የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Friday, 22 June 2018
ኤርትራ
ደርግ ከስልጣን ሲወርድ ጀምሮ ለሰባት ዓመት ህወሓት እና ሻዕብያ ከሞላ ጎደል አብረው ኢትዮጵያን ገዝተዋታል። አዎን የኢትዮጵያ መንግስት በህወሓት ነበር የሚመራው ግን በህውሓት ፈቃድ እና ድጋፍ ሻዕብያ እንደ «ሁለተኛ መንግስት» ይንቀሳቀስ ነበር። የኤርትራ መንግስት አካላት ከነ ደህንነት ክፍሉ ኢትዮጵያ ውስጥ በይፋም በስውርም ይሰራ ነበር ስልጣንም ነበረው። የኤርትራ መንግስት እና ባለ ሃብቶች በኢትዮጵያ መንግስት ፖሊሲዎች ታላቅ ሚና ይጫወቱ ነበር። ኤርትራ ከብሄራዊ ባንክ ገንዘብ ታገኛ ነበር። ኤርትራዊ ባለ ሃብቶች በምስና የባንክ ብድር፤ የምንግስት ኮንትራት፤ የቀረጥ ነጻ መብት ወዘተ ያገኙ ነበር። ኤርትራዊያን ቡና አለቀረጥ ከኢትዮጵያ ገዝተው ወደ ውጭ ሀገር ይሸጡ ነበር። ወዘተ፤ ምሳሌዎቹ ማስረጃዎቹ በርካታ ናቸው ተመዝግበዋል በአዲሱ የመንግስት ግልጽነት አካሄድ ደግሞ ይበልጥ ወደ ይፋ ይወጣሉ። ድምዳሜው ግን ከ1983 እስከ 1991 የኤርትራ መንግስት እና ኤርትራዊያን ባለ ሃብቶች ኢትዮጵያ ውስጥ አግባብ ያልሆነ ተጽኖ እና ስልጣን ነበራቸው።
ግን ይህ ሁኔታ ሊቀጥል አይችልም ነበር። ምክንያቱም የሀገር ገዥ የነበረው ህወሓት ኢትዮጵያን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር ይፈልግ ነበር። የሀገር መንግስት ሆኖ ልምንድነው ሌላው ሁለተኛ ምነግስት የሚያስተናግደው? ህወሓት የኢትዮጵያን ስልጣንን እና ከኢትዮጵያ የሚገኘውን ጥቅም ለራሱ ይፈልግ ነበር። ኢህአዴግ ውስጥ ያሉት አጋር ፓርቲዎችም እንዲሁም ኢትዮጵያ ከኤርትራ ተጽኖ ነጻ መሆን አለበት እራሳችን ሙሉ በሙሉ መግዛት አለብን የሚል አቋም ነበራቸው። በዛው መጠን ሻዕብያ በኢትዮጵያ ያለውን ጥቅም እና ስልጣን መልቀቅ አልፈለገም። በዚህ ጉዳይ መደራደር አልተፈለገም ተፎካካሪዎቹ በጡንቻ መጋጠም ወሰኑ። በአጭሩ ይህ ነበር የህወሓት እና የሻዕብያ ግጭት እና የጦርነቱ ምንጭ።
ከጦርነቱ በኋላ በህወሓት እና ኢህአዴግ ክፍፍል ምክንያት ወደ «ጦርነትም ሰላምም የለም» ("no war no peace") ዘመን ገባን። ለምን እስከ መጨረሻ ሄደን አሰብን አልወሰድንም ሻዕብያን አላፈርሰንም የሚሉ ነበሩ። ስለዚህ የህወሓት የፖለቲካ ስምምነት ያንን ባናደርግም ኤርትራን በማግለል ሻዕብያን እንጎዳለን ሆነ። ሻዕብያ በኢትዮጵያ አሳቦ የሀገራቸውን ኤኮኖሚ እና የህዝብ ሞራል ይገላል እና ቀስ ብሎ ይወድቃል ነበር በኢትዮጵያ መንግስት የነበረው አስተሳሰብ። ከዛ በኋላ ከኢትዮጵያ ጋር በተሻለ መልኩ ለመደራደር ዝግጁ የሆነ መንግስት ኤርትራ ውስጥ ስልጣን ይይዝ እና ከነሱ ጋር እንደራደራለን ነበር የኢህአዴግ አቋም።
ስለዚህ ባጭሩ የ«ጦርነትም ሰላምም የለም» ፖሊሲ ሁለት አላማ ነበረው፤ 1) ሻዕብያን ከስልጣን ማውረድ ለኢትዮጵያ ወይንም ለህወሓት የሚመች መንግስት እንዲመጣ እና 2) ኤርትራ እንደ ሀገር ኃይሏ ከኢትዮያ አንጻር እንዲመነምን እና በዚህ ምክንያት ለኢትዮጵያ አመቺ የሆነ የድርድር ሁኔታ እንዲፈጠር።
ዛሬ አንደኛው ግብ አልተመታም ግን ሁለተኛው ተመቷል ወይንም ከዚህ በላይ ሊመታ አይችልም። ማለተም ካሁን ወድያ ኤርትራን ለማድከም ተብሎ ይህ ፖሊሲ ቢቀጥል ጉዳቱ ከጥቅሙ ይበልጣል። ሻዕብያ እና ኤርትራ የሚማሩት ትምሕርትሮች ከነበሩ ተምረውታል። የኤኮኖሚ ችግር በቂ አይተውታል። ሻዕብያ መሪው ኢሳያስ አፈወርቂ ከህውየት እስኪለዩ መግዛት መቀጠሉ ግልጽ ሆኗል። ከዛ በኋላ ደግሞ ትርምስ የሚመጣ ይመስላል የሻዕብያን የመገንጠል ጦርነትን የማያስታውስ ጭቆና ብቻ የሚያስታውስ አዲስ ትውልድ ወደ ፊት እየመጣ ሲሄድ። ስለዚህ ነው የአብይ አህመድ መንግስት ይበቃል ወደ ሰላም እና ድርድር እንግባ ያለው። ትርምስ ሳይመጣ ጠላት ሀገሮች እጃቸውን አለ ቁጥጥር ኤርትራ ውስጥ መክተት ከሚጀምሩ በፊት ካሁኑኑ የቀረውን የወንድማማቾች ስሜትን ተጠቅመን እንደራደር ነው።
