Tuesday 2 October 2018

መሬት የግል ቢሆን ባለሃብት ይገዘዋል የሚባለው ሃሰት ነው

መሬት የግል መሆን አለበት ሲባል እንዱ በተለምዶ የሚሰነዘረው ተቃውሞ ገበሬዎች አግባብ ባልሆነ ርካሽ ዋጋ መሬታቸውን ይሸጣሉ እና ባለሃብት ብቻ መሬቱን ይገዛሉ። መሬት በሙሉ የባለሃብት ይሆናል ወደ «ፍዩዳል» ዘመን ከነችግሩ እንመለሳለን።

ይህ እጅግ የተሳሳተ አመለካከት ለመሆኑ ተጨባጭ መረጃ አለ። ላለፉት በርካታ ዓመታት መንግስት በሊዝ (የ55 ዓመት ሊዝ ለምሳሌ) በርካታ ትላልቅ መሬቶች ማከራየት ሞክሯል። በየክልሉ መርጥ የሆኑ ህዝብ ያለበትም የሌለበትም ለእርሻ አመቺ የሆኑ ቦታዎች ለሊዝ ኪራይ ቀርበዋል። ዋጋቸውም እጅግ ረካሽ ነበር። ለምሳሌ በጋምቤላ በዓመት 100,000 ብር አካባቢ ለመቶዎች ዬክታር ይከራያል።

ይህም ሆኖ ጥቂት ባለ ሃብቶች እና ኩባኒያዎች ናቸው ወደ እርሻ የገቡት። የቁጥር ሰነድ በእጄ የለኝም ግን ሊገን ይችላል። ግን አሁንም የሊዝ ቦታ በርካሽ ዋጋ መኖሩ የእርሻ መሬቱ ብዙ ፈላጊ እንዳልነበረው ያሳያል።

ዛሬ ባለሃብቶች በርካሽ ዋጋ ምርጥ የእርሻ መሬት ሊዝ ማድረግ ያልፈለጉ ከግል ገበሬዎች የደከመ የተበጣጠሰ መሬት ይገዛል ብለን ማሰብ አንችልም። ገበሬው መሬትን መሸጥ ቢችልም አብዛኛው ጊዜ ባለሃብት አይገዛውም።

የሚገዛው ጎረቤቱ ነው የሚሆነው። ዛሬ በየአመቱ በእኩል የሚከራየው ጎረቤት ገበሬ ከምከራይ ልግዛ ብሎ ይጠይቃል። የጎበዝ ገበሬው ይዞታ ይሰፋል የመሬት ጠቅላላ ምርቱም ይጨምራል። ጎበዝ ገበሬው በዚህ መንገድ እየተስፋፋ ታዳጊ ገበሬ ይሆናል። ይህ የሃገራችንን ጠቅላላ ምርት ይጨምራል።

(http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_47.html)

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!