Sunday 11 December 2016

ተሃድሶ

ስለ «ተሃድሶ ኦርቶዶክስ» የሚባለውን ንቅናቄ አንዳንድ ሃሳቦች ለማቅረብ እወደለሁ። በመጀመርያ ትሃድሶ በትክክል ምን እንደሆነ አይታወቅም። በጾም ጊዜ አሳ መብላት አግባብ ነው የሚሉ ተሃድሶ ተብለው ሊሰየሙ ይችላሉ። እንደ ፒያኖ ወይም ኦርጋን አይነት የሙዚቃ መሳርያ ከቤተ ክርስቲያን ውስጥ መተቀም ይቻላል የሚሉም እንደዚሁ ተሃድሶ ተብለው ይሰየማሉ። ከቤተ ክርስቲያን ውስጥ ጫማ ማድረግ ክልክል አይደለም የሚሉትም እንደዚሁ። በድንግል ማርያም አማላጅነት አምነው ግን በስብከታቸው ስለሷ ብዙ የማይናገሩ ተሃድሶ ይባላሉ። ቅድስት ድንግል ማርያምን እንደ ክርስቶስ የሚያመልኩ አሉና ይህ መሆን የለበትም የሚሉም ሳይገባ ተሃድሶ ይባላሉ። የጋራ ጾም አያስፈልጉም የሚሉም ተሃድሶ ይባላሉ። በቅዱሳን አማላጅነት አናምንም የሚሉም ተሃድሶ ይባላሉ። ወዘተ። «ተሃድሶ» የሚባለው ስያሜ በተለያዩ አግባብ ያላቸውም የሌላቸውም ምክንያቶች እንጠቀማለን።

ከዚህ ጽሁፍ ግን ተሃድሶ ስል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን እምነትንም ስርዓትንም መቀየር - በትንሹም በትልቁም - የሚፈልግ አቋምን ነው። ጫማ ከቤተ ክርስቲያን እናድረግ እስከ የቅዱሳን አማላጅነት የለም የሚሉት። እነዚህ እጅግ የተለያዩ አቋሞች እንደሆኑ እራዳለሁ! ጫማ አለማድረግ የ«ትንሽ» ስረዓት ጉዳይ ነው - የእምነት ጉዳይ ቢሆን ኖሮ ከግብጽ በተ ክርስቲያን ጋር እንለያይ ነበር። ትንሽ ስረዓት ቢሆንም ምክነያት አለው - ይህን ስርዓት ለመቀየር የሚጓጓው መንፈስ በቅዱሳን አማላጅነት አላምንም ከሚለው መንፈስ በተወሰነ ደረጃ ግንኙነት አለው። ላስረዳ...

የኦርቶዶክስ ክርስቲያን እምነት በሶስት መስፈርቶች ሊፈተሽ ይችላል። እምነቱ ከጥንት ጅምሮ ያለ ነው፤ እምነቱ በሁሉም ቦታ ይገኝ ነበር፤ እምነቱ በሁሉም ይታመን ነበር። እነዚህ መስፈርቶች ከክርስቶስ ቀጥሎ ከሃዋሪያቶቹ የወረስነውን እምነት አለማጠፍም አለ«ማደስ»ም ከመንፈቅ ትቆጥበን እምነታችንን እንደተሰጠን ይዘን እንድንጠብቅ የሚገልጹ ናቸው።

የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሃሳብ እንደዚህ ነው። አዲስ ነገርን - ትንሽም ትልቅም - በቀላሉ አታስተናግድም። ቅዱስ አታናሲዮስ መጽሃፍ ቅዱስ የትኞቹን መጸሃፍት እንደሚያካትት ሲናገሩ አዲስ ነገር ነበር። መጸሃፍ ቅዱስ እነዚህ መጸሃፍቶች ናቸው ተብሎ ተሰይሞ አያውቅም ነበር። ታድያ ይህ አዲስ ነገር ነበር ወይ? በፍጹም፤ ቅዱስ አታናሲዮስ የነበረ ሁሉም በሁሉም ቦታ ከመጀመርያ የሚያምኑበትን ነው ያረጋገጡት። ሌሎች መጸሃፍቶችን የተተውበት ምክንያትም የቤተ ክርስቲያን እረኞች ህዝቡ እነዚህን መጸሃፍት በተሳሳተ መልኩ እያነበበ ወደ ኑፋቄ ሲገባ አይተው ነው።

የቤተ ክርስቲያን ስረዓትም በተመሳሳይ ቢጠበቅም ትንሽ ላላ ይላል። ስረዓትን «ታናሽ»ና «ታላቅ» ብለን መከፋፈል ይቻላል ግን ይህ ቅፍፍል ወጥ አይደለም - ታናሽና ታላቅ ዳሮች ሆነው ከመካከል ብዙ አሉ። ታናሽ ስረዓቶች ለምሳሌ ጫማ አለማድረግ፤ ታቦት፤ ወዘተ ከኛ ጋር አንድ ከሆነችው የግብጽ ቤተ ክርስቲያን የሉም። እነሱም የራሳቸው እኛ የሌለን ስርዓቶች አሏቸው። ሆኖም ስረዓትም በቀላሉ አይቀየረም። እንደ እምነት ያህል ባይሆንም ከእምነቱ ጋር እጅግ የተያያዘ ስለሆነ መቀየሩ እጅግ አስፈላጊ መሆን አለበት።

ለምሳሌ የቅዳሴአችን ዜማ የተጻፈው በ6ኛው ክፍለ ዘመን በቅዱስ ያሬድ ነው። ከዛ በፊት የነበረው ዜማ የተለየ ነበር ወይም ዜማ አልነበረም። የቅዳሴ ዜማ የስረዓት ለውጥ በቅዱስ ያሬድ ጊዜ ተካሄደ። ይህ የሚያሳየው ስርዓት መቀየር እንደሚቻል ነው። ግን ከዛ በኋላ እስካሁን ለ15 ክፍለ ዘመን አልተቀየረም። ይህ ደግሞ የሚያሳየው ስረዓት መቀየር ቢቻልም (እንደ ስረዓቱ አይነት) እጅግ በጣም ጥቂት ጊዜ ነው የሚቀየረው። የኦርቶዶክስ አስተሳሰብ ለውጥ ስለማይወድና ጥንቱን ስለሚያስቀድም።

ስረዓት ይቀየር ሲባል ለምን ብለን እራሳችንን መጠየቅ አለብን። ኦርቶዶክሳዊ ለውጥ የሚከላከለው አንዱ ታላቅ ምክነያት አብዛኛው ጊዜ ለውጥ የሚፈለገው ለማይሆን ምክነያት ስለሆነ ነው። እንደዚህ አይነት ምክነያቶች ምሳሌዎች እንደ የመንፈቅ አስተሳሰብ፤ ፖለቲካ ወይም የስልጣን ሹኩቻ፤ ፍርሃት አይነቱ ናቸው።

በዛሬው ዘመን - «ዘመናዊነት» ግዥ ርዕዮተ ዓለም በሆነበት ዘመን - የስረዓት ለውጥ (የእምነትም ለውጥ) የሚገፋፋው ከዘመኑ ጋር አብሮ ለመሄድ ነው። ቅዱስ ያሬድን ያነሳሳቸው ጾም ጸሎትና የዳዊት መዝሙርን በመድገም እግዚአብሔርን ይበልጥ ለማመስገን ፈልገው ነው። በዛሬው ዘመን ግን ብንወድም ባንወድም ብናውቀውም ባናውቀም ከዘመኑ ጋር አብሮ የመሄድ ሃሳብ ተጽእኖ ያሳድርብናል ሳናውቀውም ይገፋፋናል። በዚህ ምክነያት ከበፊት ዘመናት - ከቅዱስ ያሬድም - ይበልት ጥንቃቄ ማድረግ አለብን። ምንም አይነት ስርዓትን እንኳን ለመቀየር በጥያቄ ምልክት ውስጥም ማድረግ የለብንም።

ብለላው ቋንቋ እላይ የጠቀኩትን የቤተ ክርስቲያናችንን አስተሳሰብን መርሳት የለብንም - ለውጥን በታቻለው ምከላከልንና መፈተሽን።

ይህ ብዬ ወደ ተሃድሶ እንመለስ። በቤተ ክርስቲያናችን ስንት የሚሰራ ስራ እያለ ለምንድነው ማደስ የሚታሰበው። ንስሃ ገብተናልን? እግዚአብሔርን በሙሉ ልባችን እንድወደዋለን? ያለንን በሙሉ እንሰጠዋለን? በሰው ላይ አንፈርድምን? ገና እንድወድቃለን እንነሳለን መውደቃችን እጅግ ቢበዛም። እረኞቻችን ታድያ ድሮም እንደነበራቸው ዛሬም እንድንነሳና ለክርስቶስ ለመቅረብ ያለንን ፍላጎት ለማዳበር ብዙ ስራ አላቸው። ይህ ሁሉ ስራ እያለ ስለማደስ ማሰብ ምን አስፈለገ?

