Showing posts with label empathy. Show all posts
Showing posts with label empathy. Show all posts

Wednesday, 16 January 2019

የድሮ ስረአት ናፋቂ ነኝ!

የአብን አመራሮች ክርስቲያን ታደለ እና በለጠ ሞላ እራሳቸውን «ትምክሕተኞች» ነን ካሉ እኔም እውነቱን ለመናገር በአቅሚቲዬ «የድሮ ስረአት ናፋቂ» ነኝ ማለት የምችል ይመስለኛል። የኃይለ ሥላሴ መንግስት ከስልጣን ሲወድቅ እድሜዬ ገና ሁለት ዓመት ቢሆንም ታሪክ በመስማት ስሜቴ ያንን ዘመን እንድናፍቀው አድርጎኛል።

ግን ዘመኑም አገዛዙም በርካታ ችግሮች ነበራቸው። የፍትህ እጦት፤ አድሎአዊነት፤ ወዘተ ነበረ። ሁላችንም እንደምናውቀው በርካታ ጪሰኞች እነሱ ወይንም አባት አያቶቻቸው ከመሬታቸው ተፈናቅለው በኢፍትሃዊ አሰራር ባላባቶችን ያገለግሉ ነበር። እንደዚህ አይነት ችግሮች እንደነበሩ እያወኩኝ እንዴት ያዘመን ይበልጥ ያስረአት ይናፍቀኛል።

ለቤተሰቦቼ ያዘመንን ጥሩ ነበር። ችግሩ እነሱን በቀጥታ አላጠቃም እና እነሱ በሰላም እና ብልጽግና ይኖሩ ነበር። ደርግ ሲመጣ ግን ችግር እየመጣ ጀመረ። የፖለቲካ ቀሱም ቤታችን ላይ ሊያንኳኳ ሆነ። በዚህ ምክንያት ደርግን ጠላሁ የጃንሆይ መንግስትን ናፈኩኝ። እንደ ማንኛውም ልጅ የራሴ ህይወት እና ልምድ (experience) አመለካከቴን ወሰነው።

መቼም አሁን ይህ አመለካከት የተሟላ እንዳልሆነ ይገባኛል። እኔ እና ቤተሰቦቼ ሰላም ስለነበራቸው ያዘመን እና ስረአት ጥሩ ነበር ማለት እንዳልሆነ ይገባኛል! ግን አሁንም ይናፍቀኛል። ለምን? ያኔ እኛ ኢትዮጵያዊያን የቆፈርነው ጉድጓድ ገና ብዙ ጥልቅ አልነበረም! ማለትም በርካታ ችግሮቻችንን በቀላሉ በአንዳንድ ትናንሽ ማስተካከያዎች ልናስወግድ እንችል ነበር። የኔ መሬት በሽ ነበር፤ ደን ነበር፤ ልሂቃኖቻችን ብዙ በማርክሲዝም አልተዋጡም ነበር፤ ጎሰኝነት አልሰፈነም ነበር። ተስፋ ቅርብ ነበር።

አሁን ግን ተጨማሪ ሌላ የ50 ዓመት የጉድጓድ ቁፈራ አካሄደናል። ጥልቅ የሆነ ጉድጓድ ውስጥ ነን። አሁንም ተግተን ሰርተን መውጣት እንችላለን ግን ስራው ከበፊቱ ይልቅ እጅግ ከባድ ነው። ብዙ በጣም የተመላሹ ነገሮች አሉ።

ስለዚህ አዎን የድሮ ስረአት ናፋቂ ነኝ። ግን የምናፍቀው ምክንያት ያኔ ችግሮች ቢኖሩም እንደ ዛሬ ያህል ለማስተካከል አይከብዱም ነበር ብዬ ስለማምን ነው። እንጂ የጃንሆይ ዘመን እና ስረአት ችግሮች አልነበረባቸውም ለማለት አይደለም!

Monday, 17 December 2018

ስለ ህገ መንግስት አንድ የውይይት ሃሳብ

አሁን ያለን የጎሳል አስተዳደር (ethnic federalism) የግጭት መንስኤ እንደሆነ የ27 ዓመት መረጃ አለን ብዬ ተከራክርያለሁ ከጽሁፎቼ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_89.html)። በህወሓት አገዛዝ የነበሩት የጎሳ እና የድንበር ግጭቶች ህወሓት ብቻውን ያካሄደው፤ የቀሰቀሰው፤ ያስተባበረው ብቻ አልነበሩም። ህወሓት በአስተዳደሩ ምክንያት ያሚመጡትን ችግሮች ለራሱ ጥቅም ያባብስ ነበር እና ያሉ ቅራኔዎችን ያባብስ ነበር እንጂ ችግሮችን ከሀ መፍጠር አቅም አልነበረውም። ዛሬም ለምሳሌ የሲዳማ እና ወላይታ ግጭት ስንመለከት አዎን የህወሓት እና ሌሎች ነበሮች እጅ ቢኖርበትም የጎሳ አገዛዙ መሰረታዊ መንስኤ ነው። በዚህ ምክንያት ዛሬ ያለው የጎሳ አስተዳደር ለሀገራችን ሰላም አይሆንም።

