ብስመ አብ! የፌደራል መንግስት ዘመን አቆጣጠራችን (calendar) ይቀየር ይላሉ አቶ አብዱ አሊ ሂጅራ?!
ከመአዛ አሸናፊ ጋር 10 ቀን በፊት ያደረጉትን ቋሚ ቃለ ምልልስ አሁን አዳመጥኩት (https://www.youtube.com/watch?v=s-ve5RiImNc)። ባጭሩ የቀን መቁጠርያችን እንደ ባህል እንጠብቀው፤ ለምሳሌ አዲስ አመትን አሁን እንደሚደረገው በመስከረም 1 ይከበር፤ ግን official ወይንም የመንግስት የቀን አቆጣጠር ወደ «ፈረንጁ» (Georgian calendar) አቆጣጠር ይቀየር። ምክነያቱ አብዛኛው ሀገራት በፈረንጁ አቆጣጠር ስለሚጠቀሙ በኢትዮጵያ አቆጣጠር መጠቀም ለበርካታ ስራ አይመችም። ሁልጊዜ ከአንዱ ወደ አንዱ መቀየር (convert) ስራን ያስተጓድላል አሉ አቶ አብዱ አሊ።
ይህ በብዞዎች ተቀባይነት ያለው አስተሳሰብ ነው። ግን ትክክል አይደለም… አይመስለኝም። ማንኛውም ትውፊታዊ ነገር እንደ ቀን መቁጠርያ እንደ «ባህል» ብቻ ይዘን በስራ ላይ ካልዋለ ቀስ ብሎ ይጠፋል! ለዚህም ነው ሀገራት የራሳቸውን ቋንቋ የሚጠብቁት። ከጃፓንኛ ወደ እንግሊዘኛ መከያየር ከባድ ስራ ነው። አብዛኛው የቴክኖሎጂ ነክ ነገሮች በእንግሊዘኛ ናቸው። ሆኖም ጃፓን በጃፓንኛ ቀልቋል። ያን ሁሉ ቴክኖሎሂ ነክ ስራዎችም ሲሰራ በጃፓንኛ ነው ያደረጉት። ድሮ የኮምፕዩተር ስራ በሌላ ቋንቋ መስራት በጣም ከባድ በሆነበት ዘመንም በጃፓንኛ ነበር የሰሩት። የማንነት ጉዳይ ስለሆነ እንደ ባህል አልትውትም። ሰሩበት አሁንም ይሰሩበታል። ይህ አስተያየት ለቋንቋ ብቻ ሳይሆን ለቀን መቁጠርያም ይሆናል።
በተዘዋዋሪ ኤርትራ የመንግስት የቀን መኩጠርያውን ሲቀይር እጅግ አዝኜ ነበር። ውጤቱ ዛሬ እና ነገ ይታያል እነ እንቁጣጣሽም እየተረሱ ይሄዳሉ።
ትንሽ ቃል ስለ ሃሳቡ ጠቅላላ መንፈስ ልጻፍ… ጣልያን ሀገር ብትሄዱ ሰንበት ሱቅ መከፈት የለበትም፤ እንደነ «ዎልማርት» አይነት ግዙፍ ሱቆች ሊኖሩ አይገባም፤ አማዞን ገደለን ወዘተ ይባላል። እነዚህ ነገሮች በማህበራዊ ኑሮ (including social capital)፤ ግለኝነት እና ብቸኝነት (individiualism and loneliness)፤ የትናንሽ ከተማ እና ሰፈር ህልውና፤ ወዘተ ላይ ያላቸው ሚና ይተቻሉ። ሁሉን ነገር 'rationalise' ማድረግ ጥቅም ብቻ ሳይሆን ጉዳትም እንዳሉእው ይታወቃል። በዚህ ምክንያት localism የሚባለው ርዕዮት ዓለም ባለፉት አስርት ዓመታት ወደ ልሂቃን መገናኛ ተመልሷል። ስለዚህ እንደዚህ አይነቱን ጉዳይ ላይላዩን ሳይሆን ጠልቀን መመርመር ይኖርብናል።
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Showing posts with label language. Show all posts
Showing posts with label language. Show all posts
Thursday, 11 October 2018
Tuesday, 4 September 2018
ተረት ተረት፤ በኢትዮጵያ ያለው የ«ቋንቋ ተኮር ፌደራሊዝም» ነው
በኢትዮጵያ ያለው በሀግም በህግ መንፈስ (letter and spirit of the law) የቋንቋ ተኮር ፌደራሊዝም ሳይሆን የጎሳ (ብሄር ብሄረሰቦች ህዝቦች) ፌደራሊዝም ነው። ልዩነቱ ምንድነው?
የቋንቋ ፌደራሊዝም ማለት የተለያየ የቋንቋ ተናጋሪዎች በቋንቋቸው የቋንቋ የቡድን መብት ይኖራቸዋል ማለት ነው። ለምሳሌ በኦሮሚያ የክልል ቋንቋ ኦሮምኛ ሆኖ ማንም ኦርምኛ የሚናገር ሰው በቋንቋ ችሎታው እኩ መብት አላቸው። እንደ እንግዳ ወይንም «መጤ» አይቆጠሩም። የክልሉ ቋንቋ ኦሮምኛ ነው ብሎ ሲሰየም ሁሉንም የቋንቋ ተናጋሪ ያካትተዋል። ስለዚህ የቋንቋ ፌደራሊዝም በዘር አይለይም። ማንም ቋንቋ እስከቻለ ቡድን ውስጥ አለ ማለት ነው። አግላይ አይደለም።
የጎሳ ፌደራሊዝም ግን ደም እና አጥንት የሚቆጥር ነው። በጎሳ ፌደራሊዝም ኦሮሚያ የኦሮሞ ተናጋሪ ክልል ሳይሆን የኦርሞ በደሙ ኦሮሞ የሆነ ሰው ክልል ነው። ኦሮሞ ያልሆነ ቋንቋውም ባህሉም «ኦሮሞ» ቢሆን የክልሉ ባለቤት አይደለም። ስለዚህ ይህ አሰራር በመሰረቱ አግላይ ነው። በሌላ ቋንቋ ዘረኛ ነው ማለት ይቻላል። አንድ ሰው ምንም ያህል ኦሮምኛ ቢችል በባህልም ሌላም ብዙ የተዋሃዶ ቢሆንም ኦሮሞ አይደለም ስለዚህ በኦሮሞ ክልል በዓድ ወይንም መጤ ነው።
