Monday 19 November 2018

በባንክ ዘራፊዎች ሽፍቶች ነበር ሀገራችን የተገዛው

የሃብታሙ አያሌው እና ኤርሚያስ ለገሰ ውይይትን አዳምጡት፤

https://www.youtube.com/watch?v=A78Tet3GCms

አንዱ ከሚወያዩበት ነጥቦች ስለ ኤፎርት (EFFORT) ድርጅት ነው። ሁላችንም የምናውቀው የህወሃት መንግስትን ከመቆጣጠሩ በፊት ሃብት በመዝረፍ ነበር የሚያካመቸው። የእርዳታ እህል/መድሃኔት ወዘተ በመሸጥ፤ ባንክ በመዝረፍ ወዘተ። ደምበኛ የሽፍታ ስራ። ሁላችንም የምናውቀው ታሪክ ነው። አልፎ ተርፎ የሚደንቅ ታሪክም አይደልም ህወሓት በመሰረቱ ሽፍቶች ነበሩና።

ይህን ብለን ጉዳዩ ከሌላው ዝርፊያ እና ሙስና ክስተቶች ለፍርድ መቅረብ አለባቸው ብሎ መደምደም በቂ አይደለም! ይህ የውሸት ወይንም የማይበቃ መደምደምያ ነው።

ለኔ ዋናው መደምደምያ ሀገራችን ኢትዮጵያ በጥቂት ሽፍቶች ለ27 ዓመት ተገዝቶ ነበር ነው! ይህ እውነት በመጀመርያ ደረጃ የሚያስከሥሠው እኛን ነው! እንዴት ነው በነዚህ ትንሽ ቁጥር ያላቸው ሽፍቶች የተገዛነው የሚለውን ጥያቄ መመለስ አለብን። ይህን ጥያቄ ካልመለስን ወደ ፊት ይህ መትፎ ታሪካችንን እንደግማለን።

ጣት መጠቆም ብቻ ያብቃ። እንደገና እንዳንወድቅ እራሳችን ላይ ስራ እንስራ።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!