አማራጩ ምንድነው የሚለው ጥያቄ ላይ ጊዜ ብናጠፋ ጥሩ የመስለኛል። በዚህ ጉዳይ የተለያየ አቋም ያለን ኢትዮጵያዊያን ስለዚህ ገና ብዙ መነጋገር አለብን እስካሁን በቂ የተነጋገርን አይመስለኝም። ስንወያይም አብዛኛው ጊዜ የራሳችን አቋም ላይ ነው የምናተኩረው እንጂ በቂ ሌላውን አንረዳም።

ዛሬ አንድ አስተያየት ልስጥ… የጎሳ አስተዳደር ደጋፊዎች ኢትዮጵያ የብሄሮች ስብስብ ነው መሆን ያለበት ነው። የመጀመርያ ማንነታችን ጎሳችን ነው፤ ኢትዮጵያዊ ዜግነታችን ሁለተኛ ነው ነው የሚሉት። የሀገር ስሜት አለን ነው። ኦሮሞ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለች ሀገር ናት። ባለቤቷም የኦሮሞ ህዝብ ነው። ግን በታሪክ ምክንያቶች እና ዛሬ ባለው ነባራዊ ሁኔታ አብሮ መኖር ስላለብን ተገንጥለን አንኖርም ብሄሮች እርስ በርስ ውል ይኖራቸዋል ነው። እንደ ብሄር ክልል ወይንም «ትንሽ ሀገር» ከሌለን የሀገራዊ መብታችን ተወሰደ ማለት ነው። ልክ እንደ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚለው ሰው ከኬንያ ጋር በግድ ሙሉለሙሉ ተቀላቅለህ አንድ ሀገር ሁን ቢባል አይ አገርነቴን መጠበቅ እወዳለሁ እንደሚል አማራውም የብሄር ክልል ይቀር ቢባል ማንነቱ እንደተወሰደበት ይሰማዋል ነው። በአጭሩ ይህ አንዱ የጎሳ አስተዳደር ደጋፊዎች አስተሳሰብ ይመስለኛል።

እስቲ ለዚህ አንድ የሚሆን አማራጭ መልስ እንስጥ። ከህገ መንግስቱ «ብሄር ብሄረሰቦች ህዝቦች» የሚለውን በሙሉ አውጥተን ግለሰባዊ ብቻ እናድርገው። ግን አሁን ያሉትን ክልሎች እንጠብቅ። ለክልሎች አሁን ካሉት ተጨማሪ መብቶች እንስጥ። ከዛ የኦሮሚያ «ሀገራዊ» ምስልን እንመልከት። በቋንቋ፤ ባህል፤ ማንነት፤ ወዘተ በኦሮሚያ አብዛኛው ኦሮሞ ስለሆነ የሚኖረው ፍላጎቱ እንዲሰፍን ያደርጋል። ይህ የድምጽ ብልጫ ኦሮሚያ ክልልን ከሞላ ጎደል ኦሮሚያ ሀገር ሊያደርገው ይችላል። ግን ሀገር አይባልም እና ኦሮሞ ዘር ያልሆኑ ከኦሮሞዎች እኩል መብት ይኖራቸዋል። ግን አናሳ በመሆናቸው ብዙ ተጽዕኖ አይኖራቸውም።

ለኔ ይህ አካሄድ የጎሳ አስተዳደርን መጥፎ ጎን ያስወግዳል ማለትም ሁሉ ጉዳያችን በጎሳ የተመሰረተ እንዳይሆን ያደርጋል። አንደኛ/ሁለተኛ/ሶስተኛ ዜጋ፤ መፈናቀል፤ የጎሳ ብቻ ፖለቲካ ወዘተ እንዳይኖር ያደርጋል። ግን የጎሳ ወይንም ብሄር መብት ያስከብራል። በዚህ በጎሳ መብት ማስከበር ከጎሳ አስተዳደር ብዙ ልዩነት አይኖረውም።

ይህ አንድ የመሃይም ለውይይት የቀረበ ፕሮፖዛል ነው። የጎሳ ብሄርተኞችን ፍላጎት ያሟላ ይሆን። የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ፍላጎትስ?

Sunday, 21 October 2018

የዜግነት ፖለቲካ ከባድ ነው!