ይህ ጥሩ አካሄድ ይመስለኛል። እንዳልኩት የ «ጦርነትም ሰላምም የለም» ፖሊሲ በቂ ሰርቷል ምቀጠሉ ለኢትዮጵያ አይጠቅማትም። ከዚህ አልፎ ተርፎ የኤርትራ ችግር ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ የቅርብ የፖለቲካ ለውጦች የሁለቱን ሀገራት የኃይል ሚዛን እጅግ ወደ ኢትዮጵያ አመዝኖታል። በህወሓት ዘመን የኢትዮጵያ ህዝብ የሚጠላው ከፋፋይ መንግስት ስለነበር ሀገሪቷን የተከፋፈለች ከሚገባት ደካማ ኃይል እንዲኖራት አድርጓል። በዛን ጊዜ ኢትዮጵያ ከኤርትራ ጋር ድርድር ብትገጥም ውጤቱ ደካማ ነበር የሚሆነው። አሁን ግን ህዝቡ በሙሉ አንድ ስለሆነ እነ አብይ አህመንድ ወደ ድርድር ሲገቡ ያንን ሁሉ ኃይል ይዘው ስለሚገቡ ታላቅ ድል ማድረስ ይችላሉ። እንደ ድሮ የሻዕብያን ብልጠት መፍራት የለም። እንደ ድሮ ኤርትራ እና ኢትዮጵያ እንደ እኩለኛማቾች አደሉም። ኢትዮጵያ ታላቅ፤ ግዙፍ እና ባለ ኃይል ናት ኤርትራ እንደሚገባት የኢትዮጵያ አንድ አስረኛ ናት። ይህ ለድርድር ጥሩ ሜዳ ነው። በእውነታ የተመሰረተ ትክክል እና ዘላቂ ስምምነት እንዲኖር የሚያደርግ ሜዳ ነው።
ባጭሩ የጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ የ«ጦርነትም ሰላምም የለም» የሚለውን ፖሊሲ ያቆመው ምክንያት ጥቅሙ ስላለቀ እና ለኢትዮጵያ አሁኑኑ ከኤርትራ ጋር ድርድር መግባት አዋጪ ስለሆነ ነው። እዚህ ላይ ማለት የምፈልገው አንድ ነገር አለ። ለኔ ኤርትራ እና ኢትዮጵያ አንድ ናቸው። የኤርትራ ህዝብ ኢትዮጵያዊ አይደለሁም ለማለት ሙሉ መብት አሉ በዚህ መብት አምናለሁ። ግን ለኔ ኤርትራኖች ሀገሬዎች ወንድሞቼ ናቸው። ከዛም አልፎ ከኢትዮጵያ የተገነጠሉት በኔ በኛ ጥፋት እንጂ በነሱ ክፋት አይደለም ብዬ ነው የማምነው። ስለዚህ ለኔ ይህ ድርድር ስለኤኮኖሚ ብቻ ሳይሆን ስለ ህዝባዊ ግንኙነተና ትሥስር ነው። የመለያየታችን ቁስሎች፤ ትዕቢቶች፤ ውሸቶች፤ ወዘተ የማስወገድ መጀመርያ ነው። እነ አብይ አህመድ ይህንን ለማድረግ እግዚአብሔር ይርዳቸው ይድራን!
Wednesday, 11 April 2018
የኢትዮጵያ ፖለቲካ እውነቶች (እንደሚመስለኝ)
1. ድሮ የነበረን የልሂቃን (elite) እራሱን አጠፋ። በኃይለ ሥላሴ መንግስት የነበረው ልሂቃን በአብዮት ምክንያት ተባረረ ተገደለ ተበታተነ። የኃይለ ሥላሴ ልጆች የሆኑት አብዮቱን የመሩት አዲስ ልሂቃን በአብዮቱ ዘመን እርስ በርስ ተፋጅተው ተላለቁ። የተረፈው የደርግ ልሂቃን በደካማ ርዕዮት ዓለም እና አስተዳደር በተጨማሪ በዓለም ፖለቲካ ክስተቶች ምክንያት ፈራረሰ። ሻእብያ ህወሓትና ኦነግ ኢትዮጵያን ሲቆጣጠሯት የበፊቱ የልሂቃን በተለይ በሀገር ብሄርተኝነት (የጎሳ ብሄርተኝነት ተቃራኒ) የሚያምነው የልሂቃን ቡድን ጠፍቶ ነበር። ኢትዮጵያ የቀራት አቅም (capacity) ያለው ልሂቃን ጎሰኛ ወይም የጎሳ ብሄርተኛ ጎራው ብቻ ነበር። እስካሁን የሀገር ብሄርተኛ ልሂቃኑ ከነበረው ጉዳት በቂ አላገገመም።
2. የዚህ የልሂቃን ቡድን መፍረስ ያለፉት 27 ዓመት የኢትዮጵያ ፖለቲካ ሁኔታ ላይ ከምናስበው በላይ ከባድ አስተዋጾ አድርጓል። በበፊቱ ልሂቃን ቡድን መፍረስ ምክንያት ነው ለ27 አመት የ«ተቃዋሚ» ጎራው ደካማ ሆኖ የቀረው። ተቃዋሚዎች ነፃነት ባለበት በውጭ ሀገርም መደራጀት ያልቻሉበት ምክንያት ልሂቃኑ ስለፈረሰ በቂ የልምድ የሰው ኃይል የመደራጀት ልምድ የታሪቅ ምሶሶ እና የተመሳሰሉት የልሂቃን ውጤቶች ስለሌለው ነው። በዚህ ምክንያት ነው ቢያንስ 70% እስከ 90% ከብዙሃኑ ድጋፍ ማግኘት የሚገባው ተቃዋሚ ለ27 ዓመት ብዙ ማድረግ ያልቻለው። ለተቃዋሚ ድክመት ሌላው የሚሰጠው ምክንያት የኢህአዴግ ጫና ከዚህ አንጻር እንደ ዋና ምክንያት ሊቆጠር አይችልም።
3. በሀገር ውስጥም በሀገር ውችም ያለው የተቃዋሚ ድክመት ምክንያት የፖለቲካ ለውጥ ከተቃዋሚ ፓርቲና ቡድኖች ሳይሆን ከብዙሃኑና ከኢህአዴግ ውስጥ ነው እየመጣ ያለው። (ተቃዋሚዎች ምንም ሚና አልተጫወቱም ለማለት ሳይሆን ከሚገባው አነስተኛ ሚና ነው የተጫወቱት አቅማቸው ውስን ስለሆነ።) እንደሚታየው የቅርብ ዓመታቱ የህዝብ ተቃውሞ የልሂቃን ማበረታጭያና ድጋፍ በጣም ያንሰዋል። ይህ የልሂቃን ወይም የመሪ እጥረት እጅግ አሳሳቢ ነው።