እንደሚታዩት በሁለቱ በቋንቋ እና በጎሳ ፌደራሊዝም ታላቅ መሰረታዊ ልዩነት አለ። አንዱ ክፍት ነው ማንንም መስፈርት እስካሟለ ያቅፋል። ሌላው ግን ዝግ ነው ማንም ምንም ቢያደርግ ሊሳተፍ አይችልም። በመሰረቱ አግላይ ነው። ዘረኛ ነው የዘረኝነትን መንፈስም ተግባርም ይጋብዛል።
ለምሳሌ ጎሳ በመታወቅያ መደረጉ። እንደ የአፓርታይድ ዘመን ደቡብ አፍሪካ! ጎሳ በመታወቅያ የሚደረገው በጎሳ ለመለየት ነው። መረጃ ብቻ ሆኖ አይቀርም መለያ ይሆናል። ማለትም ዘረኝነትን ይጋብዛል። ለዚህ ነው ደቡብ አፍሪካ ይህን ስርዓት የነበረት ዘረኝነትን ለማራመድ ስለሚጠቅም። እና ምን ማለት ነው ኢትዮጵያ ይህን የዘረኝነት ስርዓት በገልበጧ?! የጎሳ ፌደራሊዝም ምን ያህል ዘረኝነትን እንደሚያራምድ እንዳሚያስፋፋ ነው የሚገልጸው። አንዴ የሀገሪቷ ዋና ህግ (ህገ መንግስቷ) ጎሰኝነትን መዋቀራዊ ካደረገች የዘረኝነት ስርዓቶች ይከተላሉ።
በዚህ ምክንያት ነው ዓለም ዙርያ የትም ሀገር የጎሳ ፌደራሊዝም ውየንም የጎሳ መብት (ከሞላ ጎደል) የሌለው። ማንም ሀገር በህገ መንግስቱ «ጎሳ»፤ «ብሄር ብሄረሰብ ህዝብ» አይነቱን ጽንሰ ሀሳብ አይጠቀምም። የቋንቋ ፌደራሊዝም፤ የቋንቋ የቡድን መብቶች፤ የክልል ቡድን መብቶች በህግ ደረጃ ያሰፈኑ ሀገራት በርካታ ናቸው። ግን ማንኛውም ህጉን በጎሳ የመሰረተ የለም።
ለዚህ ይህ የኢትዮጵያ የ1985 ህገ መንግስት ጸንፍ (radical) የያዘ በዓለም ዙርያ መችሄም ታይቶ የማይታወቅ እጅግ ሃላፊነት-ቢስ ሙከራ (experiment) ነው የተባለው። የትም ሀገር ያልተደረገ እና አስፈላጊ ያልሆነ ህገ መንግስት በኢትዮጵያ አይነቱ ደካማ ሀገር መጫኑ ታላቅ ልክስክስነት እና ህጻንነት ነበር። በዚህ ነውረኛ ሙከራ ምክንያት በርካታ ዜጎቻችን ተሰቃይተዋል።
ይህ አይነት የጎሳ ፌደራሊዝም የትም ሀገር የሌለው ምክንያት አለ! ህዝብን በጎሳ መከፋፈል ወይን መብት በጎሳ መመደብ ማለት ኩፍኛ ግጭትን መጋበዝ ማለት ነው። ዓለም ዙርያ የታወቀ ነገር ነው። አንድ ምሳሌ ልስጣችሁ።
በካናዳ ኬቤክ የምትባል የፈረንሳይኛ ተናጋሪ ክፍለ ሀገር አለች (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2017/05/using-canada-to-understand-ethiopian.html)። ኬቤክ ለረዥም ዓመታት ከሌላው ካናዳ እለያየሁ እያለች ትሟገታለች ሁለት ጊዜም የመገንጠል ሬፈረንደም አካሄዳለች። ሁለቱም ጊዜ ህዝቡ ለጥቂት አንገንጠል አለ። የ ኬቤክ ቤርተኞች ግን ተጠንቅቀው የኛ ብሄርተኝነት የቋንቋ ነው እንጂ የጎሳ አይደለም ነው የሚሉት። ጎሳ አላቸው፤ 350 ዓመት በፊት ከፈረንሳይ ወደ ካናዳ የፈለሱት ፈረንሳዮች። ግን እኛ ኬቤክ ስንል ማንነታችን እንደ ቡድን መብት ይከበር ስንል በጎሳ ሳይሆን በቋንቋ ነው ብለው አስምረው ነው የሚናገሩት። በኬቤክ ማንም ፈረንሳይኛ ተናጋሪ እኩል የኬቤክ ዜጋ ነው ብለው ጠንክረው ይናገራሉ። ልምንድነው ጉዳዩን እንዲህ የሚያሰምሩበት? የቋንቋ ቡድን ክፍት ነው እና «ዘረኛ» መባል አይቻልም። ከሞሮኮ የመጣ ፈረንሳይ ተናጋሪ፤ ከኢትዮጵያ ወደ ኬቤክ የመጣ ፈረንሳይኛ የተማረ ወዘተ ሁሉም እኩል የኬቤክ ሰው ናቸው። በጎሳ ቢሆን ግን ፈረንጁ የድሮ የኬቤክ ሰው ብቻ ነው የክፍለ ሀገሩ ባለቤት የሚሆነው። ይህ ደግሞ ዘረኝነት ነው። የኬቤክ ብሄርተኞች «ዘረኞች» መባል እጅግ ስለሚፈሩ ያላቸውን መጤዎች ወደነሱ ማምጣትም ስለሚፈልጉ ሁልጊዜ የኛ ብሄርተኝነት የቋንቋ ነው ብለው ተጠንቅቀው ይገልጻሉ።
ሌሎችም በተለምዶ የሚጠቀሱት ሀገሮች እንደ ህንድ፤ ቤልጀም፤ ኤስፓኝ ወዘተ እንዲሁ ነው። የቡድን መብት በቋንቋ ወይንም በክፍለ ሀገር ነው የሚመሰረተው። ጎሳ፤ ብሄር፤ ብሄርተሰብ፤ ህዝብ ወዘተ ተጠንቅቆ ይወገዳል። ዘረኝነትን እና ግጭትን እንደሚጋበዝ የታወቀ ስለሆነ ነው። ዘረኝነትም ቢኖር ቢያንስ ዘረኛ ላለመባል ጥያቄአቸውም በቋንቋ ወይንም በክፍለ ሀገር ሽፋን ያቀርቡታል።
የዓለም ልምድ እንዲህ ሆኖ ኢህአዴግ ይህንን የሙከራ ህገ መንግስት ኢትዮጵያ ላይ መጫኑ የኛ ልሂቃን የጸንፈኝነት ዝንባሌን በደምብ ያሻያል። ትንሽ የቀለም ትምህርት ስንማር ቀንደኛ ጸንፈኛ መሆን የእውቀታችን መለክያ ይመስላችን ይሆን አላውቅም። በተማሪ ንቅናቄው ይህ በደምብ ታይቷል። በህወሓትም እንዲሁ። በኢህአፓም። ዛሬም በተለያዩ ፖለቲከኞች እናየዋለን። የችግር መፍትሄው ቀላላእና ሚዛናዊ ለዘብተኛ ፊት ለፊት እያለ ጸንፈ የያዘ ውስብስብ የሆነ መፍትሄ (ማባባሻ) ይፈለጋል። የኢትዮጵያ ህገ መንግስት ጉዳይ እንዲህ ነበር።
