Showing posts with label repentance. Show all posts
Showing posts with label repentance. Show all posts

Friday, 18 December 2020

የቤተ ክርስቲያን ሚና በፖለቲካ - ጥቂት ሃሳቦች

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እና ምእመናን በሀገራችን ፖለቲካ ምን አይነት ሚና መጫወት አለብን የሚለው ጥያቄ ሰፊና ውስብስብ ነው። ከዚህ ጽሁፍ በዚህ ጉዳይ ላይ አንዳንድ መሰረታዊ የሚመስሉኝን ሃሳቦችን ማቅረብ እወዳለሁ።

1. በእምነታችን እግዚአብሔር ከሁሉም ቦታ በሁሉም ጊዜ በሁሉም ዘመን ይገኛል። እግዚአብሔር የሌለበት ስፍራ የለም። ይህ ማለት ዓለምን በተለምዶ «ዓለማዊ» እና «መንፈሳዊ» ብሎ መለየት አይቻልም። እግዚአብሔር በቤተሰባችን፤ በመስሪያቤታችን፤ በንግዶቻችን፤ በትምሕርትቤቶቻችን፤ በእስርቤቶቻችን፤ በፖለቲካችን፤ በሁሉም ቦታ አለ። ስለዚህ ለእምነታችን off limits የሆነ ቦታ የለም። ሊኖርም አይችልም። ግን ጥያቄው እንዴት ነው እምነታችንን የምናንጸባርቀው ነው! እውነት እምነታችንን እናንጸባርቃለን ወይንም ኑፋቄ፤ ሰላም እናንጸባርቃለን ወይንም አመጽ፤ ደግነት እናንጸባርቃለን ወይንም ክፋት?

2. ክርስቶስ ፍቅርና ሰላም ነውና የክርስትና በፖለቲካ ላይ ያለው አመለካከት ፍቅርና ሰላም መሆን አለበት። መፈለግ ያለብን ሰላምን የሚያሰፍን እና ፍኩ ነገር የማያስደርገን (do no harm) ፖለቲካ ነው። ሁሉ አካሄዳችን በነዚህ ሁለት መርህዎች ስር መሆን አለበት። ሁሉ አቋሞቻችን በነዚህ መርህዎች መፈተሽ አለባቸው። ይህን ወይንም ያንን ፖሊሲ ወይም ፖለቲካዊ ተግባር ይጽደቅ ወይንም ይፈጸም ስንል ይህ ፖሊሲ ወይንም ተግባር ሰላም ያመጣል ወይ እና ክፉ እንዳናደርግ ይከለክለናል ወይ ብለን መጠየቅ አለብን። 

3. በሃይማኖታችን አንድ እውነት አለ፤ ይህ እውነት የኦርቶዶክሳዊ እምነታችን ነው። በዚህ በሃይማኖታችን መደራደር አይቻልም። ግን ከሃይማኖት ውች ሁሉ ነገር አሻሚ ነው። የፖለቲካ አቋም፤ ፖሊሲ፤ አተገባበር ሁሉ ትክክል ሊሆን፤ ሊሳሳት፤ መስተካከል ሊኖረው ይችላል። ፍፁም እውነት የሆነ ፖለቲካ የለም። ፖለቲካ እንደ ማንኛውም ስራ ግብአሩን እና ውጤቱን መርምሮ ገምቶ የሚሰራ ነው። ስተት ሊኖር ይችላል፤ ስተት ይኖራል። ግምቶችም ግቦችም የተሳሳቱ ሊሆኑ ይችላሉ። ስለዚህ ክርስቲያኖች የፖለቲካ አቋምን እንደ ጣኦት እንዳንቆጥር በጣም መጠንቀቅ አለብን። «ሶሽያሊዝም»፤ «ዴሞክራሲ»፤ «ሚክስድ ኤኮኖምይ»፤ «ነጻ ገበያ»፤ «ንጹህ ኤነርጂ» ወዘተ ሁሉም ሊጠቅሙ ላይጠቅሙ ይችላሉ። ከእሴቶቻችን ጋር አወራርድን የሚሆነውን ወስደን የማይሆነውን ትተን መራመድ ነው። እንደ ሁኔታው፤ ጊዜው፤ እና ችግሩ አቋምና ተግባራችንን ማስተካከል። የተለየ አቋም ያለውን አለመውቀስ ልንሳሳትንችላለንና። ፖለቲካ ጣኦት አይደለም!

4. ትህትና (humility) አንዱ የሃይማኖታችን ዋና እሴት ነው። «የተሰበርውንና የተዋረደውን ልብ እግዚአብሔር አይንቅም።» የሃይማኖት አባቶቻችን ከድርሳናቶቻቸው ትህትና ላይ በጣም ያተኩራሉ። ክርስቲያን በማንኛውም ስፍራ ትህትናውን መጠበቅ አለበት በፖለቲካ ስፍራውም እንዲሁ። የፖለቲካ አቋም ስንወስድ ተሳስተን ይሆናል ብለን ማሰብ አለብን። ከላይ እንዳልኩት ፖለቲካ ጣኦት አይደለምና አቋሞቻችንን እንደ ፍፁም አርገን መውሰድ አንችልም። ትህትና የግድ ነው። የትህትና ተቃራኒ እብሪት ክፉ ነው።

5. ንስሐ ከእግዚአብሔር የምንገናኝበት አንዱ ዋና መንገድ ነው። አለ ንስሐ ክስቲያናዊ ኑሮ የለም። እንደምንሳሳት ማመን አለብን። ስንሳሳት ማወቅና ማመን አለብን። ከዛ ንስሐ መግባት አለብን። በፖለቲካው ዓለምም እንዲሁ። ክርስቲያኖች በአቋምም በአፈጻጻምም ልንሳሳት እንችላለን። ይህን መካድ ታላቅ ስህተት ነው ኦርቶዶክሳዊ አይደለም። የንስሐ ፖለቲካ ፍቱን ነው። እኛ ኦርቶዶክሳዊ ኢትዮጵያኖች ትህትና እና ንስሐ በምሳሌ እያሳየን ፖለቲካችንን የሰላምና ፍቅር ማድረግ እንችል ይሆናል።

6. «አንቻቻልም!» መቻቻል አሉታዊ ነው፤ የማንወደውን ግን አማራጭ የሌለንን ነገር ነው የምንችለው። እግዚአብሔር ተቻቻሉ ሳይሆን ተዋደዱ ነው ያለው። ስለዚህ ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ሁሉንም ሰው ይወዳል ወይንም መውደድ አለበት። ሁሉንም ሃሳብ አይወድም፤ ሁሉንም ድርጊት አይወድም፤ ግን ሁሉንም ሰው ይወዳል። እንደ ክርስቲያኖች ይህንን የእግዚአብሔርን ፍቅር ማንጸባረቅ አለብን። 

7. ምሳሌ መሆን የክርስቲያን ዋና ተግባር ነው። ሰውን ማስተማር የምንችለው በስብከት ሳይሆን በምሳሌ ነው፤ ይህ መሰረታዊ ትህምሕርታችን ነው። «የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ አግኝና ዙርያህ ያሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ይድናሉ» የሩሲያው ቅዱስ ሴራፊም እንዳስተማረን።

Friday, 5 July 2019

እግዚአብሔር እኛ ኢትዮጵያዊያኖችን እስካሁን ምሮናል፤ ወደፊትም እንዲምረን መጸለይ ነው

Perspective አችን ትንሽ መስተካከል ያለበት ይመስለኛል። ስሜታዊ ሳይሆን ረጋ ብለን ያለንበትን ሁኔታ በረዥም መነጽር እንይ።

ሶስት ዓመት በፊት «ሀገራችን እንዴት ይሆናል?» ብዬ ብጠይቃችሁ እልቂት ነው የሚመጣው ትሉኝ ነበር። ዓመት በፊት የመጣውን አይነት ለውጥ በምንም ተዓምር አናስበውም ነበር። ህወሓት ይጨፈጭፈናል ወይንም በዓብዮት እና ሁከት ይገለበጣል እና ሀገሪቷ ይተራመሳል ነበር አብዛኞቻችን የምናስበው። ግን እንሆ እግዚአብሔር ምሮን አንጻራዊ ሰላማዊ ለውጥ መጣ። እንደ ኢትዮጵያዊያን የማይገባን ምህረት ነው ከእግዚአብሔር ያገኝነው። ለዚህ ምህረት ደግሞ ለዘላለም አመሰግነዋለው።

እናስተውል፤ በሀገራችን ባለፉት 70 ዓመታት ሶስት ዓቢዮቶች ተካሄደዋል። እንኳን ሶስት ዓቢዮቶች እነሩሲያ ከአንድ ዓቢዮት በደረሰበት ጉዳት ለመዳን ከመቶ ዓመት በላይ ወስዶበታል። እንደምናውቀው ዓብዮት ተውልዶችን ነው የሚያጠፋው። ኢትዮጵያ ብዙ ትውልድ አጥታለች። ላለፉት 60 ዓመታት political continuity የላትም ማለት ይቻላል። «ደህና» ሰው ከፖለቲካ እና ከሀገር «ኮሬንቲ» ርቋል። አሁን ያሉን ፖለቲከኞች በአብዛኞች ምራጭ ናቸው (ይህን የምለው ለመፍረድ ሳይሆን ዓቢዮቶቻችን ምን እንዳመጡ ለመግለጽ ነው)።

ይህ ታሪክና ነባራዊ ሁኔታችንን ሰከን ብለን ካየን አሁን ያለንበትን የፖለቲካ ችግር በጣም ትንሽ ሆኖ ሊታየን ይገባል። ከዚህ መቶ እጥፍ የባሰ ነበር መሆን ያለበት።

ተመስገን ለአምላካችን! Glory to God for all things!

Friday, 1 March 2019

የአዲስ አበባ ጉዳይ እና የሃላፊነት ፖለቲካ

በተለያዩ ጽሁፎቼ የኢትዮጵያ ፖለቲካ መሰረታዊ ችግር የ«ኢትዮጵያዊነት» ጎራው ለራሱ እጣ ፈንታ ሃላፊነት አለመውሰዱ ነው ብያለሁ። ላለፉት 50 ዓመታት ተደራጅቶ ፍላጎቶቹን አጣርቶ ከማስከበር ይልቅ ህልውናውን ለሌሎች ትቷል። ሃላፊነት ለሌሎች መታው ባህል አድርጎታል። ይህ አካሄድ የ«ለቅሶ ፖለቲካ» ብሄ ሰይምዬዋለሁ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/blog-post_16.html)።

ይህ ሁኔታ ምክንያት አለው፤ የኢትዮጵያዊነት ጎራው በአብዮቱ ጀምሮ እርስ በርስ ተገዳድሎ ልሂቃኑ እራሱን አጥፍቶ እስካሁን አላገገመም። (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/1.htmlhttps://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/2.htmlhttps://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/3.htmlhttps://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/4.html)። ቢሆንም በዚህ አካሄድ መቀጠል አይቻልም። ሌሎችን «ፍላቶእ እና መብታችንን አስከብሩልን» ብለን እየለመንን መቀጠል አይቻልም።

አሁን የሚያስፈልገን ከ«ለቅሶ ፖለቲካ» ወጥተን፤ ከህጻንነት እና ብሽተኝነት ወትጠን ወደ «ሃላፊነት ፖለቲካ» መግባት አለብን። ግድ ነው፤ አማራጭ የለም። እነ ለማ ይሁን አቢይ ይሁን ህወሓት ይሁን ግንቦት 7 ይሁን አብን ወዘተ እንዲህ አድርጉልን ብለን መለመን አይቻልም። ካሁን በኋላ ሁላችንም «ይህ ይሁን»፤ «ይህ ይደረግ»፤ «እከለ ይውደም» ወዘተ ከማለት ወደ «እኔ ይህን አደርጋለው» የሚለው አመለካከት መግባት አለብን። ልመና በቃ፤ የራሴን እጣ ፈንታ እራሴ ወስነዋለው ወደሚለው መግባት አለብን።