4. «አዲሱ ትውልድ መሪዎችን አልፎ ትቶ ሄዷል» ሲባል እውነት አይመስለኝም ነበር። ግን የዛሬው ትውልድ «ፖለቲካ ኮሬንቲ ነው» የሚባለውን አልፏል አባባሉንም ጭራሽ አያውቀውም። ኢህአዴግ ለ27 ዓመት ሳይቀየር የገዛበት አንዱ ምክንያት የበፊቱ ትውልድ ባለፉት አብዮቶች ተማሮ ተቃጥሎ በፖለቲካ ነክ ጉዳዮች በሚገባው መጠን ስላልተሳተፈ ነው። አሁን ግን ያ ዘመን አልፎ አዲሱ ተውልድ ለመሳተፍ ፍርሃት የለውም። አንዴ በእጽ በኳስ በገንዘብ ወዘተ ቢደነዝዝም ፖለቲካ ውስጥ እየተሳተፈ ነው። ነገር ግን አባት አያት አስተማሪ መሪ ታሪክ ትውፊት ይጎለዋል የበፊቱ ትውልድና ልሂቃን ስላላወረሰው።
5. ከውጭ ሀገር ሆኖ የፖለቲካ ወይም ማህበረሰባዊ ንቅናቄ ቡድን ድርጅት ፓርቲ አቋቁሞ መተጋል እስካሁን ውጤታማ አልሆነም ማለት ይቻላል። ወይንም አነስተኛ ውጤት ነው ያፈራው። ሰዎች እየሞከሩ አይደለም ማለት አይደለም። ከድሮ ጀምሮ እስካሁን እንደነ ኢሳት አይነት ትልቅ ሙከራዎችና ስኬቶች አሉ። ግን ከላይ እንደጠቀስኩት ኢህአዴግ የ10% ደጋፍ ድርጅት ነው ካልን እነዚህ ስኬቶች ከሚገባው እጅግ አነስተኛ ናቸው። ስለዚህ ይህ የውጭ ድርግታዊ ትግል አስፈላጊ ነው ቢባልም ዋናው ውጤታማው ትግል አይደለም።
6. ሀገር ውስጥ ያለ የይፋ ተቃውሞ በግለሰብ በቡድን በድርጅት በፓርቲም ይሁን ለ27 ዓመት በሁለት ምክንያቶች ደካማ ሆኖ ተገኝቷል። ከላይ እንደጠቀስኩት ዋናው ምክንያት የልሂቃን እጥረት ተቃዋሚዎች የመተባበር የአብሮ መስራት የቅራኔ መፍታት የመደራጀት ስልቶች እንዳይኖረን አድርጓል። ልድገመው፤ ይህ ነው ዋናው የተቃዋሚ ድክመት ምክንያት። የኢህአዴግ ጫና ሁለተኛ ደረጃ ምክንያት ነው። ሆኖም በተለይ ላለፉት 10 ዓመት ኢህአዴግ ተቃዋሚን (እንደ ቻይና) ጨርሶ ለማጥፋት ሲወስን ተቃዋሚዎች በጣም ተጎድተዋል። ዛሬ ግን ድርጅቶች ቢጎዱም በህዝብ ደረጃ ተቃውሞ ምን ያህል አዋጪ እንደሆነ ይታያል የዛሬውንም ለውጥ ያመጣው ይህ የብዙሃኑ ተቃውሞ ነው። ስለዚህ ብዙሃኑ በዚው ከቀጠለ የፖለቲካ ለውጡ እየተንከባለለ እንዲቀጥል ያደርጋል። ይህ ተቃውሞ ስኬታማ ሆኗል አሁንም ስኬታማ ይሆናል። ግን እንደገና ልበለው እየጨመረ ሲሄድ መሪ ያስፈልገዋል።
7. ያለፉት አራት ዓመታት የብዙሃኑ ተቃውሞ በዋነኝነት ስለ «የጎሳ አድሎ» ነው። ህዝቡ በ«ትግሬ አድሎ» (በተጨማሪ በ«አደርባይ አድሎ») ተማረናል እያለ ነው ሰልፍ የሚወጣው። እርግጥ የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ ነፃነት ይኑር መሬታችን አይነጠቅ ወዘተ የሚሉ መፈክሮች ይሰማሉ ግን የህዝብ ጥያቄ ቢደረግ አድሎ በዋነኝነት እንደሚጠቀስ የታወቀ ነው። ይህ አስተሳሰብ ደግሞ ከድኻ እስከ ሀብታም ከወዝ አደር እስከ ነጋዴ ይሰማል።(በአንድ በኩል ከፍቅር ሰላምና ፍትሕ ይልቅ ትኩረቱ የትግሬ አድሎ ላይ መሆኑ ያሳዝናል ግን እውነቱ ይህ ነው።)
8. ከሌሎች ጉዳዮች ይልቅ የትግሬ አድሎ ህዝቡን ያማረረው ምክንያት የጎሳ አስተዳደር ያመጣው ወይም ያበራታታው የጎሰኝነት ስሜት ነው። በኃይለ ሥላሴ ወይም በደርግ ዘመን በመደብ በዝምድና በትውውቅ በፓርቲ አድሎ ነበር። ግን በዛን ጊዜ የህዝብ ተቃውሞ በመሬት ፍትሕ ነፃነት ተመስርቶ ነበር። ትኩረቱ አድሎ ላይ አልነበረም። ለምን ብትሉ በሰው ልጅ ተፈጥሮ የጎሳ አድሎ ከመደብ ወይም ከፓርቲ አድሎ ይበልጥ ያማርራል። በዚህ ምክናይት ነው ለረዥም ዓመታት እንደተጠበቀው ህወሓትን ስልጣን ላይ ያቆየው የጎሳ አስተዳደር አሁን ከስልጣን የሚያባርረው ወይም ለውጥን የሚያመጣ የሆነው። ይህንም በማወቅ ነው ኢህአዴግ ላለፉት አምስት ዓመት እራሱን ከጎሰኝነት ወደ «ኢትዮጵያዊነት» ማሸጋገር የሚሞክረው።
9. ከላይ እንደጠቀስኩት ዛሬ የምናየው የፖለቲካ ለውጦች ሁለት ዋና ምንጮች አላቸው፤ 1) የብዙሃኑ ተቃውሞ እና 2) ከኢህአዴግ ውስጥ የመጣ ለውጥ። ሁለቱም ወሳኝ ናቸው። እስካሁን በኢህአዴግ ውስጥ የሚመጣው ለውጥ በነ ለማ መገርሳ የሚመራው «የለማ ቡድን» ነው የሚካሄደው እንበል። የለማ ቡድን በኢህአዴግን ሰርጎ ገብቶ ከውስጥ ሆኖ ድርጅቱን የመቆጣጠርና የመቀየር ስራ ነው የያዘው። ቡድኑ ተቅላይ ሚኒስቴር ዶክተር አቢይን እስከማሾም ያበቃው ከኦህዴድ ብአዴን ድህዴን ምናልባትም ከህውሓት ደጋፊዎች ተሳታፊዎች ስላሉት ነው። ይህ ቡድን በርካታ የፖለቲካ ልምድ አቅምና እውቀት አለው ተፈትኗልም። ለዚህ ነው ከ«ተቃዋሚው» ጎራ ሲነጻጸር የለማ ቡደን ለለውጥ የሚጫወተው ሚና የሚበልጠው። ተቃዋሚው ከላይ በጠቀስኳቸው የታሪካዊ ምክንያቶች ደካማ ስለሆነ። የለማ ቡድን ለውጥ ማምጣት ከሚፈልጉት የልሂቃን ቡድኖች ብቸኛ አቅም ያለው ነው። የቡድኑ ስራ ለሀገራችን በዋና አስፈላጊነት መያዝ አለበት።