ዛሬ ሀገ መንግስቱ «ብሄር፤ ብሄረሰቦች፤ ህዝቦች» የሚለውን አውጥቶ የቋንቋ ፌደራሊዝም እንዲሆን አስፈላጊ ለውጦች ቢደረግ ብቻ ታላቅ መሻሻያ ይሆናል። ለነ ይህ በቂ ባይሆንም ታላቅ ታላቅ ማሻሻያ ነው የሚሆነው። ህዝባችን እና መሪዎቻችን ይህን ለማድረግ ያብቃን።
ስለዚህ ጉዳይ አንዳርጋቸው ጽጌ ያለውን ከዚህ ቪዲዮ ብትመለከቱ ጥሩ ይመስለኛል፤ https://www.youtube.com/watch?v=mCUIw2ud8EM
የቋንቋ ፌደራሊዝም ማለት የተለያየ የቋንቋ ተናጋሪዎች በቋንቋቸው የቋንቋ የቡድን መብት ይኖራቸዋል ማለት ነው። ለምሳሌ በኦሮሚያ የክልል ቋንቋ ኦሮምኛ ሆኖ ማንም ኦርምኛ የሚናገር ሰው በቋንቋ ችሎታው እኩ መብት አላቸው። እንደ እንግዳ ወይንም «መጤ» አይቆጠሩም። የክልሉ ቋንቋ ኦሮምኛ ነው ብሎ ሲሰየም ሁሉንም የቋንቋ ተናጋሪ ያካትተዋል። ስለዚህ የቋንቋ ፌደራሊዝም በዘር አይለይም። ማንም ቋንቋ እስከቻለ ቡድን ውስጥ አለ ማለት ነው። አግላይ አይደለም።
የጎሳ ፌደራሊዝም ግን ደም እና አጥንት የሚቆጥር ነው። በጎሳ ፌደራሊዝም ኦሮሚያ የኦሮሞ ተናጋሪ ክልል ሳይሆን የኦርሞ በደሙ ኦሮሞ የሆነ ሰው ክልል ነው። ኦሮሞ ያልሆነ ቋንቋውም ባህሉም «ኦሮሞ» ቢሆን የክልሉ ባለቤት አይደለም። ስለዚህ ይህ አሰራር በመሰረቱ አግላይ ነው። በሌላ ቋንቋ ዘረኛ ነው ማለት ይቻላል። አንድ ሰው ምንም ያህል ኦሮምኛ ቢችል በባህልም ሌላም ብዙ የተዋሃዶ ቢሆንም ኦሮሞ አይደለም ስለዚህ በኦሮሞ ክልል በዓድ ወይንም መጤ ነው።
እንደሚታዩት በሁለቱ በቋንቋ እና በጎሳ ፌደራሊዝም ታላቅ መሰረታዊ ልዩነት አለ። አንዱ ክፍት ነው ማንንም መስፈርት እስካሟለ ያቅፋል። ሌላው ግን ዝግ ነው ማንም ምንም ቢያደርግ ሊሳተፍ አይችልም። በመሰረቱ አግላይ ነው። ዘረኛ ነው የዘረኝነትን መንፈስም ተግባርም ይጋብዛል።
ለምሳሌ ጎሳ በመታወቅያ መደረጉ። እንደ የአፓርታይድ ዘመን ደቡብ አፍሪካ! ጎሳ በመታወቅያ የሚደረገው በጎሳ ለመለየት ነው። መረጃ ብቻ ሆኖ አይቀርም መለያ ይሆናል። ማለትም ዘረኝነትን ይጋብዛል። ለዚህ ነው ደቡብ አፍሪካ ይህን ስርዓት የነበረት ዘረኝነትን ለማራመድ ስለሚጠቅም። እና ምን ማለት ነው ኢትዮጵያ ይህን የዘረኝነት ስርዓት በገልበጧ?! የጎሳ ፌደራሊዝም ምን ያህል ዘረኝነትን እንደሚያራምድ እንዳሚያስፋፋ ነው የሚገልጸው። አንዴ የሀገሪቷ ዋና ህግ (ህገ መንግስቷ) ጎሰኝነትን መዋቀራዊ ካደረገች የዘረኝነት ስርዓቶች ይከተላሉ።
በዚህ ምክንያት ነው ዓለም ዙርያ የትም ሀገር የጎሳ ፌደራሊዝም ውየንም የጎሳ መብት (ከሞላ ጎደል) የሌለው። ማንም ሀገር በህገ መንግስቱ «ጎሳ»፤ «ብሄር ብሄረሰብ ህዝብ» አይነቱን ጽንሰ ሀሳብ አይጠቀምም። የቋንቋ ፌደራሊዝም፤ የቋንቋ የቡድን መብቶች፤ የክልል ቡድን መብቶች በህግ ደረጃ ያሰፈኑ ሀገራት በርካታ ናቸው። ግን ማንኛውም ህጉን በጎሳ የመሰረተ የለም።
ለዚህ ይህ የኢትዮጵያ የ1985 ህገ መንግስት ጸንፍ (radical) የያዘ በዓለም ዙርያ መችሄም ታይቶ የማይታወቅ እጅግ ሃላፊነት-ቢስ ሙከራ (experiment) ነው የተባለው። የትም ሀገር ያልተደረገ እና አስፈላጊ ያልሆነ ህገ መንግስት በኢትዮጵያ አይነቱ ደካማ ሀገር መጫኑ ታላቅ ልክስክስነት እና ህጻንነት ነበር። በዚህ ነውረኛ ሙከራ ምክንያት በርካታ ዜጎቻችን ተሰቃይተዋል።
ይህ አይነት የጎሳ ፌደራሊዝም የትም ሀገር የሌለው ምክንያት አለ! ህዝብን በጎሳ መከፋፈል ወይን መብት በጎሳ መመደብ ማለት ኩፍኛ ግጭትን መጋበዝ ማለት ነው። ዓለም ዙርያ የታወቀ ነገር ነው። አንድ ምሳሌ ልስጣችሁ።