የአዲስ አበባ ጉዳይ የዚህ የአስተሳሰብ እና ተግባር ለውጥ አስፈላጊነት በደምብ ይገልጻል (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_97.html)። ልሂቃኖቻችን እስካሁን እነ ኢህአዴግን፤ ህወሓትን፤ ኦዴፓን፤ የኦሮሞ ብሄርተኞችን፤ አዴፓን፤ ጥ/ሚ አቢይን፤ ፕሬዚደንት ለማን፤ ወዘተ እባካችሁ እንዲህ እንዲያ አድርጉ አታድርጉ እያሉ ለው ዓመት ይጮሃሉ። ግን አንድ የሚባል የአዲስ አበባ ህዝብን ጥቅም የሚያንጸባርቅ እና ለማስከበር የሚሯሯት ድርጅት የለም? የአዲስ አበባ ህዝብ ህልውናውን ለሌሎች ሰጥቶ ሌሎቹ የሚፈልጉትን ሲአደርጉ ልሂቃኑ ያለቅሳል! ይህ ምን ማለት ነው? የአዲስ አበባ ህዝብ እራሱን አደራጅቶ ፍላጎቱን እና መብቱን ዘርዝሮ ማስከበር ካልቻለ እነዚህ የማይወክሉት ተቋሞች የፈለጉትን ያደርጋሉ። ይህ እኮ እጅግ basic የሆነ ነገር ነው።

እስከ ዛሬ የኛ ልሂቃን እና ሚዲያ ይህን መሰረታዊ ጉዳይ ትተው በማልቀስ እና መለመን ነው የዋሉት። የራሳችንን ጥፋት (አለመደራጀት) ላለማየት ትብሎ ህልውናችንን አደጋ ውስጥ ከትተናል! ይህ ሁሉ ችግር ስላልተደራጀን ነው እና እንደራጅ ከማለት ሌሎች ስለሚያደርጉት እናለቅሳለን። ይህ ለቅሶ ምንም ለውጥ አላመጣም አያመጣምም። ህዝባችን በንዴት እንዲደራጅ አላደረገም። ይባስ ሌሎች ላይ ጣት በመጠቆም የራሳችንን ጥፋት እንዳናይ ስበብ ሆኖናል። ጉርጓዳችንን ይበልጥ እንድንቆፍር አድርጎናል።

አሁን ግን አንዳንዶች መራራ የሆነውን መድሃኒት ውጠን ወደ ፊት መራመድ እንዳለብን የገባቸው ይመስላል።


ከዚህ ከኢሳት ዝግጅት የአዲስ አበባ ህዝብ መዋናነት መደራጀት አለበት ትባለ። ያለመደራጀታችን ጥፋታችንን አመንን ማለት ነው፤ ይህን ማመን ነው መራራው መድሃኔት። ካመንን በኋላ ሙሉ አቅማችንን ወደ መደራጀት ስራ ማሰለፍ ነው ያለብን። ካሁን ወድያ አንዳች የልሂቃን እና ሚዲያ ደቂቃ በእሮሮ፤ ለቅሶ፤ እና ልመና መጥፋት የለበትም። ሙሉ አቅማችን ወደ መደራጀት።

ምን ማለት ነው የመደራጀት ስራ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/blog-post_18.html)? ብዙ ሚስጥር የለውም፤ የህዝብ የማህበራዊ እና ፖለቲካዊ መደራጀት ለሺዎች ዓመታት የተደረገ ነገር ነው። የአዲስ አበባ ህዝብ «የአዲስ አበባ ህዝቦች ድርጅት» ያስፈልገዋል። የዚህ ድርጅት (ድርጅቶች) ተእልኮ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን ጥቅም ማስከበር ነው። ቀላል ተእልኮ ነው፤ ሌላ ጣጣ አያስፈልገውም። ድርጅቱ በርካታ (በመቶ ሺዎች የሚቆጠር) አባላት ያስፈልጉታል። ባለ ሃብቱ በደምብ መሳተፍ አለበት። ስብሰባ፤ ሰርቬ፤ ምርጫ፤ ወዘተ የሚያካሄድ መሆን አለበት። አባላቶቹ በየ ማህበራዊ ዘርፍ፤ በየ መስርያቤት፤ በዬ ሰፈሩ የሚሰሩ እና የሚኖሩ መሆን አለባቸው። ድርጅቱ ሰፊ ኔትወርክ ኖሮት «የሚፈራ» ማለትም አቅም ያለው መሆን አለበት። በተለያዩ የከተማው ጉዳዮች፤ መብራት፤ ውሃ፤ መንገድ፤ ደህንነት፤ ጤንነት፤ መፈናቀል፤ ውክልና፤ ወዘተ የሚሰራ መሆን አለበት። በዴሞክራሲያዊ መልኩ የአባላቱን ፍላቶ የሚያውቅ፤ የሚያስከበር እና የሚወክል መሆን አለበት።

ይህ ድርጅት ሲኖር፤ ዛሬ ቢኖር ስለ አዲስ አበባ ያለው ጭቅጭቅ አይኖርም ነበር። ሁሉም ተሳታፊዎች የአዲስ አበባ ህዝብ ፍላጎትን አበጥረው ያውቃሉ። የሁሉም አቋም ሰልሚታወቅ የፖለቲካ ድርድሮች በግልጽ እና በጽጋ ይካሄዱ ነበር። የለገጣፎ ሰዎች አይፈናቀሉም ነበር። ጉዳዩ ገና ሲነሳ ድርጅቱ ተሳትፎበት ድርድር ተደርጎበት በሰላም በሁሉም የሚያስማማ መልኩ ይፈታ ነበር። የኦሮሚያ «ልዩ ጥቅም» ጉዳይም እንዲሁ። ወካይ ድርጅት ቢኖርን «ልዩ ጥቅም» ብለን አናለቅስም ነበር። ድሮውኑ ተደራድረን የልዩ ጥቅም ትርጉም ላይ ተስማምተን ነገሩ በሰላም ይወሰን ነበር። ወዘተ።

የአዲስ አበባ ችግር የመጣው በህወሓት ምክንያት አይደለም። በኦሮሞ ብሄርተኞች ምክንያት አይደለም። መሰረታዊ ችግሩ የአዲስ አበባ ህዝብ እርስ በርስ ተስማምቶ አለመደራጀቱ ነው። ይህን አምነን አንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ለቅሶ እና ልመናችንን ትተን ሙሉ አቅማችንን ወደ መደራጀት ማዋል አለብን። አለበለዛ በየበታችንነት እና ተገዥነት ስሜት እንደተገዛን እንቀጥላከን። መገዛት ማለት የራስን እጣ ፈንታ ለሌሎች መተው እና በራስ ህይወት ሃላፊነት አለመውስውድ ነው። ይህ ላለፉት በርካታ ዓመታት ጉዞአችንን ይገልጻል።

Friday, 22 February 2019

ለገጣፎ ለሚከሰተው የአዲስ አበባ ህዝብ ሃላፊነት አለብን

ደርግ የ«ከበርቴን» ቤተና ንብረት ሲቀማ በምቀኝነት ተሞልተን አጨበጨብን። እርግጥ ነው አንዳንዱ አላግባብ ብዙ መሬት ይዞ በተከራዮች ይጫወት ነበር። ግን ሌሎች ትንሽ ንብረት የነበራቸው ነበሩ በዚሁ መአበል የተጥለቀለቁ። የሚያከራዩት ሶስት አራት ቤቶች ሲወረሱ ባዶአቸውን ቀሩ። ማንም አላዘነላቸውም። «እንኳን ተነጠቁ» ብለን የጅምላ ፍርድ ላይ ነበርን።

በህወሓት ዘመን ደግሞ ለ«ልማት» እና «ኢንቬስትሜንት» ተብሎ የበርካታ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ንብረት በምንግስት ተነጥቋል። አንዳንዱ ባዶውን ቀረ። አንዳንዱ እጅግ አነስተኛ ካሳ ተሰጥተው። ሌላው ከከተማ ውጭ ባዶ መሬት ላይ ተወረወረ። ይህ ሁሉ ሲከሰት የአዲስ አበባ ህዝብ (በጅምላ ለማውራት) ምንም አላደርገም። እርግጥ መጮህ እና መደራጀት ሊያሳስር እና ሊያስገድል ይችል ነበር። ግን ገንዘብ ሰብስቦ ለተፈናቀሉ ተጎጂዎች መስጠት ምንም ቅጣት አያስቀጥልም ነበር። ከኔ ጀምሮ አንዳችን ይህን አላደረግንም። የባለንጀሮቻችንን ህምም ዝም ብለን ተመለከትን።

ዛሬም እንዲሁ። ለገጣፎ የሚኖሩ ወንድም እህቶቻችን ቤቶቻቸውን እያጡ እያለ ከመጮ ሌላ ምንም አናደርግም። አንረዳቸው፤ አንደራጅ። ትንሽ ጉዳዩ ያናደደን ካለን መንግስት ላይ ጣታችንን እንጠቁማለን!

ከዛ ይልቅ እራሳችን ላይ ነው መፍረድ ያለብን። የአዲስ አበባ ህዝብ ለባለንጀራው በአግባቡ ቢራራ እስካሁን ተደራጅቶ የህ አይነት ግፍ እናይከሰት ማድረግ ይችል ነበር (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2019/02/blog-post_22.html)። ግን አላደረገውም፤ አላደረግነውም።

ስለዚህ ጥፋቱ በዋነኝነት የኛ የአዲስ አበባ ህዝብ ነው። ጣቶቻችንን ሌሎች የማይሰሙን ላይከመጠቆም ስራችንን ሰርተን ተደራጅተን እርስ በርስ ብንጠባበቅ ለሁሉም፤ ለጎጂዎቻችንም ለመላው ሀገራችንም፤ ጠቃሚ ነበር። ለችልተኛችን ንስሃ ገብተን ወደ ስራ እንግባ። ሌላ መፍትሄ የለም!

የአዲስ አበባ ህዝብ ካልተደራጀ ለገጣፎ ይደጋገማል

https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_97.html

የለገጣፎ ነዋሪዎች መፈናቀል ድርጊት በምንም ሚዛን እጅግ አሳፋሪ እና ለሁላችንም ጎጂ መሆኑ ግልጽ ያልሆነለት... ይቅርታ አድርጉልኝ እና የድሮ የፖለቲካ ደንቆሮ ነው።

ሆኖም እንደዚህ አይነት መፈናቀል እና ተመሳሳይ ክስተቶች ለ27 ዓመታት ሲካሄዱ ቆይተዋል። ወደ ኋላ ከሄድንም ደርግ የ«ከበርቴዎችን» ቤት እና መሬት አለ ፍትህ፤ ሚዛን፤ እና ርህራሄ ቀምቷል።

የአዲስ አበባ ህዝብ ይሁን ሁሉ ያትዋል አሳልፏልም። በርካታ ሰለቦች አይተናል። ግን አንዴም ጣታችንን አንስተን እንርዳችሁ፤ ይህ ክስተት እንዳይደገም ተደራጅተን ለእርስ በርሳችን እንቁም ብለን አናቅም። ይሉቅንስ ወይ ተባብረናል፤ አንገታችንን ደፍተናል፤ ወይንም ለተጎጂዎች ከመራራት ፋንታ ፈርደንባቸዋል።

በዚህ ምክንያት አሁንም ባለንጀሮቻችን፤ ጎረቤቶቻችን፤ ወንድም እህቶቻችን እጣ ፈንታቸው ከሆነ መሬት እና ቤቶቻቸውን ይነጠካሉ። ዛሬ ለገጣፎ ነው ነገ ሌላ ቦታ። የኦሮሚያ መንግስት ተወካዮች ይቀጥላል ብለዋል።

የአዲስ አበባ ህዝብ እንደዚህ አይነት ኢ-ሰባዊ ድርጊቶች እንዲቆሙ ከፈለገ ከመደራጀት በስተቀር ምንም ማድረግ አይችልም። መቾህ፤ ቂም መያዝ፤ ማዘን ወዘተ ብዙ ዋጋ የለውም። አንድ እና አንድ ምርጫ ብቻ ነው ያለው፤ መደራጀት።

ምን ማለት ነው መደራጀት? መቼስ ፖለቲከኞቻችን ሊያውቁ እና ሊያስተምሩን ይገባል ግን እስቲ ለኛ ብዙሃን በምሳሌ መልኩ ልዘርዝረው። ልብ፤ እውቀት፤ እና ገንዘብ ያላቸው «የአዲስ አበባ ዜጎች ድርጅት» የሚባል ያቋቁማሉ። የድርጅቱ ተዕልኮ የአዲስ አበባ ህዝብን ፍላጎትን እና ደህንነትን ለማስከበር መሟገት ይሆናል። ድርጅቱ በየ ቀበሌው፤ በየ ህዝብ ዘርፍ (ነጋዴ፤ ሞያተኛ፤ አስተማሪ፤ እናቶች፤ ወዘተ) አባላት እና ገንዘብ ይመለምላል። ትምሕርት ያስተምራል። በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አባላት ይሰበስባል። እነዚህ አባላት በዬ ህብረተሰብ ክፍል እና መንግስት መስርያቤቶች ያሉ ይሆናሉ እና በይፋም በህቡም ለድርጅቱ እና ለአዲስ አበባ ህዝብ ተጽዕኖ ማድረግ የሚችሉ ይሆናሉ። እንድነ ለገላፍቶ አይነት ክስተት እንደሚካሄድ ሲታወቅ ይህ ድርጅት በሁሉ ዘርፍ ተጽዕኖ ያደርጋል። እንደዚህ አይነት የማፈናቀል እና ሌላ ህዝቡን የሚጎዳ እቅድ እንዳይታሰብ ያደርጋል።