አንታለል፤ የዜግነት ፖለቲካ ከባድ ነው። የንጉሳዊ አገዛዝ እና ማርክሲዝምን የለመደ ህብረተስብን ወደ ዜግነት ፖለቲካ ማስገባት ግዙፍ ሸክም መጎተት ማለት ነው። የዜግነት ፖለቲካ እንደ ጎሳ ፖለቲካ ተጨቁነናል፤ ተንቀናል፤ ደምና አጥንታትችን አንድ ነው፤ ሀገሪቷ ችግር ውስጥ አለች እና እየተጠቃን ነው ስለዚህ ወደኛ ተሸግሸጉ፤ ወዘተ ብሎ ድጋፍ መሰብሰብ ያችልም።

1. የዜግነት ፖለኢትካ primordial አይደለም። ህዝብን ሆ! ብሎ መሰብሰብ አይችልም። ስልት ያስፈልገዋል። ስልት አያስፈልገኝም እና በstreet ፖለቲካ ልሳተፍ ማለት አይችልም። ይህ ውድቅ የነ አካሄድ ነው።

2. የዜግነት ፖለቲካ ከጎሳ ፖለቲካ ጋር ያለው ግንኝነት asymmetric ነው። ከጎሳ ፖለቲካ ጋር በተመሳሳይ ታክቲክ ፊትለፊት ግብ ግብ ልግባ ካለ ይሸነፋል። ምክንያቱ የጎሳ ፖለቲካ የስሜታዊ advantage አለው። ለምሳሌ 1) የጎሳ ፖለቲካ ከተተቸ «ጎሳዬ እየተጠቃ ነው» ብሎ ይጮሃል። እንዲህ ሲጮህ ለዘበተኞቹንም ወደሱ ሊያመጣ ይችላል። 2) የሀገሪቷ ጠቅላላ ሁኔታ (ፖለቲካ፤ ኤኮኖሚ፤ ጸትታ ወዘተ) እየተበላሸ ከሄደ የጎሳ ፖለቲካ «የነሱ የጠላቶቻችን ጥፋት ነው» ይላል። «ወደኛ ተሸሸጉ» ይላል። እንዲህ በማለት ተከታይ ይሰበስባል። ስለዚህ ይህን asymmetric ሁኔታ ተገንዝበን ተገቢውን ስልት መጠቀም አለብን።
ሁሉም የኢትዮጵያ ፖለቲካ ከቅራኔ መፍታት ዘገምተኝነት በሽታ ይጠቃል (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_21.html)። ምቀኝነት፤ በግልጽ አለመነጋገር፤ አለመቆርቆር (empathy)። መጠርጠር። ሃሳብ እና ግለሰብን ማቆራኘት። ወገናዊነት። ስም ማጥፋት። ቂም። ግትርነነት ወዘተ። በነዚህ ምክንያት በርካታ ጊዜ የራሳችንን ጥቅምንም እንጎዳለን ሌላውን ለማጥቃት ስንል! በዚህ ምክንያት ነው አብሮ መስራት፤ ቅራኔ መፍታት እና win-win ሁኔታዎችን ማየት እና መፍጠር የሚያቅተን። ይገ ዜግነት ፖለቲካም የጎሳ ፖለቲካም እነዚህን ችግሮችን ማሸነፍ አለባቸው። ግን ለጎሳ ፖለቲካ ይቀላል። «ጠላት አለን» የሚባለው ነገር ሰውን ሳይፈልግም እንዲተባበር ያደርጋል። የሚአይተባበሩ ደግሞ ሀውሓት፤ ሻዕቢያ፤ ኦነግ ሌሎች የጎሳ ድርጅቶች እንዳሳዩት በቀላሉ ይረሸናሉ። የ 'survival' ጉዳይ ነው ተብሎ ይሳበባል። የዜግነት ፖለቲካ ግን ይህን አማራጭ የለውም። ከባድ የሆነውን የፖለቲካ ባህል ለውጥ ስራን ግድ መስራት አለበት።

3. የዜግነት ፖለቲካ ለዘብተኛ እና መካከለኛውን መንገድ መውሰድ አለበት። ጽንፈኝነት በጎሰኞቹ ተቆጣጥሯልና። የዜግነት ፖለቲካ ሁሉንም አይነት ፍላጎት በተቻለ ቁጥር ሚዛን ላይ አድርጎ ማስተናገድ አለበት። «ትልቅ ዛንጥላ» መሆን አለበት፤ አቃፊ መሆን አለበት። የዜግነት ፖለቲካ የማስወገድ፤ የመግደል፤ የመረሸን፤ የመጨቆን፤ የማጥቃት ወዘተ አማራጭ የለውን። እንዲዚህ ነገር ውስጥ ከገባ የዜግነት ፖለቲካ ማንነቱን ያጣልና የጎሰኝነት ፖለቲካውን ይሆናል። በጎሳ ፖለቲካው ይሸነፋል። ምሳሌ ልስጥ፤ ዛሬ ዜግነት ፖለቲካ ደጋፊዎች ሁለት አይነት አስተሳሰብ አለ ስለ ጎሳ ፖለቲካ። የአንዱ አቋም «ህገ መንግስቱ ዛሬውኑ ካልተቀየረ አቃቂ ዘራፍ» የሚል ነው። ብዚህ ጉዳይ ድርድር የለም ይላል። ሌላው ጎራ ደግሞ «ህገ መንግስቱ መቀየር አለበት ግን ይህን ለማድረግ ገና አሁን ወቅቱ አይደለም፤ መጀመርያ ንግግር እና ድርድር ማድረግ አለብን» ይላል። ሁለተኛው ነው ለዘብተኛውም ሚዛናዊውም መንገድ። ይህ ለዜግነት ፖለቲካ ግድ ነው።

