Wednesday 3 October 2018

«የዜግነት ፖለቲካ ይስፈን» ብለን እንጮሃለን ግን አልተደራጀንም!

መቼም «ከእንቁላል ውስጥ» ያሉት እነ ጠ/ሚ አብይ በሙሉ አቅማቸው ኢትዮጵያዊነትን ለማጠንከር እየጣሩ ነው። በዚህ መንገድ እንደሚቀጥሉም ይታወቃል።

አሁን በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ያለው ትልቅ ጉድለት ነገር በኢትዮጵያዊነት የምናምን ፖለቲከኛ፤ ልሂቃን እና ብዙሃን በአግባቡ አለመደራጀቱ ነው። «የዜግነት ፖለቲካ ይስፈን» ብለን እንጮሃለን ግን አልተደራጀንም!! እንኳን በሚሊዮኖች የምቆጥር በመቶ ሺዎች የሚቆጥር አባል ያለው ድርጅት የለንም። ታድያ ሌሎች የዜግነት ፖለቲካ አይሰራም ብለው እንዲያምኑ የሚያደርጋቸው እኛ ነን ማለት ነው!

እነ ግንቦት 7 ስሙ። ቶሎ ብላችሁ የዜግነት ፖለቲካ አራምዱ። አባላት እና መሪዎች በሰፊው መልምሉ። የመዋቅር መዘርጋት ስራ ካሁኑኑ ጀምሩ። ጊዜ ይፈጃል ግን ጊዜ የለንምና።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!