Showing posts with label contradictions. Show all posts
Showing posts with label contradictions. Show all posts

Tuesday, 25 October 2016

የአንድ ዲያስፖራ ኑዛዜ

2009/2/15 ዓ.ም. (2016/10/25)

በአንድ ዲያስፖራ የተጻፈ…

ችግርን ለመፍታት በመጀመሪያ የችግሩ ዋና ምክንያቶች በትክክሉ መገኘት አለባቸው። እነዚህ ምክንያቶች ተገኝተው ሲፈቱ ነው ዋናው ችግር የሚፈታው። የችግሩ ምክንያቶች ወይም ምንጮች በትክክሉ ካልተገኙ ችግሩ መቼም አይፈታም። ይህን ሁላችንም የምናውቀው እውነታን በመጀመርያ የምጠቅሰው እኔ ከሀገሬ ኢትዮጵያ የፖለቲካና መሃበረሰባዊ ችግሮች ምክንያቶች አንዱ ነኝ ብዬ ስለማምን ነው።

ከማልፈልገው መንግስት ለመሸሽ «ኑሮ ለማሸነፍ» ብዬ ያሳደገችኝን ሀገሬ ኢትዮጵያን ትችያት ወጣሁኝ። በምሳሌ ደረጃ ቤቴን ትቼ ወጣሁኝ ማለት ይቻላል፤ በጣም በመቸኮሌም የቤቴን ቁልፍ ለማንም በአደራነት አልተውኩም። ባዶና አለ ጠባቂ የተውኩትን ቤት ሌላ ሰው ገብቶ ማስተዳደር ጀመረ። የቤቱን እቃ በሚፈልገው መልክ አሸጋሸገ፤ የማይፈልገውን እቃ ሸጠ ወይም ጣለ፤ የሚፈልገውን አዲስ እቃ ደግሞ ገዛና አስገባ። እኔ ከሩቅ ከዲያስፖራ ሆኜ እመለከተለሁ አዝናለው እናደዳለው እጮሃለውም። ቤቴን በመጀመሪያው ባልተውኩኝ ኖሮ።

በርካታ የትምህርት ጓደኞቼ እንደኔ ውጭ ሀገር ናቸው። አቃቸዋለሁ፤ ጥሩ ችሎታ ያላቸው ደህና ሰዎች ናቸው። ዩኒቨርሲቲ ለመግባት የበቁ የሀገራችን ምርጥ ተማሪዎች ነበሩ፤ ሀገሪቷን በደምብ ማገልገል የሚችሉ። ግን ዛሬ ሀገራቸውን ለቀው ውጭ ናቸው፤ አሜሪካንን ያገለግላሉ፤ ወይ ስዊድንን ያገለገላሉ። ታድያ እነዚህ ሁሉ ከሀገር ወጥተው ማን ነው የቀረው? እኔ ከሀገራችንን ከሚመሩት የተሻልኩኝ፤ እንደነሱ ክፉ ያልሆንኩኝ፤ ሀገር ወዳድ ነኝ ብዬ የማምን ከሆነ ከሀገሬ መውጣቴ ምን ይባላል። እራሴን አውጥቼ ሀገሬን ለክፉ ናቸው የምላቸው ሰዎች ትችያታለሁ ማለት ነው። ትልቅ ጥፋት አለብን።