አሁን የደረደርኩት ምሳሌ አዲስ እንዳልሆነ መቼስ ሁላችንም እናውቃለን። ዓለም ዙርያ ለሺ ዓመታት ፖለቲካ በዚህ መልኩ ነው የሚካሄደው። እንኳን የሰላም ፖለቲካ የጦር/ኃይል ፖለቲካም እንዲሁ ተደራጅቶ ነው የሚሰራው። ስለዚህ የአዲስ አበባ ህዝብ ማድረግ ያለበት የተለየ እና በተለየ መልኩ ከባድ ነገር አይደለም። ለአካባቢ ጥቅም መደራጀት ቀላል እና የተለመደ የሰው ልጅ አካሄድ ነው።

ታድያ ለምንድነው የአዲስ አበባ ህዝብ እስካሁን ያላደረገው? በነ ግምት የአዲስ አበባ ህዝብ ይሆን ሁሉም የኢትዮጵያ (ሀገር) ብሄርተኞች ከ66 አብዮቱ እና ሽብሮቹ እስካሁን አላገገመም። አብዮት ተከታታይ ትውልዶች እንደሚያተፋ ይታወቃል በሀገራችንም እንዲሁ የኢትዮጵያ ብሄርተኛ ጎራውን እርስ በርስ አፋጅቶ ድምጥማጡን አጥፍቷል። ስለዚህ የአዲስ አበባ እና ጠቅላላ የኢትዮጵያ ብሄርተኛ ፖለቲካ አሁንም እጅግ ደካማ ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/03/blog-post_38.html)።

ይህ እንደሆነ እውነታው የአዲስ አበባ ህዝብ ካልተደራጀ እንደ ለገጣፎ አይነት ኢ-ሰባዊ ክስተቶችን ማቆም እንደማይቻል ነው። የአዲስ አበባ ህዝብ ደጋግሞ ይረገጣል። ከመደራጀት በቀር ምንም መፍትሄ የለም። ለመድገም ያህል እሮሮ ማሰማት፤ ማልቀስ፤ መርገም፤ መለፍለፍ ወዘተ ዋጋ የለውም። ከባዱ የመደራጀት ስራ ግድ መሰራት አለበት።

Wednesday, 13 February 2019

የንስሐ ፖለቲካ በአሜሪካ


በአሜሪካ ይሁን በሌሎች ምዕራባዊ ሀገራት የንስሐ ፖለቲካ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/blog-post_30.html) የተለመደ አይደለም። ፖለቲከኞች የእውነት ይቅርታ ብዙ ጊዜ አይጠይቁም። ይቅርታ ከጠየቁም ለጋራ ወይንም ለሀገር ጥፋት ነው እንጂ እራሳቸው ላደረጉት ስለራሳቸው ይቅርጣ አይጠይቁም። አልፎ ተርፎ ይቅርታ ከጠየቁ የፖለቲካ ጥቅም ካለው ብቻ ነው።

የአሜሪካ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ዋልተር ጆውንዝ (Walter Jones) ግን የተለዩ ፖለቲከኛ ነበሩ (https://www.theamericanconservative.com/articles/walter-jones-cried-while-the-rest-of-them-lied/)። ዋልተር ጆውንስ እንደ ሁሉም የሪፐብሊካን ፓርቲ ፖለቲከኞች እና አብዛኞች የዴሞክራቲክ ፓርቲ ፖለቲከኞች የጆርጅ ቡሽ የኢራቅ የ2003 (እ.አ.አ) ወረራን ደግፈው ነበር። በ2001 በአሜሪካ ላይ የተፈጸመው ሽብር በኋላ የአሜሪካ ህዝብም ፖለቲከኞች ማንኛውም «ጸረ ሽብር» ጦርነትን ይደግፉ ነበር። ዋልተር ጆውንስ በዚህ በኩል አልተለዩም፤ ጭራሽ ጸንፈኛ አቋም ይዘው ነበር። የፈረንሳይ መንግስት ወረራውን አልደግፍም ሲል ጸረ-ፈረንሳይ እርምጆችን ደገፉ። ዋልተር ጆውንስ የሚወክሉት ወረዳ በጣም ጦር ሰራዊት እና ጦርነት የሚደፍግ ህዝብ ያለበት ቦታ ነበር እና አቋማቸው ይህንን አንጸባረቀ።

የአሜሪካ ወታደሮች እበጦርነቱ መሞት ሲጀምሩ እና ዋልተር ጆውንስ ሬሳዎቻቸውን በየቀኑ እና በየሳምንቱ ማየት ሲጀምሩ የ«ጦርነት ወዳጅ» አመለካከታቸውን ተመልሰው ማየት ጀመሩ። ስህተታቸውን ተረዱ። ተጸጸቱ። ወደ ንስሐ ገቡ። እስኪሞቱ ድርስ በተደጋጋሚ ይቅርታ ጠየቁ። ለያንዳንዱ ሃዘኝነቶች የይቅርታ ደብዳቤ ጻፉ! 11,000 ደብዳቤዎች ጻፉ። ደጋግመው ይቅርታ ጠየቁ። አለቀሱ። «ጦርነቱን በመደገፌ 4,000 በላይ አሜሪካኖች እንዲሞቱ አድርጊያለሁ» ብለው ተናገሩ። ለስህተታቸው ምንም ሰበብ አላረጉም። ያደገቱን «ስህተት» አላሉትም፤ «ኃጢአት» ነው ያሉት።

የዋልተር ጆውንስ ንስሐ የካቶሊክ እምነታቸውን እውን በማድረጋቸው እና በተግባር እይሚያምኑ እንደሆነ ያሳያል ይባላል። የሰው ልጅ ክቡር ነደሆነ ተረድተው ምንም ፖለቲካ ከሰው ልጅ እንደማይበልጥ ገባቸው። ሰው ቁጥር ወይንም መሳርያ ሳይሆን የእግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ተረዱ። የአሜሪካ የጦር ኢንዱስትሪ፤ የፖለቲካ ድጋፍ፤ የእስራኤል «ትቅም»፤ ገንዘብ፤ ወዘተ ከሰው ልጅ እንደማይበልጥ ከልባቸው ተረዱ። ለዚህም ይመስላል ጦርነቱን መደገፋቸው እንዲህ ያጸሰታቸው።

ዋልተር ጆውንስ በወሰዱት አቋም ምክንያት ስራቸውን ሊያጡ በጥቂት ተረፉ። ግዙፍ የፖለቲካ ኃይሎች፤ ሎቢዎች፤ እና የራሳቸው የሪፐብሊካን ፓርቲ ዋልተር ጆውንስ በእጩነትም በመርጫም እንዲሸነፉ በዙ ብር አወጡ። አልሆነላቸውም። ዋልተር ጆውንስ ሁለት ቀን በፊት ከዚህ ዓለም ሲለዩ የምክርቤት ወንበራቸውን እንደያዙ ነው የሞቱት።

የአሜሪካ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ዋልተር ጆውንስ ለሁሉም ፖለቲከኛም ብዙሃንም ታላቅ ምሳሌ ናቸው። ነፍስ ይማር።

እዚህ ላይ እኔም አንድ ንስሐ ልግባ። እኔም በወክቱ የኢራቅን ወረረ ደግፌ ነበር። አሜሪካ ለመቶ ዓመታት አምባገነኖችን ይህን ማንንም የሚጠቅማቸውን እየደገፉ ዛሬ አምባገነኑ ያውሩዱ በሚል እጅግ ደካማ አስተሳሰብ ወረራውን ደገፍኩኝ። ግን ዋና የአስተሳሰቤ ድክመት ፖለቲካን አለመረዳት አይደለም። የሰው ልጅ ማንነቱ ስላልገባኝ ነው። ጦርነት ለኔ ሃሳብ (abstract) ብቻ ነበር። የክፉ መንፈስ ማስተናገጃ እንደሆነ አልቆጠርኩትም። ሰዎች እንደሚሞቱ ባስቅም ብዛው ደረጃ አላውቅም ወይንም አይገባኝም ነበር ማለት ይቻላል። የሰው ልጅ በእግዛአብሔር ምሳሌ በመፈጠሩ ዘንድ ማንኛውም የሰው ልጅን የሚጎዳ እና የሚገል ነገር መቃወምን ግድ ነው። «ሄዶ ይዋጋልኝ (ን)» ማለት እጅግ የከፋ ኃጢአት ነው። ከሩቅ ሆኘ ለሆነ abstract ሃሳብ ሰው ይሙት ማለት የሰው ልጅ ማንነቱን አለማወቅ እና ሰውን በተዘዋዋሪ መግደል ማለት ነው።

እርግጥ እኔ አንድ ግለሰብ ነኝ። እንደ ዋልተር ጆውንስ የኢራቅ ወረራ እንዲካሄድ የመረጥቁኝ ወይንም የውሰንኩኝ አይደለም። ግን ሃሳቡን በመደገፌ ከሳቸው ምንም እንዳልለይ ያደርገኛል። «ለቀደሙት። አትግደል እንደ ተባለ ሰምታችኋል፤ የገደለም ሁሉ ፍርድ ይገባዋል። 22 እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ ፍርድ ይገባዋል፤» (የማቴዎስ ዎንጌል 5:21,22) በሃሳብ የተፈጸመ ኃጢአት ከተገበረ ኃጢአት ብዙ አይለይም። 

የዚህ ትምሕርት ምንድነው? ፖለቲካ ሆኖም ሌላ ነገር ከሰው ልጅ በላይ ካደረግን ሁልጊዜ ወደ ክፋት ነው የምንሄደው። ፖለቲካን ከእግዚአብሔር እና ቃሉ በላይ ካደረግን፤ ፖለቲካን ጣኦት ካደረግን ሁልጊዜ ወደ ክፋት ነው የምናመራው። ስለዚህ ሁሉ አቋሞቻችንን በትህትና እናስተናግድ። ራሳችንን ሁልጊዜ እንመርምር። ሁሌ የሰው ልጅን ማንነት እናስቀድም።

Thursday, 7 February 2019

በህዝብ ቆጠራው ላይ የኦርቶዶክስ አማኝ ቁጥር ከታሰበው በታች ቢሆን ምን እንል ይሆን?

በሚመጣው የህዝብ ቆጠራ ላይ የኦርቶዶክስ አማኝ ቁጥር ከታሰበው ወይንም ከሚፈለገው በታች ቢሆን እንደ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ምን እንል ይሆን? ይህን መረጃ / ሰነድ ስናገኝ ምንድነው ማድረግ ያለብን?

