban areas where the birth rate is low, and less people in rural areas where the birth rate is high, and this would have resulted in the overall population in Ethiopia being somewhat lower as well. However, because this natural rural-urban migration was artificially restricted in Ethiopia, the population of the rural ‘prison’ grew and grew, in 40 years from 28 million to 80 million. So this continued high rural-urban population ratio is a major cause of the artificially high national population today.
So what happened to Amde’s family? Recall that his children have one hectare each and seven children each. They cannot divide that one hectare into seven pieces for each of their children – the resulting plots would be too small to sustain a household. So they leave their land to only one of their children, with the remaining six children, having received a high school education thanks to the massive increase in rural public education, forced to try and make their living in the city. This is what is happening today in Ethiopia. The inevitable land deficit that we all expected by that the government ignored is now occurring. Today, millions of farmers have only enough land for one child to inherit – the rest of their children are all migrating to the city.
Hence the explosion in rural to urban migration we see today. Plot sizes have shrunk so much so as to be unsustainable. Most rural children are no longer inheriting land from their parents the plot sizes are too small to be divided. And, even though food prices are extremely high and there has never been a better time to be a farmer, if you have enough land, young people are flooding into urban areas. What we are seeing today is 40 years’ worth of pent up, accumulated, and multiplied rural-urban migration happening virtually at once. And this great rural-urban migration explosion is just starting.
But there’s more to this story – let’s go back to Amde. Amde was not a very productive farmer – he was just did not have the skills nor the desire to farm but farmed only to make a living. But his neighour Gemechu was an excellent farmer who made the most of his plot of land and wished to expand. He was, like any other business person, eager to expand is operations, could not. But, given the government land policy, he could not buy land. Amde would have been willing to sell his land to him and Gemechu would have bought it – they would have agreed on a price, but this was not allowed. So the best Gemechu could do was rent land from Amde on a seasonal basis. Gemechu wished to dig a well, plant trees, and make other long term investments, but he could not since the land was only his for a season and he could not know what would happen in the long term. He also dreamed of a time when he could buy other neighbours’ plots and expand to a level where he could learn mechanized farming, learn about growing fruit seedlings, etc. But his dreams never materialized.
Note that Gemechu was producing 20 quintals of teff per hectare, while the not very productive Amde was producing 10. If Gemechu had bought Amde’s seven hectares and planted teff, the seven hectares would have gone from producing 70 quintals to 140 quintals. Overall agricultural productivity would have increased significantly. Gemechu, with his increased income and taking advantage of economies of scale, would have gone on to greater agricultural exploits. Amde would have been able to buy cheaper teff.
What happened to Gemechu was a travesty that the government(s) of Ethiopia brought on the country’s farmers. By not allowing farmers to be entrepreneurial and to expand, the government stifled farmers’ human capital. This has had not only an economic but also psychological, political, and social impact on farmers. Unlike those in all other commercial sectors, farmers uniquely were restricted from freedom in their business – they were not allowed to expand. As a result, they were indirectly restricted from improving their agricultural skills and education and essentially forced to remain as they were, and to give up hope. Imagine if a mechanic was by law prevented from having a garage bigger than a one-car garage. He would not come close to achieving his potential. If a professor were told that he could never look for another job and he could never conduct research on anything but one subject, he too would never achieve his potential. In fact, he soon stop trying and just mindlessly do his job. Same for farmers. The system made it communism for the farmers, capitalism for the rest.
To add insult to injury, successive governments and NGO’s continued to regard farmers as almost daft – as ignorant and incapable and in need of all forms of paternalism and assistance. It is true that the agricultural sector – that farmers – have not been able to increase their human capital – their knowledge and capacity – but this was and is only because they have been restricted from being able to expand their business. In true communist fashion, the governments’ plan was to hold the most important factor – land – constant, and increase inputs such as improved seeds, fertilizer, agricultural education, etc., with the hope that this would result in greater productivity. Of course it has not worked.
Today, in Ethiopia, agricultural productivity per unit of land is low. Food prices are some of the highest in developing countries. Milk, eggs, butter, meat, and honey are more expensive in Ethiopia than in many Western countries! The agricultural sector has been unable respond to the even the high demand and high prices in today’s Ethiopia that should have resulted in greater investment and productivity. Hence the food inflation – the leading source of inflation in the country – something the government continues to battle.
Back to Amde… The once a decade drought arrived and Amde’s children suffered a tiny harvest. In the old days, when Amde had his seven hectares, he was able to withstand drought because the grain he harvested from his seven hectares was enough for more than one year. But today, Amde’s children have one hectare each with which to provide for their families, and the harvest from one hectare is barely enough for one year. So with this drought, Amde’s children’s families end up all receiving food aid for a year.
So there we have it: An artificially high national population and birth rate, an explosion of rural-urban migration that is chocking our cities, low agricultural human capital in rural areas, low agricultural productivity, high food prices and inflation, and food insecurity. All consequences of the radical land proclamation of 1975. This is one example of the dangers and risks of radical and untried policies being implemented by desperate and immature new political elites. Today’s rulers would do well to learn from this and reconsider the other radical and immoderate policy that is haunting Ethiopia – ethnic federalism.
Subscribe to:
Posts (Atom)