በካናዳ ኬቤክ የምትባል የፈረንሳይኛ ተናጋሪ ክፍለ ሀገር አለች (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2017/05/using-canada-to-understand-ethiopian.html)። ኬቤክ ለረዥም ዓመታት ከሌላው ካናዳ እለያየሁ እያለች ትሟገታለች ሁለት ጊዜም የመገንጠል ሬፈረንደም አካሄዳለች። ሁለቱም ጊዜ ህዝቡ ለጥቂት አንገንጠል አለ። የ ኬቤክ ቤርተኞች ግን ተጠንቅቀው የኛ ብሄርተኝነት የቋንቋ ነው እንጂ የጎሳ አይደለም ነው የሚሉት። ጎሳ አላቸው፤ 350 ዓመት በፊት ከፈረንሳይ ወደ ካናዳ የፈለሱት ፈረንሳዮች። ግን እኛ ኬቤክ ስንል ማንነታችን እንደ ቡድን መብት ይከበር ስንል በጎሳ ሳይሆን በቋንቋ ነው ብለው አስምረው ነው የሚናገሩት። በኬቤክ ማንም ፈረንሳይኛ ተናጋሪ እኩል የኬቤክ ዜጋ ነው ብለው ጠንክረው ይናገራሉ። ልምንድነው ጉዳዩን እንዲህ የሚያሰምሩበት? የቋንቋ ቡድን ክፍት ነው እና «ዘረኛ» መባል አይቻልም። ከሞሮኮ የመጣ ፈረንሳይ ተናጋሪ፤ ከኢትዮጵያ ወደ ኬቤክ የመጣ ፈረንሳይኛ የተማረ ወዘተ ሁሉም እኩል የኬቤክ ሰው ናቸው። በጎሳ ቢሆን ግን ፈረንጁ የድሮ የኬቤክ ሰው ብቻ ነው የክፍለ ሀገሩ ባለቤት የሚሆነው። ይህ ደግሞ ዘረኝነት ነው። የኬቤክ ብሄርተኞች «ዘረኞች» መባል እጅግ ስለሚፈሩ ያላቸውን መጤዎች ወደነሱ ማምጣትም ስለሚፈልጉ ሁልጊዜ የኛ ብሄርተኝነት የቋንቋ ነው ብለው ተጠንቅቀው ይገልጻሉ።
ሌሎችም በተለምዶ የሚጠቀሱት ሀገሮች እንደ ህንድ፤ ቤልጀም፤ ኤስፓኝ ወዘተ እንዲሁ ነው። የቡድን መብት በቋንቋ ወይንም በክፍለ ሀገር ነው የሚመሰረተው። ጎሳ፤ ብሄር፤ ብሄርተሰብ፤ ህዝብ ወዘተ ተጠንቅቆ ይወገዳል። ዘረኝነትን እና ግጭትን እንደሚጋበዝ የታወቀ ስለሆነ ነው። ዘረኝነትም ቢኖር ቢያንስ ዘረኛ ላለመባል ጥያቄአቸውም በቋንቋ ወይንም በክፍለ ሀገር ሽፋን ያቀርቡታል።
የዓለም ልምድ እንዲህ ሆኖ ኢህአዴግ ይህንን የሙከራ ህገ መንግስት ኢትዮጵያ ላይ መጫኑ የኛ ልሂቃን የጸንፈኝነት ዝንባሌን በደምብ ያሻያል። ትንሽ የቀለም ትምህርት ስንማር ቀንደኛ ጸንፈኛ መሆን የእውቀታችን መለክያ ይመስላችን ይሆን አላውቅም። በተማሪ ንቅናቄው ይህ በደምብ ታይቷል። በህወሓትም እንዲሁ። በኢህአፓም። ዛሬም በተለያዩ ፖለቲከኞች እናየዋለን። የችግር መፍትሄው ቀላላእና ሚዛናዊ ለዘብተኛ ፊት ለፊት እያለ ጸንፈ የያዘ ውስብስብ የሆነ መፍትሄ (ማባባሻ) ይፈለጋል። የኢትዮጵያ ህገ መንግስት ጉዳይ እንዲህ ነበር።
ዛሬ ሀገ መንግስቱ «ብሄር፤ ብሄረሰቦች፤ ህዝቦች» የሚለውን አውጥቶ የቋንቋ ፌደራሊዝም እንዲሆን አስፈላጊ ለውጦች ቢደረግ ብቻ ታላቅ መሻሻያ ይሆናል። ለነ ይህ በቂ ባይሆንም ታላቅ ታላቅ ማሻሻያ ነው የሚሆነው። ህዝባችን እና መሪዎቻችን ይህን ለማድረግ ያብቃን።
ስለዚህ ጉዳይ አንዳርጋቸው ጽጌ ያለውን ከዚህ ቪዲዮ ብትመለከቱ ጥሩ ይመስለኛል፤ https://www.youtube.com/watch?v=mCUIw2ud8EM
Tuesday, 14 August 2018
ተረት ተረት፤ «ጎሰኝነት ዘረኝነት ነው»
ይህም ከፊል እውነታ አለው። አማራ ማየት አማርኛ መስማት የሚጠሉ ጸንፈኛ ኦሮሞ ብሄርተኞች አሉ። ግን ጎሰኝነትን «ዘረኝነት» ብሎ መሰየሙ ችግሩን በትክክል አይገልጸውም ወደ መፍትሄም ለመምጣት አይረዳም። ላስረዳ…
«ዘረኝነት» የሚለው ቃል ብዙ ትርጉም ያለው፤ የተወሳሰበ፤ ኃይል ያለው ቃል ነው። የምንጠቀምበት አንድ ነገርን ወይንም ሰውን ክፉ መጥፎ ነው ብለን ለመሰየም ነው። ከክፉ ጋር ውይይት የለም ድርድር የለም። «ዘረኝነት» ብለን ሰይመን ከዚህ ሀሳብ ጋር ውይይትም ድርድርም አያስፈልግም ነው የምንለው «ዘረኛ» ስንለው። ትክክለኛ አካሄድ አይደለም።
ጎሰኝነትን እስቲ እንደዚህ ብናየው ትክክለኛ ግንዛቤ እንዲኖረን ይረዳል ጎሰኝነትን ለመቀነስ ለማጥፋትም ምን ማድረግ እንዳለብን እንድንረዳ ይረዳናል። ጎሰኝነት ገና ሲጀመር በውይይት፤ በማስረዳት እና በማስተማር ማጥፋት ይቻላል። ግን ጎሰኝነት አንድ ደረጃ ካለፈ ውይይት ከሞላ ጎደል አይሰራም።
ለምሳሌ ጎሰኛው ኦሮሞነቱ እጅግ አይሎ ኢትዮጵያዊነቱ እጅግ ከመነመነ ስለ ታሪክ እና ፖለቲካ ምን ብትሰብከው ለውጥ ሃሳቡን አይቀይርም። «ዘረኛ» ብትለውም ፋይዳ የለውም። ይህ ስወ ዘረኛ ሳይሆን ማንነቴ ሙሉ በሙሉ «ኦሮሞ» ነው ብሎ ወስኗል። ሀገሬ ኦሮሞ ነው ኢትዮጵያ አይደለም ነው የሚለው። ኢትዮጵያን ይጠላ አይጠላ አይደለም ዋናው ጉዳይ። ኦሮሞ ነኝ ማለቱ ነው። ልክ እንደ ኢትዮጵያ እና ሱዳን የተለያዩ ሀገሮች እንደሆኑ ሱዳናዊው በኢትዮጵያ ያለው መብት ውስን እንደሆነ እንዲሁም በተገላቢጦሽ ለኦሮሞ ብሄርተኛው በኦሮሚያ እና ኢትዮጵያ ያለው ልዩነት እንዲሁ ነው። ሌላ ሀገር ንኝ ነው የሚለው። ይህን የማንነት ስሜቱን ደግሞ ልንከለክለው አንችልም። «ዘረኛ» ማለቱ ዋጋ የለውም ምናልባትም ማባባስ ነው።
