Monday 1 October 2018

የጎሳ አስተዳደር ጎጂ መሆኑን ሁሉም ፖለቲካ ፓርቲዎች አምነዋል!

የጎሳ አስተዳደር የኢትዮጵያ ግጭት ምንጭ መሆኑ ሁሉም ፖለቲከኞቻችን ልሂቃኖቻችንም እንዳመኑበት እናውቃለን?!

1. እነ ህወሓት ከነ ቀድሞ መሪአቸው መለስ ዜናዊ ደጋግመው በሀገራችን የጎሳ እልቂት እንዳይፈጠር ያስጠነቅቁ ነበር። እንደ «ርዋንዳ» ልንሆን እንችላለን ይሉ ነበር አሁንም ይላሉ።

2. ኦሮሞ ብሄርተኞችም እንዲህ ደጋግመው ጎሳዎች በሰላም እርስ በርስ ተማምነው ተፋቅረው መኖር አለባቸው ብለው ይሰብካሉ። ካልተከባበርን የጎሳ እልቂት ሊመጣ ይችላል ብለው ያስጠነቅቃሉ። የጎሳ ግጭት እና እልቂት አንድ የሀገራችን ዋናው potential ችግር መሆኑን በተደጋጋሚ ይገልጻሉ።

3. የለማ ቡድን ከነ ጠ/ሚ አብይ አህመድም ደጋግሞ የጎሳ አብሮ መኖር አስፈላጊነት እና የጎሳ ግጭት አደጋን ደጋግመው ይቀልጻሉ።

4. የ«ኢትዮጵያዊነት» ጎራውም ደጋግሞ ስለ በጎሳዎች የሚያስፈልገው ፍቅር እና ሰላም ይሰብካል። ይህን «የመጨረሻ» የፖለቲካ እድል ካጣን ወደ ጎሳ እልቂት ልንገባ እንችላለን ይላሉ።

እንሆ በሁሉም ጎራ ያሉት ፖለቲከኞቻችን ለኢትዮጵያን ህልውና ዋና አስጊ ነገር የጎሳ ግጭት እንደሆነ እንደሚያምኑ አሳይተዋል።

ታድያ በጎሳ አስተዳደር (ethnic federalism) እና በጎሳ ብሄርተኝነት ከዚህ በላይ ፍርድ አለ! ሀገራችን የጎሳ ግጭት አደጋ ላይ ናት ከሆነ ምክንያቱ ለ27 ዓመት የነበረን የጎሳ አስተዳደር መዋቅር ነው ማለት ነው! ብያንስ ይህ ጎሳ አስተዳደር አልሰራም ግጭቶችን አባብስዋል ማለት ነው! የጎሳ አስተዳደር የግጭት ምንጭ መሆኑ ሁላችንም አይተነዋል። ማመን ብቻ ነው የቀረን።

በመጨረሻ ማለት የምፈልገው አንዳንድ የጎሳ ብሄርተኞች የጎሳ አስተዳደር ቢቀር ታላቅ ፍርሃት አላቸው። ማንነታችን ይዋጣል ይላሉ። በፍፁም። ሀገራችን ህብረ ባህላዊ ህብረ ቋንቋዊ ነው መሆን ያለበት። ኦሮምኛ በሀገራችን በሙሉ ይነገር ነው የምንለው በኦሮሚያ ብቻ አይነገር። አዲስ አበባም ኦሮሚያም የሁላችንም ነው የምንለው የኦሮሞውች ብቻ አይደለም። ሌላውም ኢትዮጵያ የኦሮሞ ነው ነው የምንለው። ይህ እንዲሆን የሚያስፈልገው ህብረ ባህላዊ/ቋንቋዊ ስርዓት ነው ንጂ የጎሳ የክልል የአጥር አስተዳደር አይደለም።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!