4. ችግር እና ሁከት የዜግነት ፖለቲካን ይጎዳል የጎሳ ፖለቲካን ያጠነክራል። (ያው ይህ ይሚያስኬደው እንደ ኢትዮጵያ አይነት የጎሳ ፖለቲካ ያለበት ሀገር ነው።) ችግር ሲኖር ሰው ወደ ጎሳ የመሸግሸግ ባህሪ አለው። የደርግ ሁከት እነ ሻዕቢያ፤ ህወሓት እና ኦነግን በጣም አጠነከረ። ዛሬም አማራ ላይ ጥቃት ሲፈጸም የአማራ ብሄርተኝነት ንቅናቄ እየጠነከረ ይሄዳል። ስለዚህ የዜግነት ፖለቲካ በአብዮት መምጣት አይችልም አብዮት ሁከት ነውና። ብዙዎቻችን ኢህአዴግ በአብዮት («ስር ነቀል ለውጥ») መገልበጥ አለበት ስንል የአብዮቱ ውጤት የዜግነት ፖለቲካ ይሆናል ብለን አስበን ነበር። ይህ ታላቅ ስህተት ነው። ዛሬም የዜግነት ፖለቲካ ጭላንጭል ማየት የቻልነው ለውጡ አለ አብዮት ስለመጣ ነው። አለ ሁከት ስለመጣ ነው።

5. ሁላችንም እንደምናውቀው የዜግነት ፖለቲካ አራማጆች እስካሁን ታሪካችን ጥሩ አይደለም። ፖለቲከኞቻችን፤ ጋዜጠኞቻችን አክቲቪስቶቻችንም አብሮ መስራት አልቻሉም። የቅንጅት ታሪክ ይህን ታላቅ ሽንፈታችንን በድምብ ይገልጻል። ይህ በመሆኑ ዛሬ የዜግነት ፖለቲካ ድርጅቶች እጅግ ደካማ ናቸው። የዜግነት ፖለቲካ የሚደግፈው ብዙሃን ብዙ ነው፤ ይህ የቅንጅት ታሪክም ይመሰክራል። ግን ይህ ግዙፍ ብዙሃን በድርጅት፤ ልሂቃን እና ፖለቲከኛ በአግባቡ አልተወከለም። ስለዚህ ዛኢረ የዜግነት ፖለቲካ የመጀመርያ ግብ መዋቅር ማለትም ድርጅትን ማጠንከር ነው መሆን ያለበት። አለ በቂ መደራጀት ምንም ማድረግ አይቻልምና። ሁሉም የዜግነት ፖለቲካ ተቀናቃኞች ሙሉ አቅማቸውን (resources) በዚህ ጉዳይ ላይ ማዋል አለባቸው። ምርጫ የለም። ሌሎች የጊዜያዊ ስራዎች ውሃ ቀዳ ውሃ ድፋ ነው የሚሆነው። ለዜግነት ፖለቲካ strong organizations are a precondition to any success።

6. የዜግነት ፖለቲካ ገና መደራጀት ላይ ስለሆነ ጠላትን ማፍራት የለበትም። እንደ ጠ/ሚ አቢይ ሁሉንም ማቀፍ መቻል አለበት። ጠላት ካፈራ የመደራጀት ስራው ይደናቀፋል። ስለዚህ ሌሎችን በአግባቡ በጥሩ ሁኔታ ይዞ የራሱን ስራ መስራት ነው ያለበት። ይህ basic ፖለቲካ ነው ግን አንዳንዶቻችን ፖለቲካን እንደ ሃይማኖት ጥቁር እና ነጭ አድርገን ስለምናይ ወደ ቀላል ስህተት እንገግባለን። ገና ሳንደራጅ፤ ገና ሳንጠነክር ወደ ጦርነት ካልገባን እንላለን። ይህ ለዜግነት ፖለቲካ አይሆንም።