አንድ አስተማሪ የቤተ ክርስትያን ተረት ልንገራችሁ… በአንድ ወክት የቤተ ክርስትያን አመራርና ካህናት በከባድ የመንፈሳዊ ፈተና ተይዘው ነበር። በካህናቱ መካከል የእምነት ጉድለት፤ የስነ መግባር ጉድለት፤ የሙስና ብዛት፤ ወዘተ ይታይ ነበር። እጅግ ከባድ ዘመን ነበር። በዚህ ጊዜ አንድ ደህና ኑሮ ያላት ሴት ወይዘሮ ወደ አንድ የታወቁ መንፈሳዊ አባት ለራስዋ ጉዳዮች ምክር ለማግኘትና ንስሀ ለመግባት ትሄዳለች። ከኚህ አባት ጋር ቁጭ ብላ መወያየት ስትጀምር ግን ዋና ጉዳይዋን ትታ ስለ ቤተ ክርስቲያን አመራሮችና ካህናት ችግር ብቻ ታወራለች ታጉረመርማለችም። የምታማክራቸው አባት በትዕግስት አቤቱታዋንና ወሬዋን እስክትጨርስ ድረስ አዳመጧት። ሁሉንም ተችታና ኮንና ጨረሰች። ቀጥሎ እኚህ ታላቅ አባት ልጆች እንዳሏት ጠየቋት። አዎን ሁለት ሴቶችና ሁለት ወንዶች አሉኝ አለች። ከነዚህ ወንድ ልጆችሽ አንዱ ቄስ ቢሆንስ ብለው ጠየቋት። በፍጹም፤ እንዴት ይሆናል ብላ ተቆጣች። እንዴት ለልጀ ገንዘብም እውቀጥም የሌለውን ስራ እመኝለታለሁ አለች! ታድያ የራስሽ ልጆች ካህን እንዲሆኑ ካልፈለግሽ ማን ነሽ በፈቃዳቸው ካህን እንሆናለን ያሉትን የምትኮንኙ ብለው ታላቁ አባት ወቀሷት አስተማሯትም።

ሀገር ችግር ላይ በሆነበት ጊዜ መሸሽ ክህደት ነው ማለት ይቻላል። እኔ ሀገሬን ከድጂያታለሁ ለማለት ወደኋላ አልልም። ጥፋትንና ድክመትን ማመን የመጀመሪያ የችግርን መፍታት እርምጃ ነው። አንድ ሰው ቤተሰብ ውስጥ ችግር ካለ ቤተሰብነቱን ክዶ ሸሽቶ አይሄድም። ልጀ ካስቸገረኝ ልጄ አይደለህም ብዬ አላባርረውም። ካባረርኩት ካድኩት ማለት ነው። ሀገርም እንደዚህ ነው። ሀገር ወዳድ ነኝ ማለትና ሀገር ችግር ላይ ስትወድቅ መሸሽ ተጻራሪ ናቸው!

እውነት ነው፤ አንዳንዴ ሽሽት ግድ ነው። ድንግል ማርያም ልጇን ክርስቶስን ይዛ ሸሽታለች። ግን ሽሽቱ አላማን ለማሳካት ነው እንጂ ለመሸሽ አይደለም። እውነቱን ለመናገር እኔ ግን ወደ ዲያስፖራ የመጣሁት ለመሸሽና የሀገሬን ችግር ለሌሎች ለመተው ነው። ለሀገሬ አላማ ኖሮኝ አይደለም። ኢትዮጵያ ያሉት ታግለውልኝ ደህና መንግስት ሲያመጡ እመለሳለሁ ብዬ ነው። ግን ያም ቢሆን የምመለስ ይመስላችኋልን? ከሃዲ ነኝ፤ እውነት ነው፤ ጥፋቴን አምናለሁ።

ግን ሀገሬን እውዳለሁ፤ ፖለቲካዋ እንደዚህ ወይም እንደዛ መሆን አለበት፤ መሃበረሰቧም እንደዚህ ወይም እንደዛ መምሰል አለበት፤ ህዝቡ መሰልጠን አለበት፤ መንግስትም አሰራሩ እንደዚህ መሆን አለበት ብዬ አስባለሁ እለፈልፋለውም። ሀሳብና ወሬ ብቻ ሀገር ወዳድ የሚያደርግ ይመስለኛል።

