English version: https://asfawdarguemeshal.blogspot.ca/2017/05/our-radical-politicians-land-to-ruler.html
በቅርብ ጊዜ ከዚህ ዓለም የተለዩት የኃይለ ሥላሴ የህግ አማካሪ የነበሩት ተሾመ ገብረማርያም በቃለ ምልልስ እነዲህ ሲሉ ሰማኋቸው፤ «መሬት ለአራሹ» ነበር ያልነው፤ «መሬት ለመንግስት» ሆኖ ቀረ። የ«መሬት ለአራሹ» የሚባለው ፖሊሲ አላማው ከባላባት «ተከራይቶ» የሚያርሰውን መሬት ለጪሰኛው መስጠትና የመረቱ ባለቤት ማድረግ ነበር። የኃይለ ሥላሴ መንግስት ይህን ፖሊሲ ለማጽደቅ ቢሞክር በፖለቲካ በፍትህ በአፈጻጸም ደረጃ ችግሮች ያጋጥሙት ነበር። ሆኖም ለነበረው ኢፍትሃዊ ሥርዓትና ከነበረው የገበሬውችግር አንጻር ይህ «መሬት ለአራሹ» ፖሊሲ ትክክል ተገቢ አስተዋይና መጠነኛ እርምጃ ይሆን ነበር። በተቃራኒው ከደርግ ጀምሮ የዋለው «መሬት ለመንግስት» ፖሊሲ የመሬት ባለቤትነት ሙሉ በሙሉ ለመንግስት ማስተላለፉ ለነበረው የመሬትችግር የከረረና ጸንፈኛ መልሰ ነበር። የፖለቲካ ልሂቃኖቻችን ተገቢውን መጠነኛውን እርምጃ ከመውሰድ አክራሪና ጸንፈኛውን እርምጃ ወሰዱ።
የሚያሳዝነው ነገር በኢትዮጵያ የቅርብ ዘመን ታሪቅ ልሂቃኖቻችን በቁልፍ ጊዜዎች በተደጋጋሚ ወደ ጸንፍ ማድላታቸው ነው። በተለይ የኃይለ ሥላሴ «ልጆች» የሆኑት በሳቸው ጊዜ ከ1950 ወዲህ የቀለም ትምሕርት የተማሩት ልሂቃን በተደጋጋሚ ጸንፈኛ የፖለቲካ ውሳኔዎች በመወሰን አገራችንን ወደ ከባድ ያልተጠበቁ አደጎች መርተዋታል። ኢትዮጵያ እስካሁን ድረስ ለነዚህ አጉል ውሳኔዎች ዋጋ እየከፈለች ነው።
ከዚህ ጽሁፍ የኢትዮጵያን ህዝብ የጎዳው እስካሁንም እያሰቃየው ያለው የመሬት ባለቤትን መንግስት ያደረገው የፖሊሲ ውሳኔን እንመልከት። ይህ ፖሊሲ ባጭሩ ስድስት ችግሮች ፈጥሯል አባብሷል፡
1. የህዝብ ቁጥርን ባልተጠበቀና በኢተፈትሮ ሁኔታ መናር
2. አሁን ያለውን ታላቅ የገጠር ወደ ከተማ ፍልሰት
3. ዝቅተኛ «የሰው አቅም» (human capital) በትለይ የግብርና ሙያ በገጠር ቦታዎች
4. ዝቅተኛ የእርሻ ምርት መጠን
5. ከፍተኛ የእህል የምግባ ዋጋ ግሽበት
6. የምግብ ዋስትና እጥሮትና ረኃብ
እነዚህ ችግሮች እንዴት ተፈጠሩ? በመጀመርያ መሬት የመንግስት መደረጉ ገበሬዎች መሬታቸውን መሸጥ መለወጥ ስለከለከላቸው የገጥር ህዝብን ከሞላ ጎደል እስረኛ አድርጓቸዋል። ገበሬዎችና ቤተሰቦቻቸው ወደ ከተማ መዘዋወር እንዳይችሉ ከልክሏቸዋል። ይህ እንዴት እንደሆነ በምሳሌ ላስረዳ።
ዐምዴ የሚባል አንድ ገበሬ በ1968 በቂ የሆነ ወደ ሰባት ሄክታር የሚሆን እርሻ ነበረው። ዐምዴ ቤተሰቡን ይዞ ወደ ከተማ መዘዋወር ይፈልጋል። ግን ይህን ለማድረግ የመቋቋምያና ስራ መጀመርያ ገንዘብ ያስፈልገዋል። ይህን ገንዘብ ለማግኘት መሬቱን በሙሉ ወይም በከፊል መሸጥ አለበት መሬቱ ዋና ንብረቱ ስለሆነ። ያኔም አሁንም የኢትዮጵያ ገበሬዎች ከመሬታቸው ሌላ ብዙ ዋጋ ያለው ንብረቶች የላቸውም።