ታድያ ጎሰኝነት ይህ ከሆነ ምን ችግር አለው ትሉ ይሆናል? የሀገሩ ማንነት መምረጥ የሰው ልጅ «መብት» ከሆነ ምን ክፋት አለው? «ዘረኝነት» ካላልነው መጥፎነቱን እንዴት እንግለጽ? መልሱ ቀላል ነው፤ ጎሰንኘት «መብት» ቢሆንም የታላቅ ግጭት ምንጭ ነው። በአንድ ሀገር ጎሰኝነት በተለይም ጎሰኝነት እና ብሶት (grievance) አብረው ሲኖሩ ከፉ ግጭቶች ይኖራሉ። ይህ በቴኦሪ ወይንም በሌሎች ሀገራት ብቻ የሚታይ ሳይሆን ለ27 ዓመት በኢትዮጵያ የታየ ነው። ለግጭቶች ደግሞ በመንግስት አምባገንነት አናሳብብ፤ መንግስት ያልተሳተፈበት ግጭቶች ብዙ ነበሩ አሁንም አሉ። አልፎ ተርፎ መንግስት በግጭቶቹ ቢሳተፍባቸውም ባለ ክፍተት ነው እየገባ እየበጠበጠ የነበረው እንጂ የሌላ ልዩነት የመፍጠር አቅም አልነበረውም።
ስለዚህ ጎሰኝነት ወይንም የጎሳ እና ሀገር ሚዛን ከልክ በላይ ወደ ጎሳ ሲያመዝን ችግሩ ጎሰኝነት «ዝረኝነት» መሆኑ ሳይሆን የግጭት ምንጭ መሆኑ ነው። መፍትሄውም የግጭት ምንጭ ነው ብለን ጎሳን እንደ ጽንሰ ሀሳብ ከሀገሪቷ ህገ መንግስት ማውጣት እና በ«ቋንቋ እና ባህል» ጽንሰ ሀሳቦች መተካት ነው።
«ዘረኝነት» የሚለው ቃል ብዙ ትርጉም ያለው፤ የተወሳሰበ፤ ኃይል ያለው ቃል ነው። የምንጠቀምበት አንድ ነገርን ወይንም ሰውን ክፉ መጥፎ ነው ብለን ለመሰየም ነው። ከክፉ ጋር ውይይት የለም ድርድር የለም። «ዘረኝነት» ብለን ሰይመን ከዚህ ሀሳብ ጋር ውይይትም ድርድርም አያስፈልግም ነው የምንለው «ዘረኛ» ስንለው። ትክክለኛ አካሄድ አይደለም።
ጎሰኝነትን እስቲ እንደዚህ ብናየው ትክክለኛ ግንዛቤ እንዲኖረን ይረዳል ጎሰኝነትን ለመቀነስ ለማጥፋትም ምን ማድረግ እንዳለብን እንድንረዳ ይረዳናል። ጎሰኝነት ገና ሲጀመር በውይይት፤ በማስረዳት እና በማስተማር ማጥፋት ይቻላል። ግን ጎሰኝነት አንድ ደረጃ ካለፈ ውይይት ከሞላ ጎደል አይሰራም።
ለምሳሌ ጎሰኛው ኦሮሞነቱ እጅግ አይሎ ኢትዮጵያዊነቱ እጅግ ከመነመነ ስለ ታሪክ እና ፖለቲካ ምን ብትሰብከው ለውጥ ሃሳቡን አይቀይርም። «ዘረኛ» ብትለውም ፋይዳ የለውም። ይህ ስወ ዘረኛ ሳይሆን ማንነቴ ሙሉ በሙሉ «ኦሮሞ» ነው ብሎ ወስኗል። ሀገሬ ኦሮሞ ነው ኢትዮጵያ አይደለም ነው የሚለው። ኢትዮጵያን ይጠላ አይጠላ አይደለም ዋናው ጉዳይ። ኦሮሞ ነኝ ማለቱ ነው። ልክ እንደ ኢትዮጵያ እና ሱዳን የተለያዩ ሀገሮች እንደሆኑ ሱዳናዊው በኢትዮጵያ ያለው መብት ውስን እንደሆነ እንዲሁም በተገላቢጦሽ ለኦሮሞ ብሄርተኛው በኦሮሚያ እና ኢትዮጵያ ያለው ልዩነት እንዲሁ ነው። ሌላ ሀገር ንኝ ነው የሚለው። ይህን የማንነት ስሜቱን ደግሞ ልንከለክለው አንችልም። «ዘረኛ» ማለቱ ዋጋ የለውም ምናልባትም ማባባስ ነው።
ታድያ ጎሰኝነት ይህ ከሆነ ምን ችግር አለው ትሉ ይሆናል? የሀገሩ ማንነት መምረጥ የሰው ልጅ «መብት» ከሆነ ምን ክፋት አለው? «ዘረኝነት» ካላልነው መጥፎነቱን እንዴት እንግለጽ? መልሱ ቀላል ነው፤ ጎሰንኘት «መብት» ቢሆንም የታላቅ ግጭት ምንጭ ነው። በአንድ ሀገር ጎሰኝነት በተለይም ጎሰኝነት እና ብሶት (grievance) አብረው ሲኖሩ ከፉ ግጭቶች ይኖራሉ። ይህ በቴኦሪ ወይንም በሌሎች ሀገራት ብቻ የሚታይ ሳይሆን ለ27 ዓመት በኢትዮጵያ የታየ ነው። ለግጭቶች ደግሞ በመንግስት አምባገንነት አናሳብብ፤ መንግስት ያልተሳተፈበት ግጭቶች ብዙ ነበሩ አሁንም አሉ። አልፎ ተርፎ መንግስት በግጭቶቹ ቢሳተፍባቸውም ባለ ክፍተት ነው እየገባ እየበጠበጠ የነበረው እንጂ የሌላ ልዩነት የመፍጠር አቅም አልነበረውም።
ስለዚህ ጎሰኝነት ወይንም የጎሳ እና ሀገር ሚዛን ከልክ በላይ ወደ ጎሳ ሲያመዝን ችግሩ ጎሰኝነት «ዝረኝነት» መሆኑ ሳይሆን የግጭት ምንጭ መሆኑ ነው። መፍትሄውም የግጭት ምንጭ ነው ብለን ጎሳን እንደ ጽንሰ ሀሳብ ከሀገሪቷ ህገ መንግስት ማውጣት እና በ«ቋንቋ እና ባህል» ጽንሰ ሀሳቦች መተካት ነው።
ተረት ተረት፤ የትግራይ ገዥ መደብ አገዛዝ እና የ«አማራ ገዥ መደብ» አገዛዝ አንድ ናቸው
«የትግራይ ገዥ መደብ አገዛዝ እና የ«አማራ ገዥ መደብ» አገዛዝ አንድ ናቸው»። ይህ ተረት ተረት (myth) በበርካታ ሰዎች ሲደጋገም ወደ እውነታ እያማራ ነው። በቅርቡ ባደረጉት ኑዛዜአቸው የቀድሞ ጠ/ሚ ታምራት ላይኔም ደግመውታል። «የአማራ ገዥ መደብ ብይ አማራ ብዙሃን እንደነገዱት ነው ህወሓት የትግራይ ገዥ መደብ በትግራይ ብዙሃን የነገዱት» ብለዋል። ይህ አስተያየት እጅግ የተሳሳተ ነው።
