Showing posts with label አክራሪነት. Show all posts
Showing posts with label አክራሪነት. Show all posts

Thursday, 22 March 2018

የመሬት ፖሊሲ በጸንፈኛ ፖለቲከኞቻችን እጅ

English version: https://asfawdarguemeshal.blogspot.ca/2017/05/our-radical-politicians-land-to-ruler.html

በቅርብ ጊዜ ከዚህ ዓለም የተለዩት የኃይለ ሥላሴ የህግ አማካሪ የነበሩት ተሾመ ገብረማርያም በቃለ ምልልስ እነዲህ ሲሉ ሰማኋቸው፤ «መሬት ለአራሹ» ነበር ያልነው፤ «መሬት ለመንግስት» ሆኖ ቀረ። የ«መሬት ለአራሹ» የሚባለው ፖሊሲ አላማው ከባላባት «ተከራይቶ» የሚያርሰውን መሬት ለጪሰኛው መስጠትና የመረቱ ባለቤት ማድረግ ነበር። የኃይለ ሥላሴ መንግስት ይህን ፖሊሲ ለማጽደቅ ቢሞክር በፖለቲካ በፍትህ በአፈጻጸም ደረጃ ችግሮች ያጋጥሙት ነበር። ሆኖም ለነበረው ኢፍትሃዊ ሥርዓትና ከነበረው የገበሬውችግር አንጻር ይህ «መሬት ለአራሹ» ፖሊሲ ትክክል ተገቢ አስተዋይና መጠነኛ እርምጃ ይሆን ነበር። በተቃራኒው ከደርግ ጀምሮ የዋለው «መሬት ለመንግስት» ፖሊሲ የመሬት ባለቤትነት ሙሉ በሙሉ ለመንግስት ማስተላለፉ ለነበረው የመሬትችግር የከረረና ጸንፈኛ መልሰ ነበር። የፖለቲካ ልሂቃኖቻችን ተገቢውን መጠነኛውን እርምጃ ከመውሰድ አክራሪና ጸንፈኛውን እርምጃ ወሰዱ።

የሚያሳዝነው ነገር በኢትዮጵያ የቅርብ ዘመን ታሪቅ ልሂቃኖቻችን በቁልፍ ጊዜዎች በተደጋጋሚ ወደ ጸንፍ ማድላታቸው ነው። በተለይ የኃይለ ሥላሴ «ልጆች» የሆኑት በሳቸው ጊዜ ከ1950 ወዲህ የቀለም ትምሕርት የተማሩት ልሂቃን በተደጋጋሚ ጸንፈኛ የፖለቲካ ውሳኔዎች በመወሰን አገራችንን ወደ ከባድ ያልተጠበቁ አደጎች መርተዋታል። ኢትዮጵያ እስካሁን ድረስ ለነዚህ አጉል ውሳኔዎች  ዋጋ እየከፈለች ነው።

ከዚህ ጽሁፍ የኢትዮጵያን ህዝብ የጎዳው እስካሁንም እያሰቃየው ያለው የመሬት ባለቤትን መንግስት ያደረገው የፖሊሲ ውሳኔን እንመልከት። ይህ ፖሊሲ ባጭሩ ስድስት ችግሮች ፈጥሯል አባብሷል፡

1. የህዝብ ቁጥርን ባልተጠበቀና በኢተፈትሮ ሁኔታ መናር
2. አሁን ያለውን ታላቅ የገጠር ወደ ከተማ ፍልሰት
3. ዝቅተኛ «የሰው አቅም» (human capital) በትለይ የግብርና ሙያ በገጠር ቦታዎች
4. ዝቅተኛ የእርሻ ምርት መጠን
5. ከፍተኛ የእህል የምግባ ዋጋ ግሽበት
6. የምግብ ዋስትና እጥሮትና ረኃብ

