Sunday 7 October 2018

የ«ኢትዮጵያዊነት» ጎራው በቂ አለመደራጀቱ ነው የሀገራችን ፖለቲካ መሰረታዊ ችግር!

የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ሁኔታ ገደል የገባው በኃይለ ሥላሴ ዘመን አስፈላጊ ለውጦች ባለመደረጋቸው ማርክሲዝም እና አብዮት በሀገራችን መስፈኑ ነው። በዚህ ሂደት በሀገራዊ ብሄርተኝነት የሚያምነው የፖለቲካ ልሂቃን ተከፋፍለው እና እርስ በርስ ተፋጀተው የሀገራችን ፖለቲካ በጎሳ ብሄርተኞች እንዲወረር ተው።

ይህ የፈጠረው ሁኔታ ይህ ነው፤ የጎሳ ብሄርተኝነትን የሚከተለው ብዙሃን በፖለቲካ ድርጅት፤ ኃይል እና ልሂቃን ደረጃ በአግባቡ ተወክሏል። በአንጻሩ በኢትዮጵያ ብሄርተኝነት የሚያምነው ብዙሃን አልተወከለም ማለት ይቻላል። ከ100 ሚሊዮን ህዝብ ቢያንስ ግማሹ ጠንካራ ኢትዮጵያ ብሄርተኛ ነው። ግን ይህ ግዙፍ የሆነው ህዝብ ብዛቱ የሚገባው ድርጅት የለውም። ግንቦት 7 ነው ያለው አቅሙ ግን የ50 ሚሊዮን ህዝብ የሚወክል ድርጅት ያህል አይደለም። ቅርቡም አይደለም።

ይህ ነው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ዋና እና መሰረታዊ ችግር። በታም ግዙፍ የሆነ የብዙሃኑ ክፍል የልሂቃን፤ ምሁራን፤ እና የፖለቲካ መደብ ውክልና የለውም። ይህ የተዛባ (distorted) ሁኔታ ፖለቲከኞቻችን የተዛባ ውሳኔዎች እንዲወስዱ ያደርጋል እና ሀገሪቷን ግጭት በግጭት የደርጋል።

አልፎ ተርፎ በአግባቡ ያልተወከለ ግዙፍ ብዙሃን አንድ ቀን ይፈነዳልና ወደ አብዮት ያመራል። የአማራ ብሄርተኝነት ማደግ ይህን ያመለክታል። በዜግነት መደራጀት ስላቃተን በጎሳ እንደራጅ ነው የአማራ ብሄርተኝነት መሰረታዊ ግፊቱ። ይህ ሁኔታ በዚ አቅጣጫ ከቀጠለ ምሃል ሀገሩ (centre) ባዶ ቀርቶ የፖለቲካ ኃይል በሙሉ ከጠረፎቹ (periphery) ይሆናል። ይህ ደግሞ እንደምናውቀው የጎሳ ውድድር፤ ከዛ ግጭት፤ ከዛ ጦርነት ያመጣል። ለዚህ የ27 ዓመት መረጃ አለን።

ስለዚህ የፖለቲካችን ችግር ለመፈታት ዘንድ የኢትዮጵያ ብሀኢርተኝነት ጎራው በአግባቡ መደራጀት ግድ ነው። ቅድመ ሁኔታ (necessary precondition) ነው። በአስር ሚሊዮኖች የሚቆጠረው የኢትዮጵያ ብሄርተኛ ብዙሃኑ ቁጥሩን የሚመጥን ፖለቲካዊ ውክልና ያስፈልገዋል። የመሃል እና ጠረፍ (centre and periphery) ሚዛን መስተካከል አለበት። ይህ ከሆነ የፖለቲካ መደቡ በእውነታ የተመሰረተ ድርድር ማድረግ ይችላል። ሁሉም ህዝብ በተወከለበት ማለት ነው።

ይህን ነጥብ እንዴት አጠንክሬ ማስደምደም እንደምችል አላውቅም! የኢትዮጵያዊነት ጎራው በአግባቡ አለመደራጀቱ ነው እስካሁን ያለውን የፖለቲካ ችግር የሚቀጥለው። ካሁን በኋላም ካልተደራጀ ፖለቲካችን ወደ ቀውስ እና ሁከት መሄዱ አይቀርም።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!