10. ኢትዮጵያ የሚኖር ለፖለቲካ ለውት መታገል እፈልጋለሁ የሚል ተቀናቃኝ ልሂቅ ምሁር ወይንም ማንም ሰው አንድ ትልቅ ሚና መጫወት የሚችለው አንዱን የኢህአዴግ ፓርቲ ውስጥ በመግባት ነው። የለማ ቡድን ኢህአዴግን ለመቆጣጠር በርካታ የሰው ኃይል ያስፈልገዋል። ኦህዴድ ብአዴን ደህዴን ውስጥ ያሉትን የዚህ ሥርዓት ደጋፊዎች አክራሪዎችን በሰው ቁጥር ኃይል መብለጥ ማሸነፍ አለባቸው። እስካሁን የደረሱበት ደረጃ የደረሱት ቀስ በቀስ የነሱን ደጋፊዎችና ተሳታፊዎች ቁጥር እየጨመሩ እና ሌሎችን እያሳመኑ እየለወጡ ነው። አሁንም የለማ ቡደን ወደ ፊት ለመራመድ ከነሱ ሀሳብ የሚጋራ ስራ መስራት የሚችል የሰው ኃይል ያስፈልገዋል። የሰው ቁጥር ብቻ ሳይሆን ሀሳብ መስጠት ስራ ማስፈጸም በጠቅላላ አቅም የሚገነባ የሰው ኃይል ያስፈልገዋቸዋል። በዚህ መንገድ ነው የለማ ቡድን ኢህአዴግንም አልፎ ተርፎ ጦር ሥራዊቱንም ደህንነቱንም መቆጣጠር የሚችለው።
11. ለውጥ የሚመጣው በብዙሃኑ ተቃውሞና በለማ ቡድን የሚባለው የኢህአዴግ ተሃድሶዎች ነው ብለናል። የብዙሃኑ እንቅስቃሴ ከደከመ በህወሓት የሚገዙት የኢህአዴግ አክራሪዎች ከለማ ቡድን ያይላሉ። የለማ ቡድን ከደከማና የብዙሃኑ ትግል ከቀጠለ ወደ መሪ አልባ አብዮት እንሄዳለን። ሁለቱም የማንፈልጋቸው ውጤቶች ናቸው። ስለዚህ የብዙሃኑም ትግል የለማ ቡድንም መጠንከር አለባቸው ግን መናበብ መቀናበርም አለባቸው። ልድገመው፤ መናበብ መቀናበርም አለባቸው።
12. የኢትዮጵያ ልሂቃን ምሁራን ላለፉት 50 ዓመታት በትክክሉ ያልተደረገውን የፖለቲካ ውይይት ዛሬውኑ ጀምሮ ማድረግ አለባቸው። ላለፉት 50 ዓመታት ጊዜአችንን ወይ ኃይለ ሥላሴን ወይ ደርግን ወይ ኢህአዴግን ስንወነጅል እንጂ ሃሳቦች ስንገነባ አይደለም ያጠፋነው። የተቃዋሚው ድክመት ምክንያት አንዱ ይህ ነው። አሁንም እነዚህን ውይይቶች ማድረግ ግድ ነው። አሁን የፖለቲካ ውድድር ጊዜ ሳይሆን የሀገር መገንባት ጊዜ ነው። ሊዚህ ስራ ደግሞ ጣት መጠቆም መተቸት መጯጯህ ሳይሆን መወያየት መግባባት መተማመን መስማማት ነው የሚያስፈልገው። ለዚህ ውይይት ሀገር ውስጥም ውጭም ያለነው ትልቅ ሚና መጫወት እንችላለን።
13. የዛሬው የኢትዮጵያ ጦር ስራዊት በአብዛኛው ኦሮሞ አማራ እና ደቡብ ነው። የትግሬ ወታደር ቁጥር አናሳ ነው እየመነመነም ነው። መሪዎቹ ባብዛኛው የህወሓት ደጋፊዎች እንደሆኑ እናውቃለን ግን ጠመንጃው በሌላው እጅ ነው። በዚህ ምክንያት ጦር ስራዊቱ ለተወሰነ ጊዜ በላይ ሀገሩን በአስጨኳይ ጊዜ አዋጁ ተመስርቶ ሊያፍን አይችልም። ጦር ስራዊቱ ህዝቡን የሚጨቁንበት ጊዜና መጠን በጨመረ ቁጥር ውጥረቱ በጨመረ ቁጥር እርስ በርሱ ልዩነቶች እየበዙ ይሄዳሉ የጎሳ ክልልፍ ያድርበታል። የስራዊቱ መሪዎች ይህንን ያውቁጣል በትንሽ ጊዜ ሀገሪቷን ጠቆጣጥረን ወደ ጊቢዎቻችን መመለስ እንችላለን ብለው ነው ተስፋ የሚያደርጉት። ግን የዝቡ ተቃውሞ እንዳለፉት አራት ዓመት ከቀጠለ ጦር ስራዊቱ ግድ ወደ ኋላ መመለስ ይኖርበታል። ስለዚህ የጦር ስራዊቱ በመሪነት በህወሓት ደጋፊዎች መቆጣጠሩ አሁን ብዙ ትርጉም የለውም።
14. የማንም ሀገር ደህንነት ጎራ የኢትዮጵያም ተጨምሮ አስቸጋሪ ነው። ደህንነት በባህሪው ስነ መግባር ቢስ የሆነ በህብረተሰቡ ብሶት የላቸውን ሰዎች ወደሱ ይጋብዛል ይቀጥራል። የሁላችንም ኃጢአት ክምችት በደህንነት ድርጅቶች ይታያል። ግን ደህንነት አለ ፖለቲካ ጎራው እጅግ ደካማ ነው። አሁን የፖለቲካው ጎራ በነ ለማ ቡድን እየተቀየረ ነው። የህዝብ ትግልና የለማ ቡድን ስራ በዚሁ ከቀጠለ ጦር ሰራዊቱም ወደ ባራኩ ይመለሳል። ሁለቱ ጎራ ዎችን ከተቆጣጠርን ደህንነት አቅም የለውም እሱም ግድ ይለወጣል።