እነዚህ ችግሮች እንዴት ተፈጠሩ? በመጀመርያ መሬት የመንግስት መደረጉ ገበሬዎች መሬታቸውን መሸጥ መለወጥ ስለከለከላቸው የገጥር ህዝብን ከሞላ ጎደል እስረኛ አድርጓቸዋል። ገበሬዎችና ቤተሰቦቻቸው ወደ ከተማ መዘዋወር እንዳይችሉ ከልክሏቸዋል። ይህ እንዴት እንደሆነ በምሳሌ ላስረዳ።

ዐምዴ የሚባል አንድ ገበሬ በ1968 በቂ የሆነ ወደ ሰባት ሄክታር የሚሆን እርሻ ነበረው። ዐምዴ ቤተሰቡን ይዞ ወደ ከተማ መዘዋወር ይፈልጋል። ግን ይህን ለማድረግ የመቋቋምያና ስራ መጀመርያ ገንዘብ ያስፈልገዋል። ይህን ገንዘብ ለማግኘት መሬቱን በሙሉ ወይም በከፊል መሸጥ አለበት መሬቱ ዋና ንብረቱ ስለሆነ። ያኔም አሁንም የኢትዮጵያ ገበሬዎች ከመሬታቸው ሌላ ብዙ ዋጋ ያለው ንብረቶች የላቸውም።

ግን የዐምዴ መሬት የመንግስት ነው ተብሎ ስለተሰየመ መሸጥ መለወጥ በሱ መበደርም አይችልም። ስለዚህ ለከተማ ኑሮ የሚያስፈልገውን ገንዘብ ማግኘት አልቻለም። በተጨማሪ መሬቱን ትቶ ቢሄድ ደግሞ ይወሰድበታል። ስለዚህ በተዘዋዋሪ ዐምዴ ወደ ከተመ መዘዋወር እንዳይችል ተከለከለ ማለት ነው። 1) መሬቱን ሽጦ ወደ ከተማ ለመሄድ ገንዘብ ማግኘት አይችልም። 2) እንደምንም አድርጎ ገንዘብ አግኝቶ ቢሄድም ሀሳቡን ቀይሮ ልመለስ ቢል ምሬቱ ተወስዶበት ነው የሚያገኘው! ይህን ሁሉ ስለሚያውቅ ዐምዴ ወደ ከተማ መሄድን አያስበውም። ሌሎቹም የኢትዮጵያ ገበሬዎች እንደ ዐምዴ ከተማ መሄድ ቢፈልጉም ገጠር ቁች ብለዋል። በዚህ የመሬት ፖሊሲ ምክነያት ከ1975 እስከ ቅርቡ ጊዜ ገበሬዎች በሚገባው ቁጥር ወደ ከተማ አልፈለሱም።

በዐምዴ ታሪክ እንቀጥልና የለት ኑሮው እንዴት ነበር ብለን እንጠይቅ። እንደ አብዛኛው የገጠር ነዋሪ ዐምዴ ብዙ ልጆች ወልዷል። ሰባት ልጆች ወልዷል። በ2000ዓ.ም. በገጠር የሚኖሩ ሴቶች በአማካኝ 6.5 ልጆች ነበር የሚወልዱት በአዲስ አበባ 2.2 ነበር። ይህ በከተማና በገጠር ያለው የልጅ መውለድ መጠን ልዩነት ዓለም አቀፍ ያለ ነው፤ የገጠር በአንጻሩ ብዙ ይወልዳል የከተማ አይወልድም። ደሃ ባንጻሩ ብዙ ይወልዳል ሃብታም አይወልድም። ይህ ዓለም በሙሉ የሚታይ ሁኔታ ነው።

የዐምዴ ልጆች ሲያድጉ መሬቱን ከፋፍሎ ለእያንዳንዳቸው አንድ ሄክታር አወረሰ። ከብዙ ዓመታት በኋላ ልጆቹም እያንዳንዳቸው ሰባት ልጆች ወለዱና አንድ ሄክታር መሬቶቻቸው ጠበቡ። ይህ ችግር በአገር አቀፍ ደረጃ እየባሰ ሄዷል። ዛሬ በኢትዮጵያ የአማካኝ የእርሻ ይዞታ ከአንድ ሄክታር በታች ነው። የገጠር መሬት ተጨናንቋል።