የሁለቱ አገዛዞች መሰረታዊ ልዩነት ይህ ነው፤ በደርግ እና በንጉሳዊው ስርዓት ጎሳ፤ ዘውግ፤ ብሄር አይነት ጽንሰ ሀሳቦች በህግ ደረጃ አልነበሩም። አገዛዙ በህግ ደረጃ ከጎሳ እና ከጎሰኝነት ውጭ ነበር። በህወሓት አገዛዝ ግን ጎሳ እና ጎሰኝነት በህግ የተደነገገ ነው። ጎሰኝነቱ በልምድ ወይንም በባህል ደረጃ ሳይሆን ህጋዊ ነው። ይህ መሰረታዊ ልዩነት ነው።
በኃይለ ሥላሴ መንግስት ማንኛውም ግለሰብ በጎሳ ምክንያት ከመንግስታዊ ስልጣን እና ሹመት አይከለከልም ነበር። አይከለከልም ብቻ ሳይሆን ጎሳው ጭራሽ እንደ ጉዳይ አይነሳም፤ በህግ እና ስረዓት ደረጃ ጎሳ የሚባል ጸንሰ ሀሳብ የለም። በዚህም ምክንያት በኃይለ ሥላሴ መንግስት በርካታ ከተለያዩ ጎሳ የሆኑ ባለ ስልጣኖች ነበሩ።
ሆኖም የአስተዳደር ቋንቋው አማርኛ ነበር። ይህ ከጅማ ለተወለደው ኦሮሞ መሰናከል ነበር። የገዥ ስረዓቱ ንጉሳዊ ነበር። ይህ ከኮንሶ የተወለዱት ባዕዳዊ ስረዓት ነበር። በነዚህ አይነት ምክንያቶች አማራ ያልሆኑ ወደ ስልጣን ለመቅረብ ከአማራ ይልቅ ይከብዳቸው ነበር ማለት ይቻል ይሆናል። አማራ ቋንቋውን በማወቅ ከሌላው ይበልጥ እድል ነበረው ማለት ይቻላል። እንዲሁም የአዲስ አበባ ተወላጅ ይበልጥ እድል ነበረው ማለት ይቻላል። በዚህ ደረጃ በተለያዩ የጎሳ ተወላጆች የስልጣን እና ሹመት እድል ልዩነት መኖሩን መካድ አይቻልም። ግን ይህ ልዩነት የታሪክ አጋጣሚ ነው እንጂ በህግ የተደነገገ አልነበረም። ስለዚህ አማራ ያልሆነው ቢከብደውም ወደ ስልጣን መምጣት ይችል ነበር። አድሎ ነበር ግን አድሎው ህጋዊ አልነበረም ስለዚህ ሊቀለበስ የሚችል አድሎ ነበር።
የህወሓት አገዛዝ ግን መሰረቱ ጎሰኝነት ነበር። ህወሓት የትግራይ ድርጅት ለትግራይ ህዝብ ነው። አማራው በአማራነቱ ቦታ የለውም። ቋንቋ ባለመቻሉ ወይንም የፖለቲካ ባህሉን ባለማወቁ ሳይሆን በአማራነቱ ምክንያት ስልጣን ሊይዝ አይችልም። በህወሓት ዘመን አድሎ መቀልበስ የማይችል የጎሳ የደም አድሎ ነበር።
ይህን የ«ትግራይ ገዥ መደብ» እና የ«አማራ ገዥ መደብ» አገዛዝ ልዩነት ስንመለከት አንድ ትልቅ ትምሕርት እንማራለን። ይህ ስለ የጎሳ አገዛዝ አደገኝነት ነው። ጎሳ የትውልድ የደም ጉዳይ ስለሆነ በመሰረቱ ህዝብን የሚለይ እና አድሎ (discrimination) የሚያመጣ ነው። በዚህ ምክንያት ነው የጎሳ አገዛዝ የግጭት (conflict) ፋብሪካ የሚሆነው።
የጎሳ መብቶችን ለማስተናገድ የጎሳ አስተዳደርን ከመጠቀም ወይንም የጎሳ መብቶች በህግ ከማወጅ የቋንቋ እና የባህል መብቶችን ማደንገድ ይሻላል። ቋንቋ እና ባህል ማንም መማር መቀየር የሚችለው ስለሆነ መሰረታዊ አድሎ የላቸውም። በዚህ ምክንያት በአድሎ የተነሳ የተጨቋኝ ስሜቶችን አያዳብርም ስለዚህ ግጭትን አያበዛም።
ይህን ተመስርተን ነው የኢትዮጵያ ህገ መንግስት ጸንፈኛ ነው የምንለው። ዓለም ዙርያ ሀገራት የቋንቋ እና ባህል መብቶችን በህጋቸው ያስተናግዳሉ። የጎሳ መብቶችን በዚህ መንገድ ያስተናግዳሉ። ግን የትም ሀገር ጎሳን በህጋቸው አያስተናግዱም። በጎሳ እና በቋንቋና ባህል ያለውን ልዩነት በግጭት መጋበዝ አኳያ በድምብ የታወቀ ስለሆነ ነው እንዲህ የሆነው። ግን ኢትዮጵያ ብቸኛዋ ጎሳን በህግዋ ውስጥ ያካተተች ናት። ለሀገራችን ህልውና ይህን መቀየሩ አስፈላጊ ነው።
የሁለቱ አገዛዞች መሰረታዊ ልዩነት ይህ ነው፤ በደርግ እና በንጉሳዊው ስርዓት ጎሳ፤ ዘውግ፤ ብሄር አይነት ጽንሰ ሀሳቦች በህግ ደረጃ አልነበሩም። አገዛዙ በህግ ደረጃ ከጎሳ እና ከጎሰኝነት ውጭ ነበር። በህወሓት አገዛዝ ግን ጎሳ እና ጎሰኝነት በህግ የተደነገገ ነው። ጎሰኝነቱ በልምድ ወይንም በባህል ደረጃ ሳይሆን ህጋዊ ነው። ይህ መሰረታዊ ልዩነት ነው።
በኃይለ ሥላሴ መንግስት ማንኛውም ግለሰብ በጎሳ ምክንያት ከመንግስታዊ ስልጣን እና ሹመት አይከለከልም ነበር። አይከለከልም ብቻ ሳይሆን ጎሳው ጭራሽ እንደ ጉዳይ አይነሳም፤ በህግ እና ስረዓት ደረጃ ጎሳ የሚባል ጸንሰ ሀሳብ የለም። በዚህም ምክንያት በኃይለ ሥላሴ መንግስት በርካታ ከተለያዩ ጎሳ የሆኑ ባለ ስልጣኖች ነበሩ።