Friday, 17 November 2017
What's Ethnic Nationalism? Again...
Thursday, 11 May 2017
Using Canada To Understand Ethiopian Ethnic Federalism Today
I am fortunate to have acquired a somewhat intimate knowledge of Canadian politics and have found that, unlike US politics for example, Canadian politics holds wonderful parallels and lessons for Ethiopia in the area of federalism and ethnic federalism. So in this article I will briefly describe the history and nature of Canadian politics and how it can help us understand the Ethiopian political reality today, especially concerning ethnic federalism.
Here’s the (very) brief history… Canada was settled by English and French colonists beginning in the 1600’s. Soonafter, the English and French began warring for control of Canada (and North America as a whole), and around 1770, the English won decisively. However, in order to avoid problems with the large French population that had already settled in what is today known as the province of Quebec, the English government allowed the French to use their own language, worship in their own religion (Catholic), and to keep their own system of law (civil law). Over the following decades and centuries, the English continued to grant Quebec various such levels of autonomy and self-governance, both official and unofficial. For example, Quebec had its own legislature and French and both provincial and federal government services were provided in French and English. Unofficially, almost every second Canadian Prime Minister from 1867 (the official formation of Canada) onwards was French.
Nevertheless, despite such increasing levels of autonomy and recognition of language rights (note that it was always refered to as ‘language’, not ‘ethnic’ rights), ethnic nationalism in the French province of Quebec did not go away. The idea that Quebec was different from the rest of Canada, to the extent that it should secede and be a different country, actually grew over the decades despite increasing political and economic fortunes. So much so that in the late 1960’s and early 1970’s, there was a small armed resistance advocating for the separation of Quebec. This was followed by increasing support for even more autonomy and even secession among both the Quebec population and its French elite.