ሀገር ወዳድ ሆኜ ግን እንዴት ነው ተግባሬ ያንን የሀገር ፍቅርን ሊያንጸባርቅ የሚችለው? ልጆቼን እንኳን ቋንቋቸውን አላስተማርኳቸውም። ሀገረ ወዳድነት ይህ ነው? ያውም «አላስተማርኳቸውም» የሚለው ቃል በቂ አይገልጸውም፤ አላስተማርኳቸውም ሳይሆን እንዳይማሩ ከልኪያቸዋለሁ። ሌላው ሁሉ መጤ፤ ሂስፓኒኩ፤ ቻይናው፤ ሶማሌው፤ ጣሊያኑ፤ ወዘተ ቋንቋውን ከቤት እየተናገረ ልጆቻቸው በተዘዋዋሪ ቋንቋቸውን ይችላሉ። እኔ ግን ከቤቴ በደምብ የማልችለውን እንግሊዘኛ (ወይም ጀርመን ስዊድኛ ወዘተ) እየተናገርኩኝ ልጆቼ ቋንቋቸውን እንዳይችሉ አረጋለሁ። ባህላቸውን ወጋቸውንም ላይላዩን ብቻ ነው የማስተምራቸው። እውነቱን ለመናገር ልጆቼን ፈረንጅ እንዲሆኑ አድርግያለሁ። ኢትዮጵያዊ ትውልድ በኔ ቆሟል። ታድያ ምን አይነት ሀገር ወዳድ ነኝ?

ወደ ክህደቴ ልመለስና… እርግጥ እራሴን ለማጽናናት ያህል አንዳንድ ግዜ ለክህደቴ ስበቦችና አጉል ምክንያቶች እፈጥራለሁ። አንዱ «ከሀገሬ ብቆይ እታሰር ነበር» ነው። «ህሊናዬን ሽጥቼ ካልሆነ ሀገሬ መስራት አልችልም።» ታድያ ሀገር ቤት ያሉት ወገኖቼ በሙሉ ወይ ታስረዋል ወይ ህሊናቸውን የሸጡ አደርባዮች ሆኖዋል ማለት ነው? ወይ ፍርድ! በአንድ በኩል ገዥው መንግስት የአናሳ ህዝብ ነው እላለሁ። በሌላው በኩል ሁሉንም ይቆጣጠራሉ እላለሁ። እነዚህ የሚጻረሩ ሀሳቦች ናቸው! እውነቱ እንደዚህ ነው፤ አብዛኛው ህዝብ ክፉ ላለማድረግ ከወሰነ ከተባበረ በሀገሪቷ ያለውን ክፋት ይጠፋ ነበር። እራሴን እንደዚህ ማታለል አልችልም፤ ከሀገሬ ሆኜ ለሀገሬ በርካታ ጠቃሚ ነበር አፈራ ነበር።

አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ክሀገሬ የሸሸሁት ኑሮ አሸንፌ ቤተሰቤን ለመርዳት ነው ብዬ እራሴን ማጽናናት እሞክራለሁ። ከቅዠቴ ስነቃ ግን ለዚህም አጉል ምክንያት መልስ አለኝ። ሀገር የሚያድገው ገንዘብ ሲያገኝ ነው ወይም ህዝቡ በእውቀትና ችሎታ ሲበለጽግ ነው? ጃፓን ምንም ተፈጥሮ ሃብት ሳይኖራት ህዝቧን በእውቀትና ችሎታ እንዲበለጽግ አድርጋ ነው ያደገችው። ሳውዲ ደግሞ በተፈጥሮ ሃብት ምክንያት በገንዘብ ሃብታም ሆና ግን በህዝብ ደሃ ናት። ገንዘብ ለቤተሰቤ መላክ ምን ያህል ሀገሪቷንም እነሱንም ይጠቅማል? እርገጥ አንዳንድ ቤተሰብ ገንዘቡን ለዘላቂ ነገር ለትምህርት ለንግድ ወዘተ ይጠቅምበታል። በርካታው ደግሞ ለለት ኑሮ ይጠቀምበታል። ምንም ቢሆን ገንዘቤ እኔን አይተካም ሊተካም አይችልም ይተካል የሚለው አስተሳሰብም ጎጂ ነው። ማንም በድጎማ አይበለጽግም። ይህ ከሀገር ለመሸሽ ምክንያቴ ሊሆነ አይገባም።

አዎን ለክህደቴ ምንም ስበብ የለም። አምኛለሁ። ንስሀ ገባለሁም። እግዚአብሔር ሀገር ቤት እንድመለስና ከወገኖቼ አብሬ ደስታቸውንም ችግራቸውንም እንድካፈል ብርታቱ ይስጠኝ። እራሴንም ማታለል እንዳቆም ይርዳኝ። አሜን።

Monday, 10 October 2016

የትግሬ አድሎ

2009/1/29 .. (2016/10/9)