በ1968 የመሬት አዋጁ ሲታወጅ ከ28 ሚሊዮን የነበረው የኢትዮጵያ ህዝብ ወደ 85% የገጠር ነዋሪ ነበር። 40 ዓመት በኋላ በ2008 ከ97 ሚሊዮን ጠቅላላ የህዝብ ቁጥር 80% በገጠር ይኖራል። በ40 ዓመት በገጠር የሚኖረው የህዝብ መጠን ከ85% ወደ 80% በአምስት ብቻ ነው የቀነሰው። ግን የገጠር ነዋሪዎች ከላይ እንደጠቀስኩት በአማካኝ 6.5 ልጅ ስለሚወልዱ ጠቅላላ የገጠር የህዝብ ቁጥር ናረ። ለምን? ለ40 ዓመት ገበሬዎች ሲፈልጉ መሬታቸውን ሽጠው ወደ ከተማ መዘዋወር ስላልቻሉ ከሚገባው በታች ቁጥር ነው ወደ ከተማ የፈለሰው። የመሬቱ ፖሊሲ ባይኖር ኖሮ የገጠሩ ሰው ዓለም ዙርያ እንደሚታየው በራሱ በተፈጥሮና በነፃነት መንገድ ቀስ በቀስ ውደ ከተማ ይፈልስ ነበር። ይህ የተፈጥሮ መጠነኛ ፍልሰት በመሬት ፖሊሲው ምክነያት ባይታገድ ኖሮ የገጥር የህዝብ ቁጥር ዛሬ ከ80% ፋንታ ምናልባት ወደ 65% ወይም ከዛም ዝቅ ብሎ ይወርድ ነበር።

በዚህ መልክ የገጠሩ የህዝብ ቁጥር ቅስ በቅስ እየወረደ ቢሄድ የከተማ ህዝብ ቁጥር እየጨመረ ሲሄድ የአገሪቷ የጠቅላላ የህዝብ ቁጥር እንዳሁኑ አይንርም ነበር። ምክነያቱ የከተማ ሰው እንደ ገጠሬው ያህል አይወልድም። በዐምዴ ምሳሌ ከቀጠልን ወደ ከተመ ቢዘዋወር ኖሮ ልጆቹ እያንዳንዳቸው ሰባት ልጆች ከሚወልዱ ከተማ ስለሚኖሩ እንደሌሎች የከተማ ነዋሪዎች ሁለት ይወልዱ ነበር። ግን ወደ ከተማ እንዳይመጣ «ተከልክሎ» ዐምዴ ከገጠር ታስሮ ቆየ። በዐምዴ ምሳሌ እንደምናየው ይህ «የገጠር እስርቤት» መተንፈስ ስላልቻለ የህዝብ ቁጥሩ በ40 ዓመት ከ24 ሚሊዮን ወደ 77 ሚሊዮን ገባ። ይህ የገጠር/ከተማ የህዝብ መጠን አላግባብ ከፍ ያለ በመሆኑ ነው የኢትዮጵያ የህዝብ ቁጥር በኢተፈጥሮ መንገድ የናረው እስካሁን የሚንረው።