7. «የወሬ ፖለቲካ» ለዜግነት ፖለቲካ አይሆንም። የወሬ ፖለቲካ ማለት ተቃራኒዎችን በወሬ ዘመቻ ማጥቃት እና የራስን ወገን እንደ ሰለባ አድርጎ ማውራት። የጥላቻ ፖለቲካ ማለት ነው። የወረ ፖለቲካ አላማው ህዝቡ ተናዶ እንዲነሳ ማድረግ ነው። ካላይ እንዳስረዳሁት ህይ አይነት አካሄድ ለጎሳ ፖለቲካ ነው የሚጠቅመው እንጂ የዜግነት ፖለቲካ (ስሜታዊ ስላልሆነ) እንዲህ አይሰራም። ለዚህ ደግሞ የ27 ዓመት ማስረጃ አለን። ለ27 ዓመት እኛ ተቃዋሚዎች ወያኔ ሴጣን ነው ብለን ብንቾህ ምንም አልሰራም። ለውጡ የመጣው ህዝቡ የትግሬ የባላይነት በተግባር ሰልችቶት ነው እንጂ ኢሳት ስለነገረው አይደለም። ለ27 ዓመት ስለ ወያኔ ከማውራት አቅማችንን በመደራጀት ስራ ብናውል ወያኔ ገና ድሮ ወርዶ ነበር።

8. አንዱ ከላይ ከጠቀስኳቸው የፖለቲካ «ጎጂ ባህሎች» የሁሉም አሸናፊ (win-win) ውጤት አለማወቅ ነው። ይህ እንዳልኩት የዜግነት ፖለቲከኞች እና ተቀናቃኞች ይበልጥ የሚጠቁበት በሽታ ነው። (የጎሳ ፖለቲከኞች በጎሳ ስሜት ስለሚቆጣጠሩ ይህ ችግር ቢኖራቸውም አነስተኛ ነው።) ይህ በቅንጅት እና ቀጥሎ ባለው ታሪክ በደምብ ይታያል። ገና ትንካሬ ሳይሰበሰብ ስለ ፖለቲካ ክፍፍል ማሰብ፤ ስለ ስልጣን ማሰብ። ትንሽ ስልጣን በግዙፍ መዋቀር ከሚኖረኝ ትልቅ ስልጣን በባዶ መዋቀር ይሻላል የሚል አስተሳሰብ ነው። ይህን ማስወገድ ማለት አለብን። አብሮ ከሰራን ትልቁን ውጤት አምጥተን ለሁላችንም በቂ ስልጣን ይኖራል (ፖለቲከኞች)።

9. ባለፉት የ50 ዓመት የፖለቲካ ታሪካችን በተለይም አብዮት እና ሁከት የዜግነት ፖለቲካ ወይንም የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ልሂቃን ጎራ ተገድሎ፤ ተሰድዶ፤ እርስ በርስ ተፋጅቶ ቁጥሩ መንኗል (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_38.html)። የዜግነት ፖለቲካ መዋቅሮቻችን የደከሙበት ምክነያት አንዱ ይህ ነው። እነ ኃይሉ ሻውል፤ ብርሃኑ ነጋ እና ልደቱ አያሌው የቅንጅት ዋና መሪዎች ሆነው ሲገኙ በሺዎች የሚቆጠሩ የፖለቲካ ልሂቃን ሞትዋል፤ ተሰዷል ወይን ፖለቲካ ኮሬንቲ ነው ብሎ ትቶታል። ስለዚህ እነ ብርሃኑ ነጋ ከዚህ የተረፉት ጥቂቶች ናቸው። እነሱ ሲደናቀፉ የሚደግፋቸው ወይንም ቦታቸውን የሚወስድ ማንም አልነበረም። የህ የልሂቃኑ መመንመን ዛሬም ሚና ይጫወታል። ሁለት የዜግነት ፖለቲካ ልሂቃን ትውልድ ነው ያጣነው። አዲሱ ትውልድም «አለ አሳዳጊ» ነው ያደገው። ይህን ችግር ተገንዝብን የሚያስፈልገውን የአካሄድ ለውጦች ማድረግ ይኖርብናል።