(pdf)

ፖሊሱን ምንድነው የሚያበሳጭህ ብዬ ስጠይቀው እንደዚህ ይለኛል«አድሎው በዛ፤ እድገት «ለነሱ ሰው» ብቻ ነው፤ ምርጥ ቦታ «ለነሱ»የማይፈለግ ስራ ለሌላው። አይን ያወጣ ነው እኮ! ሰዉ እጅግ መሮታል»

ለመንግስት እቃ የሚያቀርብ ነጋ እንደዚሁ ብሎ ይነግረኛል«ኮንትራቶች አገኛለሁ። ግን ምርጥ ኮንትራቶች «ለነሱ» ብቻ ነው። ጊዜ ቢያሳልፉም ጥራት ቢያጎሉም ምንም አይባሉም እንደ በፊቱ አይደለም፤ አሁን አይን ያወጣ ሆኗል፤ ሰ በጣም ተናዷልና ሁኔታው ያስፈራል»

ባለ ሀብቱም እንደዚሁ አይነት እሮሮ ያሰማኛል«አዎ ደህና መሬት ማግኘት ለሁ ግን ምርጥ ቦታዎቹ «ለነሱ» ሰው ነው። አንድ ቆንጆ ቦታ አግንቼ ከፍተኛውን ብር ተጫርቼ «ለነሱ» ተሰጠ። እጅግ ተበሳጭቻለሁ። አይን ውጣ አድሎ ነው» ይለኛል። በተዘዋዋሪ ይህ ባለ ሀብት ከ ፓርቲው ጋር በሚያስፈልገው ደረጃ ግንኙነት አለው

የዩኒቨርሲቲ ተማሪውም ከትንሽ ውይይት በኋላ ወደዚሁ አርእስት የገባል። «የነሱ» ተማሪዎች የሚያገኙትን እርዳታ ብታይ። ትርፍ ትምህርታዊ ምክር፤ ሳምፕል ፈተናዎች፤ ከነሱ አስተማሪዎች በትርፍ ግዜ እርዳታ» ዝምብሎ ከማማረር ለምን እናንተም እንደዚህ አታረጉም ብዬ ጠይቀዋለሁጥያቄዬን ያልፈዋል፤ ስለ «እነሱ» ነው ማውራት የሚፈልገው

«እነሱ» ማን እንደሆኑ ሁላችንም እናውቃለን። አዎ በትክክሉ ለመናገር የኢህአዴግ አባላትና አደርባዮቻቸው ናቸው። ግን ሰ«እነሱ» ሲል ባጭሩ ትግሬዎች ማለቱ ነው፤ አድሎ ሲል የትግሬ አድሎ ማለቱ ነው።

እውነቱን ለመናገር የትግሬ አድሎ ገርሞኝም አያቅም። የመንግስታችን አወቃቀር ይህን አድሎ የሚያስከትል ነውየአንድ ፓርቲ አገዛዝ ነው ያለንፖለቲካ ተቀናቃየለም አይፈቀድምም። እንኳን የነፃ ምርጫ ከፊል ነፃ ምርጫ የለም። በዚህ አይነት «አውራ ፓርቲ» አገዛዝ ሁልግዜ ለፓርቲ አባላትና አደርባዮቻቸው ከፍተ አደሎ ይኖራል። በደርግ ዘመን ለኢሳፓ አባላት አድሎ አልነበረም? በኃይለ ስላሴ ዘመን ከቤተ መንግስት ግንኙነት ያላቸው የተሻለ ያገኙ አልነበረም? የዛሬውም እንደዚህ ነው።