ሆኖም የአስተዳደር ቋንቋው አማርኛ ነበር። ይህ ከጅማ ለተወለደው ኦሮሞ መሰናከል ነበር። የገዥ ስረዓቱ ንጉሳዊ ነበር። ይህ ከኮንሶ የተወለዱት ባዕዳዊ ስረዓት ነበር። በነዚህ አይነት ምክንያቶች አማራ ያልሆኑ ወደ ስልጣን ለመቅረብ ከአማራ ይልቅ ይከብዳቸው ነበር ማለት ይቻል ይሆናል። አማራ ቋንቋውን በማወቅ ከሌላው ይበልጥ እድል ነበረው ማለት ይቻላል። እንዲሁም የአዲስ አበባ ተወላጅ ይበልጥ እድል ነበረው ማለት ይቻላል። በዚህ ደረጃ በተለያዩ የጎሳ ተወላጆች የስልጣን እና ሹመት እድል ልዩነት መኖሩን መካድ አይቻልም። ግን ይህ ልዩነት የታሪክ አጋጣሚ ነው እንጂ በህግ የተደነገገ አልነበረም። ስለዚህ አማራ ያልሆነው ቢከብደውም ወደ ስልጣን መምጣት ይችል ነበር። አድሎ ነበር ግን አድሎው ህጋዊ አልነበረም ስለዚህ ሊቀለበስ የሚችል አድሎ ነበር።
የህወሓት አገዛዝ ግን መሰረቱ ጎሰኝነት ነበር። ህወሓት የትግራይ ድርጅት ለትግራይ ህዝብ ነው። አማራው በአማራነቱ ቦታ የለውም። ቋንቋ ባለመቻሉ ወይንም የፖለቲካ ባህሉን ባለማወቁ ሳይሆን በአማራነቱ ምክንያት ስልጣን ሊይዝ አይችልም። በህወሓት ዘመን አድሎ መቀልበስ የማይችል የጎሳ የደም አድሎ ነበር።
ይህን የ«ትግራይ ገዥ መደብ» እና የ«አማራ ገዥ መደብ» አገዛዝ ልዩነት ስንመለከት አንድ ትልቅ ትምሕርት እንማራለን። ይህ ስለ የጎሳ አገዛዝ አደገኝነት ነው። ጎሳ የትውልድ የደም ጉዳይ ስለሆነ በመሰረቱ ህዝብን የሚለይ እና አድሎ (discrimination) የሚያመጣ ነው። በዚህ ምክንያት ነው የጎሳ አገዛዝ የግጭት (conflict) ፋብሪካ የሚሆነው።
የጎሳ መብቶችን ለማስተናገድ የጎሳ አስተዳደርን ከመጠቀም ወይንም የጎሳ መብቶች በህግ ከማወጅ የቋንቋ እና የባህል መብቶችን ማደንገድ ይሻላል። ቋንቋ እና ባህል ማንም መማር መቀየር የሚችለው ስለሆነ መሰረታዊ አድሎ የላቸውም። በዚህ ምክንያት በአድሎ የተነሳ የተጨቋኝ ስሜቶችን አያዳብርም ስለዚህ ግጭትን አያበዛም።
ይህን ተመስርተን ነው የኢትዮጵያ ህገ መንግስት ጸንፈኛ ነው የምንለው። ዓለም ዙርያ ሀገራት የቋንቋ እና ባህል መብቶችን በህጋቸው ያስተናግዳሉ። የጎሳ መብቶችን በዚህ መንገድ ያስተናግዳሉ። ግን የትም ሀገር ጎሳን በህጋቸው አያስተናግዱም። በጎሳ እና በቋንቋና ባህል ያለውን ልዩነት በግጭት መጋበዝ አኳያ በድምብ የታወቀ ስለሆነ ነው እንዲህ የሆነው። ግን ኢትዮጵያ ብቸኛዋ ጎሳን በህግዋ ውስጥ ያካተተች ናት። ለሀገራችን ህልውና ይህን መቀየሩ አስፈላጊ ነው።
Tuesday, 3 April 2018
ሃይማኖታዊ መቻቻል
በዚህ ዘመን የቃላቶች ትርጉም ተተንቅቀን ነጣጥለን ማየት አለብን።
እስቲ በመጀመርያ «መቻቻል» ምን ማለት እንደሆነ እንመርምር። ሰው የሚወድውን ነገር «ቻለው» ይባላል? አይባልም! የማይወደውን ግን በተለያዩ ምክንያቶች ስለነገሩ ምንም ማድረግ የማይችለውን ወይም ማድረግ የማይፈልገውን ነገር ነው «ቻለው» የሚባለው።
ለምሳሌ… ሙስሊም ጎረቤቴ በየጊዜው ድምጽ የበዛው የጸሎት ዝግጅት ያካሄዳል ከበቱ። ጩኸቱን አልወደውም ግን ለሰላም ብዬ ዝም እላለሁ። ይህ የመቻቻል አንድ ምሳሌ ነው።
እዚ ጋር አንድ ነገርን ልብ እንበል። ጎረቤቴን ዝም ያልኩት ስለምወደው ወይም ጥሩ ልሁንለት ብዬ አይደለም። «ነግ በኔን» አስቤ ነው። ለራሴ ጥቅም ብዬ ነው። እኔም ዝግጅቶችህን ተው ብዬ አላስቸግረውም እሱም እኔ እንደዚሁ አይነት ፕሮግራም ባዘጋጅ ዝም ይለኛል። አልፎ ተርፎ ጸብ ስለሌለን ግንኙነታችን ሰላማዊ ስለሆነ ወደ ፊት በተለያዩ የሚጠቁሙን ጉዳዮች መተባበር መረዳዳት ቀላል ሊሆን ይችላል።
ስለዚህ «መቻቻል» የአብሮ መኖር ስልት ነው። የጥሩነት ወይም በጎ መግባር ውጤት አይደለም የመዋደድ የፍቅርም ውጤት አይደለም።
መቻቻል እንዲህ ከሆነ ለኛ ኦርቶዶክስ ክርስትያኖች ምን ማለት ነው? መቻቻል አለብን ወይ? የሌላ ሃይማኖት ተከታዮችን «መቻል» አለብን ወይ? «የሃይማኖት መቻቻልን» መተግበር አለብን ወይ? በፍፁም! በመጀመርያ እንደ ክርስትናችን «መውደድ» ነው ያለብን። አምላካችን እንዳለን እሱ እንደሚወደን ያህል ባለንጀራችንን መውደድ አለብን። የኛ የክርስትያኖች ተዕልኮ «ፍቅር» ነው እንጂ «መቻቻል» አይደለም! ማንም ሰው ከልምድና ምቾት አንጻር መቻቻል ይችላል፤ ግን ክርስትያኖች መውደድ ነው ያለብን።
ወደ ቅድሙ ምሳሌአችን ከተመለሰን የሙስሊም ጎረቤቴን ስለ ጸሎት ዝግጅቶቹ የማላስቸግረው ምክንያት «መቻቻል» ሳይሆን «ፍቅር» ነው መሆን ያለበት። ስለ ዝግጅቱ ካላማረርኩኝ አለማማረሬ ከፍቅር የመነጨ መሆን አለበት እንጂ ለራሴ ጥቅም ብዬ መሆን የለበትም። እሱም ይሉኝታ ኖሮት ዝም ይለንኛል ብዬ ከሱ ጠብቄ ሳይሆን ምንም ሳልጠብቅ ምሆን አለበት። ስለዚህ ክርስትያኖች መቻቻልን መተግበር አለባቸው ማለት ትርጉም የለውም። ከመቻቻል በላይ ሰማይ ጠቀሱን ፍቅር መተግበር ነው ያለን።