10. እውናትዊ የዜግነት ፖለቲካ ለብዙ አይነት ሃሳቦች መቆርቆር አለበት (empathy)። ሚዛናዊ መሆን ስላለበት። አንዱ የብዙ የዜግነት ፖለቲካ ተከታዮች ችግር ለጎሳ ፖለቲካ ምንም አለመቆርቆር ነው። የጎሳ ፖለቲካ ከዘረኝነት ውጭ ምን እንደሆነ አይገባንም ወይንም ሊገባን አንፈልግም። ይህ ታልቅ ድክመት ነው። ሌላውን አለማወቅ፤ ተቃራኒውን በአግባቡ አለማወቅ ታልቅ ሽንፈትን ያመጣል። የጎሳ ፖለቲካ ዓለም ዙርያ ያለ ነገር ነው ከነ አውሮፓ እና ሰሜን አሜሪካ። «ዘረኝነት ነው» ብሎ መሰየሙ የውሸት ማቅለልያ ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2017/11/whats-ethnic-nationalism-again.html)። እውነት ነው በርካታ ዘረኞች የሆኑ ጎሳ ብሄርተኞች አሉ። ግን «ዘረኝነት» የጎሳ ፖለቲካን ሙሉ በሙሉ አይገልጸውም። የጎሳ ብሄርተኝነት ጎሳውን እንደ ሀገር (nation) ማየት ማለት ነው። ይህ ደግሞ ስሜት ነው፤ ማንነት ነው። እንደዚህ አይነት ነገር በlogical ሙግት አይቀየርም። ስልት ያስፈልጋል። ለዘብተኞቹን ማቀፍ ያስፈልጋል። ህዝብን በመቀላቀል አንዱ የሌላውን ቋንቋ እንዲያውቅ ብማድረግ የሃገር ውስጥ መዘዋወር እንዲጨምር በማድረግ ህዝብ እንዲወሃድ መባድረግ ነው ችግሩ የሚፈታው። ዝም ብሎ መጮህ ጉዳት ነው የሚያመጣው። የለዘብተኛ (moderate) አስተሳሰብ ነው እንዲህ አይነቱን ነገር ሊገነዘብ የሚችለው።

Thursday, 23 August 2018

ስለ አማራ ብሄርተኝነት ንቅናቄ ልሟገት

እስቲ በጠ/ሚ አብይ የተለምዶ አካሄድ (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/08/blog-post_10.html) ልጀምር… የድሮ ንጉሦቻችን ታላቅ ውሳኔዎች ለመወሰን ዘንድ አማካሪዎቻቸውን ሰብስበው ጉዳዩን እየገለባበጡ ከጫፍ እስከ ጫፍ ተሟገቱበት እና ፈትሹት ይሏቸው ነበር። አማካሪዎቻቸው ሁሉንም የሚቃረኑትን ሀሳቦችን ወክለው እርስ በርስ ተከራክረው አሸናፊውን (አሸናፊዎቹን) ለንጉሡ ያቀርባሉ። ንጉሡ ይህን መረጃ ተጠቅመው ይወስናሉ። ይህ ትውፊታችን ነው።

በአማራ ብሄርተኝነት ፅንሰ ሃሳብ አልስማማም። ሆኖም ሃሳቡን በሚገባው ለመረዳት እና ለመፈተሽ ሃሳቡን ደፌ ለመሟገት እወዳለሁ። በአማራ ብሄርተኝነት እና ኢትዮጵያዊ ብሄርተኝነት ያለው ውይይት ትንሽ የረከሰ ነው ማለት ይቻላል። ውይይትም ማለት አይችላልም። በስድብ፤ ዘለፋ እና በመግባባት እጦት የተሞለ ነው። አንዱ ወገን (እዚህ ላይ እራሴን አካትቼ ነው የምናገረው) ለሌላው ወገን አይቆረቀሩምጅ("empathy" የለም)። የዚህ ጽሁፍ አንዱ አላማ ይህንን ለማስተካከል ነው።

ሌላው አላማ ይውይይት ነጥቦቹን ለማጠንከር ነው። ይህን ማድረግ የሚቻለው የሌላውን ወገን ክርክሮች ስንመለከት ጠንካራ ጎኑን (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_21.html) በማየት ነው። ፉክክር ላይ ደካማ ጎን ላይ እናተኩራለን። ገምቢ ውይይት ላይ ግን ጠንካራ ወገን ላይ ነው ማተኮር ያለብን። ስለዚህ ከአማራ ብሄርተኝነት መከራከርያ ነጥቦቻቸው ደካማ ወይንም ስሜታዊ ወይንም መሰረት የሌላቸውን ነጥቦች ትተን ምክንያት እና አቅም ያላቸውን ነጥቦች ማየት ይገባል።

ክዚህ ጽሁፍ ልመልሰው የምፈልገው ጥያቄ ይህ ነው፤ « ለመን በአማራነት መደራጀት አስፈለገ በኢትዮጵያዊነት መደራጀት አይሻልም ወይ?»። ለዚህ ጥያቄ አጭር መልሱ ይህ ይመስለኛል፤

1. የጎሳ ብሄርተኝነት አሁንም በኢትዮጵያ ዙርያ ሰፍኗል እያደገም እያለ ነው እነ ጠ/ሚ አብይ ለመቀነስ ምንም እየሞከሩ ቢሆንም። የጎሳ ብሄርተኝነት በደምብ ያልነገሰው ቦታ የአማራ ክልል ነው። ሌሎች ክልሎች በሙሉ ፖለቲካቸውን በጎሰኝነት እና ጎሰኝነት ብቻ አደራጅተዋል።