እንዳልኩት የዘመኑ ርዕዮተ አለም በፍጹም ሳናውቀው ከባድ ተእጽኖ ያደርግብናል። ካቶሊኩንና ፕሮቴስታንቱን እያየን ሳናውቀው በአፋችን እንደተሳሳቱ እየተናገርንም በልባችን አንዳንድ ነገሮቻቸው በነበር ብለን እንመኛለን። ስነ ስረዓት፤ ንጽህና፤ ፍልስፍና፤ ሃብት፤ ብልጠት፤ ስነ መግባር ወዘተ። ቤተ ክርስቲያናችን ትታደስ ስንልም እንደነዚህ ትንሽ ትሁን ማለታችን ነው። ምንጩ ይህ ነው አደጋውም ይህ ነው።

ታድያ እንደዚህ ስንል ሌላው አብዛኞቻችን በተለይ ካህናቶቻችን በተለይ እናድስ የሚሉት የማናውቀው ነገር ምህ ያህል ካቶሊኩና ፕሮቴስታንቱ - በተለይ ፕሮቴስታንቱ - ችግር ውስጥ እንዳለ ነው። «ፔንጤ» የምንላቸው በትክክሉ «ኤቫንጄሊካል» የሚባሉት ለምሳሌ ባለፉት 50 ዓመታት ኢትዮጵያ ውስጥ ቢያድጉም ባሁኑ ጊዜ በምንጫቸው ሃገር አሜሪካ እየመነመኑና ታላቅ አደጋ ላይ ናቸው። መሰረታው እምነታቸው የግል ስለሆነ - ቤተ ክርስቲያን ሳይሆን ግለ ሰብ ነው ሃይማኖቱን ብቻውን ከመንፈስ ቅዱስ ጋር እይሚያውቀው ብለው ስለተነሱ - አሁን እስከ 30,000 አይነት ክፍፍሎች አላቸው። ስንቶቻችን ነን ይህን የምናውቀው። የቆዩት ፕሮቴስታንቶች (በኢንግሊዘኛ «ሜይንላይን» ይባላሉ) እንደ አንግሊካን ደግሞ ከሁሉም ክርስቲያን ከሚባሉት የመነመኑና ምእመናን ያጡ ናቸው። ይህን ስንቶቻችን ነው የምናውቀው? አሜሪካን ሀገር ትልቁ የክርስቲያን ፍልሰት ከፕሮቴስታንት ወደ ኦርቶዶክስ እንደሆነ ስንቶቻችን ነን የምናውቀው? ባንዳን የኦርቶዶክስ ሃገረ ስክበቶች አብዛኛ ካህናት ከፕሮቴስታንትነት ውደ ኦርቶዶክስ የተቀየሩ እንደሆነ ስንቶቻችን እናውቃለን? ኦርቶዶክእነሱ ወደ ኦርቶዶክስ ይመጣሉ እኛ ደግሞ ወደነሱ መሄ እንፈልጋለን!

ክሃገራችን ውጭ ብንመለከት ይበጀናል። ውጭ ሃገር ያለነው - በተለይ ካህናት - ስራችን ብለን ዙርያችን እንመልከት። የክርስትና ድርጅቶች አካሄድን እንመልከት። ዛሬ ከምንጩ አሜሪካ እየጠፋ ያለው ፕሮቴስታንት ሃይማኖት ነገ ኢትዮጵያ በዚሁኑ ምክነያት እንደሚጠፋ እንወቅ። ባለፉት ዓመታት በሃገራችን የተከናወነው የኦርቶዶክስ ወደ ጴንጤ ፍልስትን ብቻ አንይ። ሃገራችን ውስጥ እራሱ እነዚህ ድጅጅቶች እንዴት ቀንበቀን እየተፈረካከሱ እንደሆነና እየተባዙ እንደሆነ እንይ።

ምን አልባት ዞር ዞር ብለን ይህን ሁሉ ካየን የፕሮቴስታንት አደጋም የዘመኑ ፈተናንም ልንረዳው እንችላለን። ይህን ተረዳነው ማለት ደግሞ እንታደስ የሚለው ስሜት ይቀንስልናል። አስተያየታችንን ያስተካክላል ሚዛናዊም ያደርጋል።

Wednesday 7 December 2016

የተማረ ገደለን

የኢትዮጵያ ወዳጅ ዶናልድ ሌቪን (ነፍሳቸውን ይማረው) ከ50 ዓመታት በፊት ጅምሮ ባህልንና ማንነትን የማያከብርና የሚክድ ህብረተሰባዊ ለውጥ አገር አፍራሽ ነው እያሉ ኢትዮጵያዊያንን ያስጠነቅቁ ነበር። ኃይለ ሥላሴ ወደ ምዕራብ አገር የላኳቸው ተማሪዎች በኢባህላዊ የሆነ  ከራስ ጋር የሚያጣላ ርዕዮት ዓለም ተነክረው ወደ አገራቸው ሲመለሱ በአስተሳሰባቸው ሰውዉን አስተንግጠዋል። አቶ ዶናልድ ሌቪን አንድ ያጋጠማቸውን እንደዚህ አስታወሱ ነበር፤ አንዱን «የተማረ» ምሁራንን እንደዚህ ብለው ጠየቁት «እንደምትመኘው የሶሽያሊስት አብዮት ቢካሄድ በሚሊዮን የሚቆጠር ህዝብ እንደሚሞቱ ታውቃለህን?» ይህ የተማረ ምህር «በ10 ሚሊዮንም ቢሞቱ ይህን ርዕዮት ዓለምን ለማድረስ ስለሆነ ያዋጣል» ብሎ መለሰላቸው። ከራስ ባህል፤ ወግ፤ ትውፊት፤ ምንጭና ማንነት መራቅ እንደዚህ አይነቱን ቅዠታዊ አስተሳሰብ ነው የሚያመጣው።

ዛሬም ይህ አይነት የቀለም ትምህርት አምልኮ ለኢትዮጵያ ዋናው አጥቂና ጠላት ነው። የምዕራብ ዘመናዊ የቀለም ትምህርት በአገራችን እንደ ጣዎት እንደሚመለክ የሚገልጸው በኃይለ ሥላሴ ዘመን የተሰየመው አባባል «የተማረ ይግደለኝ» ነው። ይህ ዛሬም በኢትዮጵያዊያን ጭንቅላት ይንጸባረቃል። ፖለቲካችንን ካየን አብዛኛው የሚንጸባረቁት ሃሳቦችና አስተያየቶች ከኢትዮጵያ ውጭ የመነጩ ናቸው። የኛ ምሁራኖች እነዚህ ሃሳቦችን እየሰገዱላቸው ኢትዮጵያን ወደ እኒዝህ ርዕዮት አለምን ማስተካከል ይፈልጋሉ። ቢያንስ መደረግ የነበረበት እነዚህን ርዕዮት ዓለሞችን ለኢትዮጵያ እንዲሆኑ ማስተካከል።

ይህ አቋሜን የሚደግፉ አንዳንድ ማስረጃዎች እንመልከት። በመጀምርያ ወደ ኋላ ሄደን የኃይለ ሥላሴ መንግስትን ተመልስን እንመልከት። የዛን ጊዜ ውጤቶች ዛሬ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ስለሆነ። በሳቸው መንግስት ዘመነ የምዕራብ «ዘመናዊ» ትምህርት በኢትዮጵያ ውስጥ ተስፋፋ። ተማሪዎች በሞላ ጎደል አለምንም መበረዝ ቀጥታ የምዕራብ ትምህርት ነበር የሚማሩት። ስለአገራቸው ጥቂት ውይም ምንም ነገር ሳይማሩ ይመረቁ ነበር። ለምሳሌ ስለ ዓለም ዙርያ መልክአምድር ተምረው ስለኢትዮጵያ መልክአምድር ምንም አያቁም ነበር! ስለራሳቸው ታሪክ፤ ትውፊት፤ ባህልና ሃይማንቶ አይማሩም ነበር። ሳይታወቅ ግራ የገባው ከፊል ኢትዮጵያዊ ከፊል ፈረንጅ የሆነ ትውልድ ተወለደ። የዝቅተኛ መንፈስ ያደረበት ትውለድ ተፈጠሪ። ሳያውቀው እራሱን የሚንቅና የሚጠላም ትውልድ ተፈጠረ። ግን ከዚህ ትውልድ ልጆች መካከል ግማሾቹ ኢትዮጵያዊነታቸው ቢሸረሸርም ለኃይለ ሥላሴ ታማኝ ነበሩ በሳቸውም «የዘመናዊ ስልጣኔ እቅድ» ይስማሙ ነበር። ሌሎቻቸው ግን እንኳን ታማኝ ለመሆን ጠላት ሆነው ተገኙ። አገሪቷን ያስከወሰ አብዮትን አስነሱ። ሁላችንም እንደምናውቀው ይህ አብዮት በአገራችን አስፈላጊ የሆኑ ለውጦችና መስተካከሎች ከማምጣት ፋንታ በጸረ ኢትዮጵያ የሆነውን በምዕራባዊያኑ ርዕዮት ዓለም በኮምዩኒዝም ስር አገራችንን እንድትወድቅ አደረጋት።