ይህን ሃሳብ ስናገር አብዛኛው አዳማጭ ይገረመዋል«የዛሬው አድሎ ግን በዘር ነው እኮ» ይሉኛል። አዎን የዘር አድሎ ነው ግን ህይ የዘር አድሎ፤ ማለት የትግሬ አድሎ፤ መኖሩ ልንገረም አይገባም። ሁላችንም የኢህአዴግ ታሪካዊ አመጣጥን እናውለን። ከመጀመሪያው ህውከኢህአዴግ ከፍተኛ ኃይል ያለው ፓርቲ ነበር ዛሬም ነው፤ ቶር ስራዊቱንና በተለይ ደህንነቱን እንደሚቆጣጠር እናውቃለን። ደግሞ በአንድ ግንባር ወይም ፓርቲ አገዛዝ ከዛ ፓርቲ ውስጥ ኃይል ያለው ቡድን ይበልጥ ስና አድሎ ይታይበታል! ለምን ቢባል ሙስናና አድሎ ዋና የኃይል ማከማቸትና ማንጸባረቅ መንገድ ናችሀው። ምርጫ ወይም የፖለቲካ ውድድር ሰለሌለ ኃይል በዚህ መልኩ ነው የሚከማቸው። በአውራ ፓርቲ አገዛዝ ሌላ አካሄድ ሊኖር አይችልም

ይህ ሁሉ እያልኩኝ ሳለ ኔ አመለካከት የትግሬ አድሎ ካሉት የሀገራችን የፖለቲካና ህብረተሰባዊ ችግሮች ንሹ ነው። ለኢህአዴግ ግን ዋናው ችግ ነው! ይህ እንዴት ይሆናል? ለኔ ዋናው ችግር የአንድ ፓርቲ የልማት መንግስት አገዛዙ የህዝቡን የአንድነትና የህብረተሰባዊ መንፈስ እያጠፋ መሆኑ ነው። ከሌሎች ጽሁፎች እንደጠቀስኩት የኢህአዴግ መንግስት ለህዝቡ ያቀረበው ውል እንዲህ ነው፤ ልማት ሰጥሃለሁአንተ ደግሞ በልጣኔም ይሁን በሙስናዬ አትምጣብኝ። በዚህ ውል መሰረት ሰዎች ከመሬታቸው ይፈነቀላሉ። መሬታችሁ ለባለ ሀብት ይፈለጋል እየተባለ ሳንቲም ተሰተው ይባረራሉ፤ ክስ ላይ ባለስልጣኑ ወይም አደርባዩ ጥፋተና ቢሆንም ይረታል፤ ሰዎች ትንሽ ጸረ ኢህአዴግ ነበር ቢናገሩ ይታሰራ ህዝቡ ከፍርድ ቤት ፍትህ አያገኝም ጉቦ ካልሰጠ ውይም ወዳጅ ከሌለው ንብረቱን ስራውን ወዘተ ያጣ ይችላል። ለኔ እነዚህ ችግሮች ከትሬ አድሎ እጅግ የሚበልጡ ናቸው። ፍትህ፤ ነፃነት፤ ወዘተ አለመኖራቸው ነው ዋናው ችግር። ሁለተኛ ደረጃ ችግር የማንም አድሎ። ሶስተኛ ደረጃ ችገር የትግሬ አድሎ ነው

በተዘዋዋሪ ባለንጀራችን መሬቱን ሲቀማ፤ አለ አግባብ ሲታሰር፤ ፍትህ ሲያጣ፤ ወዘተ ማንኛችንም ዞር ብለን እንርዳህ አንለውም። አይዞህ ብለን የገንዘብም ወይም ሌላ ድጋፍ አንሰጠውምየራሳችንን ኑሮ፤ የራሳችንን«ልማት» ድርሻ እያሳደድን ባለንጀራችን እየተጎዳ ዝም እንላለንምንስት ላይ ጮኸን እንታሰር አደለም። እንርዳው፤ ግን አንረዳውም። ታላቁ ችግር ይህ ነው። እውነቱን ለመናገር ኢህአዴግን በስልጣን እስካሁን የጠበቀውም ይህ መንፈስ ነው።

ግን ይህ መሰረታዊ ችግር እያለ መንግስቱን የሚያናጋው የዘር ችግሩ ነው። ይህ የሰውን አስገራሚ ባህሪ ያሳያ። «ሀገሬን በዚህም በዛም አበላሽ ግን በዘሬ አትምጣብኝ! ጉቦኛና ዘራፊ ሁን ግን በዘር ስም አታድርገው!» እኛ ኢትዮጵያዊያን እንዲህ እንላለን። ያሳዝናል።

ይህን አውቆ ኢህአዴግ የዘራውን ነው የሚያጭደው። ግን ለሀገሪቷ ህልውና አይበጅም። እኛ የ«ትግሬ አድሎ» ሳይሆን ምንም አይነት «አድሎ»ን አንፈልግም ስንል ነው ሀገራችን የሰላም መንገድ የምትጀምረው።

Tuesday, 4 October 2016

Ethnic federalism kills Meles' developmental state

2009/1/23 (Ethiopian calendar)
2016/10/3 (European calendar)

[Note: An Amharic version of this post will appear sometime!]