This resulted in two referendums on secession. In the first referendum of 1980, the ‘yes’ side – the secession side - lost by a significant margin. But, the fact that it was held at all and that it gained 40% support scared enough people that the federal government took even further steps to give Quebec more autonomy, to increase the prominence of French throughout the country, and to unofficially increase the amount of money Quebec got from the federal government. Yet, despite this, a second referendum was held 1995, strategically at a time when the economy was in recession and people were angry. This referendum was again won by the ‘no’ side, but by only one percentage point 50.5% to 49.5%! Significantly, 60% of native French speakers voted for secession, but almost 100% of English and other language speakers voted against secession. Thus, despite being a small minority, non-French speakers were the decisive voters in the referendum.
Today, there is little interest in secession in Quebec – or to put it more accurately, it seems impossible for the 40% of Quebec who still support secession to get enough support from the rest of the population to win a referendum.
What are the lessons to learn from this Canadian example for Ethiopia?
Modernization, rather than reducing ethnic nationalism, can actually increase it. As Quebec modernized, became less religious, more affluent, etc. support for ethnic nationalism, manifested in reduction in English and other (non-French) language rights, secession from Canada, etc. actually increased! Modernization and increased ethnic nationalism go hand in hand.
Canada over the centuries embarked on various policies aimed at accommodating and satisfying the demands of French Quebecers such as the granting of extensive language rights, allowing the suppression of English and other languages in Quebec, making French an official language of the entire country despite only a tiny French population outside Quebec, transfering large amounts of federal money to Quebec despite the wealth of Quebec, etc. The political calculation was that if the demands of French Quebecers were met, they would be less likely to manifest their ethnic nationalism in ways that would cause dramatic damage the rest of Canada, such as secession. This shows that ethnic nationalism cannot be defeated by a stick – it requires plenty of carrot.
However, all over the above policies may have slowed the pace of increasing ethnic nationalism, but did not stop it. The results of the 1995 referendum, which almost initiated a process of secession or at least more separated federal arrangement, shows that accommodating ethnic nationalism, though helpful for some time, will not at the end stop the movement.
Ethnic nationalism does not fundamentally mean secession. It is the desire of a certain group for special rights above the rights of the rest of the population, in recognition that this group is a nation, or a pseudo-nation. For hardline ethnic nationalists, this recognition can only be realized within a politically separate nation. For ‘softer’ nationalists, having asymmetric rights within one nation is enough. Having more autonomy than other provinces, having a French-only province, having the federal language use French equal to English, etc. is enough for them to express their nationhood. The common theme however is that it has to have special rights as a group, even though these rights impinge upon the rights of other citizens.
An immigrant to Quebec cannot send his child to English school. English has not official status as a language in Quebec. Anyone in Quebec who does not speak French is de facto a second class citizen. More so than someone who does not speak English and lives in the English parts of Canada. ‘Native’ Quebecers – those who trace their ancestry to the original French Quebecers – are a privileged class in Quebec, even more so that ‘native’ English are in the rest of Canada. These are the practical consequences of ethnic nationalism – asymmetric rights and privilege that impinge on others’ rights.
Quebec nationalists go out of their way to emphasize that theirs is not an ‘ethnic’ nationalism, but a geographic (Quebec) or language-based (French) nationalism. The reason is that ethnic nationalism is seen within Canadian politics as a whole as primitive and potentially discriminatory. Thus when after the failed 1995 referendum one of the leaders of the Quebec separatist movement (truthfully) said that they lost the vote because of English speakers and immigrants, he was roundly denounced by his own side. What he said was true but not the perception of Quebec separatism that separatists wanted to portray. They wanted to portray their side as open to all, especially immigrants, with the common goal of having an independent Quebec. Ethnic nationalism is in a mature political arena seen as too divisive and dangerous by all sides.
Ethnic nationalism is politically costly. Since its inception, Canada has an extraordinary amount of its political energy on this issue. This energy could have been better spend on the myriad of other matters, such as the economy, trade, government organization, etc. that are everyday political issues in any other nation. The cost has been not only to Canada as a whole, but particularly to Quebec. In Quebec, most issues are sign primarily or at least secondarily through ethnic nationalist implications. Even political parties are organized around this issue, instead of around other ideology or interest groups.
Ethnic nationalist is economically costly. Canada spends significant amounts of money implementing the asymmetrical rights and privileges to Quebec that I mentioned above. The Quebec economy, too, has long been held hostage to the ethnic nationalist movement’s desire to use the economy first and foremost as a tool to promote its ethnic nationalist agenda.
Ethnic nationalism can only be significantly weaked through demographics, including integration and assimilation with the rest of the population. As I said above, though accommodation is often necessary and helpful, at the end of the day, it will only slow the tide of ethnic nationalism, not stop it. If it were not for the changing demographics in Quebec resulting from increasing numbers of immigrants, today Quebec might be a separate country or a very separate province in Canada. Immigrants and their children have increased the population of those whose mother tongue is not French to over 20%, and This group is not only not part of Quebec nationalism, but against it. Whereas accommodation could not defeat ethnic nationalism, demographics has done the job. For now.
These lessons are, as far as I am concerned, very much applicable to today’s Ethiopia. For me, Quebec mirrors Oromia. Oromia, notwithstanding the policies of the EPRDF, is today the one and major Ethiopian state where ethnic nationalism has a significant political impact. Yes, there is ethnic nationalism in other states, but where it is strongest and has to be dealt with ‘specially’ is in Oromia. Oromia, because of history and EPRDF policies, is Ethiopia’s asymmetric state – the one that requires special political attention, the one that is most costly, and the one for whom policies of accommodation, but more importantly integration and assimilation have to be especially targeted. I will address how I think this should be done in another article.