በደርግ ዘመነ መንግስት ደግሞ አብዛኛው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ንቅናቀዎች የጸረ ኢትዮጵያ አቋምና ርዕዮት ዓለም ይዘው ነበር የሚራመዱት። ጸረ ሃይማኖት ነበሩ። ጸረ ባህልና ጸረ ትውፊት ነበሩ። እርግጥ በዛን ዘመን ሙዚቃ ጭፈራ ወዘተ «ትስፋፍቷል»። ግን የተስፋፋው በምዕራባዊያን አመለካከት ዘንድ ነው - ስር የሰደደ የማንነት የሆነ ሳይሆን እንደ ልብስ ከላይ የሚለበስ ወይም እንደ ቴአትር የሚታይ ነበር። በመጀመርያ ኮምዩኒስት ነን፤ ግን እስክስታ የምንጨፍር ኮምዩኒስት ነን! በጠቅላላ አብዛኛው ፖለቲከኞችና ምሁራንም የኢትዮጵያ ማንነት መቀየር አለበት ብለው የሚያምኑ ነበሩ።

በኢህአዴግ ዘመን ይህ ወደ ውጫዊ አመለካከት ማድላት ወደ ጸንፍ ደረሰ። በሶሺአሊዝም የተሞላ በጎሳ የተመሰረተ ጸንፈኛ ህገ መንግስት በኢትዮጵያ ተጫነባት። ይህ ክስተት ከኢትዮጵያዊ «የተማረ» ኃይል በተደጋጋሚ የሚታይ አንድ ጸባይን በደምብ ያብራራል። ይህ ጸባይ ጸንፈኝነት ነው። የኢትዮጵያ መሰረታዊ ችግር የብሄር እኩልነት ነው ብሎ ቢታመንም ቋንቋ፤ ባህል፤ መልክአ ምድር፤ ጎሳም የሚያካተት ግን ለዘብተኛ የሆነ ህገ መንግስት ሊመሰረት ይቻል ነበር። ግን ያኔ የነበሩት ኃይሎች ጸንፍ ካልያዝን አሉ! በምድረ ዓለም ታይቶ የማይታውቅ አይነት ህገ መንግስት - ከሶሺያሊስት በላይ ሶሺያሊስት የሚያሰኝ ህገ መንግስት ካልደነገግን አሉ። ጭራሽ ከደቡብ አፍሪካ በቀር የሌለውን ጎሳ በመታወቅያ ጀመሩ! ሁላችንም እንደምናውቀው እስካሁን ይህ መርዝ ነው እያሳመመን ያለው።

ይህ ሁሉ ሆኖ የአገራችን ገዥም ተቃዋሚም ፖለቲከኞችና ምሁራን አሁንም ውጫዊ በተለይ ምእራባዊ አመለካከት ነው ያላቸው። ገዝ ፓርቲ «ዘመናዊነት» የሚባለው አመለካከት ነው ያለው። ሃይማኖት ኋላ ቀር ነው። እግዚአብሔር ሳይሆን ሰው ነው የዓለም ቁንጮ። ባህል፤ ትውፊትና ወግ ውሸት ናቸው። ህዝብ ባህልን ትቶ ወደዚህ አይህነት አመለካከት እስኪ ገባ ድረስ እንደ ያላደገ ህጻን ነውና እኛ ስልጣን ተቆጣጥረን ልናሳድገው ይገባል። ካደገ በኋላ፤ ማለት እንደኛ የ«ዘመናዊ» አስተሳሰብ ካደረበት በኋላ - ስልጣናችንን እንለቃለን። በሌላ አባባል ኢትዮጵያዊነቱን አርግፎ ከኛ ይበልጥ «ያደጉትንና የሰለጠኑትን» ምእራባዊያን ከመሰለ በኋላ ነው ሰው የሚሆነው። ይህ ራስን ማንነትን መጥላት ካልሆነ ምንድነው?

ተቃዋሚው ደግሞ እንደ አሜሪካ ወይም እንደ አውሮፓ እንሁን ነው! (በጅምላ እየተናገርኩኝ ስለሆነ ይቅርታ።) የኢትዮጵያዊነት ራዕይ የለውም። እርግጥ አንዳንድ ጥሩ የሆነ ሃሳቦች እንደ ገዳ አሰራር አጥንቶ በተወሰነ መጠቅም ተነስተዋል። አንዳንዱም ደፋር የንጉሳዊ አስተዳደር (በወግ ደረጃ ብቻ ቢሆንም) ይመለስ የሚሉ አሉ። እነዚህ ሃሳቦች በርካታ ውይይትና ክትትል ያስፈልጋቸዋል ከነዚህ አይነቱ ባህላዊ መንገድ ነውና የአገራችን ውበት የሚመለሰው።

በብዙሃኑ ደረጃ ደግሞ ቤተሰብ ልጁን የምእራባዊ ባህልና ቋንቋ ለማስተማር ይሯሯጣል! ለልጁ ከቀለም ትህምሕርት በላይ በዚህ ዓለም ምንም የለም የሚል መልክት ነው ደጋግሞ የሚያስተላልፍለው። ልጁም የቀለም ትምሕርትን ጣኦት አድርጎታል። ከዛ በኋላ የልጁ አኗኗር ግራ የገባው ሲሆን፤ ትምሕርትና ስራ አለው ግን በሌላው ንሩው ያልተረገጋ መሰረተ ቢስ የሆነ ሲሆን - ወላጅ ግራ ይገባዋል። የዛሬው ትውልድ እንደዚህ ነው እንደዛ ነው ብሎ ያማርራል። ታድያ ባህሉን ያልወረሰ ሰው ሁልጊዜ ኑሮው እንደሚናወጥ አናውቅምን?

በትህትና ባይመስልም ግን የትህትና ምክሬ እንደዚህ ነው። በመጀመርያ የዘመናዊ ትምህርት ምን ያህል ጸረ ባህል፤ ጸረ ትውፊት፤ ጸረ ማንነት፤ ጸረ ኢትዮጵያ እንደሆነ እንረዳ። ሞያ፤ ሳየንስና ቴክኖሎጊ ችግር የለውም ከጥንትም የነበሩ ዘርፎች ናችሀው ከምንምም ጋር አይጋጭም። አደገኛው ግን «ዘመናዊነት» የሚባለው ርዕዮት ዓለም ነው። ቅድም የጠቀስኩት ጸረ ሃይማኖትና ጸረ ባህል የሆነ አስተሳሰብን እንደ መርፌ ይወጋል። ይህን አውቀን ስንዴውን ከንክርዳዱን መለየት አለብን። ጠቃሚውን ትምህርት እየተማርን ጎጂውን እራሳችንን እንድንጠላ የሚያደርገውን ለይተን አውቀን እንተው። የምንማረውን በባህልና ሃይማኖታችን መነጽር ወይም አመለካከት እንማረው። ለልጆቻችንም እንደዚሁ።

ይህ ነው ምክሬ። ዶናልድ ሌቪን እንዳሉት - ክሁሉ ጥቅሳቸው ይህን ነው እጅግ የምወደው - "The vitality of a people springs from feeling at home in its culture and from a sense of kinship with its past. The negation of all those sentiments acquired in childhood leaves man adrift, a prey to random images and destructive impulses…" ከኔ የምትሻሉት ተርጉሙት!