በመጀመርያ ደረጃ ንስሃ ነው መግባት ያለብን። የኦርቶዶክስ አማኝ ቁጥር ከመነመነ ዋናው ጥፋት የኛ የኦርቶዶክስ ምዕመናን ስለሆነ። እምነታችን፤ ክርስቶስም፤ የሃይማኖት አባቶችም አስረግጠው ይነግሩናል፤ እኛ ጥሩ ክርስቲያኖች ከሆንን እንደ ብርሃን ሌሎችን ወደ ብርሃን፤ ወደ ቃሉ፤ ወደ ክርስቶስ እናመጣለን። በአንጻሩ ጥሩ ክርስቲያኖች ካልሆንን፤ ጭለማዎች ከሆንን፤ ሌሎችን ወደ ክርስትና እንዳይመጡ እናደርጋለን። አልፎ ተርፎ ከኛም ያሉትን እንዲወጡ እናደርጋለን።

ይህን እውነት በአጭሩ ለመግለጽ የሩሲያዊው ቅዱስ ሴራፊም (ሱራፌል) ዘ-ሳሮቭ  እንዲህ ብለዋል፤

«መንፈስ ቅዱስ እንዲያድርባችሁ ከፈቀዳችሁ ዙርያችሁ ያሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ይድናሉ።»

በዚህ ጉዳይ ላይ ለተጨማሪ ማብራርያ ይህን የታወቁት የቆጵሮስ (ሊማሱ ከተማ) ጳጳስ አታናሲዮስ ቃለ ምልልስ ያንብቡ፤ http://orthochristian.com/79957.html። «ክርስቶስን የማያውቁ ሰዎች መኖራቸው የኛ (የክርስቲያኖች) ጥፋት ነው» ይላሉ። ይህ መሰረታዊ እምነታችን ነው።

በመንፈሳዊ ህግ ኃጢአት የቦታ እና የጊዜ ግድብ የለውም። የሁላችንም ኃጢአት ሁላችንንም በተለያየ መንገድ ይነካል። ለምሳሌ፤ እንዴ ወንድሜን ከበደክሉኝ ችግሩ ከኔ እና እሱ መካከል ሆኖ አይቀርም። ይተላለፋል። ወንድሜ ተበሳጭቶ ሌሎችን ይበድላል። ቤት ሲሄድ ቤተሰቡ አክሩፎ ያገኙታል። እኔ ስለበደልኩት ህይወቱን በሙሉ ቁስሉን ተሸክሞ በቁስሉ ምክንያት አስተሳሰቡም ድርጊቶቹም ሊሳባ ይችላል። ቂም ሊይዝ ይችላል። ሰውን በጥርጣሬ ሊያይ ይችላል። በዚህ መንገድ የኔ ኃጢአት እንደ ተላላፊ በሽታ ይንሰራጫል።

ክርስቲያኖች በመንፈሳዊ ህግ ኃጢአት ከቦታ ቦታ ብቻ ሳይሆን ዘመናትን ይሸጋገራል ብለን እናምናለን። ይህ ማለት ኃጢአት ለትውልድ ይተላለፋል። ይህ የሃይማኖታችን መሰረታዊ እምነት ነው። የአዳም ኃጢአትን መውረሳችን ይህን ይገልጻል። ለአዳም ኃጢአት ሃላፊነት ባይኖረንም ውጤቱን ወርሰናል። እኛም ኃጢአት በመስራታችን እንዲሁም አስተላልፈንዋል። ለምሳሌ ከወላጆቼ የወረስኩት ችግርን ተሸክሜ ለልጆቼ በትወሰነ ደረጃ አስተላልፋለሁ። ችግሩ በሃሳብ ብቻ ሳይሆን በደምም (በዲኤኔአችን) ይተላለፋል።

በመንፈሳዊ ህግ ኃጢአት በሀገር ደረጃም ይታወቃል። የእስራኤል ህዝብ ለሀገራዊ ኃጢአታቸው የታዋቁ ናቸው በራሳቸው በኦሪት ታሪክም በወንጌልም ይህ ታሪካቸው ተዘርዝሯል። ሌሎች በርካታ ህዝቦች እንደ ህዝብ ወይንም ሀገር ለኃጢአቶቻቸው ዋጋ ከፍለዋል። ዛሬም እንዲሁ ነው (https://blogs.ancientfaith.com/glory2godforallthings/2015/06/27/dostoevsky-and-the-sins-of-the-nation/)።

ስለዚህ እንደ ግለሰብም እንደሀገርም ኃጢአቶቻችን በቦታ እና ጊዜ ይተላለፋል። ለዚህ ኃጢአቶቻችንን አምነን ንስሃ መግባት አለብን። ይህ መሰረታዊ የክርስትና እምነት ነው። እንኳን በኢትዮጵያ በዓለም ዙርያ ችግር ሲከሰት ወደ ራሳችን ተመልክትን «ምን አድርጌ ወይህም ምን ባለማድረጌ ነው ይህ የሆነው» ብለን እራሳችንን መጠየቅ አለብን።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ መእመን ቁጥር ከቀነሰ ወይንም ካልጨመረ እሄኑኑ ጥያቄ እራሳችንን መጠየቅ ነው ያለብን። አማራጭ የለንም። እውነቱ ይህ ነው። ለዚህ ችግር ሌሎችን ጥፋተኛ ማድረግ ኢ-ክርቲያናዊ አካሄድ ነው። እንደ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች «ጴንጤዎቹ»፤ «ሙስሊሞቹ»፤ ወይንም «ሴኩላሪስቶቹ» ናቸው ምእመኖቻችንን የወሰዱብን ማለት አንችልም። ወደራሳችን ብቻ ነው መመልከት ያለብን። እኛ ብርሃን ከሆንን ምንም አይሳነንም፤ ዓለም በሙሉ ወደ ክርስቶስ ይመጣ ነበር። እዚህ ላይ ነው ማተኮር ያለብን። ይመስለኛል።

Friday, 25 January 2019

የሮማኒያው እስር ቤት…


ቀሲስ ጊኦርጊስ ካልቹ በቅርብ ጊዜ ያረፉ ታላቅ የሮማኒያ ኦርቶዶክስ ካህን ናቸው። ከዚህ ቪዲዮ የሳቸውን እና የሌሎች በሮማኒያ የቀድሞው ስረአት የተሰቃዩ ሰዎች ታሪክን ይናገራል…

Tuesday, 20 November 2018

የደርግ ኢሰባዊ ድርጊቶች በአግባቡ ለህዝብ ቢገለጽ ኖሮ ታሪክ (ብሶ) እንዳይደገም ይረዳ ነበር...

በደርግ ዘመን የሚካሄዱት ኢሰባዊ ድርጊቶች እንደ ግድያ፤ እስር፤ ማሰቃየት ወዘተ ለኢትዮጵያ ህዝብ በበቂ ደረጃ በይፋ አልቀረበም። «የእርቅ እና ሰላም» እና የፍትህ ሂደት በታላቅ መድረክ ለህዝብ አልቀረበም። መቀረብ ነበረበት። ህዝቡ ከተጎጂዎች ታሪኮቸውን በደምብ መስማት ነበረበት። የጨቋኞችን የፍርድ ሂደት በደምብ መስማት ነበረበት። ይህ ሳይደረግ ቀርቶ ጉዳዩ ላይላዩን ብቻ ታይቶ ህዝቡ «የደርግ ባለስልጣኖች ታሰሩ ቀጥሎ ተፈረደባቸው» ተብሎ ጉዳዩ በዛው ተዘጋ። ለስነልቦና የሚያስፈልገው ግልጽ የሆነ የእርቅ፤ ሰላም እና ፍትህ ሂደት አልተካሄደም።

በዚህ ምክንያት ዛሬ ብዙ ሰው ስለ ደርግ፤ ነጭ ሽብር እና ቀይ ሽብር አያውቅም። የለማወቅ ብዛቱ ይገርማል፤ አዲሱ ትውልድ ብቻ ሳይሆን የደርግ ዘመነን የሚያውቁትም በአግባቡ ታሪኩን አያውቁትም። ይህ «ማህበራዊ መርሳት» አንዱ ምክንያት ይመስለኛል ኢህአዴግ የደርግን ጭቆና በባሰ ሁኔታ እንዲደግም እድል የተሰጠው።

ሰሞኑን ከአንድ ዘመዴ ጋር ስለ ቅርብ ቀናት የደህንነት፤ የፖሊስ እና የሌሎች «መርማሪዎች» እና ሥቃይ አዛዥ እና አስፈጻሚዎች መታሰር እየተወያየን ነበር። ይህ ዘመዴ በደርግ ጊዜ ታስሮ ነበር። በታሰረበት ጊዜ እሱ እና ሌሎች ላይ የደረሰባቸውን የእስር ስቃይ በትንሹ አካፈለኝ/አስታወሰኝ፤
1. ዘመዴ ብዙ ከተገረፉት አንዱ ቢሆንም የደረሰብኝ ከሌሎች ይሻላል ይላል፤ ቆሻሻ ካልሲ ከአፍ ውስጥ ወትፈው ነው ለሳምንታት የገረፉት።  
2. አሰቃዮች ሴቶችን በሲጋራ መለኮሻ ነበር «እንትናቸውን» የሚያቃጥሉት። 
3. ጥፍር መንቀል ወዘተ ተራ እና የተለመደ ነበር። 
4. አንድ የታወቀ ዘመዴ የሚያውቀው አሰቃይ ነበር። ለሊቱን በየ እስር ቤቱ እየዞረ አንዳንድ እስረኞችን መርጦ አውጥቶ በሚኪና ይወስዳቸዋል። ሜዳ ላይ ለቆ «ሩጡ» ብሎ ያዛቸው እና በካላሹ ተረከዛቸውን መሬት መሬቱን ይተኩስባቸውል። «ጨዋታው» ሲያልቅ ይገላቸዋል። ይህ አሰቃይ መጨረሻ ላይ ደርግ እራሱ አስሮት ወደ ዘመዴ ያለበት እስር ቤት ገባ። አዕምሮውን ክፉኛ ሳተ፤ ጨርቁን ጣለ።
እንደዚህ አይነት ታሪኮች ብዙ ናቸው ግን ህዝባችን በደምብ አልተነገረውም። አስቀየሚ ዝርዝሮቹ  በይፋ ይነገሩ አደለም የምለው። ላያስፈልጉ ይችላሉ። ግን ክስተቶቹ፤ ተጎጂው፤ ወንጀለኛው፤ ወዘተ በህዝብ መደረክ በሚገባው ደረጃ መቅረብ አለበት። አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ይህን አሳፋሪ ታሪካችንን ማወቅ አለበት።

ለምን የደርግ ጭካኔ ታሪክ በደምብ አይልተነገረም? እንደሚመስለኝ ኢህአዴግ እራሱ ለሰው ልጅ የሚሰጠው ዋጋ ትንሽ ስለሆነ ነው። እራሱ እንደ ደርግ ህዝብን እንደሚረግጥ ስለሚያውቅ ይመስለኛል። ስለዚህ ኢህአዴግ በደርግ ግፎች ትልቅ የፖለቲካ ትርፍ ማትረፍ ቢፈልግም የራሱ እምነቶች እና ስራዎች ይህን እድልም እንዳይጠቀም አድርጎታል።

አሁን የ«እርቅና ሰላም» ኮሚሽን ሲቋቋም ያንን የደርግንም ታሪክ እንዲያካትት እና እንዲያሰማ መደረግ ያለበት ይመስለኛል። ኮሚሽኑ የ44 ዓመታት ግፍን ያስተናግድ። እኛ ኢትዮጵያዊያን ለረዥም ዓመታት ወንጀለኞች፤ ገዳዮች፤ አሰቃዮች ወዘተ እየወለድን እያሳደግን ወደ ስልጣን እያመጣን መቆየታችንን ማየት አለብን። የዚህ ቀጥታ ሰለቦች ታሪካቸውን የመናገር እድል ማግኘት አለባቸው። ሌሎቻችን ጥፋት እና ሃላፊነታችንን በነሱ በደረሰባቸው ማየት እና ማመን አለብን።

ይህ የንስሀ ሂደት ባለፈው 27 ዓመት ብቻ ከተገደበ እራሳችንን በሚገባው እንዳንወቅስ ይረዳናል። «እነሱ ናቸው ጥፋተኞቹ» ብለን የራሳችንን ሃላፊነት እንዳናይ ያረገናል። ግን ከደርግ ጀምሮ ታሪክን ካየን ሙሉ ግንዛቤ ይኖረናል። የኛ የማህበራዊ ጉድለታችንን እንድናምን ይረዳናል። አንድ ህበረተሰብ በተደጋጋሚ ጨቃኞች ሲወልድ እራሱን ምፈተሽ አለበት።

Monday, 19 November 2018

የቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ አሁንም ኋላ እንዳይቀር፤ የሙስና ማስወገድ ስራውን ያፋጥን

ወራት በፊት የሀገራችን ፖለቲካ አውንታዊ ለውጦች እያመጣ እያለ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ እራሱን በቅድምያ አላስተካከልም። ፖለቲካው ከተቀየረ በኋላ በፖለቲከኞች (እነ ጠ/ሚ አቢይ) ግፊት እና ማበረታታት ቤተ ክርስቲያን ወደ ትክክለኛ ሰላም መንገድ ገባች። የቤተ ክርስቲያናችን ሲኖዶስ ከመምራት ፋንታ ተከታይ ሆነ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/02/blog-post_15.html)። ያሳዝናል። ግን መከተሉም እራሱ ተመስገን ነው።

አሁን ደግሞ መንግስት የፍትህ እና ሰላም ስራዎች በሰፊው እየጀመረ ነው። ያለፉትን ጥፋቶች ከነ ሙስና እንዲመረመሩ እና ሰላም፤ ፍትህ እና እርቅ እንዲመጣ ሂደቶች እና መዋቅሮች እያቋቋመ ነው። በቤተ ክርስቲያናችን የሚፈፀም የነበረው ኢሰባዊነት እና ሙስና ይታወቃል። የምርመራ ስራዎች በትንሹ የተጀመሩ እንደሆነ ይታወቃል። ግን ስራው ገና ነው፤ መዋቀራዊ አልሆንም እና ለመላው ሀብረተሰብ ግልጽ እንዲሆን አልተደረገም።