እንግዲህ አንዳንዶቻችሁ «አምላካችሁ ውደዱ ቢላችሁም አትሰሙትም» ትሉኝ ይሆናል። «እናንተ ኦርቶዶክስ ክርስትያኖች ድሮም አሁንም ፍቅርን አታውቁም።» አልክድም፤ እውነት ነው፤ እኔ ኦርቶዶክስ ክርስትያን ብሆንም ኃጢአተኛ ነኝ ፍቅር ይጎለኛል። ፍቅር የሆነውን ተልዕኮኤን ሁል ጊዜ እየሳትኩኝ ነው የምኖረው። ይህ ኃጢአተኝነቴ ግን የሚስተካከለው ወይንም በትክክሉ ቋንቋ የሚታከመው መቻቻልን መተግበር በመሞከር አይደለም። ፍቅርን በመተግበር ነው። ካልቻልኩኝ ከወደቅኩኝ ተመልሼ መሞከር መነሳት ነው። ይህ ነው የክርስትና ኑሮ። እንጂ መውደድ አልችልም ብዬ ተስፋ ቆርቼ እስቲ መቻቻልን ልሞርክ ማለት ውድቅ ሀሳብ ነው።
ስለዚህ ፕሮቴስታንት ወንድሜ፤ ሙስሊም እህቴ፤ ሴኩላሪስት ወንድሜ፤ ካስቀየምኩህ ካስቸገርኩህ ከጎዳሁህ እኔን ኃጢአተኛውን ይቅር በለኝ። መሻሻል እሞክራለሁ። ልችልህ ሳይሆን በእግዚአብሔር እርዳታ ልወድህ እሞክራለሁ።
እስቲ በመጀመርያ «መቻቻል» ምን ማለት እንደሆነ እንመርምር። ሰው የሚወድውን ነገር «ቻለው» ይባላል? አይባልም! የማይወደውን ግን በተለያዩ ምክንያቶች ስለነገሩ ምንም ማድረግ የማይችለውን ወይም ማድረግ የማይፈልገውን ነገር ነው «ቻለው» የሚባለው።
ለምሳሌ… ሙስሊም ጎረቤቴ በየጊዜው ድምጽ የበዛው የጸሎት ዝግጅት ያካሄዳል ከበቱ። ጩኸቱን አልወደውም ግን ለሰላም ብዬ ዝም እላለሁ። ይህ የመቻቻል አንድ ምሳሌ ነው።
እዚ ጋር አንድ ነገርን ልብ እንበል። ጎረቤቴን ዝም ያልኩት ስለምወደው ወይም ጥሩ ልሁንለት ብዬ አይደለም። «ነግ በኔን» አስቤ ነው። ለራሴ ጥቅም ብዬ ነው። እኔም ዝግጅቶችህን ተው ብዬ አላስቸግረውም እሱም እኔ እንደዚሁ አይነት ፕሮግራም ባዘጋጅ ዝም ይለኛል። አልፎ ተርፎ ጸብ ስለሌለን ግንኙነታችን ሰላማዊ ስለሆነ ወደ ፊት በተለያዩ የሚጠቁሙን ጉዳዮች መተባበር መረዳዳት ቀላል ሊሆን ይችላል።
ስለዚህ «መቻቻል» የአብሮ መኖር ስልት ነው። የጥሩነት ወይም በጎ መግባር ውጤት አይደለም የመዋደድ የፍቅርም ውጤት አይደለም።
መቻቻል እንዲህ ከሆነ ለኛ ኦርቶዶክስ ክርስትያኖች ምን ማለት ነው? መቻቻል አለብን ወይ? የሌላ ሃይማኖት ተከታዮችን «መቻል» አለብን ወይ? «የሃይማኖት መቻቻልን» መተግበር አለብን ወይ? በፍፁም! በመጀመርያ እንደ ክርስትናችን «መውደድ» ነው ያለብን። አምላካችን እንዳለን እሱ እንደሚወደን ያህል ባለንጀራችንን መውደድ አለብን። የኛ የክርስትያኖች ተዕልኮ «ፍቅር» ነው እንጂ «መቻቻል» አይደለም! ማንም ሰው ከልምድና ምቾት አንጻር መቻቻል ይችላል፤ ግን ክርስትያኖች መውደድ ነው ያለብን።
ወደ ቅድሙ ምሳሌአችን ከተመለሰን የሙስሊም ጎረቤቴን ስለ ጸሎት ዝግጅቶቹ የማላስቸግረው ምክንያት «መቻቻል» ሳይሆን «ፍቅር» ነው መሆን ያለበት። ስለ ዝግጅቱ ካላማረርኩኝ አለማማረሬ ከፍቅር የመነጨ መሆን አለበት እንጂ ለራሴ ጥቅም ብዬ መሆን የለበትም። እሱም ይሉኝታ ኖሮት ዝም ይለንኛል ብዬ ከሱ ጠብቄ ሳይሆን ምንም ሳልጠብቅ ምሆን አለበት። ስለዚህ ክርስትያኖች መቻቻልን መተግበር አለባቸው ማለት ትርጉም የለውም። ከመቻቻል በላይ ሰማይ ጠቀሱን ፍቅር መተግበር ነው ያለን።
እንግዲህ አንዳንዶቻችሁ «አምላካችሁ ውደዱ ቢላችሁም አትሰሙትም» ትሉኝ ይሆናል። «እናንተ ኦርቶዶክስ ክርስትያኖች ድሮም አሁንም ፍቅርን አታውቁም።» አልክድም፤ እውነት ነው፤ እኔ ኦርቶዶክስ ክርስትያን ብሆንም ኃጢአተኛ ነኝ ፍቅር ይጎለኛል። ፍቅር የሆነውን ተልዕኮኤን ሁል ጊዜ እየሳትኩኝ ነው የምኖረው። ይህ ኃጢአተኝነቴ ግን የሚስተካከለው ወይንም በትክክሉ ቋንቋ የሚታከመው መቻቻልን መተግበር በመሞከር አይደለም። ፍቅርን በመተግበር ነው። ካልቻልኩኝ ከወደቅኩኝ ተመልሼ መሞከር መነሳት ነው። ይህ ነው የክርስትና ኑሮ። እንጂ መውደድ አልችልም ብዬ ተስፋ ቆርቼ እስቲ መቻቻልን ልሞርክ ማለት ውድቅ ሀሳብ ነው።
ስለዚህ ፕሮቴስታንት ወንድሜ፤ ሙስሊም እህቴ፤ ሴኩላሪስት ወንድሜ፤ ካስቀየምኩህ ካስቸገርኩህ ከጎዳሁህ እኔን ኃጢአተኛውን ይቅር በለኝ። መሻሻል እሞክራለሁ። ልችልህ ሳይሆን በእግዚአብሔር እርዳታ ልወድህ እሞክራለሁ።
Subscribe to:
Posts (Atom)