Sunday 4 December 2016

መደጋገም አለመሻሻል

እንደጠበኩት የ2008-2009 የህዝብ ዐመፅ ተረጋግቷል። የተረጋጋው መንግስት የአስሸኳይ አዋጅ ስላወጀ፤ የማይሸነፍ ኃይልና አቅም ስላለው፤ ህዝቡ አቅም ስለሌለው፤ ህዝቡ ስለተከፋፈለ፤ አብዛኛው ህዝብ ኢህአዴግን ስለሚደግፍ፤ ወዘተ አይደለም። ዐመፁ የመነመነው ህዝቡ በተለይም የፖለቲካ መደቡ የኢትዮጵያ የመንገስት አገዛዝን ለመቀየር የሚያስፈልጉ ቀድመ ዝግጅቶች ስላላሟሉ ነው።

እነዚህ ቀድመ ዝግጅቶች ምንድናቸው? አንድ አገዛዝን ለመቀየር በመጀመርያ አማራጭ መቅረብ አለበት። አማራች የፖለቲካ ራዕይ ወይም ሰፊ አመለካከት፤ ርዕዮት ዓለም፤ መዋቅርና ኃይል ያስፈለጋል። ከዛ በኋላ ነው ህዝቡ በሰላም ወይም በዐመፅ፤ በቀስታ ወይም (ቢቀርብን ይሻላልንጂ) በአብዮት፤ ካሉት የመንግስት አስተዳደር አማራቾች የሚመርጠው።

ላለፉት 25 ዓመታት ግን የኢህአዴግ ተቃዋሚዎች፤ ማለት ህዝብም የፖለቲካ መደቡም፤ እነደዚህ አይነት የፖለቲካ አማራጭ ማዘጋጀት አልቻለም። በመጀመርያ የፖለቲካ አመለካከቱም ርዕዮት ዓለሙም የተበታተነና ያልሰከነ ነው። የተለያዩ አመለካከቶች አሉ ከጎሰኝነት እስከ አንድነትና ሌሎች ከመካከል። ይህ ልዩነቶች ተገቢ ቢሆንም እነዚህ አመለካከቶች እንደሆነው ሆኖ ለመስማማት ተስማምተው አብሮ መስራት አልቻሉም። ይባስ ተመሳሳይ የፖለቲካ አስተያየት ያላቸው እርስ በርስ በተራ ምክነያቶች እየተጣሉ አይስማሙም። በኦሮሞ ብሄርተኞች መካከል ወይም በኢትዮጵያ ብሄርቶኞች ወይም የአንድነት ፖለቲካ ደጋፊዎች መካከል ያለው አለመስማማትና አብሮ አለመስራት ነው ዋናው ችግር። ለመድገም ያህል በጎሳና በአንድነት አመለካከት ያለው አለመስማማት አደለም ትሉቁ ችግራችን። ዋናው ችግራችን አንድ አመለካከት ያላቸው ወገኖች ትስማምተው መስራት አለመቻላችን ነው። የኢትዮጵያ የፖለቲካ ችግር በአንድ አረፍተ ነገር ለመቋጨት ከተፈለገ ይህ ነው። በዚህ ምክነያት የኢህአዴግ ተቃዋሚ አንድ የሆነ ወይም ሁሉን አቀፍ የሆነ የፖለቲካ አማራጭ አመለካከትና ርዕዮት ዓለም ለ25 ዓመት መገንባት አልቻለም።

አንድ የአማራጭ አመለካከት ከሌለ ደግሞ መዋቅር ሊኖር አይችልምና ለዚህም እስከ ዛሬ አማራጭ መዋቅር የለም። ሻእቢያና ህወሃት በደርግ ጊዜ የነበራቸውን መዋቀር እናስታውስ። የዘመኑ ተቃዋሚ እነደዚህ አይነት ነገር በኢትዮጵያ ውስጥም ውጭም የለውም። እነ ሻእቢያ በጄታቸው በሚሊዮን ብር ሲቆጠር የዛሬ የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች በሺዎች ይቆጠራሉ! እንደዚህ አይነት መዋቅሮች ምን ብለው ነው መንግስት የሚወርሱት?

መዋቅር ስለሌለ ደግሞ ኃይል የለም። የተቃዋሚ የህዝቡም ኃይል በሺዎች ነው የሚቆጠረው። በፊሊፒንስ ሀገር የህዝብ አብዮት ሲነሳ ህዝቡ በሚሊኦን ነበር ወደ ሰልፍ የወጣው። አንድ ጥይት ሳይተኮስ  መንግስት በሰላም ተቀየረ። ኢትዮጵያ ግን ውስን ቁጥር ነው ሰልፍ የሚወጣው። የተቃዋሚ የጦርም ኃይል ኢሚንት ነው። ረብሻ ለመፍጠር ያህል አቅም ቢኖራቸው ነውንጂ በዚህ ሁኔታ ከዛ አልፎ የተም አይደርስም።

እሺ፤ የፖለቲካ አመለካከት ወይም ርዕዮት ዓለም የለም። መዋቅርም የለም። ኃይልም የለም። ታድያ ምንድነው የሚጠበቀው? ከ25 ዓመታት በኋላ ተቃዋሚው ጎራ በሞላ ጎደል ምንም መሻሻል አላሳይምም የበፊቱንም ስህተቶች ደጋግሞ ይደጋግማል።

የዛሬውን የምሁራንና የተቃዋሚ መሪዎች ውይይት ሲታይ ከ25 ዓመት በፊት ከነበረው ብዙ ለውጥ የለውም። ምናልባትም ወደ ኋላ ሄደናል። 25 ዓመት በፊት የታተመ ኢትዮጵያን ሪቭዩ መጽየትን ብንመለከት ያው ዛሬም የምንወያይበት ጉዳዮች ያኔም (ያኔ በተሻለ ቋንቋና ብስለት) እየተወያየን ነበር። በውይዩቱ ውይም በመግባባቱ ምንም ለውጥ አይታይም!

ገጣሚው አቶ ፍቅሬ ቶሎሳ 25 ዓመት በፊት በገጣሚ አቅሙ ስለኦሮሞና አማራ ግንኙነት የሚገጥሙትን ዛሬም ይጽፋሉ ያኔም ዛሬም በቂ የተረዳቸው ስለሌለ። አንድ ኦሮሞ ብሄርተኛ ኢትዮጵያ መገነጣጠል አለባት ሲሉ ጉዳዩን እንደተለመደ አድርጎ በበሰለና በሰከነ መንገድ ተመልክቶ የሚገባውን መልስ ከመስጠት ልክ እንደ 25 ዓመት በፊት በድንጋጤ - ይህ ያላሰብነው የጎሳ ብሄርተኝነት እውነት ሊመጣብን ነው እንጂ እያልን - የተበታተነና መላ የሌለው መልስ መለስን ፍረሃትንም አንጸባረቅን። ትናንሽ የስራ አለመግባባት ሲያጋጥማቸው «የአማራ ንቅናቄ ደጋፊዎች» በፖለቲካ አመለካከት የሚጋሩትን ግንቦት 7 ደግሞም ኢሳትን መሳደብ ጀመሩ ልክንደ 25 ዓመት የአንድነት ደጋፊዎች ከላይ የጠቀስኩትን ታላቅ ኢትዮጵያን ሪቪዩ መጽየት ተጣልተው እንዳፈረሱት። ለማስታውስ ያህል ከዛም በኋላ መላው ኢትዮጵያ ወይም መላው አማራ ትብሎ ኃይለኛ ፍጅት ተቅሄደ። ቀጥሎ የቅንጅት ፍጅቶች፤ የአንድነት ፓርቲ ፍጅት፤ ዛሬም የሰማያዊ ፓርቲ ፍጅት! እንሆ ከ25 ዓመት በኋላ ታሪክ እየተደገመ ነው!

መፍትሄው ምንድነው? በዋና ጉዳዩ ላይ ስራ መስራት ነው። የሰው ልጅ ችግር እንዳለውና ማስተካከል ካልፈለገ ለመሸሽ ያህል ሌሎች ላይ ወይም በሌላ ጉዳይ ያተኩራል። ዋናው ችግሩ እንዳለ ወይም እየባሰ ይቀጥላልም። እስካሁን የኢትዮጵያ የተቃዋሚ ጎራ  እንደዚህ ነን። በዋናው ጉዳይ ስራ ከመስራት መጣላትና መናቆር ላይ ቆይተናል። ግን ወደ ግብ የምሄድ ፍላጎት ካለን እነዛን አሳሳች ተግባሮችን ትተን ወደ ስራ መግባት አለብን።