ግን የዐምዴ መሬት የመንግስት ነው ተብሎ ስለተሰየመ መሸጥ መለወጥ በሱ መበደርም አይችልም። ስለዚህ ለከተማ ኑሮ የሚያስፈልገውን ገንዘብ ማግኘት አልቻለም። በተጨማሪ መሬቱን ትቶ ቢሄድ ደግሞ ይወሰድበታል። ስለዚህ በተዘዋዋሪ ዐምዴ ወደ ከተመ መዘዋወር እንዳይችል ተከለከለ ማለት ነው። 1) መሬቱን ሽጦ ወደ ከተማ ለመሄድ ገንዘብ ማግኘት አይችልም። 2) እንደምንም አድርጎ ገንዘብ አግኝቶ ቢሄድም ሀሳቡን ቀይሮ ልመለስ ቢል ምሬቱ ተወስዶበት ነው የሚያገኘው! ይህን ሁሉ ስለሚያውቅ ዐምዴ ወደ ከተማ መሄድን አያስበውም። ሌሎቹም የኢትዮጵያ ገበሬዎች እንደ ዐምዴ ከተማ መሄድ ቢፈልጉም ገጠር ቁች ብለዋል። በዚህ የመሬት ፖሊሲ ምክነያት ከ1975 እስከ ቅርቡ ጊዜ ገበሬዎች በሚገባው ቁጥር ወደ ከተማ አልፈለሱም።
በዐምዴ ታሪክ እንቀጥልና የለት ኑሮው እንዴት ነበር ብለን እንጠይቅ። እንደ አብዛኛው የገጠር ነዋሪ ዐምዴ ብዙ ልጆች ወልዷል። ሰባት ልጆች ወልዷል። በ2000ዓ.ም. በገጠር የሚኖሩ ሴቶች በአማካኝ 6.5 ልጆች ነበር የሚወልዱት በአዲስ አበባ 2.2 ነበር። ይህ በከተማና በገጠር ያለው የልጅ መውለድ መጠን ልዩነት ዓለም አቀፍ ያለ ነው፤ የገጠር በአንጻሩ ብዙ ይወልዳል የከተማ አይወልድም። ደሃ ባንጻሩ ብዙ ይወልዳል ሃብታም አይወልድም። ይህ ዓለም በሙሉ የሚታይ ሁኔታ ነው።
የዐምዴ ልጆች ሲያድጉ መሬቱን ከፋፍሎ ለእያንዳንዳቸው አንድ ሄክታር አወረሰ። ከብዙ ዓመታት በኋላ ልጆቹም እያንዳንዳቸው ሰባት ልጆች ወለዱና አንድ ሄክታር መሬቶቻቸው ጠበቡ። ይህ ችግር በአገር አቀፍ ደረጃ እየባሰ ሄዷል። ዛሬ በኢትዮጵያ የአማካኝ የእርሻ ይዞታ ከአንድ ሄክታር በታች ነው። የገጠር መሬት ተጨናንቋል።
በ1968 የመሬት አዋጁ ሲታወጅ ከ28 ሚሊዮን የነበረው የኢትዮጵያ ህዝብ ወደ 85% የገጠር ነዋሪ ነበር። 40 ዓመት በኋላ በ2008 ከ97 ሚሊዮን ጠቅላላ የህዝብ ቁጥር 80% በገጠር ይኖራል። በ40 ዓመት በገጠር የሚኖረው የህዝብ መጠን ከ85% ወደ 80% በአምስት ብቻ ነው የቀነሰው። ግን የገጠር ነዋሪዎች ከላይ እንደጠቀስኩት በአማካኝ 6.5 ልጅ ስለሚወልዱ ጠቅላላ የገጠር የህዝብ ቁጥር ናረ። ለምን? ለ40 ዓመት ገበሬዎች ሲፈልጉ መሬታቸውን ሽጠው ወደ ከተማ መዘዋወር ስላልቻሉ ከሚገባው በታች ቁጥር ነው ወደ ከተማ የፈለሰው። የመሬቱ ፖሊሲ ባይኖር ኖሮ የገጠሩ ሰው ዓለም ዙርያ እንደሚታየው በራሱ በተፈጥሮና በነፃነት መንገድ ቀስ በቀስ ውደ ከተማ ይፈልስ ነበር። ይህ የተፈጥሮ መጠነኛ ፍልሰት በመሬት ፖሊሲው ምክነያት ባይታገድ ኖሮ የገጥር የህዝብ ቁጥር ዛሬ ከ80% ፋንታ ምናልባት ወደ 65% ወይም ከዛም ዝቅ ብሎ ይወርድ ነበር።