2. የዛሬው ሁኔታ ይህ በመሆኑ እና ሀገሪቷ ለ27 ዓመት በጎሳ አስተዳደር ፕሮፓጋንዳ መሞላቱ ለአማራው ህልውና እና ጠቃሚ ስልት (strategy) ሲባል ለአማራው በጎሳ ብብሄርተኝነት መልክ መደራጀት ይመረጣል በኢትዮጵያዊነት ወይንም አንድነት ከመደራጀት ይልቅ።

3. የአማራ ህዝብ ላለፉት 27 ዓመት ስለተጨቆነ እና የሀገራዊ ብሄርተኝነት ራዕይ አልሰራም የሚል አመለካከት አንዳንዱ ላይ ስላለ የአማራ ህዝብ የሀገራዊ ብሄርተኛ የሆኑት ድርጅቶችን ደግፍ ቢባልም በሙሉ ልቡ አይደግፍም።

4. ሀገሪቷ በጎሳ ብሄርተኝነት ስለጥለቀለቀች ከአማራ ውጭ ለሀገራዊ ብሄርተኝነት ያለው ድጋፍ እጅግ ዝቅተኛው ነው የሚሆነው። የነ ለማ ቡድን ኢትዮጵያ ብሄርተኛ ቢሆንም ፖለቲካ ውድድር ቢካሄድ (እንደ ምርጫ) የኦሮሞ ብሄርተኞች በቀላሉ እነ ለማ ቡድንን ያሸንፏቸዋል። ሰለዚህ በመጨረሻ የሀገራዊ ብሄርተኛ ፓርቲዎች ከአማራ ውጭ ኢሚንት ድጋር ይኖራቸዋል በአማራ ክልል ደግሞ ደካማ ድጋፍ ይኖራቸዋል። ስለዚህ ሀገር ዙርያ ሲደመር የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ንቅናቄው ደካማ ይሆናል ከጎሳ ብሄርተኝነት አንፃር። የጎሳ ብሄርተኝነት በደምብ አይሎ አሸናፊ ሆኖ ይገኛል።

5. ይህ ብዙ ድጋፍ የሌለው የኢትዮጵያ ብሄርተኝነት ፓርቲ የኢትዮጵያ ብሄርተኝነትን የሚደግፈው ህብረተሰብ ከነ አማራውን በሚገባው መወከል አይችልም ኃይሉ ከጎሳ ብሄርተኞች እጅግ ደካማ በመሆኑ። በድርድር ጠረጵዛ፤ ፓርላማ፤ ወይንም በፖለቲካ ኃይል ሙግት የሀገራዊ ፓርቲው ይጨፈለቃል።

6. ገን አማራው በአማራ ብሄርተኝነት ስር ከተደረጀ ለአመታት የተከማቸውን ብሶት እንደ ኃይል ተጠቅሞ ጠንካራ አማራውን በማንኛውም ደረጃ መወከል የሚችል ድርጅት ይገነባል። አሁን ባለው የጎሳ ብሄርተኝነት ያጥለቀለቀው የሀገራችን የፖለቲካ ሁኔታ የአማራ ህዝብን የብሶት ስሜት እንደ ኃይል ተጠቅሞ ጠንካራ እና ቋሚ ድርጅት ማቋቋም ለአማራው ህልውና ግዴታ ነው።

7. ጠንካራ የአማራ ፓርቲ ከተቁቁመ ሌሎች የጎሳ ፓርቲዎችን በኃይል ሚዛን ይይዛቸዋል። ምክንያቱም የአማራ ብሄርተኛ ፓርቲው የጎሳ ፓርቲ ቢሆንም አማራ ጎሰኝነት በባህሪው ከኢትዮጵያ ብሄርተኝነት የተቆራኘ ስለሆነ። በዚህም ብምክንያት የአማራ ብሄርተኝነት ፓርቲው ከክልል ውጭ ላሉት አማሮች ያገለግላል።

እኔ እንደሚመስለኝ የአማራ ብሄርተኝነት ንቅናቄ መኖር ምክንያት ባጭሩ ይህ ነው።

እስካሁን ባየሁት የተለየዩ ሰዎች አስተያየት ሌሎች የክርክር ነጥቦች ይነሳሉ። ለምሳሌ «አምራ ከሁል ተጨቁኗል»፤ «ሌላው ሲደራጅ ልምን አማራ ይጠየቃል»፤ «በአማራ ብሄርተኝነት ምን አገባችሁ»፤ «ኢትዮጵያዊ ድርጅቶች በአማራ ትከሻ ላይ ነው የተቁቁሙት»፤ «የአንድነት ኃይሎች አማራን ዘርፈውታል ነግደውታል»፤ «የአንድነት ኃይሎች ሌቦች ናቸው» ወዘተ። እነዚህ ስሜታዊ፤ ከመሰረተ ጉዳዩ ውጭ፤ ወይንም ሃሰት የሆኑ የክርክር ነጥቦች ስለሆኑ አልተጠቀምኳቸውም ክርክሩን ያደክማሉ እና።