እነዚህ ስራዎች ምንድናቸው? የፖለቲካ አመለካከትን ተወያይቶ ቀስ ብሎ ጨምቆ ሰፊ ግን አንድ የሆነ የአገዛዝ አመለካከት አዘጋጅቶ በዚ ላይ መስማማት። ይህ ስምምነት መዋቅር ለመዘርጋት ዋና ቀድመ ዝግጅት ነው። መተዋወቅ፤ መግባባት፤ መስማማትና አንድ ልብ መሆን ግድ ናቸው። ይህ ደግሞ ረጅም ጊዜ የሚወስድ ሂደት ነው። በቅርቡ ባደረጉት ቃለ ምልልስ አቶ ጁኔዲ ሳዶ በአንድ ወቅት ኦኸድድ የ20 የሙሉ ቀን ውይይት ከወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ጋር እንዳካሄደ ተናግረዋል። ይህ ረጅም ውይይት በተዋቀረ ድርጅት ውስጥ ነበርና አዲስ ድርጅት ወይም ስብስብ ምን ያህል ውይይት እንደሚያስፈልገው እናስብ።

አንድ ሰፊ ግን አስማሚ አመለካከት ላይ ከተደረሰ በኋላ መዋቅር መዘርጋት ነው የሚቀጥለው እርምጃ። ይህ በተነጻጻሪ ቀላሉ እርምጃ ነው የሚሆነው። አንድ ልብ የሆነ ሰው እጅግ ስኬታማ ይሆናልና። ይህ መዋቅር አንድ ድርጅት ብቻ ሊሆን አይገባም። የተለያዩ መዋቅሮች - የታወቁም የህቡ - በተለያዩ የህብረተሰብ ዘርፍ ይቋቋማሉ። በርካታ ሰዎችም ዛሬ ባሉት የሀገሪቱ መዋቅሮች ከነ ኢህአዴግ ውስጥ ሰተት ብሎው ገብተው የራሳቸውን የሚያምኑበትን አቋም በድብቅ ያራምዳሉ።

ይህ መደራጀት እይጠነከረ ሲቀጥል በራሱ ትልቅ ኃይል ዪሆናል። በዚህ ወቅት የጠመንጃ ኃይል አያስፈልግም! እያንዳኑ የሀገሪቷ ዘርፍ በነዚህ የተቃዋሚው ጎራ ሰዎች ሞልቶ ይገኛልና ትንሿ እንቅስቃሴ አገዛዙን በሰላም ግልብጥ ያረገዋል። የነባር መንግስቱ ተራም ቀንደኛም ባለስልጣኖች በግድ ቢሆንም በተቃዋሚው ብስለት ምክንያት አለ ፍርሃት ለውጡን ይቀበላሉ።

በኔ እምነት የኢትዮጵያ የፖለቲካ መሻሻል ቀደም ተከተል እንዲህ ነው መሆን ያለበት። የተሻለ ምርጫ የለም። ግን ከ25 ዓመት በኋላ አሁንም በተወሰነ ደረጃ ገና አንደኛ እርምጃው ላይ ነን። ስራችንን እንጀምር።

Tuesday 8 November 2016

የሲኖዶሱ ጉዳይ በ2009

2009/2/29 .. (2016/11/8)

(pdf)

እንደሚታወቀው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያናችን ሁለት የተወጋገዙ ሲኖዶሶች አላት፤ በኢትዮጵያ ያለው ሲኖዶስና ስደተኛው ሲኖዶስ። ይህ ሁኔታ የተፈጠረው ኢህአዴግ ስልጣን ሲይዝ የቤተ ክርስቲያናችን ፓትሪያርክ አቡነ መርቆርዮስ በመሰደዳቸው ነው። ስለ መሰደዳቸው ሁኔታ በዛን ጊዜ ጠቅላይ ሚኒስቴር የነበሩት አቶ ታምራት ላይኔ ከመንበር እንዲወርዱ ያዘዝኩት እኔ ነኝ ብለው እንደመሰከሩ ይታወሳል። ምንም ቢሆን በአቡነ መርቆርዮስ መሰደድና በአቡነ ጳውሎስ መሾም መካከል ጳጳሳቱ የመንግስት ጫና አድሮባቸው እንደነበረ ግልጽ ነው። ሆኖም መንግስት በቤተ ክርስቲያን ላይ ጫና ሲያደርግ ይህ የመጀመርያ ጊዜ አልነበረም። በደርግ ጊዜም እንዲሁ ነበር፤ በኃይለ ሥላሴም፤ ከዛም በፊትም በነግስታቱ ዘመን የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ጳጳሳቶችዋ ይህ ፈተና ሁልጊዜ ዪደርስባቸው ነበር። ሆኖም የዛሬው ክፍፍል ምንጭ ይሄው የመንግስት ጫና በሲኖዶሱ ላይ በመሆኑ ነው።

ታድያ መፍትሄው ምንድነው? እንደሚታወሰው በሲኖዶሶቹ መካከል እርቅ ለማምጣት በተለያየ ጊዜ ግለሰቦችም፤ ሽማግሌዎችም፤ እንዲሁም የቤተ ክርስቲያን ሃላፊዎች ሞክረዋል። አንዳንዱም ሙከራ ጥሩና ያልተጠበቀ የማቀራረብ ውጤቶችን አሳይተዋል። ግን እስካሁን ጉዳዩ አልተቋጨም።

በዚህ ጽሁፍ የጉዳዩን ጠቅላላ ይዞታ አልተችም፤ ጉዳዩና የእርቅ ስራው እጅግ ከባድና ውስብስብ ናቸውና። በዚህ ጽሁፍ ከጉዳዩ አንዱን ንብርብር ለመላጥ ነው የምሞክረው፤ ይህ ደግሞ ሲኖዶስ ሊሰደድ ይችላል ወይ የሚለው ጥያቄ ነው።

ይህን ጉዳይ ለዘብ ባለ መንገድ ከታየ ስምምነት ላይ እንደሚደረስና ችግሩም መፍትሄ አንደሚያገኝ እርግጠኛ ነኝ። ነገር ግን አክራሪ አስተያየቶች ናቸው የሰፈኑት። እነዚህ «ሲኖዶስ ሊሰደድ አይችልም» እና «መንግስት ሲኖዶስ ላይ ጫና ካደረገ ፓትሪያርኩ ግድ መሰደድ አለባቸው ስለዚህ ሲኖዶሱ ውጭ ይሆናል ማለት ነው» የሚሉት ናቸው።

በመጀመሪያ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በማንም የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና ሲኖዶስ መንቀሳቀስ አይችልም የሚል ህግ የለም፤ ሊኖርም አይችልም። ጣልያን ኢትዮጵያን ወርራ ከአንድ በስተቀር ጳጳሳቱን በሙሉ ረሽና ቢሆን እኚህ አንድ የቀሩት ጳጳስ ተሰደው ቤተ ክርስቲያኑን ካሉበት ቢመሩ ህገ ወጥ ነው? በፍጹም። ግን ዋናው ጥያቄ ህገ ወጥ ነው ወይ ሳይሆን ክርስቲያናዊ አይደለም ወይ? ቤተ ክርስቲያን በዚህ መንገድ እራስዋን ማዳንና በጎቿን መጠበቅ አለባት። አንዳንድ ሁኔታ መሰደድን ያስገድዳልም ይመክራልም።

እነዚህ ሁኔታዎች ምን እንደሆኑ አስቀድሞ አይታወቅም፤ ጊዜው ሲደርስ ሁኔታው ተጠንቶ ነው መወሰን የሚቻለው። ለዚህም ነው ከላይ ስለ ሲኖዶስ መሰደድ ቤተ ክርስቲያናዊ ህግ ሊኖር አይችልም ያልኩት። እንደ ሁኔታው፣ እንደ አደገኛነቱና እንደ አስፈላጊነቱ ውሳኔው ይለያያል።

ለዚህ እውነታ ጥሩ ምሳሌው የሩሲያ ኦርቶዶክስ ሲኖዶስ በ1910 በሩሲያ ኮምዩኒስት አብዮት ምክንያት መሰደዱ ነው። የሶቪዬት ኮምዩኒስት መንግስት በቤተ ክርስቲያንዋ ላይ ያደረሰው ጥቃት እጅግ ከባድ በመሆኑ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ካህናትና አማኞች በህሊናም ቢሆን ለማሰብ ያስቸግራል። በመቶ ሺዎች የሚቆጠር ያህል ካህናት ናቸው በተለያየ መንገድ የተገደሉት። ሌሎቹ በሞት እስር ቤቶች ታሰሩና አብዛኞቻቸው ሞቱ።

