Monday 4 March 2019

የጎሳ ፌደራሊዝም ችግር አንድ ነው፤ የግጭት መንስኤ ነው!

ዛሬ አንድ ሁለት ውይይቶች ስለ ሀገራችን «የጎሳ ፌደራሊዝም» ተመልክቼ ነበር። ውይይቶቹ ያተኮሩት በጎሳ ፌደራሊዝም እንደ ጽንሰ ሃሳብ ነው። ተናጋሪዎቹ ታሪክን እና ርዕዮት ዓለምን ፈትሸው የጎሳ ፌደራሊዝም ለሀገራችን ይበጃል ወይንም አይበጅም ብለው ተከራከሩ። Of course ውይይት/ክርክሩ የትም አልደረስም። The participants, as usual, talked right past each other።

በመጀመርያ ደረጃ አንዱ የሌላውን ፍላጎት የማይረዳበት ውይይት ውይይት አይደለም። ስለ ጎሳ ፌደራሊዝም የሉን ውይይቶች እንዲህ ናቸው። እኛ አቋማችንን እንናገራለን ሌላውም እንዲሁ አንድ ሌላው አይገባውም ውይይቱም ባለመግባባት ያልቃል።

ይህ የሚሆንበት አንዱ ምክንያት የውይይት እና ቅራኔ መፍታት ስልት በማጣት ነው። ግን አሁን ማተኮር የምፈልገው እዚህ ላይ አይደለም። ሁለተኛው ምክንያት ነው፤ ይህ ደግሞ የጎሳ እና ማንነት ጉዳይ ስሜታዊ በመሆኑ ለውይይት አይመችም። አይሆምም ማለት ይቻላል። «እኔ መጀመርያ ኦሮሞ ነኝ ቀጥሎ (ምናልትባት) ኢትዮጵያዊ» ሲል አንዱ ሌላው «እንዴት እንዲህ ትላለህ» ብሎ ሁለቱም በስሜታቸው ይመራሉ። አንዱ ሌላውም ማሳመን አይችልም።

ለዚህ ነው በጎሳ ፌደራሊዝም ጉዳይ ታሪክን እና ርዕዮት ዓለምን ፈትሸን መከራከር የትም የማያደርሰን። በጎሳ ፌደራሊዝም የሚያምን እና የጎሳ ፌደራሊዝምን የሚጠላው ሁለቱም ምክንያቶች በመሰረቱ ስሜታዊ የማንነት ናቸው። እነዚህን በርዕዮት ዓለም እና ታሪክ (in the eye of the beholder) ማስታረቅ አይቻልም።

ሁለቱን ጎራዎች ለማግባበት ወደ ሌላ level መሄድ ያስፈልጋል። ይህ ደረጃ እንዲህ ነው፤ እኔ የጎሳ ፌደራሊዝም ለኢትዮጵያ አይሆንም የምልበት ምክንያት ታሪክ እና ርዕዮት ዓለም ሳይሆን በ evidence ምክንያት ነው። የ24 ዓመት ታሪክ ከነ ያለፈው አንድ ዓመት የለውጥ ዘመን ታሪክ የሚያሳየው የጎሳ ፌደራሊዝም የግጭት መንስኤ መሆኑ ነው። የጎሳ ፌደራሊዝም በጎሳዎች መካከል በርካታ ግጭቶች እንዲኖሩ አድርጓል። ሰዎች በጎሳቸው ምክንያት የሚጎዱበት ዘመን አምጥቷል። ይህ ጉዳት ለተወሰኑ ጎሳዎች ብቻ ሳይሆን በመላው ሀገሩ ነው። ለዚህ በርካታ የ25 ዓመት evidence አለ።

ለዚህ ነው የጎሳ ፌደራሊዝም መቀየር አለበት ብለን መከራከር ያለብን። የ24 ዓመት የጭቆና እና የአንድ ዓመት የአንጻራዊ ነጻነት መረጃ የሚያሳየን የጎሳ ፌደራሊዝም ህግ እና መንፈስ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎቻችንን እንደጎዳ ነው። ሶማሌ በሶማሌነቱ፤ ኦሮሞ በኦሮሞነቱ፤ ጊዴኦ በጊዴኦነቱ፤ አማራ በአማራነቱ፤ አንዋክ በአንዋክነቱ፤ ወላይታ በወላይታነቱ፤ ስዳማ በሲዳማነቱ፤ ወዘተ ተጎድቷል። የጉዳት ፈጻሚዎቹም እንዲሁ የተለያዩ ናቸው። «ህወሓት» ወይንም የህወሓት አሽከሮች ብቻ አይደሉም ጨቋኞቹ። ህዝቡ እራሱ ይጭቋቆናል። ለዚህ በርካታ መረጃ አለን።

አንድ ታካቅ መራጀ ደግሞ የሁሉም ጎራ ፖለቲከኞች «ካልተጠነቀቅን እርስ በርስ እንፋጃለን» ማለታቸው ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/blog-post.html)! የጎሳ ፌደራልዚምን የሚደግፉትም የማይደግፉትም የጎሳ እልቂት is right around the corner ብለው ደጋግመው ይነግሩናል። ለጎሳ ፌደራሊዝም ከዚህ የባሰ indictment የለም!

ስለዚህ ለ«ዜግነት ፖለቲካ» ደጋፊዎች እና ሌሎች የዚህ የጎሳ ፖለቲካ የሚጠሉ ሰዎችን የምመክረው፤ ስሜትን በሃሳብ አትከራከሩ፤ የትም አትደርሱም። በመሰረቱ የጎሳ ፌደራሊዝም ሰውን የሚጎዳ ባይሆን ምን ችግር አለው? ምንም። የጎሳ ፌደራሊዝም ኢትዮጵያን በሰላም ቢያስተዳደር እኔ የሚጀመርያ ደጋፌው ሆን ነበር። ግን አይደለም። ሃቁ ይህ ነው። የጎሳ ፌደራሊዝም የምንጠላው የግጭት እና ጭቆና መንስኤ ስለሆነ ነው። ይህ ደግሞ በመረጃ የተመሰረተ statement ነው። ክርክራችን በታሪክ እና ርዕዮት ዓለም የተገደባ ሳይሆን ሙሉ በሙሉ መረጃ የተመሰረተ ነው። ይህ መከራከርያ መንገድ ነው አዋጪ ብዬ የማስበው።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!