በዚህ መልክ የገጠሩ የህዝብ ቁጥር ቅስ በቅስ እየወረደ ቢሄድ የከተማ ህዝብ ቁጥር እየጨመረ ሲሄድ የአገሪቷ የጠቅላላ የህዝብ ቁጥር እንዳሁኑ አይንርም ነበር። ምክነያቱ የከተማ ሰው እንደ ገጠሬው ያህል አይወልድም። በዐምዴ ምሳሌ ከቀጠልን ወደ ከተመ ቢዘዋወር ኖሮ ልጆቹ እያንዳንዳቸው ሰባት ልጆች ከሚወልዱ ከተማ ስለሚኖሩ እንደሌሎች የከተማ ነዋሪዎች ሁለት ይወልዱ ነበር። ግን ወደ ከተማ እንዳይመጣ «ተከልክሎ» ዐምዴ ከገጠር ታስሮ ቆየ። በዐምዴ ምሳሌ እንደምናየው ይህ «የገጠር እስርቤት» መተንፈስ ስላልቻለ የህዝብ ቁጥሩ በ40 ዓመት ከ24 ሚሊዮን ወደ 77 ሚሊዮን ገባ። ይህ የገጠር/ከተማ የህዝብ መጠን አላግባብ ከፍ ያለ በመሆኑ ነው የኢትዮጵያ የህዝብ ቁጥር በኢተፈጥሮ መንገድ የናረው እስካሁን የሚንረው።
ወደ ዐምዴ ቤተሰብ እንመለስ። ልጆቹ እያንዳንዳቸው ሰባት ልጆች ወልደው የአንድ ሄክታር መሬታቸውን ለሰባቱ መከፋፈል አይችሉም አንድ ሰባተኛ ሄክታር ለአንድ ቤተሰብን በቂ ስላልሆነ። ስለዚህ መሬታቸውን ለአንድ ልጃቸው ያወርሱትና ሌሎቹ ስድስት ልጆቻቸው ሁለተኛ ደረጃ ትምሕርታቸውን ጨርሰው ግድ ወደ ከተመ መዘዋወር ይኖርባቸዋል። አሁን በአገራችን የምናየው ሁኔታ ይህ ነው። የጠበቅነው ግን መንግስቶቻችን ችላ ያሉት የመሬት መጥበብ ደርሷል። በሚሊዮን የሚቆጠሩ ገበሬዎች ለአንድ ወራሽ ብቻ የሚበቃ መሬት ነው ያላቸውና ሌሎች ልጆቻቸው ወደ ከተማ እየፈለሱ ነው። አሁን ያለውን ታላቅ የገጠር ወደ ከተማ ፍልሰት ይህ ነው ምክነያቱ። ለ40 ዓመት የተጠራቀመ ፍልሰት ነው አሁን ባንዴ የሚታየው። ግና ይቀጥላል።
ከዐምዴ ጋር እንቀጥል። ዐምዴ እግዚአብሔር ይባርከው እንጂ ጎበዝ ገበሬ አይደለም። ሙያውም ፍላጎቱም የለውም ግን ቤተሰቡን ለማስተዳደር ብሎ ያርሳል። ጎረቤቱ ገመቹ ግን እጅግ ጎበዝ ገበሬ ነው። የግብርና ንግዱን ማስፋፋት ይፈልጋል። ግን በመሬት ፖሊሲው ምክነያት እንዴት አድርጎ ተጨማሪ መሬት ይግዛ። ዐምዴ በደስታ መሬቱን ይሸጥለት ነበር ገመቹም ችሎታውን ተማምኖ ጥሩ ዋጋ ይሰጠው ነበር ግን አይፈቀድም። ስለዚህ የሚፈቀደውን አደረጉ ገመቹ ከዐምዴ የተወሰነ መሬት በየዓመቱ እየተከራየ ማረስ ጀመረ። ገመቹ ጉድጓድ መቆፈር ዛፍ መትከልና ተመሳሳይ የረዥም እቅድ ስራዎችና ኢንቬስትሜንቶች ማድረግ ይፈልጋል ግን መሬቱ የሱ ስላልሆነ ኪራዩም በየዓመቱ የሚታደስ ስለሆነ ስለረዥም እቅዶች ማሰብ አይችልም። ገመቹ ከሌሎች ጎረቤቶቹ ተጨማሪ መሬት ገዝቶ ስራውን አስፋፍቶ ምናልባት በትራክተር ማረስ፤ ሙያውንም ማዳበር፤ ስለ ፍራፍሬ ማምረት መማር፤ ወዘተ ያልማል። ግን ችሎታ ቢኖረውም በመሬት ፖሊሲው ምክነያት ምኞቶቹን በተግባር መዋል አልቻለም።