በዚህ ሁኔታ በ1913 የሩሲያ ኦርቶዶክስ ፓትሪያርክ ቅዱስ ቲኾን ቤተ ክርስቲያንዋ ታላቅ ችግር ላይ መሆንዋንና የሶቪዬት መንግስት ካህናት እየገደሉ የራሱን ካድሬዎች ካህን አድርጎ ወደ ቤተ ክርስቲያን እያስገባ እንደሆነ ተገንዝበው በውጭ ያሉት የተሰደዱት ጳጳሳት እራሳቸውን እንዲያስተዳደሩ አዘዙ። ያሉበትን ሁኔታም ለመገምገምና ይህ ውሳኔ ላይ ለመድረስ ሶስት አመት ፈጀባቸው። ሲኖዶሱ፣ ማለትም ጳጳሳቱ በመንግስት ቁጥጥር ስር እንደሆኑ ሲያውቁ ነው ፓትሪያርኩ ውጭ ላሉት ጳጳሳት ካሁን ወዲያ በኛ መተማመን አትችሉምና እራችሁን ቻሉ ያሏዋቸው።

ሆኖም የውጩ ፓትሪያርክ ወዲያው አልተሾመም። ፓትሪያርክ ቲኾን ከተሰዉ (አሁን ቅዱስ ቲኾን ናቸው) በኋላና የሩሲያ (ሞስኮብ) ሀገረ ስብከት ከመጠን በላይ የካድሬ ግዛት ሲሆን የውጭ ሲኖዶሱ ፓትሪያርክ ሾመ። ከዛ ቀጥሎ እስከ 1999 የሩሲያ የውጭ ሲኖዶስ (ROCOR) እና የሞስኮብ ሲኖዶስ ተለያይተው እንዲሁም ሲወጋገዙ ቆዩ።

1999 ሁለቱ ሲኖዶሶች ተታረቁ። የውጭ ሲኖዶሱ ከማን ጋር ነው የትታረቀው፤ የሩሲያው ሲኖዶስ በካድሬ የሞላ አልነበረምን ብላችሁ እያሰባችሁ ይሆናል። በሚገርም ሁኔታ ካድሬ ያልሆኑ ታላላቅ አባቶችና መነኮሳት አንገታቸውን ደፍተው ከፖለቲካ ራሳቸውን አርቀው እየሰሩ እየተፈቱ እየተደበቁ የሶቪዬት ኮምዩኒስት ዘመንን ያሳለፉ ነበሩ። አንዳንዶቹ ጭራሽ ራሳቸውን እንደ ካድሬ አስመስለው ሌሎች ወንድሞቻቸው ካህናትን ክጥቃት የመጠበቅ ስራ ይዘው ነበር። አሁንም በሀገራችን ኢትዮጵያ ከጳጳሳቱና ሀገረ ስብከቱ የካድሬ መንፈስ፤ የካድሬ ብቻ ሳይሆን ሲብስ የተራ ሙስናና ሐጥያት መንፈስ፤ ቢኖርም ከዛ መካከል እጅግ ብፁ የሆኑ አገልጋዮች እንዳሉ እናውቃለን። ካድሬ የሚባሉት ውስጥም እንደሁላችንም ከራሳቸው ጋር እየተሟገቱ ንስሀ እየገቡ እየወደ እየተነሱ የሚኖሩ አሉ። በሩሲያም ሲኖዶስ እንዲሁ ስለነበር ነው እርቅ ላይ ሊደርሱ የቻሉት

በተዘዋዋሪ በዚህ በሩሲያ ታሪክ ሌላ አስደናቂ ሁኔታ ተፈጥሮ ነበር። በሁለተኛ የአለም ጦርነት ጀርመኖቹ ለተወሰነ ጊዜ ምእራብ የሶቪዬት ህብረትን ተቆጣጥረው የሩሲያ ኦርቶዶክስ ሀገረ ስብከት የተዘጉትን በሺህ የሚቆጠሩ ቤተ ክርስቲያኖችን እንደገና እንዲከፍት ፈቀዱ። ከግድያ የተረፉት እውነተኛ የሆኑት ካህናት ይህን ነፃነት ተጠቅመን ህዝቡን እናገልግል ወይስ የሀገራችን ወራሪ የሰጠንን ነፃነት ለክርስቶስም ቢሆን ልንጠቀምበት አይገባም በሚለው ጥያቄ ልባቸው ተከፋፍሎ ነበር። ምእመናኑ ሃይማኖቱ እጅግ ጠምቷቸው ስለነበር በርካታ ካህናት ወደ ቤተ ክርስቲያኖቻቸው ተመልሰው አገለገሉ። ጦርነቱ ሲይበቃም የሶቬት መንግስት እንደዚህ አይነት ካህናትን እንደጠበቁት እስር ቤት ላካቸው ወይም ረሸናቸው። (ስለዚህ ታሪክ «ካህኑ» የሚባለውን የሩሲያ ፊልም እንድታዩ እጋብዛችኋለው፤ እጅግ አስተማሪ ነው።)

የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የመሰደድ ታሪክ የሚያሳየን የሲኖዶስ መሰደድ ጉዳይ እንደ በርካታ የቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ጉዳዮች «ጥቁርና ነጭ» አይደለም። እንዲህ ቢሆን ይሰደዳል እንዲህ ቢሆን አይሰደድም የሚል አስቀድሞ ሁሉንም ሁኔታ የሚያካትት ህግ የለም። እንደ ሁኔታው ነው ውሳኔ የሚወሰነው።

ታድያ በኢትዮጵያ በ1983 የነበረው ሁኔታ አቡነ መርቆርዮስ የሲኖዶስ መንበራቸውን ይዘው እንዲሰደዱ ያስገድዳቸው ነበር? ይህ ጥያቄ እውነት ወይ ውሸት የለውም፤ እንደ እያንዳንዱ ሰው አመለካከት ነው። አዎን መንግስት በጳጳሳቱ ላይ ጫና እያደረገ ነው ግን ያን ያህል ስላልሆነ መሰደድ አያስገድድም፤ ጳጳሳቱ ጫናውን ሊቋቋሙ ይገባል ማለት ይቻላል። ወይም ጫናው የቤተ ክርስቲያኑን መሰረት አናግቶታልና በነፃነት ምእመናኑን ለማገልገል ሲኖዶሱ ከሀገር ውጭ መሆን ነበረበት ማለት ይቻላል። ሁለቱም አስተያየቶች ያስኬዳሉ።

ከዚህ መማር የምንችለው ታላቅ ትምህርት ሁሉም ነገር እንደ ሃይማኖት ዶግማ ወይም ቀኖና ማየት የለብንም። በነዚህ ታሪኮች አንድ እውነት ብቻ ነው ያለው። ስለሆነም እነዚህን የመሰሉ ችግሮችን እንደ ዶግማ እና ቀኖና እንደ አስፈላጊነቱ የማይሻሻሉ አድርገን ማየት የለብንም። ከሃይማኖታችን መሰረተ ትምህርትና ስርዓት በቀር ሌላውን ጉዳይ በሙሉ በትህትና ነው ማየት ያለብን። አቋሞቻችንንም በትህትና መያዝና ሃሳቦቻችንን መቀየር መቻል አለብን። ጥሩ ክርስቲያን አንድ አምላክ እግዚአብሔርን እንጂ ሃሳቡን፣ የሚከተለውን ርዕዮት አለም፤ ወይንም አቋሙን አያመልክም።

በመጨረሻ አንደ ልጠቅስ የምፈልገው ነገር አለ፤ ሁለቱ ሲኖዶሶቹ ቢታረቁ ለሀገራዊ እርቅ ሰላምና የመንፈሳዊ ደስታና መረጋጋት ታላቅ ድል ይሆናል። በዛሬ ኢትዮጵያ ህዝቡ ያጣው መሪ ነው የሚባለው እውነት ነው። ልጄ ሲያድግ እንደ ከሌ ቢሆንልኝ የሚባል መሪ በየትኛውም በመንግስትም በሃይማኖትም በመሃበራዊም ዘርፍ የለም። ከግዥ መደቡ ጥሩ ምሳሌ የሚባልና የሚደነቅ የለም፤ ጭሽ ህዝቡ ሙስናና ተመሳሳይ መትፎ ስነ መግባር ውስጥ ሲገባ መሪዎቻችንም ያረጉታል ለምን እኛም አናደርገውም እያለ ነው። ስለዚህ እንደ ሲኖዶስ እርቅ አይነቱ ዜና ከቤተ ክርስቲያን መሪዎች ቢመጣ ለህዝባችን ታላቅ ምሳሌና ለሀገራዊ እርቅ ታላቅ ድል ነው የሚሆነው። ይህ እርቅን ለማምጣት ደግሞ በሃይማኖታዊም በፖለቲካውም አቅጣጫ ቢታይ ከባድ ያልሆነ ጥቅሙ ከጉዳቱ እጅግ ከፍ ያለ ነግር ነው። ከሌሎች ጉዳዮች ይልቅ ብዙም ከባድ አይደለም። እግዚአብሔር ይህንን እርቅ ለማድረስ ልቦናውን ይስጠን።

Thursday 3 November 2016

Some Basics on Interacting with Ethnic Nationalism

2009/2/24 (Ethiopian calendar)
2016/11/3 (European calendar)

(pdf)

[Note: An Amharic version of this post will appear sometime!]