አሁንም ቤተ ክርስቲያን ከመምራት ፋንታ ኋላ ቀር ሆኖ እንዳይገኝ። ሙስና እና ሌሎች ኢ-ክርስቲያናዊ ድርጊቶች ቤተ ክርስቲያኗን ማለትም ምዕመኗንም እጅግ እንደሚጎዳ በታሪክ የታወቀ ነገር ነው። የህልውና ጉዳይ ነው። ይህ ስለሆነ ቤተ ክርስቲያን አሁንም መንግስትን ቀድማ እራሷን ማጽዳት አለባት። ለመላው ሀገራችን ምሳሌ መሆን አለባት።

ስለዚህ ቤተ ክርስቲያንን ከሙስና እና ሌሎች ኃጢአቶች የማጽዳታ ዘመቻ አሁኑኑ ጠንክሮ መጀመር አለበት። ይህ ካልሆነ መንፈሳዊ ጉዳቱ እጅግ የከፋ ነው የሚሆነው።

በባንክ ዘራፊዎች ሽፍቶች ነበር ሀገራችን የተገዛው

የሃብታሙ አያሌው እና ኤርሚያስ ለገሰ ውይይትን አዳምጡት፤

https://www.youtube.com/watch?v=A78Tet3GCms

አንዱ ከሚወያዩበት ነጥቦች ስለ ኤፎርት (EFFORT) ድርጅት ነው። ሁላችንም የምናውቀው የህወሃት መንግስትን ከመቆጣጠሩ በፊት ሃብት በመዝረፍ ነበር የሚያካመቸው። የእርዳታ እህል/መድሃኔት ወዘተ በመሸጥ፤ ባንክ በመዝረፍ ወዘተ። ደምበኛ የሽፍታ ስራ። ሁላችንም የምናውቀው ታሪክ ነው። አልፎ ተርፎ የሚደንቅ ታሪክም አይደልም ህወሓት በመሰረቱ ሽፍቶች ነበሩና።

ይህን ብለን ጉዳዩ ከሌላው ዝርፊያ እና ሙስና ክስተቶች ለፍርድ መቅረብ አለባቸው ብሎ መደምደም በቂ አይደለም! ይህ የውሸት ወይንም የማይበቃ መደምደምያ ነው።

ለኔ ዋናው መደምደምያ ሀገራችን ኢትዮጵያ በጥቂት ሽፍቶች ለ27 ዓመት ተገዝቶ ነበር ነው! ይህ እውነት በመጀመርያ ደረጃ የሚያስከሥሠው እኛን ነው! እንዴት ነው በነዚህ ትንሽ ቁጥር ያላቸው ሽፍቶች የተገዛነው የሚለውን ጥያቄ መመለስ አለብን። ይህን ጥያቄ ካልመለስን ወደ ፊት ይህ መትፎ ታሪካችንን እንደግማለን።

ጣት መጠቆም ብቻ ያብቃ። እንደገና እንዳንወድቅ እራሳችን ላይ ስራ እንስራ።

Friday, 16 November 2018

ብራቮ ኤርሚያስ ለገሰ!

ይህን የኤርሚያስ ለገሰ ቃለ ምልልስን እዩት!

https://www.youtube.com/watch?v=WB2enMd2Ilk&t=3990s

ሁለት ታላቅ ነገሮች ያስተምረናል፤

1) ሃላፊነት፤ ጸጸት፤ እና ንስሃ፤ ኤርሚያስ ከመጸሃፎቹ ሺያች ገንዘብ ለተለያዩ የኢህአዴግ ሰለቦች (እንደ አበበ ክንፈ ሚካኤል)መስጠቱን አውቅ ነበር (ይታወቃል)። ለምን ብሎ ሲጠየቅ የሰጠው መልስ ሃላፊነት፤ ጸጸት እና ንስሃ ምን እንደሆኑ በጥሩ መንገድ የሚያስተምር ነው።

ኤርሚያስ ለኢህአዴግ በመስራቴ ኢህአዴግ ላደረገው ኃጢአቶች ህሊናዬ ስለሚወቅሰኝ ቢያንስ እንደ አቶ አበበ አይነቱን ተጎጂዎች በመርዳት ከራሴ ጋር እታረቃለሁ እና ላደረግኩት እንደ ካሳ ይሆናል ነው። ኤርሚያስ ማንንም አላሰረም አላሰቃየምም። ግን ሃላፊነት እንዳለበት አምኖ በሚመስለው መንገድ ይቅርታ እየጠየቀ ነው። ይህ የሚያስተምረን ሁላችንም በማድረግም ባለማድረግም ከመንግስት ሩቅ ብንሆንም በኢትዮጵያ ለተደረጉት ጥፋቶች ቢያንስ የተወሰነ ሃላፊነት እንዳለብን ነው። ታላቅ ትምሕርት ነው። ሁላችንም ይህን ትምሕርት ተምረን እራሳችንን እንደ ንፁሃን ከመቁጠር እንደ ኤርሚያስ ካሳ ለመክፈል ብናስብ ጥሩ ይመስለኛል።

2) የሰው ልጅ አስተዳደግ እና ጠቅላላ የኑሮ ጉዞ ለባህሪው እና ድርጊቱ አስተዋጾ አለው። ኤርሚያስ ስለ በረከት ስምዖን እና ባልደረባው ሽመልስ ሲጠየቅ «የሰው ልጅ ከመሬት ተነስቶ ክፉ አይሆንም» ብሏል። አስተዳደግ እና ታሪካዊ ምክንያቶች አሉ አለ። ይህን ሃቅ ሁላችንም ብናውቀውም ለመፍረድ ስንቸኩል እንረሳዋለን።

ይህ ሰውን አስተዳደግ እና ታሪክ ድርጊቱ ላይ ሚና አለው ስንል ለድጊታቸው ሰበበ ለማግኘት አይደለም። ለሁለት ምክንያት ነው፤ 1) ከመፍረድ እንዲቆጥበን ነው እና 2) መሰረታዊ ችግሮችን እንድናርም ነው። ለምሳሌ ከሰፈራችን አንድ ቤተሰብ ከማህበረሰቡ አላግባብ ተገልለው ኖረው ልጃቸው የደርግ/ህወሓት ጨቃኝ አሳዳጅ እና አሳቃይ ከሆነ ብዙ ሊገርመን አይገባም። ህብረተሰባችን እንደዚህ አይነት ሰዎችን የማይወልድ አይነት እንዲሆን መስራት እንዳለብን ያስታውሰናል።

አንድ መንግስት ጥሩ የሚሆነው እህታችን፤ ዘመዳችን፤ ጎረቤታችን፤ ወዘተ ሲመሩት ነው። ማለትም በህብረተሰቡ ክብር እና ተቀባይነት ያላቸው ሰዎች ሲመሩት ነው። በህብረተሰቡ ላይ ቂም ያላቸው ሰዎች (እንደ መለስ ዘናዊ) መንግስትን ሲመሩ መንግስቱን የቂም መወጫ ነው የሚያደርጉት። የማህበረሰባችን ዋና ስራ ቂም ያላቸውን ሰዎች አለመፍጠር ነው፤ ሁሉንም አቅፎ መያዝ።

ለማንኛውም ይህን የኤርሚያስ ቃለ ምልልስ እዩት። በጣም አስተማሪ ነው።

Thursday, 15 November 2018

ሁለት ተከታታይ አብዮቶች

በ1967 እና 1983 ሀገራችን በአብዮት ክፉኛ ተተረማመሰች። ለነዚህ አብዮቶች የተማሪ ንቅናቄ ይወነጀልበታል። አዎን ይህ ንቅናቄ ታላቅ ጥፋት አለበት። ግን ምንድነው የተማሪ ንቅናቄውን የፈጠረው? ይህን ግልጽ ጥያቄ በቂ አንመረምርም። በጃንሆይ ጊዜ በቂ ከባድ ችግሮች ነበሩ። በውቅቱ ባለመስተካከላቸው ነው ለአብዮት ያበቃን። ግን የጃንሆይ መንግስት ስህተቶችም ምክንያት አላቸው፤ ከዘመነ መሳፍንት ወዘተ የወረዱ ችግሮች ነበሩ።

ግንዛቤአችን በዚህ መልኩ ነው መሆን ያለበት ይመስለኛል። ጥፋትን አንድ ሰው ወይንም ቡድን ላይ መለጠፍ ህፃናዊ አስተሳሰብ ነው። እውነታው የፖለቲካ ችግሮቻችን ብዙ ምክንያቶች አላቸው። ይህን እውነታ ስንረዳ ነው ወደ ትክክለኛ መፍትሄ መሄድ የሚቻለው። በዚህም መንገድ ነው የሌሎችን ብቻ ሳይሆን የራሳችን ጥፋት አይተን መስተካከል የምንችለው።

ማን ነው የሚተርፈው?

አሉ የኢሳት ተንታኞች። በኢህአዴግ ዘመን የተከሰቱ የጭካኔ እና ሙስና ወንጀሎች ክር መተርተር ሲጀምር ማን ከኢህአዴግ እና ዙርያ ይተርፋል? ማን ያላጠፋ አለ?

ወይ ሁሉንም ማሳሰር ነው ወይንም እንደ ደቡብ አፍሪካ የእርቅ ስርዓት አቋቁሞ ፍትህ በእርቅ እንዲመጣ ማድረግ ነው ተባለ። ከነዚህ ደግሞ ሁለተኛው የእርቅ ስርዓት መንገዱ ጥሩ እና እውነት የያዘ አማራጭ ነው።

ለኔ ግን ከዚህ ሁሉ በላይ ዋናው ጓይ ይህ ነው፤ ማን ይተርፋል ብለን ስንጠይቅ ለምንድነው ስለኢህአዴግ እና ሌሎች ብቻ የምናወራው? «እኛሳ»? ጥፋት በማድረግም ባለባድረግም ነው ልንከሰስ ይገባል።

አዎን መስረቅ ጥፋት ነው። ግን የሚጎዳን አለመርዳትም እንዲሁ ጥፋት ነው። ስንቶቻችን «ብዙሃን» ባልደረቦቻችን በተለያየ መንገድ የፖለቲካ እና ማህበረሰባዊ ጥቃት ሲደርስባቸው ዝም ያልነው እና ያልረዳናቸው? ጎረቤታችን ተቸግሮ ቢያንስ «ይሄው 100ብር፤ ስለተቸገርክ ስለተጎዳህ አዝናለሁ» ያልን ስንቶቻችን ነን? እርግጥም ስንቶቻችን ነን ከጎረቤትና ባልደሮቦቻችን የከፋ ግጭት እና ቅራኔ ያለን። እርስ በርስ ተከፋፍለን ለከፋፍሎ መግዛት መንግስት እራሳችንን ያመቻቸን?!

የፖለቲካ እና ማህበራዊ ጥፋቶች የማህበሩ ማለትንም የእያንዳንዶቻችን ነው። No man is an island። ጥፋታችንን አምነን ወደ ንስሃ ከገባን ብቻ ነው እርፍት እይሚኖረን። እንጂ ዎንጀሎችን አስረን ሰላም ይመጣል ማለት ታሪክን አለማወቅ እና እራስን ማታለል ነው።

ታዋቂው ሩሲያዊ የፖለቲካ እስረኛ እንዳሉት፤
«ከእስርቤታችን አልጋ የሆነው የበሰበሰው ገለባ ላይ ጋደም ብዬ ነው ለመጀመርያ ከውስጤ የበጎ መንፈስ የተሰማኝ። ቀስ በቀስ መረዳት የጀመርኩት ይህ ነው፤ ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር በሀገሮች፤ መደቦች፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም መካከል አይደለም የሚያልፈው፤ ይህ መስመር የሚያልፈው በያንዳንዱ የሰው ልብ መኻል ነው። መስመሩ እድሜአችን በሙሉ ከውስጣችን ወደፊት ወደኋላ ይላል። በክፉ የተሞሉ ልቦችም ቢያንስ ቅንጣት ያህል ጥሩነት ይኖራል፤ ከሁሉም ጥሩ ከሚባለውም ልብ ከአንድ ጥጓ ትንሽ ክፉነት ይኖራል።
በየቦታው እየዞሩ ያሉ ክፉ ስራ የሚሰሩ ክፉ ሰዎች ቢኖሩና እነሱን ከኛ መለየትና ማጥፋት ብቻ ቢሆን ኖሮ እንዴት ቀላል ነበር? ግን ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር ከያንዳንዱ የሰው ልጅ ልብ መካከል ነው የሚያልፈውና ማን አለ ከራሱ ልብ ቁራጭ ቆርጦ ለማጥፋት ፈቃደኛ ይሆነ?»
https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/blog-post_30.html

Tuesday, 6 November 2018

አንድ የሊሂቃን ንስሃ፤ ዶ/ር ታደሰ ወልዴ

ይህንን ቪዲዮ ብትመለከቱ ጥሩ ይመስለኛል።

https://youtu.be/qSPFi8xsbBo?t=1696

ረዥም ከአንድ ሰአት በላይ የሚወስድ ቢሆንም ከላይ ባስቀመትኩት ሊንክ ጀምሮ ብታዩት ስለ ንስሃ ታላቅ ትምሕርት በተለይም ታላቅ ምሳሌ ታያችሁ።

አቶ ታደሰ ወልዴ፤ ታላቅ የኦክስፎርድ መምህር፤ ለኛ ሁሉ ንስሃ ለመግባት ምሳሌ በመሆኖ እግዚአብሔር ይስጦት።

Thursday, 25 October 2018

የሀገራችን የኢትዮጵያ ድህነት «የንስሐ ፖለቲካ» ነው!