ገመቹ ከዐምዴ በተከራየው መሬት 20 ኪንታል በሄክታር ጠፍ ያመርታል። ዐምዴ 10 ነበር የሚያመርተው። ገመቹ የዐምዴ መሬት ሙሉ በሙሉ ሰባቱንም ሄክታር ገዝቶ ጠፍ ቢተክልበት ኖሮ በዐምዴ 70 ኪንታል የሚያበቅለው መሬት በገመቹ እጅ 140 ኪንታል ያበቅል ነበር። የአካባቢው የምርት መጠን ይጨምር ነበር። ገመቹ ደግሞ የሚያገኘውን ትርፍ ተጠቅሞ መሬቱ ላይ ኢንቬስት አድርጎ የግብርና ንግዱን የምርት መጠኑን ይበልጥ ያሻሽል ነበር። የአካባቢው የጠፍ ምርት ይጨምር ነበር የጤፍ ዋጋ ደግሞ ይቀንስ ነበር። ዐምዴ ከተማ ገብቶ ጠፍ በመጠነኛ ዋጋ ያገኝ ነበር።
ገመቹ ላይ የደረሰው የስራ ክለላ ወይም የማስፋፈትና ማደግ ክለላ የኢትዮጵያ መንግስታት በአገሪቷ ገበሬዎች ላይ ያሳደሩት አሳዛኝ ድርጊት ነው። ገበሬዎች ስራቸውን እርሻቸውን ንግዳቸውን እንዳያሰፋፉ በማገድ መንግስት የገበሬዎቻችን «የሰው አቅም» (human capital) አፍነዋል። ይህ የኤኮኖሚ ብቻ ሳይሆን የሥነ ልቦና የፖለቲካ የማኅበራዊ ተጽዕኖ ገበሬዎች ላይ አሳድሯል። ከሁሉም የግል ነጋዲዎች ተለይተው ገበሬዎች ነፃነት እንዳይኖራቸው ንግዳቸውን ማስፋፋት እንዳይችሉ ተደርገዋል። በዚህ ምክነያት በሙያ ችሎታም በሙያ ትምሕርትም እንዳይሻሻሉ ተደርገዋል። እንደነበሩት እንዲቆዩ ተደርገዋል። እስቲ አንድ ሜካኒክ ስራውን ንግዱን ከማስፋፋት በህግ ቢከልከል እናስበው። ከአንድ መኪና በላይ የሚችል ቦታ ሊኖርህ አይችልም ቢባል። ይህ ሜካኒክ መቼም የችሎታውን አቅም ሳያሟላ ይቆያል። ወይም አንድ የዩኒቨርሲቲ መምህር ስራ መቀየር አትችልም ከአንድ ርዕስ ውጪ ጥናት ማካሄድ አትችልም ቢባል። ይህ መምህር በሙያው የተም አይደርስምና እራሱን ለማሻሻል አይጥርም። ስራውም እየሰለቸው ይሄዳል። ስለዚህ የመሬት ፖሊሲው ለገበሬዎች ኮምዩኒዝም ለሌሎች ካፒታሊዝም ነው ያደነገገው።
ይባስ ተብሎ መንግስቶቻችን የመንግስት ያልሆኑት ድርጅቶችም (ንጂኦ) ገበሬዎችን ወደታች አድርገው በንቀት ይመለከታሉ። እንደ ሞግዚት የሚያስፈልጋቸው ደንቆሮች ያይዋቸዋል። ከላይ እንዳልኩት ይህ የሆነው ገበሬዎች አቅማቸውን እውቀታቸውን ከማሻሻል ስለተገደቡ ነው። መንግስት እራሱ በነፃነት እንዳይሰሩ ስለከለከላቸው ነው። እንደ ጥሩ ኮምዩኒስቶች መንግስት ዋናውን የምርት ግበዓት የሆነውን መሬት አፍኖ ሌሎችን ግብአቶች እንደ ምርጥ ዘር ማዳበርያ ተባይና አረም ምጥፍያ የ«ኤክስቴንሽን» ትምሕርት ወዘተ በመጨመር የአገሪቷ የምርት መጠንን መጨመር ሞከረ። ግን አልሰራም።
ዛሬም በኢትዮጵያ የሰብል መርት በሄክታር ዝቅተኛ ነው። የምግብ ዋጋ ከሌሎች ታዳጊ ዓገሮች ውድ ነው። ወተት እንቁላል ቂቤ ሥጋ ማር ከአደጉ አገሮች ይልቅ ኢትዮጵያ ይወደዳሉ። የሰብል ዋጋ ውድ ቢሆንም የግብርና የንግድ ክፍል ተስፋፍቶ ያለውን ፍላጎት በአግባብ ማስተናገድ አልቻለም። ፈላጊ እየበዛ ሲሄድ አቅራቢ በቂ ማቅረብ አቅቶታል። ገበሬው ኢንቬስት ማድረግ አልቻለም። ለዚህ ነው የእህል የምግባ የዋጋ ግሽበቱ አሳሳቢ ሁኔታ ላይ የሆነውና መንግስትን የሚያስጨንቀው።
