Wednesday 7 November 2018

የጎሳ አስተዳደርን አደገኝነት አለመረዳት ትንሽ ግትርነት ይመስለኛል

ከዚህ ገንቢ ውይይት (https://www.youtube.com/watch?v=tVqQW7Sh_G0) ስለ ጎሳ አስተዳደር (ፌደራሊዝም) ብዙ ጊዜ የሚነሳ ነጥብ ተነስቶ ነበር። ይህም፤

«የጎሳ ፌደራሊዝም በትክክሉ አልተሞከረም። እስካሁን ዴሞክራሲ አልነበረም፤ የአምባገነናዊ ጭቆና ነበር። የህዝቡ ኤኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ጥቅምም አልተከበረም። ለዚህ ነው ፖለቲካዊ ችግሮች የሚታዩት። ዴሞክራሲ፤ የኤኮኖሚ እና ማህበራው ፍትህ ሲኖሩ የጎሳ አስተዳደር በደምብ ይሰራል።»

አንዱ ተንጣኝ ይህንን አቋም ለመግለጽ "You can't judge a philosophy by its abuse" አይነት አባባል ተናግረዋል።

መቼስ ስለ ኮምዩኒዝምም እንዲህ ማለት ይቻላል! በትክክል ቢፈጸም ገነትን ያመጣልን ነበርና።

የጎሳ አስተዳደር ችግሮች ለማንኛውም አጉል risk ወይንም የራቀ እና ጸንፍ የያዘ ፍልስፍና ማቀፍ ለማይፈልግ ሰው ግልጽ የሆነ ይመስለኛል። ምክንያቶቹ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_89.html)፤

1. ደጋግሞ እንደሚባለው የትም ሀገር የጎሳ አስተዳደር የለም። ይህ በራሱ የጎሳ አስተዳደር እጅግ ጸንፍ የያዘ አስተዳደር እንደሆነ ይገልጻል።

2. በተለያዩ ሀገራት የጎሳ አስተዳደር የሌላቸውም ግን በተለያየ በፖለቲካ ክፈተቶች ጎሰኝነት ሲሰፍን ያለው ጉዳት አይተናል። የጎሰኝነት ችግር አንዳንድ ሀገሮች እስከ የጎሳ ፓርቲዎችም መከልከል አድርሷቸዋል።

3. የ27/22 ዓመት የሀገራችን የጎሳ አስተዳደር ተለምዶ ለጎሳ አስተዳደር አደገኝነት በቂ ማስረጃ ነው። አዎን ዴሞክራሲ አልነበረም ግን የጎሳ ተኮር ግጭቶች እና ቅራኔዎች በዴሞክራሲ እጦት ማሰበብ አይቻልም። መቼም ማንም reasonable ሰው እንዲህ የሚያየው አይመስለኝም። ምንም አይነት ችግሮች በጎሳ ግጭት መልኩ እራሳቸውን የሚገልጹ ከሆኑ ጎሰኝነት ነው ችግሩ ማለት
 ነው! አልፎ ተርፎ አሁን ዴሞክራሲ እየመጣ ግጭቶቹ ቀጥለዋል ወይንም በዝተዋል!

እነዚህን ግልስ የሆን ማስረጃዎች እያለን እና ግጭቶች እየበዙ እያሉ አሁንም የጎሳ አስተዳደር experimentአችንን እንቀጥል ማለት የሰከነ አስተያየት ነው? ይቅርታ አድርጉልኝ እና አይመስለኝም።

ይህን ስል የጎሳ አስተዳደርን የሚፈልጉት ሰዎችን መሰረታዊ ጥያቄዎች ማስተናገድ አንዳለብን ይገባኛል። አማራጭ ሊኖር ይገባል። አለ ጎሳ አስተዳደር እንዴት ነው የጎሳ መብቶች (እነዚህ መብቶች አይነታቸው አከራካሪ ቢሆንም) ማስከበር የሚቻለው።

መልሱ ቀላል ነው እና እንደ ጎሳ አስተዳደር አዲስ ፈጠራ ውስጥ እንድንገባ አያስገድደንም።
ከኢትዮጵያ አስር እጥፍ በላይ የጎሳ መብቶች (ቋንቋ፤ ባህል፤ አስተዳደር) የሚያስከብሩ ሀገራት አሉ። ህንድ፤ ስዊትዘርላንድ፤ ካናዳ ወዘተ። እነዚህ ሀገራት ሁሉም ሀገ መንግስታቸውን በዜግነት ነው የመሰረቱት። የጎሳ መብቶች በክፍለ ሀገር አቀራረጽ፤ የቋንቋ ህጎች፤ ለክፍለ ሀገር የሚሰጠው የማስተዳደር መብት ወዘተ ያስከበራሉ። ግን መሰረቱ ዜግነት ነው። እነዚህን እንደ ምሳሌ ወስዶ መጠቀም ነው።

ለመዝጋት አንድ አጭር ምሳሌ ልስጥ። ዛሬ ከህገ መንግስቱ «ብሄር፤ ብሄረሰቦች እና ህዝቦች» የሚለው ጥቅስ ከህገ መንግስቱ አወጣን እንበል። የክልል ቋንቋ በክልል ህዝብ ነው የሚወሰነው እንበል። ኦሮሚኛ የፌደራል ቋንቋ አደረግን እንበል። ይህ ሁኔታ (scenario) በርካታ የጎሳ መብት ያስከብራል። ኦሮሚያ ውስጥ በድምጽ ብልጫ የክልል ቋንቋ ኦሮምኛ ሆኖ ይቀራል። ይህ ማለት የምንግስት መስሪያቤት፤ ትምሕርት ቤት ወዘተ። የኦሮሚያ ክልል አስተዳደርም በኦሮሞ ባህል እንዲሆን በድምጽ ብልጫ ይፈጸማል። ወዘተ። ይህ አንድ ምሳሌ ነው። አለ ጎሳ አስተዳደር በርካታ የጎሳ መብቶች ሊፈጸሙ ይችላሉ።

ስለዚህ ወደ ህልም፤ ጸንፍ፤ አጉል ሙከራ አንሂድ። ቀላሉን መንገድ እንውሰድ። እንደ ኮምዩኒስቶቹ ህልማችንን እስከ መቃብራችን አቅፈን አንቆይ!

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!