Tuesday, 25 October 2016
An Exercise in Empathy
Thursday, 13 October 2016
ኦርቶዶክስ ክርስትናና ፖለቲካ
«እግዚአብሔር በሁልም ስፍራ አለ በሁሉም ነገርም ይገኛል» (God is everywhere present and in all things) አንድ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት መሰረታዊ እምነት ነው። ይህ አባባል እግዚአብሔር የፈተራት ዓለም በሁለት በ«አለማዊ» እና በ«ሃይማኖታዊ» ስፍሮች እንዳልተከፈለች ይገልጻል። ወደ ቤተሰባችን፤ ስራችን፤ ንግዳችን፤ ዘፈናችን፤ መዝኒያናችን፤ ስፖርታችን፤ ትምህርትቤታችን፤ እርሻችን፤ ፖለቲካችንም ስንሄድ እግዚአብሔርንና እምነታችንን ትትን መሄድ አይቻላም! እግዚአብሔር በነዚ ስፍሮች ሁሉ አለና። ግድብ የለውም። ስለዚህ ፖለቲካና ክርስትና የተለያዩና የማይገናኙ ናቸው ማለት አይቻልም።
ስለዚህ ክርስትያኖች በፖለቲካ ልንሳተፍ እንችላለን። የማህበራዊ ኑሮ ፖለቲካን ስለሚይካትት ብንፈልግም ባንፈልጉም በተወሰነ ደረጃ ቢሆንም ፖለቲካ ውስጥ ተሳትፈናል። ሁለት ምሳሌዎች ልስጣችሁ፤ ቀረጥ መክፈል ማለት ገንዘብ ለመንግስት መስጠት ነው። የዚህን ገንዘብን አጥቃቀም የሚወስኑት ፖለቲከኞች ናቸው። በገንዘባችን ለሚያደርጉት ግን ተጠሪ ነን ግንዘባችን ነውና። በቀበሌ ወይም በማንኛውም የምንግስት መሥሪያቤት ስንገለገል ፖለቲከኞች የዘረጉትን የአስተዳድራዊ ዘዴ መቀበል ማለት ነው። ብለት ኑሮአችን ፖለቲካ አይጠፋም። ፖለቲካ አንዱ የህይወታችን ዘርፍ ነው።
ታድያ የአንድ ክርስትያን ፖለቲካዊ ኑሮ እንዴት መሆን አለበት? ይህን ለመመለስ በመጀመርያ አንዳንድ መሰረታዊ የሆኑ የክርስትና እምነቶች እንመልከት። ከላይ እግዚአብሔር ከሁሉም አለ የሚለውን አባባል ጠቅሽያለሁ። ቀጥሎ «በዐይነህ ውስጥ ያለውን ግንድ ሳትመለከት፤ በወንድምህ ዐይን ያለውን ጉድፍ ለምን ታያለህ» የሚለውን እስቲ እንመልከት። ባለንጀራችሁን እንደራሳችሁ ውደዱ ይበልጥ ደግሞ እኔ እንደምወዳችሁ ያህል ውደዱት ብሎ ክርስቶስ አዞናል። ይህን አባባልንም እንመልከት።
ሌላ አባባል፤ ቅዱስ ባስሊዮስ እንደዚህ አሉ፤ « የባለንጀራህ ሀጥያት ብቻ ከሆነ የሚታይህ ያንን ብቻ ከማየት ይልቅ በፊትም አሁንም የሚያደርገውን ጥሩ ነገሮች እንዳሉ ተገንዘብ። መፍረድን ትተህ ይህን ለማድረግ ስትሞክር ጭራሽ እርሱ ካንተ የተሻለ እንደሆነ ትረዳለህ።» ይህ አባባል ሁለት መሰረታዊ እምነቶታችንን ይገልጻል፤ እግዚአብሔር የፈጠረው ሁሉም ሰው ትንሽም ቢሆን ጥሩነት ስላለው በሌላ ሰው መፍረድ ተገቢ አይደለም።
ክርስቶስ «እኔ በልቤ የዋህና ትሑት ነኝ» ብሎ እኛም እንደሱ እንድንሆን አዞናል። ትሕትና የቀደመውና ዋናው ሀጥያታችን «ትዕቢት» ተቃራኒና መድሀኒት ስለሆነ የሃይማኖት አባቶች የምያተኩሩበት መልካ መግባር ነው። አባ ይስሐቅ ዘሶሪያ እንዲህ ብለዋል፤ «ጨው ለምግብ እንደሚሆን ትህትና ለሁሉ መልካ መግባር ይሆናል።»
የክርስትያን ፖለቲካ ኑሮ ከላይ በጠቀስኳቸው አባባሎች የሚያስተምሩን መልካ መግባሮች ነው መካተትና መመራት አለበት፤ 1) እግዚአብሔር ከሁሉም አለ፤ 2) የሌላውን ሀጥያት ከማየት ፋንታ የራሳችንን ሀጥያት አይተን ንስሃ እንጋባ እናርማቸውም፤ 3) ባለንጀራችንን ክርስቶስ እንደሚወደን እንውደድ፤ 4) በሰው አንፍረድ፤ ትሑት እንሁን ከትዕቢትና ትምክህት እንራቅ።
በዛሬው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሁኔታ አንድ ክርስትያን እነዚህን እምነቶች ተከትሎ ምን ሊያደርግ ይገባዋል? አትፍረዱ፤ ትሑት ሁኑ፤ የራሳችሁን ሀጥያት ተመልከቱ፤ አብዛኞቻችን በፖለቲካ ዙርያ የሌላው ሰው፤ ወገን፤ ጎሳ፤ ፓርቲ ጥፋት ብቻ ነው የሚታየን። የኢህአዴግ፤ የህወሓት፤ የኦነግ፤ የሻእቢያ፤ የኢዴፓ፤ የደርግ፤ የኢሀፓ፤ የኃይለ ስላሴ፤ የዘንድሮ ተቃዋሚ፤ የዲያስፖራ፤ ወዘተ። አንድ ክርስትያን እራሱን ሳይመረምር የራሱን ጥፋቶች ተረድቶ ንስሀ ሳይገባ የማንንም፤ የኢህአዴግንም፤ ጥፋትና ስህተትን ላይ ማተኮር የለበትም።