ወደ ዐምዴ እንመለስ… ኢትዮጵያ በ10 ዓመት አንዴ የሚደርስባት ድርቅ መጥቶ የዐምዴ ልጆች በአንድ ሄክታሮቻቸው በጣም አነስተኛ መርት ያገኛሉ። ዐምዴ ሰባቱን ሄክታር በሚያአርስበት ጊዜ ድርቅ ቢኖርም የሰባት ሄክታሩ ምርት ብዙ ስለነበር ለድርቅ ጊዜ በቂ የተከማቸ እህል ነበረው። አሁን ግን የዐምዴ ልጆች በአንድ ሄክታር እጅ ወደ አፍ ስለሚኖሩ የአንድ ዓመት ምርታቸው ከቀነሰ በቂ አይኖራቸውም። ስለዚህ ሰባቱም የዐምዴ ልጆችና ቤተሰቦቻቸው ወደ ምግብ እርዳታ ተሸጋሸጉ።
ታሪኩ በዚ ይጠቃለላል፤ የህዝብ ቁጥርን ባልተጠበቀና በኢተፈትሮ ሁኔታ መናር አሁን ያለውን ታላቅ የገጠር ወደ ከተማ ፍልሰት ዝቅተኛ «የሰው አቅም» (human capital) በትለይ የግብርና ሙያ በገጠር ቦታዎች ዝቅተኛ የእርሻ ምርት መጠን ከፍተኛ የእህል የምግባ ዋጋ ግሽበት የምግብ ዋስትና እጥሮትና ረኃብ። ሁሉም ችግሮች ብያንስ በከፊሉ የ1968 የመሬት አዋጁ ውጤቶች።
የዚህ ፖሊሲ ጎጂ ውጤቶች ያልበሰሉ ጸንፈኛ የፖለቲካ ልሂቃን በችኩልነታቸው አገሪቷ ላይ ሊያመጡ የሚችሉትን ጉዳት ያሳያል። ከጽንፈኝነት መካከለኛውን መንገድ መያዝ ይሻላል። የዛሬም ግዥዎቻችን ከዚህና ሌሎች ታሪኮች ተምረው ሌላውን ጸንፈኛ የአገራችን ፖሊሲ የጎሳ አስተዳደርን እንደገና ቢያስቡበት ይሻላል።
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Showing posts with label አክራሪነት. Show all posts
Showing posts with label አክራሪነት. Show all posts
Thursday, 22 March 2018
Tuesday, 4 October 2016
Where the TPLF went wrong
2009/1/23
(Ethiopian calendar)
2016/10/3
(European calendar)
[Note:
An Amharic version of this post will appear sometime!]
A
lot has been written about this over
the past 25 years,
but it doesn't hurt repeating, especially
given
today's political circumstances in Ethiopia.
The TPLF's biggest historical
mistake
was
interpreting its coming to power in 1991 as a full
mandate
from the vast majority of Ethiopians and
assuming
it
meant a complete rejection of everything that preceded it. This
mistaken assumption involved
a typically
modern Ethiopian exercise in black and white or
zero sum thinking.
Basically,
this is how the thought process worked... The Haile Selassie
