Thursday 15 November 2018

ማን ነው የሚተርፈው?

አሉ የኢሳት ተንታኞች። በኢህአዴግ ዘመን የተከሰቱ የጭካኔ እና ሙስና ወንጀሎች ክር መተርተር ሲጀምር ማን ከኢህአዴግ እና ዙርያ ይተርፋል? ማን ያላጠፋ አለ?

ወይ ሁሉንም ማሳሰር ነው ወይንም እንደ ደቡብ አፍሪካ የእርቅ ስርዓት አቋቁሞ ፍትህ በእርቅ እንዲመጣ ማድረግ ነው ተባለ። ከነዚህ ደግሞ ሁለተኛው የእርቅ ስርዓት መንገዱ ጥሩ እና እውነት የያዘ አማራጭ ነው።

ለኔ ግን ከዚህ ሁሉ በላይ ዋናው ጓይ ይህ ነው፤ ማን ይተርፋል ብለን ስንጠይቅ ለምንድነው ስለኢህአዴግ እና ሌሎች ብቻ የምናወራው? «እኛሳ»? ጥፋት በማድረግም ባለባድረግም ነው ልንከሰስ ይገባል።

አዎን መስረቅ ጥፋት ነው። ግን የሚጎዳን አለመርዳትም እንዲሁ ጥፋት ነው። ስንቶቻችን «ብዙሃን» ባልደረቦቻችን በተለያየ መንገድ የፖለቲካ እና ማህበረሰባዊ ጥቃት ሲደርስባቸው ዝም ያልነው እና ያልረዳናቸው? ጎረቤታችን ተቸግሮ ቢያንስ «ይሄው 100ብር፤ ስለተቸገርክ ስለተጎዳህ አዝናለሁ» ያልን ስንቶቻችን ነን? እርግጥም ስንቶቻችን ነን ከጎረቤትና ባልደሮቦቻችን የከፋ ግጭት እና ቅራኔ ያለን። እርስ በርስ ተከፋፍለን ለከፋፍሎ መግዛት መንግስት እራሳችንን ያመቻቸን?!

የፖለቲካ እና ማህበራዊ ጥፋቶች የማህበሩ ማለትንም የእያንዳንዶቻችን ነው። No man is an island። ጥፋታችንን አምነን ወደ ንስሃ ከገባን ብቻ ነው እርፍት እይሚኖረን። እንጂ ዎንጀሎችን አስረን ሰላም ይመጣል ማለት ታሪክን አለማወቅ እና እራስን ማታለል ነው።

ታዋቂው ሩሲያዊ የፖለቲካ እስረኛ እንዳሉት፤
«ከእስርቤታችን አልጋ የሆነው የበሰበሰው ገለባ ላይ ጋደም ብዬ ነው ለመጀመርያ ከውስጤ የበጎ መንፈስ የተሰማኝ። ቀስ በቀስ መረዳት የጀመርኩት ይህ ነው፤ ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር በሀገሮች፤ መደቦች፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም መካከል አይደለም የሚያልፈው፤ ይህ መስመር የሚያልፈው በያንዳንዱ የሰው ልብ መኻል ነው። መስመሩ እድሜአችን በሙሉ ከውስጣችን ወደፊት ወደኋላ ይላል። በክፉ የተሞሉ ልቦችም ቢያንስ ቅንጣት ያህል ጥሩነት ይኖራል፤ ከሁሉም ጥሩ ከሚባለውም ልብ ከአንድ ጥጓ ትንሽ ክፉነት ይኖራል።
በየቦታው እየዞሩ ያሉ ክፉ ስራ የሚሰሩ ክፉ ሰዎች ቢኖሩና እነሱን ከኛ መለየትና ማጥፋት ብቻ ቢሆን ኖሮ እንዴት ቀላል ነበር? ግን ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር ከያንዳንዱ የሰው ልጅ ልብ መካከል ነው የሚያልፈውና ማን አለ ከራሱ ልብ ቁራጭ ቆርጦ ለማጥፋት ፈቃደኛ ይሆነ?»
https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/blog-post_30.html

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!