In his recent interview with ESAT, Ato Abebe Bogale presents us with a text book lesson on how to interact with ethnic nationalism, specifically Oromo nationalism. In this article, I attempt to expand on some of the principles and lessons he presented.

The subject of the interview was a recent conference on Oromo nationalism in London, during which one speaker strongly advocated for the break up of Ethiopia in the name of freeing the imprisoned Oromo nation from Ethiopia. This speech raised a lot of hackle in the media and among Ethiopian nationalists, even though it was just a repetition of a decades old position of not only Oromo nationalists but all those Ethiopians who starting in the 1960's, imbibed with socialist theories, think of Ethiopia as a prison of nationalities which needed to be freed. Somehow this repetition of a well known political position appeared to create panic in a number of people.

This leads me to the first and most important lesson we can learn from Ato Abebe, which is to remain calm and avoid at all costs projecting any kind of fear or panic about ethnic nationalism. When ethnic nationalists, including moderates, perceive the other side as being hysterical, they tend to become offended and are pushed to take a more defensive and radical position. Why are our heartfelt ideas raising such emotion – why don't they even try to understand us – we just can't relate to them – these are the questions and sentiments raised. In the end, this ends up increasing the support for ethnic nationalism, making non-nationalists moderate nationalists and moderates into hardliners.

Every politician in every country that has had to deal with ethnic politics knows this. I will given an example: During the Quebec referendum, when the province of Quebec was voting on the question of seceding from Canada, one of the Quebec nationalist tactics in their campaign was to provoke anti-secessionists in the rest of Canada into saying something insulting about Quebecers. They would then use these incidents and have their media broadcast them repeatedly in order to fan ethnic sentiment and promote their agenda. Knowing this, most Canadian politicians would be very careful to prevent such incidents. Instead, they would organize various events to promote 'friendship propaganda'. One such event was sending via bus, train, and plane hundreds of thousands of Canadians to Quebec to hold a demonstration whose motto was to show how much Canadians love Quebec! This is the politics of dealing with ethnic nationalism.

Ethiopian nationalists must practice the same type of politics. We must avoid not only inflammatory statements, including equating ethnic nationalism with tribalism and other similar sentiments that could be interpreted as derogatory, but also statements that question people's right to choose their identity and deny the existence any sort of ethnic rights. All such statements and positions only serve to actually promote the desires ethnic nationalists, especially hardcore nationalists.

Note how Ato Abebe was careful in this regard during the interview. While the interviewer tried to impress upon him the impending danger of secession, Ato Abebe completely avoided saying anything inflammatory or anything that could be interpreted as being offensive to Oromo nationalism. Instead, he calmly explained that Oromo secession is not a new position at all. Further, he explained that today, even among Oromo nationalists, and even among those who in previous years advocated secession, secession is now the position of a small minority. This is a fact, and though it is a fact, many Ethiopian nationalists tend to forget it, become hysterical, and unintentionally promote the cause of radical ethnic nationalists.

The second, related, lesson is that there is a diversity of opinions on ethnic nationalism in Oromo politics, all the way from Ethiopian nationalism to soft Oromo nationalism to hardline Oromo nationalism. The fact there are multiple Oromo political organizations and that, even in today's charged political atmosphere, these organizations are holding several conferences to reach some kind of consensus shows that they are far from reaching consensus. They are even far from agreeing to disagree, from agreeing to tolerate each others' views. (Doesn't this remind us of Ethiopian nationalist politics!) This is another reason for Ethiopian nationalists to keep our reaction to ethnic politics proportional to its dangers.

Third, Ato Abebe shows us that we have to look all of reality in the face all the time instead of being distracted by the winds of the day. He reminds us that the Ethiopian constitution today supports the idea of secession! Have we forgotten this? It is a radical ethnic nationalist constitution, the most radical in the world, an 'experiment' according to the EPRDF. (Imagine conducting such an experiment in one of the poorest and at risk countries in the world!). This is the reality we have to deal with. Given that this is what we are living with every day, why do the comments of a single Oromo secessionist at a conference take so much of our time? Rather, Ethiopian nationalists should be focusing on getting their own house in order to as to be able to harness the power blunt the edge of this constitution, a constitution which is everyday proving to be more and more dangerous for the country.

The fourth point that Ato Abebe beautifully explains is that despite the constitution, despite the government putting up fences, so to speak, around the ethnic regions so as to minimize integration and assimilation, which is the key to creating any kind of shared destiny, Ethiopia remains to this day. This is perhaps the strongest testimony against the theory of Ethiopia as a prison of nations. Ethiopia is a country, a nation, where significant integration and assimilation has taken place in the past, and a significant portion of the population, from all ethnic groups, is Ethiopian nationalist.

I remind you that in 1991, the only forces with power (guns) in Ethiopia were ethnic liberation forces. The Ethiopian nationalist elite along was completely absent. The ethnic nationalists – EPLF, TPLF, OLF, etc – could have easily carved up the country in pieces, as per their ideologies. Eritrea seceded, but apart from that, the rest found that they could not, collectively, that is, disintegrate the country. Further, as the years went by, the EPRDF found itself discovering more and more the dangers of ethnic nationalism. TPLF members who in the 1990's would insist they were Tigrean first then Ethiopian today claim to be most 'Ethiopian' of all, much more Ethiopian than their 'anti-Ethiopian' opposition! As Ato Abebe pointed out in his interview, Prime Minister Meles, who would never miss an opportunity to belittle Ethiopian nationalism and who once called the Ethiopian flag but a rag, eventually ended up establishing a national holiday commemorating the flag! Thus, despite the decades long failings of the Ethiopian nationalist elite, the country has managed to remain alive. Ailing, but alive.

The final principle that Ato Abebe brought up and that I would like to emphasize is that healthy politics should always be related to reality on the ground, not ideology or fantasy. An example of this was, during the 2005 elections, Kinijit's position regarding the constitution, which was to accept it and if necessary change it only according to its provisions. This was an acknowledgement of changes in Ethiopia's political landscape with regard to ethnic nationalism, especially in Oromia. Kinijit did not adopt an ethnic nationalist position, but rather proposed to promote its Ethiopian nationalism agenda in another way, working within the constitution that many ethnic nationalists loved. This was very much a feasible proposition. Politics is the art of the possible, after all.


In conclusion, I do hope that we Ethiopian nationalists generally learn to become more nuanced in dealing with ethnic nationalism. We are a large constituency, the largest in Ethiopia, and we have a big responsibility to fix our failures over five decades. One of the ways of fixing our failures is to find the right way to interact with a major reality in today's Ethiopia, ethnic nationalism.

Thursday 27 October 2016

One Response to the ODF's “Our Common Future: A Proposal”

2009/2/17 (Ethiopian calendar)
2016/10/27 (European calendar)

(pdf)

[Note: An Amharic version of this post will appear sometime!]

It was with great pleasure that I read the Oromo Democratic Front's (ODF) discussion paper “Our Common Future: A Proposal.” It has been a long time since I read a constructive and inviting paper from an Ethiopian political party, a paper inviting us to do work rather than mire ourselves in sloganeering and pity. I commend the ODF for their initiative, and my aim here is to answer their invitation for a response to their proposal. I am but an individual commentator, a mere layman representing no one but myself, but I hope that my comments do the proposal some justice. I shall make my comments on the ideas in the proposal based on the order they were presented in the paper.

I fully agree with the ODF that a country-wide consensus” on Ethiopia is indeed urgently required, but it has been urgently required for 22 years. The last 'consensus', the 1994 FDRE constitution was in my opinion too radical and not consultative enough, and so we've been waiting for a better one ever since. However, such consensuses are not created overnight, or in a conference or two. It takes years of discussion and deliberation to develop positions, let alone agreements on such a complicated matter as a country's political structure. It is remarkable that the Ethiopian opposition in all its forms has for 25 years hardly made any progress in this matter. We seem to be discussing the same issues over and over again, with the same confrontational zero-sum mindset as in the past. So we would all do well to heed what the ODF recommends and begin work immediately on this “country-wide consensus”.