ወደ ዐምዴ ቤተሰብ እንመለስ። ልጆቹ እያንዳንዳቸው ሰባት ልጆች ወልደው የአንድ ሄክታር መሬታቸውን ለሰባቱ መከፋፈል አይችሉም አንድ ሰባተኛ ሄክታር ለአንድ ቤተሰብን በቂ ስላልሆነ። ስለዚህ መሬታቸውን ለአንድ ልጃቸው ያወርሱትና ሌሎቹ ስድስት ልጆቻቸው ሁለተኛ ደረጃ ትምሕርታቸውን ጨርሰው ግድ ወደ ከተመ መዘዋወር ይኖርባቸዋል። አሁን በአገራችን የምናየው ሁኔታ ይህ ነው። የጠበቅነው ግን መንግስቶቻችን ችላ ያሉት የመሬት መጥበብ ደርሷል። በሚሊዮን የሚቆጠሩ ገበሬዎች ለአንድ ወራሽ ብቻ የሚበቃ መሬት ነው ያላቸውና ሌሎች ልጆቻቸው ወደ ከተማ እየፈለሱ ነው። አሁን ያለውን ታላቅ የገጠር ወደ ከተማ ፍልሰት ይህ ነው ምክነያቱ። ለ40 ዓመት የተጠራቀመ ፍልሰት ነው አሁን ባንዴ የሚታየው። ግና ይቀጥላል።

ከዐምዴ ጋር እንቀጥል። ዐምዴ እግዚአብሔር ይባርከው እንጂ ጎበዝ ገበሬ አይደለም። ሙያውም ፍላጎቱም የለውም ግን ቤተሰቡን ለማስተዳደር ብሎ ያርሳል። ጎረቤቱ ገመቹ ግን እጅግ ጎበዝ ገበሬ ነው። የግብርና ንግዱን ማስፋፋት ይፈልጋል። ግን በመሬት ፖሊሲው ምክነያት እንዴት አድርጎ ተጨማሪ መሬት ይግዛ። ዐምዴ በደስታ መሬቱን ይሸጥለት ነበር ገመቹም ችሎታውን ተማምኖ ጥሩ ዋጋ ይሰጠው ነበር ግን አይፈቀድም። ስለዚህ የሚፈቀደውን አደረጉ ገመቹ ከዐምዴ የተወሰነ መሬት በየዓመቱ እየተከራየ ማረስ ጀመረ። ገመቹ ጉድጓድ መቆፈር ዛፍ መትከልና ተመሳሳይ የረዥም እቅድ ስራዎችና ኢንቬስትሜንቶች ማድረግ ይፈልጋል ግን መሬቱ የሱ ስላልሆነ ኪራዩም በየዓመቱ የሚታደስ ስለሆነ ስለረዥም እቅዶች ማሰብ አይችልም። ገመቹ ከሌሎች ጎረቤቶቹ ተጨማሪ መሬት ገዝቶ ስራውን አስፋፍቶ ምናልባት በትራክተር ማረስ፤ ሙያውንም ማዳበር፤ ስለ ፍራፍሬ ማምረት መማር፤ ወዘተ ያልማል። ግን ችሎታ ቢኖረውም በመሬት ፖሊሲው ምክነያት ምኞቶቹን በተግባር መዋል አልቻለም።

ገመቹ ከዐምዴ በተከራየው መሬት 20 ኪንታል በሄክታር ጠፍ ያመርታል። ዐምዴ 10 ነበር የሚያመርተው። ገመቹ የዐምዴ መሬት ሙሉ በሙሉ ሰባቱንም ሄክታር ገዝቶ ጠፍ ቢተክልበት ኖሮ በዐምዴ 70 ኪንታል የሚያበቅለው መሬት በገመቹ እጅ 140 ኪንታል ያበቅል ነበር። የአካባቢው የምርት መጠን ይጨምር ነበር። ገመቹ ደግሞ የሚያገኘውን ትርፍ ተጠቅሞ መሬቱ ላይ ኢንቬስት አድርጎ የግብርና ንግዱን የምርት መጠኑን ይበልጥ ያሻሽል ነበር። የአካባቢው የጠፍ ምርት ይጨምር ነበር የጤፍ ዋጋ ደግሞ ይቀንስ ነበር። ዐምዴ ከተማ ገብቶ ጠፍ በመጠነኛ ዋጋ ያገኝ ነበር።