የንስሐ ፖለቲካ ምን ማለት ነው? «ንስሐ» በመጀመርያ ስህተትን መገንዘብ እና ማመን ማለት ነው። «ተሳስቻለሁ»፤ «አውቄም ሳላውቅም አጥፍቻለሁ»፤ «በድያለሁ»፤ «የውሸት መንገድ ተከትያለሁ» ብሎ ማመን ነው የመጀመርያ የንስሐ ተግባር።

ይህ ስህተትን ማመን ብዙ ጥቅም አለው። በመጀመርያ እውነትን እንድናውቅ እና እንድናምን ያደርጋል። ለምሳሌ አንድ ፖለቲከኛ በማርክሲዝም አምኖ ሰዎችን «ጸረ አብዮት» ናችሁ ብሎ ጨቁኗል እንበል። ይህ ሰው መሳሳቱን ሲያምን አብሮ ማርኪስዝም ውሸት ነው፤ እውነቱ ስብዓዊነት ነው ብሎ ያምናል ማለት ነው። ንስሐው እውነትን እንዲረዳ እና እንዲቀበል አደረገው።

ሌላው የንስሐ ጥቅም የመንፈስ እርካታ ነው። የስህተት እና ሓጢአት ሸክም ከባድ ነው። ይቅርታ ስንጠይቅ ይህ ግዙፍ ሸክምን እናወርዳለን ማለት ነው። ሸክሙ ሲወርድልን ስራችንን በአግባቡ እንድንሰራ ይጠቅመናል።

ሶስተኛ የንስሐ ትቅም ተጎጂን ማጽናናት ነው። የሰው ልጅ «ይቅርታ አድርግልኝ» ሲባል ልቡ ይለሰልሳል እና ይረካል። ከበቀል ወደ ሰላም ይመለሳል። ይህ የልብ እርካታ እዚህ ላይ አይቆምም። በዳዩ ይቅርታ ሲጠይቀው ተበዳዩም የራሱን ስህተቶች እንዲገነዘብ ይረደዋል። የራሱን ስህተቶች እንዲያምን እና ይቅርታ እንዲጠይቅ ይገፋፈዋል። በዚህ መንገድ የይቅርታ፤ መግባባት እና ቅራኔ መፍታት መንፈስ በማህበረሰቡ ይንሰራጫል።

ሌላው የንስሐ ትቅም ስህተትን አውቆ ማረምያውንም ማወቅ ነው። አንዴ ስህተታችንን ካመንን ለችግሩ መፍትሄውን ማግኘት እንችላለን። በተቃራኒው ስህተታችንን ካላመንን ችግራችንን መፍታት አንችልም። ይህ ሁላችንም የምናውቀው ነገር ነው። አንድ መሪ የተሳሳተ እርምጃዎች እየወሰደ እና ችግሮችን እያመጣ እያለ ስህተቱን ካላወቀ እና ካላመነ ችግሩ መቼም አይፈታም። ስህተትን ማመን የችግር መፍታት ቅድመ ሁኔታ ነው። ስለዚህ ስህተታችንን ካመንን መፍትሄ ይመጣል።

ስለዚህ የንስሐ ሁለተኛ ተግባር ለስህተታችን የፈጠረው ችግሩ መፍትሄ አግኝቶ በተግባር መዋል ነው። ይቅርታ ከጠየቅን እና ስህታችንን ላለመድገም ከማልን በኋላ እንደ ሁኔታው ካሳ እንሰጣለን። ካሳ ማለት የተፈጠረውን ችግር ማስተካከል ማለት ነው። ከሰረቅኩኝ መመለስ። ከጎዳሁኝ ማደስ። ከዋሸሁኝ እውነቱን መናገር፤ ካበላሸሁኝ ማስተካከ፤ ወዘተ። አልፎ ተርፎ እንደዚህ አይነት ስህተትን ደግሜ እንዳልሰራ ተገቢውን ጸሎት፤ ተግባር፤ ትምሕርት ወዘተ ማድረግ እና መፈጸም ነው ያለብኝ። ይህ ነው ችግሩን መፍታት ማለት፤ ማስተካከል እና እንዳይደገም የሚያስፈልገውን ነገሮችን ማድረግ።

ይህ ካደረግን በጠቅላላው የተበላሸውን አስተካከልን ማለት ነው። ወደ እውነት መመለስ ነው። «ወደ ራስ (እውነት ማለት ነው) መመለስ ነው»።

ንስሐን በዚህ መልኩ ከተረዳነው «የንስሐ ፖለቲካ» ጥቅሙን እና አስፈላጊነቱን መገንዘብ ቀላል ይመስለኛል። በአጭሩ ለማስቀመጥ ያህል፤ ንስሐ መግባት የችግርን መፍታት ቁንጮ ነው። ፖለቲካችንም የመሃበራዊ ሁኔታችንም በርካታ የምናውቃቸውም የማናውቃቸውም ችግሮች አሏቸው። እነዚህን ችግሮችን ምንጮቻቸውን ሳናውቅ ወይን ሳናምን እንፈታቸዋለን ማለት ሃሰት ነው። ችግሮቹ የሚፈቱት መጀመርያ ችግር እንደሆኑ ካመንን፤ የራሳችንን ድርሻ ካመንን፤ ይቅርታ ከጠየቅን፤ መፍትሔ ከፈለግን እና እራሳችንን ከቀየርን ነው። ሌላ መንገድ በሙሉ አይሰራም። አልፎ ተርፎ ይህንን መንገድ ካልተከተልን ችግሮቻችን ይቀጥላሉ እየባሱም ይሄዳሉ።

የንስሐ ፖለቲካ በተግባር በታላቅ የፖለቲካ መድረክ ያየነው በጠ/ሚ አብይ አህመድ ስራዎች ነው። ጠ/ሚ አብይ ለአለፉት የኢህአዴግ ጥፋቶች «እንደ ግለሰብ» ተሳስችያለሁ ብለው ይቅርታ ጠይቀዋል። ንስሐ ገቡ ማለት ነው። ይህ በማድረጋቸው በርካታ ስኬቶች አምጥተዋል፤

1. ስህተታቸውን ተገነዘቡ እና አመኑ። ችግሮችን በአግባቡ ስለተረዱ ወደ መፍትሄ መሄድ ችለዋል።

2. ተጎጂውን በሙሉ ይቅርታ በመጠየቃቸው ህዝቡ የመንፈስ እርካታ እንዲያገኝ አድርገዋል። ብሶት እና ቂም በመጠኑ መቀነስ ችለዋል።

3. ሌሎቻችንም ለራሳችን ጥፋቶች ይቅርታ እንድንጠይቅ አስተምረውናል። ስህተታችንን አምነን የጎዳናቸውን አዝናንተን ወደ መፍትሄ እንድንሄድ ገፋፍተውናል። መሪአችን እንዲህ ካደረገ እኛም እንችላለን ነው።

4. አንጻራዊ የብሄራዊ ሰላም አምጥተዋል። ጠ/ሚ አብይ ይቅርታ በመጠየቃቸው አብዮት እና ሁከት እንዳይመጣ አድርገዋል። ሰው ይቅርታ ጠይቆ ይቅር ብሎ በሰላም እንዲኖር ገፋፍተዋል። የ«እውነት እና እርቅ» (truth and reconciliation) አይነት ሂደት ወደፊት እንዲጀመር ሜዳውን አብጅተዋል።

5. ይቅርታ፤ ትህትና እና ሃላፊነት መውሰድን በማንጸባረቃቸው የህዝብን እምኔታ አገኝተዋል።

የጠ/ሚ አብይ የ«ንስሐ ፖለቲካ» ከሞላ ጎደል በታላቁ ስኬታማ ሆኗል። አንድ ወይንም ሁለት ዓመት በፊት የአምባገነናዊ አገዛዛችን በዚህ መልኩ አለ አብዮት እና አለ ሁከት ይቀየራል ብንባል ሁላችንም አናምንም ነበር። የማሆን ነገር ነው እንል ነበር። ይህ ያልጠበቅነው ታላቅ ድል አለ «ንስሐ ፖለቲካ» አይሳካም ነበር።

እንደሚመስለኝ ከዚህ ታላቅ ትምሕርት መማር ያለብን «ኢትዮጵያ ብሄርተኝነት»፤ «አንድነት» ወይን የ«ዜግነት ፖለቲካ» የምናራምደው ጎራ ነን። ደጋግሜ እንደጻፍኩት ይህ የፖለቲካ ጎራ በርካታ የሀገራችን ፖለቲካ ችግርን ያመጣ ነው። በጃንሆይ ዘመን ተሃድሶ ማድረግ ባለመቻሉ፤ ግማሹ ማርክሲስት ሆኖ አብዮት እና ሁከት በማምጣቱ፤ እርስ በርስ በመጨራረሱ፤ በኢህአዴግ ዘመን አብሮ ስርቶ ተገቢ የተቃዋሚ ኃይል ማደራጀት ባለመቻሉ፤ ወዘተ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/07/blog-post_15.html)። እስከ ዛሬ የ«ኢትዮጵያዊነት ኃይሉ» መቢገባን ደረጃ መደራጀት አልቻልንም። ግንቦት 7 ነው ያለው ግን እሱም ከሚገባው እጅግ ትንሽ እና አቅም ያነሰው ድርጅት ነው። የሀገራችን እምብዛም ብዙሃን በ«ኢትዮጵያዊነት» የሚያምን ሲሆን ልሂቃኑ እና ፖለቲከኛው ይህን ብዙሃን ወክሎ ሊያደራጅ አልቻልም። የልሂቃኑ የክሽፈት ታሪኩ ተጭኖታልና።

የንስሐ ፖለቲካ ይህን የተጫነውን መንፈስ ያወርድላታል ብዬ አምንዳለው። ልክ እንደ ለነ ጠ/ሚ አብይ እንዳረገው። እንደ ግንቦት 7 አይነቱ ድርጅት ወደ ኋላ ሄደው እንደ ድርጅት፤ መሪዎቻቸው እንደ ግለሰብ፤ እራሳቸውን ፈትሸው ያደረጉትን ስህተቶች አምነው በይፋ ቢናገሩ ይበጃል። ስህተቱ ትንሽም ሊሆን ይችላል፤ ቅራኔን መፍታት አለመቻል ይሆናል። ግን ይህ ፍተሻ እጅግ ጠቃሚ ነው የሚሆነው። መማርያ ይሆናል።

ታሪክን በአግባቡ ፈትሾ ያሉን ችግሮች ከየት እንደተነሱ ማወቅ አስፈላጊ ነው። ይህ ሲደረግ የሁላችንም ጥፋት ይታያል። ችግሩን በህወሓት ብቻ መለጠፍ ተገቢ አይደለም እውነትም አይደለም። እንደዚህ አይነት የህጻን አስተያየት ነው ችግሮቻችን በአግባቡ እንዳይታወቁ እና እንዳይፈቱ የሚያደርገው። የራስ ሃላፊነትን ማምለጫ መንገድ ነው። ለሀገራችን ችግር ሁላችንም ትልቅ ሚና ተጫውተናል፤ በመስራትም ማለመስራትም። ይህ መታመን እና መነገር ያለበት ይመስለኛል። ይህን ካደረግን ችግሮቻችንን በደምብ አውቀን ትክክለኛውን መፍትሄዎችን እናገኛለን። በህዝቡም እምኔታ እናገኛለን። ከስህተት መማር እና መሻሻል ባህል እናደብራለን። የትህትና ባህል እናደብራለን። የሃላፊነት መውሰድ ባህል እናዳብራለን። ጠ/ሚ አብይ እንደሆኑት ስኬታማ እንሆናለን።