Next, the proposal frames the current political problem as one between two opposing sides – the current regime as one side and those wanting a “unitary nation” as the other. It implies that “core Oromo demands” have been “sidestepped” or ignored in this debate. This framing is, to put it bluntly, wholly inaccurate. First, though I'm sure there are many that wish for a unitary nation, that is no federal system whatsoever, they form a small minority. To illustrate this, consider the official position of Kinijit and its successor parties in this regard, which was to maintain the current (federal) constitution as it is for the foreseeable future, and past that, amend it as per its own provisions! What kind of amendment it would be was not decided, but there were many proposals, ranging from language-based federalism, which would be almost the same as the current arrangement but simply replacing the concept of ethnicity with language, to federalism with states with redrawn boundaries removing ethnicity entirely. None of this makes for a centralized “unitary nation” -- it is at the very least federalism of some sort. Given Kinijit's large constituency as shown by its electoral victory, this is the majority position, not that of a “unitary nation”.

Second, unless I am mistaken, the main “core Oromo demand” is that the current constitution actually be respected rather than the EPRDF and TPLF in particular using its extrajudicial power to exercise undue influence. This demand is not sidestepped and has not been sidestepped in the debate in any way since all sides that have significant constituencies affirm the current constitution as a political reality, whether they like it or not. I would like to note here that if anything is being sidestepped it is the core demands of the Ethiopian nationalists, since the status quo already fulfils a large portion of the “Oromo demands”, which is a multinational state! The status quo has already brought Ethiopia, constitutionally speaking, from one extreme to the other extreme. There is no possible going further! Thus Oromo demands in this regard have been exceedingly fulfilled, save for the actual implementation portion.

Other demands, such as Oromiffa becoming an official federal language are also supported by all major constituencies. All this to say that talk about the “unitary nation” constituency is a red herring, and therefore presenting the current regime and the “unitary nation” constituency as the poles in the debate is incorrect.

Instead, the debate is multipolar, perhaps too multipolar. If we consider Oromia as one constituency, we have in Oromia a spectrum all the way from Ethiopian nationalists to soft Oromo nationalists to hardline Oromo nationalists. These factions themselves have a lot to sort out in terms of simply agreeing to disagree, let alone being able to unite into one constituency.

Then we have the Ethiopian nationalist constituency, which includes perhaps most of Amhara region, but also that large disenfranchised group of non-Amhara Ethiopians and mixed Ethiopians who consider themselves not to be ethnic nationalists. This constituency is the one that voted for Kinijit, and since its diversity means that it does not have ethnicity as a binding material, so to speak, it is an extremely fractious constituency. The inability of this constituency to “avoid the hair-splitting type of exchanges” and other dysfunctional traits in order to reach a basic consensus has, in my opinion, been the main reason for Ethiopia's current troubles and will end up being the ruin of the nation(s).

Third, there is the EPRDF, which though it has internal divisions is certainly the most united and coherent constituency. As the ODF proposal says, the EPRDF is convinced, or tries to convince itself, that there is no alternative to it. Well, we must admit that there is some truth in this, and the ODF proposal is proof of this in that it clearly outlines divisions in Ethiopian politics that have nothing to do with the EPRDF. We all know that were the EPRDF to vanish today, as the proposal implies, there is no consensus among the rest of us, so there would be anarchy. However, the lack of a consensus amongst the opposition has not stopped the EPRDF from the increasing “social rejection” that the proposal speaks of. Indeed, if we look to the past, both the Haile Selassie and Dergue regimes fell into some sort of anarchy, not into a ready opposition. So a weak opposition is no guarantee of long life for the EPRDF – it is only a guarantee of a hard fall. Thus the EPRDF had better start doing something to actually aid the opposition to develop rather than persecuting it.

Next, I would like to comment on the ODF conviction that the current constitution – Ethiopia as a multinational state – was “unavoidable”, implying that it is Ethiopia's destiny and natural state. Of course, it is the conviction of us Ethiopian nationalists (non ethnic nationalists) that Ethiopia as a multinational state, let alone being its natural state, is an unstable state ripe for conflict. Here we agree to disagree, but as I stated above, as was Kinijit's official position, most Ethiopian nationalists accept political reality and work within the current constitution. I would just like to add that talk of inevitability of the multinational state completely ignores other factors in Ethiopia's recent political past, including pseudo-feudalism, communism, and the Cold War, all of which are not ethnicity and yet have played a significant role in forming today's political reality. Ignoring these factors is I think a misreading of history that affects our perception of current political reality.

Now on to the numbered sections of the ODF proposal. The first, about the benefits of non-violent versus armed struggle is a case well made and there is little to argue about here. We agree to disagree with those who favour armed struggle! I would just like to add a point about 'democracy' however, as the document states that one thing all Ethiopian movements agree on is the goal of democracy. What we laymen think of us democracy is one man one vote, which immediately excludes group rights, especially huge group rights such as ethnic rights. Our problem is precisely that we do not agree with what democracy means and we cannot agree until we come to a general consensus about what our country should look like – in other words its constitution not only as it is formally written, but its spirit. So the term democracy becomes, I believe, a distraction as we work on the “country wide consensus” that this proposal advocates for. If we keep talking about democracy, we'll end up with the same problem as the Egyptian Arab Spring movement, which upon realizing that what it thought was democracy ended up empowering the Muslim Brotherhood a little too much decided it didn't want democracy after all.

The second section, on the divisive role of Ethiopian history, is excellent. I completely agree that short of some sort of miracle, we are going to have to learn to agree to disagree about Ethiopian history. I actually think that reasonable people can agree on a set of unbiased facts about Ethiopian history – that's not the main problem. The problem is that we all interpret these facts with our own political lens. Let's take the simple example of the concept of the Oromo nation. The Oromo in Ethiopia have at various times in history formed various nations, perhaps even a single nation, been an integral part as an ethnic group, not a nation, of the Ethiopian nation as we know it, assimilated into and assimilated other groups, invaded and have been invaded, terrorized and have been terrorized, etc. Most reasonable people would agree on this set of facts. I interpret this history as the Oromo being one of the ethnic groups in Ethiopia while others interpret this as the Oromo nation being distinct from what it calls Ethiopia, as having had various interactions with Ethiopia, but as a nation unto itself. Same facts, different interpretations, but these differences have major implications on building the “country-wide consensus”.

The good thing is that if we “can agree to disagree with different readings” of Ethiopian history, then we can take history out of the Ethiopian nationalism vs ethnic nationalism debate, and this would greatly help unfog the debate. The debate then will simply be about political position rather than history, grievance, etc. This kind of development is would not be new – the example of Canada and Quebec is a case in point. The history of Canada is simple and well-documented – there's not much to argue about its contents. Quebec nationalists interpret the history as that of a Quebec nation invaded and with a right to independence, while others view the history as a competition between two North American colonialists which one party won and is a fait accompli. Same facts, different interpretations. But the only important fact here is that Quebec nationalists want independence today, regardless of history, and the opposite side wants a single Canada, regardless of history. It is current political competition that drives the debate.

The third section on self-determination is also excellent in that it nicely breaks down a large idea – ethnic self determination in the context of Ethiopia – into smaller principles that are much easier to discuss and come to agreement on. I agree with all the premises as they apply in this context. (I disagree with “being an Oromo was officially portrayed as antithetical to being an Ethiopian”, but that's not one of the principles, just an aside.) However, there is more to go – it is a bare minimum, not surprisingly, as this is proposal is just a starting point. One can agree with all the premises, as I do, yet disagree on their political interpretation, as I do with the interpretation of the ODF.

Finally, the fourth and fifth sections dealing with the zero sum attitudes in Ethiopian politics, particularly as it relates to demonizing opponents and lacking empathy. The proposal makes it clear that in order to properly learn from the past, we have to empathize not only with current opponents but with past actors and understand why they did what they did. If we do so, we will realize that there was and in the case of the EPRDF there is some good that they have done, and these should be built upon, rather than everything having to be torn down and built up again.

I completely agree with these thoughts. The zero sum mentality means for a complete absence of introspection, which in turn means continual conflict. With a little bit of empathy and introspection, much of the current conflict would be easily transformed. I think Ethiopians have to start giving the saying 'a people get the government they deserve' much more weight than we currently do. As I am fond of saying, much of the reason Ethiopia today has an ethnic-based constitution that Ethiopian nationalists do not like (but accept!) is because Ethiopian nationalists committed political suicide over the two decades before the new constitution was formed, so that they were unable to be at the table. Yet we Ethiopian nationalists continue to blame the EPRDF for it, as if the EPRDF could suddenly reverse its cherished ideology and take a huge political risk once in power! Unfortunately, it is this focus on continually blaming the EPRDF for everything that has kept us unable to fix our own problems and therefore kept us weak and inept.

In conclusion, I think the ODF proposal is an excellent document that all stakeholders in Ethiopian politics should read, discuss, and build upon. However, let us reflect on why previous such attempts, such as Medrek, for example, have stuttered and failed, and learn from those mistakes. Also, let us ask ourselves where the other stakeholders are while the grassroots, leaderless, is up in arms.