ግን ምን የፖለቲካ ሀጥያት አለብኝ ብለን የምንጠይቅ ብዙ ነን። ከበርካታ ሰዎች ከገደለው ካሰቃየው ኢህአዴግ፤ ደርግ፤ ወዘተ ምኔ ሊወዳደር ይችላል። እስቲ ይህን ጥያቄ በምሳሌዎች ለመመለስ ልሞክር።
ጎረቤቴ ለ«ኢንቬስተር» ተብሎ መሬቱን ሲነጠቅ ረዳሁትን? ትንሽም ነገር አደረግኩለት?የምፍረአቸውን የሰፈሬን ዱሪዬዎችን ለመርዳትና ጥሩ መስመር ለማስያዝ ያረግኩት ነገር አለ? ወይም የራሳቸው ጉዳይ ብዬ ዞር ብዬም አላያቸውም። ችግር እስኪያመጡ። በፖለቲካ ዙሪያ «ኦሮሞ» ሲባል በልቤ ፍርሃትና ጥርጣሬ አይሰፍንም? ነው በንጹ ልቦና ጉዳዩን እመለከታለሁ? «እነሱ ከሚገዙን ወያኔ ይግዛን» ብዬ አስቤ አላቅምን? ግን አንድ ቀንም «ከነሱ» ጋር ቁጭ ብዬ ተወያይቼ አላቅም። ከጎረቤቶቼ ጋር ድሮ ተጣልቼ አሁንም አልተቀየምኳቸውም? በዚህ ጥላቻ ምክነያት እንኳን ለፖለቲካ ለውጥ ለምንም ነገር ከነሱ ጋር መተባበር አልችልም አይደ? ከባልደረባዬ ምሁር በትንሽ አስተሳሰብ ልዩነት ምክነያት ጠላቶች አልሆንም? እንኳን አብረን ለመስራት መተያየትም አንፈልግም አይደለምን? ስራተኞቼን እንደ ሰው ቆጥሬ አላውቅም እሁድ ቤተክርስትያን ለመሄድም እድል አልሰጣቸውም! ዘላለማዊ ቂም አልፈጠርኩባቸውም? ኢህአዴግ ይህንን ቂም ተጠቅሞ እነዚህን ሰራተኞቼን እኔን ለመግዳት ወይም የኔን አቋም ለማዳከም መጠቀም አይችልምን? የማይገባኝ ጥቅም ለማግኘት ጉቦ ሰጥችሄ አላውቅምን? ከስራ ቦታዬ በኔ ሃሳቦች የማይስማሙትን አልኮንንም? ሰራተኞች ሲሳሳቱ ችግራቸውን ከመረዳት ፋንታ አልፈርድባቸውም? ልጄ ውትድርና ገብቶ የማያምንበትን ክፉ ድርጊቶች እንዲያደርግ ይታዘዛል ያደርጋል። ልጄ ነው የሚጦረኝ እና እንደዚህ አይነቱን ጉዳይ ለሱ በማንሳት ላበሳጨው አልፈልግም እላለሁ። ታድያ እንደ የኢግዚአብሔር ልጅ ሃላፊነቴን አልካድኩምን?
እራሳችንን በደምብ ከመረመርን እነዚህ አይነቶቹ ሀጥያቶች እንዴት ከኛ ወደ ህብረተሰቡ፤ ከህብረተሰብ ወደ መንግስታችን እንደሚተላለፍ እንደሚያንጸባርቅ ልንገነዘብ እንችላለን። ክርስትያኖች የሁላችንም ኃጢአት የተገናኘው እንደሆነ እናምናለን። ለሌሎችንም ኃጢአት ሃላፊነት እንዳለብን እናምናለን። አባቶች ይህን ተጠንቅቀው ነው የሚያስተምሩን። ከላይ እንደምሳሌ የጠቀስኳቸው ኃጢአቶች እንዴት አሁን ካለው የምንግስት ስረዓት ባህሪ ጋር እንደሚገናኙ ግልጽ እንደሆነ ተስፋ አለኝ።
ክርስትያን በመሆኔ መጠን ለነዚህ ኃጢአቶች ንስሃ ገብቼ እየወደኩኝ እየተነሳሁኝ እያስተካከልኩኝ መኖር ነው የሚጥበቅብኝ። የፖለቲካ ኑሮዬም እንደዚህ ነው መሆን ያለበት። የምደግፈው የፖለቲካ አቋም፤ አመለካከት፤ ፓርቲ፤ ርዕዮተ ዓለም፤ ወዘተ ከክርስትያንነቴ ስር ነው መሆን ያለባቸው። እንደ ክርስትያን እስከኖርኩኝ ድረስ ፖለቲካው እራሱን ያስተካክላል።
ሆኖም ማንም ሰው አጥፊና ክፉ ነበር የሚያደርግ መንግስት ወይም ተቋምን መታገል የለበትም ማለት አይቻልም። እያንዳንዱ የራሱን ልብ ያውቃልና ልታገል ቢል በሱ ልፈርድ አልችልም፤ ግን ትግሉ ውጤታማ እንዲሆን በመጀመርያ የራሱን ልብና ገበና መፈተሽ አለበት። ሳይፈትሽ ሌላውን ለማስወገድ ብቻ ከታገለ ትግሉን አያሸንፍም። ወይም ይባስ ያሸንፍና ከታገለው የባሰ ሆኖ ይገኛል። ይህን እውነታ ሃይማኖታችን ያስተምረናል። እውነታም ስለሆነ በታሪክ በትደጋጋሚ ሲከሰት አይተናል! ስለዚህ በመጀመርያ ክርስትያን እንሁን፤ ሙሉ ክርስትያን እንሁን። ከሆንን ሌላው እራሱን ያስተካክላል።