አልፎ ተርፎ የ«ንስሐ ፖለቲካ» ከባህል እና ከወጋችን አብሮ የሚሄድ በመሆኑ ድል የመሳካት እድሉ ከፍ ያለ ነው። «ህዝባችን የዴሞክራሲ ባህል የለውም» ይላሉ የዘመኑ ምሁራናችን። «ገና መማር አለብን እና የስነ ልቦና ለውጥ ያስፈልጋል» ይባላል። ለኔ ይህ አስተያየት የሚመነጨው ከሀገራችን ባህላዊ እሴቶችን በአግባቡ አለማወቅ እና አለመፈተሽ ነው። ከ«ምዕራብ ዓለም» የጫነብን ፕሮፓጋንዳ ማመን ነው ይህ አስተያየት የሚመጣው። ግን የጢ/ሚ አብይ ስኬታማ ስራ የሚያሳየው የኛ የትህትና፤ የይቅርታ፤ የንስሐ፤ እሴቶች በፖለቲካችን ታላቅ አውንታዊ ሚና መጫወት እንደሚችሉ ነው። ሌላ (የምዕራብም) ሀገር መፈጸም የማይቻል ድል ነው የጠ/ሚ አብይ አካሄድ ያመጣው! የት ሀገር ነው መሪ ለሌላ የፈጸመው ሳይሆን ለራሱ ስህተቶች ይቅርታ የሚጠይቀው? የት ሀገር ነው እንደዚህ በቀላሉ ህዝቡ ይቅርታውን የሚቀበለው?! የት ሀገር ነው ትህትና ያሚያንጸባርቅ መሪ የሚወደደው? ይህ አካሄድ ሀገራችን የሰራው ምክንያት ከሃይማኖቶቻችን ቀጥታ የመጡ እሴቶችንም ስለተጠቀመ ነው። ስለዚህ የንስሐ ፖለቲካ በመሰረታዊ ደረጃ ኢትዮጵያዊ አካሄድ ነው። የኢትዮጵያዊነት ፓርቲዎች፤ ይህን የንስሐ ፖለቲካ እንስራበት!

Tuesday, 23 October 2018

ብስለት የሞላው ውይይት

ይህንን ውይይት ጠንቅቃችሁ አዳምጡት ብዬ እለምናለሁ።

https://www.youtube.com/watch?v=PY9RFsmu_ks

የተነሱት ዋና ዋና ነጥቦች፤

1.ዛሬ ያለንበት ፓለቲካዊ እና ማህበረሰባዊ ሁኔታ እና ችግሮች 27 ወይን 44 ወይን 50 ዓመት የፈጠረው አይደለም። ከዛ በፊት ያለን የረዥም ዓመታት ታሪክም አስተዋጾ ያለው ነው። ይህን አውቀን ነው ወደ እውነት እና ትክክለኛ መፍትሄ ምድረስ የሚቻለው።

2. ራስን መመርመር ግድ ነው። ችግሮቻችን በመንግስት እና በፖለቲከኞች ምክንያት ነው የመጣው ማለት ልክ አይደለም። እውነት አይደለም። ሁሉም ዜጋ በራሱ በኩል ሚና ተጫውቷል እና ላለፈውም ለወደፊቱም ሃላፊነት መውሰድ አለበት።

3. ፖለቲካ አንድ የማህበረሰባዊ ኑሮ ክፍል ነው። በመሆኑ ሁሉ ዜጋ በአቅሙ እና በአግባቡ መሳተፍ አለበት። እናት እንደ እናት፤ አባት እንደ አባት፤ ልጅ እንደ ልጅ፤ ሃይማኖት መሪ እንደ ሃይማኖት መሪ፤ ምሁር እንደ ምሁር፤ ሰራተኛ እንደ ሰራተኛ ወዘተ።

4. የግብረ ገብ እጦት ታላቅ ችግር ነው እና ሊሰራበት ይገባል። እንደማንኛውም ችግር ይህ ችግር የሚፈታው መጀመርያ አመጣጡ፤ ምክንያቱ እና ምንጩ ሲታወቁ እና ሲታመኑ ነው።

5. ለውጥ ማለትም ወደ የተሻለ ፖለቲካ እና ማህበራዊ ሁኔታ መቀየር ጊዜ ይፈጃል። ትዕግስት ይጠይቃል። ምርጫ እና ተመሳሳይ ስርዓቶች አለ ቅድመ ዝግጅት እና የአስተሳሰብ ለውጥ ጎጂ ነው የሚሆኑት።

6. ዛሬ ከሞላ ጎደል የፖለቲካ «ነፃነት» አለ። ቋሱ በኛ በህዝቦቹ ሜዳ ነው ያለው። ችግር ካለ መፍታት የኛ ሃላፊነት ነው። ሃላፊነታችንን እንደ ዜጎች መቀበል ግድ ነው። በሌላ ለምሳሌ በመንግስት ባሳበብ አብቅቷል።

Wednesday, 10 October 2018

የቅራኔ መፍታት (conflict resolution) ጉድለታችን

አንዱ ከብዙ የጠ/ሚ አብይ አህመድ ልዩ የሚያረጋቸው ችሎታዎች የቅራኔ መፍታት አቅማቸው ነው። ትዕቢት፤ ቂም፤ አሉታዊነት፤ ትቶ የሁሉንም ትቅም የሚያስከብር ለሁሉም ተመራጭ የሆነ ግባ ላይ በማተኮር ችግሮችን ፈትተዋል አሁንም እየፈቱ ይገኛሉ። ይህ አቅማቸው ከኢትዮጵያ ፖለቲካዊ መሪዎች ለዘመናት ታይቶ አይታወቅም (https://ethsat.com/2018/10/ethiopia-soldiers-show-up-unannounced-at-national-palace-pm-orders-pushups/)።

@Samuel Abebe (በዚህ ትችት ላይ https://www.facebook.com/abdurahman.ahmedin.7/posts/2120966214582614?comment_id=2121015731244329) ሁላችንም በውስጣችን የምናስበውን ታላቅ ጥያቄ ጠየቀዋል፤

«መለወጥ ስህተትን ከመቀበል ይጀምራል ይባላል ትልቅ ስህተት ተፈጽሞም ከቅንጅት አመራሮች ስህተቱን ተቀብሎ እዚህ ላይ ይህን ባንሳሳት ኑሮ የሚል አመራር እንዴት ይጠፋል? ሁሉም ወደ ሌላ ሰዉ ጣቱን ይቀስራል፡ እኛስ የትኛዉን አምነን የትኛዉን እንቀበል?»

ዋና እና ተገቢ ጥያቄ ነው። ብስለት እና እውቀት የሞላው። በማንኛውም ቅራኔ አንድ ጥፋተኛ እና ሌላው ንፁሃን የለም (there are two or more sides to any conflict)። ይህን ሃቅ ማንኛውም ስለቅራኔ የሚያውቅ ባለሙያ፤ ማንኛውም የካህን፤ ማንኛውም አስተዳዳሪ፤ ማንኛውም ወላጅ የሚያውቀው ነው። ግን ብናውቀውም እንዳማናውቀው አድርገን ነው የምንኖረው። ቅራኔ ውስጥ በተገኘን ቁጥር እራሳችንን ፍፁም ንፁህ ሌላው ፍፁም ጥፋተኛ አድርገን ነው የምንቆጥረው።

ይህ ከገባን በቅንጅት ቅራኔ ህሉም ተሳታፊዎች የተወሰነ ሚና መጫወታቸውን ሊገባን ይገባል። የፈረደበት ልደቱ ጥፋት ብቻ ሊሆን አይችልም። ዋናው ችግር የሱ ነው ቢባልም ያንን ችግር ማስተናገድ አለመቻል በራሱ ትልቅ ድክመት ነው! መታመን ያለብት እና ይቅርታ የሚጠየቅበት ድክመት ነው። ታላቅ መማርያ የሚሆን ድክመት ነው።

እንደ ቅንጅት አይነት ታላቅ ድርጅት፤ እጅግ ግዙፍ የሆነ የሀገር ሃላፊነት ያለው ድርጅት ሲፈርስ ሁሉም በአመራር ያሉት በመፍረሱ ሚና ተጫውተዋል እና ሁሉም ድክመታቸውን አምነው ይቅርታ ሊጠይቁ ይገባል። እኛም ደጋፊዎቻቸው እንዲሁም። ያደረግነውን ስህቶቻችንን ካመንን በኋላ ብቻ ነው መማር የምንችለው እና እንዳንደግማቸው ማድረግ የምንችለው።

የቅንጅት ታሪክ ከብዙ የሀገራችን ፖለቲካ የቅራኔ መፍታት አለመቻል ታሪኮቻችን አንዱ ነው። እንዳውም በኔ እምነት የፖለቲካ እና ማህበራዊ ችግሮቻችን ዋና ጎልቶ የሚታየው ምክንያት «የቅራኔ መፍታት (conflict resolution) ጉድለታችን» ነው። በዚህ ዙርያ ብዙ ተጽፏል እና ተነግሯል ግን በቂ አልተደረገም። ዛሬም የምናያቸው ነገሮች አሉ፤

1. አንድ «አቋም»፤ ርዕዮት ዓለም፤ አስተያየት ኖሮን አብሮ መስራት አለመቻል
2. የራሳችንን ጥቅም ጎድተን ቂማችንን ለመወጣት የምናደርጋቸው ስህተቶች
3. የጋራ ማሸነፍን ከመፈለግ (አሁንም የራሳችንን ጥቅም ቢጎዳም) ሌላው እንዲሸነፍ መመኘት እና መስራት
4. ፖለቲካን እንደ ሃይማኖት ፍፁም እውነት እንዳለው መቁጠር።

የፖለቲካ አካሄዳችን እንዲሻሻል ከተፈለገ ስለነዚህ ጉዳዮች መያየት እና መፍትሄ ማግኘት ግድ ነው።

ቅራኔ መፍታት ለኛ ኢትዮጵያዊያን አዲስ ነገር አይደለም። የድሮ ንጉሶቻንን አድርገውታል። ይህን የሚያስፈጽሙ በርካታ ባህላዊ መንገዶች አሉን። ከሃይማኖታችን ደግሞ መሰረታዊ ቅራኔ መፍታት ምክንያቶችንም ዘዴዎችም አሉ። ለምሳሌ በክርስትና «ንስሃ» ማለት ማለት 1) ስተትን ማመን 2) እንዳይደገም 3) ሌላው እንዲገባው 4) እራስን ለማረም 5) እራስን ለማወቅ ወዘተ። ውየንም «አለመፍረድ» ማለት 1) ለሌላው መቆርቆር (empathy) 2) የተሳሳተ ድምዳሜ ላይ ችኩሎ አለመድረስ 3) ጣት ጠኩሞ የራስን ችግር መርሳት ወዘተ።

ስለዚህ አሁን ማድረግ ያለብን እነዚህን (ምናልባት የተረሱ) ባህላዊ እሴቶችን እንደገና ማስነሳት እና ማሰራጨት ነው። ከባድ ስራ ነው ግን ምርጫ የለንም!

http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_21.html

Monday, 1 October 2018

በሌሎች መፍረድ

ሁል ጊዜ ሌሎች ሰዎችን ጥሩ ካልሆናችሁ ብለን የምንጠብቀው የራሳችንን ድክመት በነሱ ላይ እየጫንን ስለሆነ ነው። እራሳችን ጥሩ መሆን እንፈልጋለን። ግን ባለመቻላችን ምክንያት ሌሎችን ጥሩ ካልሆናችሁ ብለን እንጫናለን። ይህን አስተሳሰብ ተከትለን አብዛኛው ጊዜ እንጨነቃለን፤ በሌሎች እንበሳጫለን እና እንፈርዳለን። ሆኖም ሁሉንም ነገር በፀሎት ማሸነፍ ይቻላል።

ቅዱስ ፖርፎሪዮስ
Elder St Porphyrios, 'Wounded by Love'

Friday, 21 September 2018

ጎጂ ፀባዮች ላይ ዘመቻ ማካሔጅያ ጊዜ አሁን ነው!

12 ዓመት በፊት በ1998 ቅንጅት ሲፈራርስ በንዴት እና በሃዘን በሌላው የብእር ስሜ (ደሳለኝ አስፋው) የጻፍኩት ጽሁፍ። አሁንም የሚያስፈልገን ይመስለኛል።

የኢትዮጵያ ብሄርተኞች በተለይም ግንቦት ሰባት፤ ሃላፊነታችን ግዙፍ ነው። አሁንም አንዳናጠፋ (http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/07/blog-post_31.html)። ከበፊቱ እንማር።

(አማርኛው ከታች ይቀጥላል)
---------------------------------------------

Time to Declare War on Dysfunctional Behaviours


The recent controversy surrounding Kinijit supporters in the diaspora—Kinijit USA (KUSA) and Kinijit International Leadership (KIL)—is the latest in a history of feuding and infighting among Ethiopian political interest groups and parties. Indeed, over the past few decades, we have seen countless political organizations created, only to be shortly disbanded, abandoned, or rendered ineffective, often because of intra-group conflict—conflict among the membership—and an inability to resolve conflict.