ገመቹ ላይ የደረሰው የስራ ክለላ ወይም የማስፋፈትና ማደግ ክለላ የኢትዮጵያ መንግስታት በአገሪቷ ገበሬዎች ላይ ያሳደሩት አሳዛኝ ድርጊት ነው። ገበሬዎች ስራቸውን እርሻቸውን ንግዳቸውን እንዳያሰፋፉ በማገድ መንግስት የገበሬዎቻችን «የሰው አቅም» (human capital) አፍነዋል። ይህ የኤኮኖሚ ብቻ ሳይሆን የሥነ ልቦና የፖለቲካ የማኅበራዊ ተጽዕኖ ገበሬዎች ላይ አሳድሯል። ከሁሉም የግል ነጋዲዎች ተለይተው ገበሬዎች ነፃነት እንዳይኖራቸው ንግዳቸውን ማስፋፋት እንዳይችሉ ተደርገዋል። በዚህ ምክነያት በሙያ ችሎታም በሙያ ትምሕርትም እንዳይሻሻሉ ተደርገዋል። እንደነበሩት እንዲቆዩ ተደርገዋል። እስቲ አንድ ሜካኒክ ስራውን ንግዱን ከማስፋፋት በህግ ቢከልከል እናስበው። ከአንድ መኪና በላይ የሚችል ቦታ ሊኖርህ አይችልም ቢባል። ይህ ሜካኒክ መቼም የችሎታውን አቅም ሳያሟላ ይቆያል። ወይም አንድ የዩኒቨርሲቲ መምህር ስራ መቀየር አትችልም ከአንድ ርዕስ ውጪ ጥናት ማካሄድ አትችልም ቢባል። ይህ መምህር በሙያው የተም አይደርስምና እራሱን ለማሻሻል አይጥርም። ስራውም እየሰለቸው ይሄዳል። ስለዚህ የመሬት ፖሊሲው ለገበሬዎች ኮምዩኒዝም ለሌሎች ካፒታሊዝም ነው ያደነገገው።

ይባስ ተብሎ መንግስቶቻችን የመንግስት ያልሆኑት ድርጅቶችም (ንጂኦ) ገበሬዎችን ወደታች አድርገው በንቀት ይመለከታሉ። እንደ ሞግዚት የሚያስፈልጋቸው ደንቆሮች ያይዋቸዋል። ከላይ እንዳልኩት ይህ የሆነው ገበሬዎች አቅማቸውን እውቀታቸውን ከማሻሻል ስለተገደቡ ነው። መንግስት እራሱ በነፃነት እንዳይሰሩ ስለከለከላቸው ነው። እንደ ጥሩ ኮምዩኒስቶች መንግስት ዋናውን የምርት ግበዓት የሆነውን መሬት አፍኖ ሌሎችን ግብአቶች እንደ ምርጥ ዘር ማዳበርያ ተባይና አረም ምጥፍያ የ«ኤክስቴንሽን» ትምሕርት ወዘተ በመጨመር የአገሪቷ የምርት መጠንን መጨመር ሞከረ። ግን አልሰራም።

ዛሬም በኢትዮጵያ የሰብል መርት በሄክታር ዝቅተኛ ነው። የምግብ ዋጋ ከሌሎች ታዳጊ ዓገሮች ውድ ነው። ወተት እንቁላል ቂቤ ሥጋ ማር ከአደጉ አገሮች ይልቅ ኢትዮጵያ ይወደዳሉ። የሰብል ዋጋ ውድ ቢሆንም የግብርና የንግድ ክፍል ተስፋፍቶ ያለውን ፍላጎት በአግባብ ማስተናገድ አልቻለም። ፈላጊ እየበዛ ሲሄድ አቅራቢ በቂ ማቅረብ አቅቶታል። ገበሬው ኢንቬስት ማድረግ አልቻለም። ለዚህ ነው የእህል የምግባ የዋጋ ግሽበቱ አሳሳቢ ሁኔታ ላይ የሆነውና መንግስትን የሚያስጨንቀው።