In a nutshell, the EPRDF's deal or social contract with the Ethiopian population over the past 15 years or so has been as follows: I will give you development and growth. In exchange, you will not challenge my political power and you will ignore the fact that my membership will have certain economic and other privileges that the rest of you will not have.

This is what a 'developmental state' led by a 'vanguard party' basically is. The classic example is China. We all know that the Chinese people, in aggregate, have prospering for years. People have been getting richer, there's more education, better health care, better infrastructure, etc. Again, this is in aggregate – large sections of the population have suffered for this and continue to suffer, but let's set that aside for the moment. As far as Ethiopians are concerned, when they see China, they see prosperity.

Now, the only political party in China – the Communist Party – has no political competition, which means there is little accountability. Party members can enrich themselves through corruption and other means and the population can do nothing about it because it cannot get rid of the party – that's part of the deal. Now, if this corruption threatens economic development and therefore threatens the Communist Party's deal with the people, which would then lead to revolt and overthrow of the party, then there's a crackdown on corruption. So as we all have seen, every so often, the party campaigns against corruption, arrests a few thousand party members and cronies, and then when it all dies down forgets about it for a while. Corruption goes up again.

Now, why isn't this working in Ethiopia? Development is taking place, economic growth is pretty good, the big projects such as the Nile Dam are still going strong. So why the unrest? Why the revolt?

The answer is ethnic federalism. You see, in China, there is more or less only one ethnicity. The population resents the privileges of the members of the Communist Party. People resent that party members are rich, have preferential treatment in everything, including the legal system, jobs, contracts, etc. However, the resentment is what we might call class resentment. The upper class is the Communist Party and the lower class the rest of the population. The upper class makes sure the lower class does quite well – not as well as the upper class but well enough to keep politically quiet.

In Ethiopia not only do we have many ethnicities, but ethnicity is part of the government! The vanguard party EPRDF is composed of ethnic parties, and the most powerful party as everyone knows and perceives is the TPLF. Just as in China, the population resents the privileges of the members of the EPRDF and their relatives and cronies. But this resentment is much greater and politically dangerous than in China because the resentment is not just class resentment, but ethnic resentment, and ethnic resentment is extremely dangerous.

As I have written before, people are far more tolerant of oppression by their own ethnic group or no ethnic group than by another ethnic group, or by what they perceive to be another ethnic group. When it comes to political oppression, ethnic feelings are strong. This is why the combination of developmental state and ethnic federalism is not working in Ethiopia.

By the way, this understanding of ethnicity as a strong political force is precisely the basis of of ethnic federalism! We need ethnic federalism, ethnic group rights above all else, etc., because ethnicity is the basis our polity, is what Meles and the EPRDF said when creating the constitution. If we do not give ethnicity this primacy, then there will be an ethnic revolt, they said. What irony then, that the ethnic division they laid in place for this reason is precisely that which is is proving their downfall.

Now, how can the EPRDF get out of this quagmire. The band aid solution is to try and severely clamp down on corruption, which it has tried to do repeatedly. But how can the EPRDF do that given the nature of the vanguard party / developmental state model, since party privilege and corruption is an unavoidable consequence of it? The other option is to do something about ethnic federalism. Of course the EPRDF can't touch the constitution, but as we have heard there is a proposal within the party to change it from a multi-ethnic front to a single non-ethnic party, thereby reducing the ethnic glare, so to speak, from the population. But this will alienate the EPRDF's more fervent ethnic nationalists, but at the same time it won't attract civic nationalists. This might have been a good option 20 years ago, but now it's too little too late.


In a later article, I will discuss what I think is a better solution for the EPRDF.