government fell, not because it failed to make some sensible reforms,
but because it
failed to make all the radical changes demanded of it by the students
movement. The fall of the Dergue government had nothing to do with
the Cold War, a failed Communist economy, or the war with Somalia,
but
because Ethiopia was a prison of nationalities that had to be
liberated. The rise
of the TPLF
had
nothing to do with the end of the Cold War and a bankrupt regime, but
because the TPLF and its ethnic
ideology
best
represented the interests of a majority of Ethiopians. The
TPLF blinded itself to obvious facts in a bid to convince itself of
its monopoly on truth and ability to rule Ethiopia.
Thus,
after
gaining
power, the TPLF, in the form of
the EPRDF, began
a ruling style that involved continually trying to do the radical
and the impossible,
its
hubris deluding it into believing that
it was
special enough to do anything politically.
This
mindset
is what emboldened
the EPRDF to saddle Ethiopia (and itself) with perhaps the most
radical ethnic based constitution in world history. With
a little more maturity,
it would have realized that this constitution was not only unpopular
and
fundamentally at odds with the interests of
a
large
section of the population, but so
radical, untested, and risky that there was a good chance it would in
the future make governing impossible. For
everyone except the EPRDF and other ethnic nationalists, it was clear
that
a more moderate constitution would have easily satisfied
all constituencies, including
ethnic nationalists
and made governing far easier for the EPRDF.