ወደ ዐምዴ እንመለስ… ኢትዮጵያ በ10 ዓመት አንዴ የሚደርስባት ድርቅ መጥቶ የዐምዴ ልጆች በአንድ ሄክታሮቻቸው በጣም አነስተኛ መርት ያገኛሉ። ዐምዴ ሰባቱን ሄክታር በሚያአርስበት ጊዜ ድርቅ ቢኖርም የሰባት ሄክታሩ ምርት ብዙ ስለነበር ለድርቅ ጊዜ በቂ የተከማቸ እህል ነበረው። አሁን ግን የዐምዴ ልጆች በአንድ ሄክታር እጅ ወደ አፍ ስለሚኖሩ የአንድ ዓመት ምርታቸው ከቀነሰ በቂ አይኖራቸውም። ስለዚህ ሰባቱም የዐምዴ ልጆችና ቤተሰቦቻቸው ወደ ምግብ እርዳታ ተሸጋሸጉ።

ታሪኩ በዚ ይጠቃለላል፤ የህዝብ ቁጥርን ባልተጠበቀና በኢተፈትሮ ሁኔታ መናር አሁን ያለውን ታላቅ የገጠር ወደ ከተማ ፍልሰት ዝቅተኛ «የሰው አቅም» (human capital) በትለይ የግብርና ሙያ በገጠር ቦታዎች ዝቅተኛ የእርሻ ምርት መጠን ከፍተኛ የእህል የምግባ ዋጋ ግሽበት የምግብ ዋስትና እጥሮትና ረኃብ። ሁሉም ችግሮች ብያንስ በከፊሉ የ1968 የመሬት አዋጁ ውጤቶች።

የዚህ ፖሊሲ ጎጂ ውጤቶች ያልበሰሉ ጸንፈኛ የፖለቲካ ልሂቃን በችኩልነታቸው አገሪቷ ላይ ሊያመጡ የሚችሉትን ጉዳት ያሳያል። ከጽንፈኝነት መካከለኛውን መንገድ መያዝ ይሻላል። የዛሬም ግዥዎቻችን ከዚህና ሌሎች ታሪኮች ተምረው ሌላውን ጸንፈኛ የአገራችን ፖሊሲ የጎሳ አስተዳደርን እንደገና ቢያስቡበት ይሻላል።

Tuesday, 4 October 2016

Where the TPLF went wrong

2009/1/23 (Ethiopian calendar)
2016/10/3 (European calendar)

[Note: An Amharic version of this post will appear sometime!]


A lot has been written about this over the past 25 years, but it doesn't hurt repeating, especially given today's political circumstances in Ethiopia. The TPLF's biggest historical mistake was interpreting its coming to power in 1991 as a full mandate from the vast majority of Ethiopians and assuming it meant a complete rejection of everything that preceded it. This mistaken assumption involved a typically modern Ethiopian exercise in black and white or zero sum thinking.

Basically, this is how the thought process worked... The Haile Selassie government fell, not because it failed to make some sensible reforms, but because it failed to make all the radical changes demanded of it by the students movement. The fall of the Dergue government had nothing to do with the Cold War, a failed Communist economy, or the war with Somalia, but because Ethiopia was a prison of nationalities that had to be liberated. The rise of the TPLF had nothing to do with the end of the Cold War and a bankrupt regime, but because the TPLF and its ethnic ideology best represented the interests of a majority of Ethiopians. The TPLF blinded itself to obvious facts in a bid to convince itself of its monopoly on truth and ability to rule Ethiopia.

Thus, after gaining power, the TPLF, in the form of the EPRDF, began a ruling style that involved continually trying to do the radical and the impossible, its hubris deluding it into believing that it was special enough to do anything politically.

This mindset is what emboldened the EPRDF to saddle Ethiopia (and itself) with perhaps the most radical ethnic based constitution in world history. With a little more maturity, it would have realized that this constitution was not only unpopular and fundamentally at odds with the interests of a large section of the population, but so radical, untested, and risky that there was a good chance it would in the future make governing impossible. For everyone except the EPRDF and other ethnic nationalists, it was clear that a more moderate constitution would have easily satisfied all constituencies, including ethnic nationalists and made governing far easier for the EPRDF.