ስለዚህ የአብን ከአንድነት ይልቅ በአማራነት መደራጀት ምክንያት እንዲህ ነው። እስቲ ህልችሁም በሁለቱም ወገን ያላችሁ ይህን አንብቡ እና እናንተም ከአቋማችሁ ተቃራኒ የሆነውን ወገን ይዛችሁ መከራከር ሞክሩ። እንዲህ እያደረግን ወደ መስማማት ወይንም በሰላም ላለመስማማት ደረጃ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/10/blog-post.html) እንደርሳለን ብዬ እገምታለሁ።

Thursday, 4 January 2018

Freeing Political Prisoners

Undoubtedly most of you have heard that the Ethiopian government is going to free all political prisoners, or pardon those who have broken laws concerning treason and terrorism, or some such thing. Anyway, it appears that many of the known political prisoners will be freed.

This is a great measure. I don't think anyone could say otherwise. A lot of these folks have been suffering cruelties at the hands of the security apparatus, cruelties unbecoming Ethiopia. The Ethiopian tradition is, as practiced in the past, honour and civility and magnanimity. Political prisoners, even those who were a grave threat to the ruling monarch, were imprisoned, preferably far away, on Mount Wehni for example, but given a comfortable imprisonment, if there is such a thing. Modern torture, or ancient torture for that matter, was unthinkable. If anyone even happened to hear of such a thing, they would have immediately thought it dishonourable and dismissed it out of hand.

So, this is a step that shows magnanimity, honour, and civility, it's good for the country, but most of all, it is good for the prisoners, who have been bearing on their shoulders the guilt of all of us Ethiopians.

Nevertheless, a note of caution. Remember what happened that last time several high-profile political prisoners were released. The opposition descended into a downward spiral from which it has not recovered to this day. And yes, I am not forgetting the release of Birtukan Mideksa, but I shudder to recall it and what she went through in the prison. All I can say is, may God bless her and keep her and may God forgive us for what we have done to her and all the unknown Birtukans out there.

I humbly urge all of us Ethiopians to keep in mind today that Rome was not built in a day, and when the EPRDF deigns to do something good and noble is not the time to shout and scream for it to step down from power. There is nobody to replace the EPRDF. Our past 50 years of history, including our elite's long suicide from 1960 to 1991 as well as the EPRDF's monopoly on power has made sure that the protests of the grassroots have no viable elite to lead them. Today is the time to renew our efforts to work on feasible, yes, feasible, politically realistic projects to improve our political and social environment. In our little small circles. We're not all kings and we're not meant to be. A good deed is worth a thousand good words. The line between good and evil cuts through all our hearts. Let's point our fingers at ourselves, particularly those of us in the diaspora who have betrayed our country by leaving it, and see how we can fix ourselves and our surroundings. Maybe then we can build a solid grassroots capable of growing and nurturing a political elite that is a viable foil and partner for the EPRDF.

Tuesday, 25 October 2016

An Exercise in Empathy

2009/2/15 (Ethiopian calendar)
2016/10/25 (European calendar)

(pdf)

[Note: An Amharic version of this post will appear sometime!]

In the next few posts, I will attempt, just attempt, an exercise in empathy. I will try and put myself in the shoes of Ethiopia's various political groups and constituencies and describe the truth about Ethiopian politics how they see it – from their perspective. I will start with either Oromo ethnic nationalists or the EPRDF, or maybe just the TPLF. And I'll keep going as much as I can.

Why this exercise? I'll first answer from within the 'conflict resolution' paradigm. Empathy – trying to grasp the point of view, the feelings, the thoughts, etc of others – is an important tool, perhaps the most important, in conflict resolution. The idea is that if you can empathize, you can communicate better, that is you can communicate in a way that your opponents can understand, and of course you can better envision solutions that your opponents can accept. Empathy also builds trust and understanding, which needless to say are important for living together peacefully.

Second, as this blog is written from an Orthodox Christian perspective, I'll explain from this point of view as well. Empathy is basic Christianity. Our fundamental belief is that Christ came and died for us out of compassion – to share our suffering and redeem it. This is similar to empathy, but greater, as it involves not only sharing the Other's experience, but doing so with the hope of bring about something better. Further, avoiding judgement is a basic teaching of the Church. “To judge sins is the business of one who is sinless, but who is sinless except God?... To judge a man who has gone astray is a sign of pride, and God resists the proud.” says St Dorotheus of Gaza. So, following Christ's example of compassion and his command not to judge, a Christian as a matter of course must try to be empathetic.

I hope my little exercise will help shed some light on solutions for Ethiopia's problems. So, I'll give it a try over my next few articles. Your feedback as always is much appreciated.