Building
on the constitution, the
EPRDF
embarked on an ethnic
policy that
can only be described as playing
with fire. It
engaged
in
policies (such as official identification by ethnicity) and rhetoric
('reactionaries'
and 'narrow
nationalists')
that emphasized differences among Ethiopians and diminished
commonalities. It thought that it could promote
ethnic nationalism
and at
the same time control ethnic strife, knowing
full well that its ethnic political base, Tigray, was
composed
of a small minority! An
impossibly
delicate formula
if there ever was one. However,
thanks
to various factors, especially the sad state of the Ethiopian
nationalist elite, the EPRDF has managed so
far to survive on this knife's edge.
But
the fundamentals remain wrong, and
this explains today's smoldering dissent.
It's
a political reality that a people
can tolerate far more oppression from their own ethnic group or in a
non-ethnic context than they can from
another ethnic group.
The TPLF knows
this quite well, having leveraged
the
political tool of ethnicity to its fullest during
its liberation struggle. Yet, the EPRDF continued a policy of
promoting ethnic nationalism while real power and
perception of real power, remained
in the hands of the TPLF. This has inevitably
resulted in widespread resentment against the TPLF and Tigray. This
was all predictable from the beginning; there have been ever
increasing signs of it in the past two decades, yet hubris has
prevented the EPRDF from changing course.
Note
that this policy from
the beginning was
the antithesis of what is best for Tigray. A small minority can
flourish in a multi-ethnic society, but not in
a
society where ethnic division and tension dominate, since the
minority is dependent on
migration and integration to prosper. The region of Tigray, like
all the small ethnicities in Ethiopia,
would do best in a
country
that is more united than divided. Yet,
the
ideology of the TPLF (and its big brother EPLF) was so ingrained that
they basically
ignored this danger and continued promoting ethnically divisive
policies.
To
be fair,
the EPRDF
did eventually realize the seriousness of the problem. Part of the
reasons for the full mobilization of party resources towards the
developmental state project
('lemat', for
the masses)
that begin during the
mid part Prime
Minister Meles' tenure was to
mitigate ethnic division.
The
rhetoric of economic development was ramped
up
as a political tool to promote civic
nationalism
– to give all parts of the country something in common to unite
around – and
counter the obvious damage of ethnic nationalism. But of course the
economy cannot by itself bring down ethnic boundaries and
increase civic nationalism.
Inter-ethnic integration, which the EPRDF's
constitution essentially prevents, is the only way to do so.
The
above is just a small list of the radical and reckless policies of
the EPRDF over the past 25 years, which aros a consequence of the
circumstances around its rise to power, including the absence of an
opposing elite power to act as a moderating influence. Now, what does
this history teach us about what is happening today? What is
happening today?
Well,
we continue to hear from hardline EPRDF
leaders
the same old rhetoric about reactionaries and narrow nationalists –
the
same old hubris. But there are moderates in the EPRDF and TPLF who
have long
ago come
to realize the folly in their fundamental assumptions. These
moderates and hardliners are discussing behind closed doors how to
address the current revolt. The moderates are right and sensible, of
course, but what has always handicapped them is external leverage.
They need a strong Ethiopian nationalist movement and elite, the
opposing elite power which I mentioned above,
with power on the ground, that they can count on as a foil for the
hardliners. They need a political partner on the other side, in other
words, so
that they can say to the hardliners, “Look, you've
tried it your way, and now
there is an opposition that your hardline policies cannot dislodge.
It's time for you to step aside and let us negotiate a new
system of governance.”
Unfortunately,
this Ethiopian nationalist movement is not yet there. The
soft and hard ethnic nationalists in Oromia who are against TPLF
domination have been doing their part for years, but not the
Ethiopian nationalists. Now we have the
uprisings in Amhara Region, and
this is
a huge
step
in the right direction, but there is no organization yet. It
is important that these uprisings soon coalesce into a tangible
political movement so that it can work
with
the moderates
in EPRDF
to
find
a way out if its quagmire. Failing this, we have to count on the
EPRDF reforming by itself. It's a tall order for any organization,
especially on with the historical baggage of the TPLF.
Subscribe to:
Posts (Atom)