Building on the constitution, the EPRDF embarked on an ethnic policy that can only be described as playing with fire. It engaged in policies (such as official identification by ethnicity) and rhetoric ('reactionaries' and 'narrow nationalists') that emphasized differences among Ethiopians and diminished commonalities. It thought that it could promote ethnic nationalism and at the same time control ethnic strife, knowing full well that its ethnic political base, Tigray, was composed of a small minority! An impossibly delicate formula if there ever was one. However, thanks to various factors, especially the sad state of the Ethiopian nationalist elite, the EPRDF has managed so far to survive on this knife's edge.

But the fundamentals remain wrong, and this explains today's smoldering dissent. It's a political reality that a people can tolerate far more oppression from their own ethnic group or in a non-ethnic context than they can from another ethnic group. The TPLF knows this quite well, having leveraged the political tool of ethnicity to its fullest during its liberation struggle. Yet, the EPRDF continued a policy of promoting ethnic nationalism while real power and perception of real power, remained in the hands of the TPLF. This has inevitably resulted in widespread resentment against the TPLF and Tigray. This was all predictable from the beginning; there have been ever increasing signs of it in the past two decades, yet hubris has prevented the EPRDF from changing course.

Note that this policy from the beginning was the antithesis of what is best for Tigray. A small minority can flourish in a multi-ethnic society, but not in a society where ethnic division and tension dominate, since the minority is dependent on migration and integration to prosper. The region of Tigray, like all the small ethnicities in Ethiopia, would do best in a country that is more united than divided. Yet, the ideology of the TPLF (and its big brother EPLF) was so ingrained that they basically ignored this danger and continued promoting ethnically divisive policies.

To be fair, the EPRDF did eventually realize the seriousness of the problem. Part of the reasons for the full mobilization of party resources towards the developmental state project ('lemat', for the masses) that begin during the mid part Prime Minister Meles' tenure was to mitigate ethnic division. The rhetoric of economic development was ramped up as a political tool to promote civic nationalism – to give all parts of the country something in common to unite around – and counter the obvious damage of ethnic nationalism. But of course the economy cannot by itself bring down ethnic boundaries and increase civic nationalism. Inter-ethnic integration, which the EPRDF's constitution essentially prevents, is the only way to do so.

The above is just a small list of the radical and reckless policies of the EPRDF over the past 25 years, which aros a consequence of the circumstances around its rise to power, including the absence of an opposing elite power to act as a moderating influence. Now, what does this history teach us about what is happening today? What is happening today?

Well, we continue to hear from hardline EPRDF leaders the same old rhetoric about reactionaries and narrow nationalists – the same old hubris. But there are moderates in the EPRDF and TPLF who have long ago come to realize the folly in their fundamental assumptions. These moderates and hardliners are discussing behind closed doors how to address the current revolt. The moderates are right and sensible, of course, but what has always handicapped them is external leverage. They need a strong Ethiopian nationalist movement and elite, the opposing elite power which I mentioned above, with power on the ground, that they can count on as a foil for the hardliners. They need a political partner on the other side, in other words, so that they can say to the hardliners, “Look, you've tried it your way, and now there is an opposition that your hardline policies cannot dislodge. It's time for you to step aside and let us negotiate a new system of governance.”

Unfortunately, this Ethiopian nationalist movement is not yet there. The soft and hard ethnic nationalists in Oromia who are against TPLF domination have been doing their part for years, but not the Ethiopian nationalists. Now we have the uprisings in Amhara Region, and this is a huge step in the right direction, but there is no organization yet. It is important that these uprisings soon coalesce into a tangible political movement so that it can work with the moderates in EPRDF to find a way out if its quagmire. Failing this, we have to count on the EPRDF reforming by itself. It's a tall order for any organization, especially on with the historical baggage of the TPLF.