I believe that these conflicts are a fundamental reason for the absence of democracy in Ethiopia today. Indeed, it is these conflicts, magnified to a national level, that have resulted in dictatorship after dictatorship in Ethiopia. Endless feuding and infighting from the grassroots level on upwards have made it difficult for Ethiopians to attain the organic solidarity necessary to build and sustain the institutions necessary for democracy. I think it is imperative that pro-democracy activists make awareness of intra-group conflict a top priority in the struggle for democracy. But before I make my case, I would like to describe the nature of the problem in greater detail.

Here are a few interesting points. First, the intra-group conflicts we see in Ethiopian collectives are seldom caused by differences in ideology, organizational structure, or other substantive reasons. Nor are they confined to organizations whose members come from a wide variety of backgrounds and perspectives. Indeed, the most virulent conflicts occur in apparently homogenous groups whose memberships have not only similar ideologies, but similar frames of reference, perspectives, and interests. The current KUSA/KIL conflict, for the most part, is an example of this.

Another interesting point is that such conflicts occur just as much in the Ethiopian diaspora as they do in Ethiopia. This is interesting because, in the diaspora, factors such as poverty, political oppression, lack of education, etc., do not exist.

Finally, intra-group conflicts are not restricted to organizations of a political nature. They are found in all types of Ethiopian collectives. We can observe chronic feuding and infighting in families, extended families, non-political civic organizations such as professional associations, churches, local community organizations, charity organizations, and others.

So, why is there so much intra-group conflict, characterized by personal feuds and infighting, in Ethiopian society? And when there is conflict, why is conflict resolution so difficult? One explanation is that we have been brought up in an environment where certain dysfunctional behaviours that hamper effective communication and cause conflict are the norm. Below is a list of some of these behaviours that I have observed. I ask readers to reflect on whether you have seen them in yourself; in others; in meetings and other group settings.
  1. Personalization of issues: This is when we are unable to conceptually distinguish between people and their ideas or thoughts. For example, if someone objects to a suggestion I make, I see the objection as personal attack, not as a simple difference of opinion. In response to the perceived personal attack, I respond with a personal attack, instead of discussing the issues. Hence, the initial disagreement over ideas turns into a personal struggle, and because it is a personal struggle where pride and survival are at stake, we end up unable to constructively ‘agree to disagree’. Groups whose members find it difficult to ‘agree to disagree’ become paralyzed by feuding and infighting and eventually collapse.

  2. Parochialism (weganawinet): We tend to irrationally favour those from our own kin or wegen—family, village, team, ethnic group—no matter what the cost. For example, if a person from my wegen has a conflict with a stranger (be’ad), a person outside my wegen, I automatically favour my colleague, no matter what the substance of the disagreement. Furthermore, I extend the conflict to a dislike of the stranger and his entire wegen—his family, friends, place of employment, ethnic group, etc. This is the root of blood feuds (dem). Parochialism within organizations leads to ineffectiveness, as decisions are made based on who supports the decisions, rather than on their merit. It also leads to organizations being split into smaller and smaller factions, and eventually collapsing. For example, an organization may split into two main factions. Factions will develop within those factions, and further splitting will occur, until the organization fails.

  3. Chronic suspicion and mistrust (teretaray): We view each other first and foremost as potential threats. With such a heightened level of threat-awareness, any idea or thought, no matter how innocuous, is quickly considered to have negative ulterior motives behind it. Even the most innocent comments by the closest of friends can be misinterpreted as sinister, resulting in the breakup of fruitful relationships. This behaviour is a fundamental cause of conflict in a group setting. By definition, no group can be effective without trust.

  4. Paranoia: As we view everyone as a threat, we tend to disproportionately develop a paranoid outlook in our interaction with others, with the ‘threat’ foremost in our minds in all our interactions. This paranoia, in a group setting, results in organizational paralysis, with everyone looking over their shoulder and hesitant, instead of working towards the common goal.

  5. Lack of empathy and empathetic understanding: Empathy, the ability to identify with or understand others’ situation, feelings, and actions, is critical for effective communication and teamwork. However, in Ethiopian society, we are not sensitized to the importance of empathy. We do not ask questions such as ‘what in his background might have caused him to react this way’, or ‘what would I have done in his shoes’. This leads us to make erroneous judgements based on incomplete understandings, which leads to misunderstanding and conflict within groups.

  6. Lack of suspending judgement or giving others the benefit of the doubt: Suspending judgement is fundamental to effective communication. Unfortunately, the combination of chronic suspicion and lack of empathetic understanding lead to the absence of awareness about the concept of suspending judgement and giving others the benefit of the doubt. If someone does something we do not understand, we do not ask, ‘Perhaps there is something he knows that I don’t,’ or ‘Let me wait and see before making a judgement.’ We judge hastily, without taking time to examine all possibilities. This results in erroneous judgements and personal conflicts.

  7. Character assassination (sem matfat and alubalta): Rather than addressing conflict directly, we chronically spread rumours and innuendo about those with whom we disagree. We engage in character assassination because we know that it is an effective weapon in our society. Since we do not give each other the benefit of the doubt, we tend to believe bad things about others! A strategy of muddying someone’s reputation will render them useless, as people will simply have had their existing suspicions confirmed. Obviously, character assassination quickly leads to infighting and paralysis in groups, a scenario with which most of us are familiar.

  8. Lack of openness: Openness facilitates effective communication. As Ethiopians, we are not open and forthcoming about our thoughts and expect the same guarded approach from others. This is related to our lack of empathy, which makes us afraid of being judged hastily and incorrectly if we speak openly. This fear leads us to be initially vague, unclear, and non-committal, which inevitably leads to communication gaps and communication breakdown, as others persistently try to interpret the hidden meaning of what we say, and often end up interpreting negatively and incorrectly. Lack of openness leads to misunderstanding and conflict.

  9. Holding grudges (qim and mequeyem): We tend to chronically hold on to personal grudges. Understanding or forgiveness of perceived affronts is seen as weakness, as it is assumed that everyone is and remains to be a threat. In a group setting, there are bound to be conflicts, and if people hold on to grudges, there can be no effective teamwork.

  10. Envy (mequegnenet): We hate it when others are better off than us in any context, but instead of struggling to improve our own lot, we work to reduce others’! This comes from our ingrained perception that everything in life is a zero-sum game. If someone is rich, it is because another is poor. If someone is happy, it is because another is sad. It is as if the world has been alloted a fixed amount of wealth, happiness, etc., and it has been ordained that everyone should have more or less the same amount. Failing this, the ones with more must have committed some kind of crime to improve their lot and the ones who have less must be cursed.

  11. Stubbornness and lack of compromise (getterenet): Because of our zero-sum view of the world, compromise is seen as a weakness. We do not understand the concept of compromise as a building block for future win-win endeavours. Instead, compromise is seen as a loss forever.
I am sure that all of us have seen first hand these behaviours manifested in various contexts. We have also seen the resulting conflicts in our various collectives, from families to religious groups to political organizations.

On the other hand, most of us in the diaspora have been exposed to non-Ethiopian collectives where, generally speaking, such conflicts occur far less often. We have also observed that these collectives are, as a result, far more effective and efficient than Ethiopian collectives.

In order to bring Ethiopian collectives, including Ethiopian pro-democracy and human rights organizations such as KUSA and KIL, to this level, it is crucial that we find a way to raise awareness that intra-group conflict is a fundamental barrier to democracy, to put an end to our dysfunctional group behaviours, and to promote positive, constructive behaviours that reduce conflict, increase our capacity for conflict resolution, and increase collective consciousness and organic solidarity.

To this end, as a first step, I suggest that all organizations draft a code of conduct document. The aim of this document should be primarily to raise awareness about dysfunctional behaviours, the problem of intra-group conflict, and the importance of effective communication. In addition, the code of conduct should provide guidelines of behaviour and conduct, along with explanations for the guidelines.

My second suggestion is that there should be a collective attempt to stigmatize dysfunctional behaviours in our everyday lives. For example, we must make it telek newur to attack anyone personally instead of addressing issues. We must not only refuse to listen to character assassination, but openly chastise and correct those who do it. In a charitable and constructive manner, of course—we have to keep in mind that most of us engage in such behaviour almost unknowingly, because of the culture we have grown up in. Unless sensitized to the ramifications of such speech and actions, we cannot become fully aware of the consequences.

I believe that these two actions alone will result in a significant reduction in the chronic feuding and infighting in our collectives and organizations. The resulting increase in organic solidarity and collective consciousness will, in due course, crowd out dictatorship at all levels of our society, including the political. The democratic culture at the grassroots will end up being reflected at the national level.

Indeed, imagine diaspora pro-democracy groups devoid of feuding and infighting. They would make great strides in improving the prospects for democracy in Ethiopia. Imagine that behaviours such as suspicion and paranoia were no longer the norm inEthiopia. Dictatorship, which thrives on suspicion and paranoia, would disappear shortly.

Doing away with dysfunctional behaviours and intra-group conflict is the only way to achieve democracy. To those who believe in democracy for Ethiopia, I say, we need an all-out campaign: Let us declare war on dysfunctional behaviours!

Dessalegn Asfaw

--------------------------------------------

ጎጂ ፀባዮች ላይ ዘመቻ ማካሔጅያ ጊዜ አሁን ነው!


ባሳለፍናቸው ብዙ አመታት ውስጥ ብዙ ድርጅቶች ተመስርተው አይተናል። ይሁን እንጂ የእነዚህ ድርጅቶች አባሎች በውስጣቸው የሚፈጠረውን ቅራኔ መፍታት ባለመቻላቸው ድርጅቶቹ እንደሚገባቸው ያህል አይሰሩም።

እኔ እንደተመለከትኩት እነኝህ ቅራኔዎች በኢትዮጵያ ውስጥና በውጭም በምንኖር በተለያዩ ኢትዮጵያውያን ስብስቦች ውስጥ አሉ። ስብስቦች ስል የፖለቲካ ድርጅቶችና ሌሎችም ታላላቅ ስብስብ ብቻ ሳይሆን፤ የቤተሰብ፣ የዘመድ፣ የጓደኝነት፣ የሞያ ማኅበራት፣ የሲቭል ተቋማት፣ የቤተክርስትያንና ሌሎች የሃይማኖታዊ ስብስቦች፣ የኮምዩኒቲ ድርጅትና የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ይጨምራል። ከላይ የጠቀስኳቸው ሁሉ ሥር የሰደዱ ውስጠ-ቡድን ቅራኔዎችና ሽኩቻዎች ይገኝባቸዋል።

እነዚህ ውስጠ ቡድን ቅራኔዎች የሚፈጠሩት እምብዛም በርእዮተ ዓለም፣ በድርጅት አወቃቀርና በአንኳር ምክንያቶች አይደለም። እነዚህ ቅራኔዎች የተለያዩ አመለካከትና አነሳስ ያላቸው አባሎች በመሠረቱት ድርጅት ውስጥ ብቻ የተወሰነም አይደለም። እንዲያውም ቅራኔዎች በይብስ የሚታዩት በርእዮተ ዓለም፣ በአመለካከት፣ በግንዛቤና በፍላጎት በጣም የሚመሳሰሉ ሰዎች ባሉባቸው ድርጅቶች ውስጥ ነው።

እነዚህ ቅራኔዎች በኢትዮጵያ ውስጥ የሚንፀባረቁትን ያህል በውጭ አገር ባሉ ኢትዮጵያውያን ውስጥም ይንፀባረቃሉ። ይህ አስገራሚ ነው፡ ምክንያቱም በውጭ አገር ድህነት፣ የፖለቲካ ችግር፣ የአስተዳደር ጉድለት ወይም የትምህርት እጥረት ሳይኖር ቅራኔዎች ግን እንደ አገር ቤት መኖራቸው ነው።

ታዲያ ለምንድነው በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር በኢትዮጵያውያን ማህበረ ሰብ፣ በግላዊ አመለካከት ውስጠ ቡድን ቅራኔ የሚኖረው? እናም ውስጠ ቡድን ቅራኔ ሲኖር ቅራኔውን ማስወገድ ለምንድነው አስቸጋሪ የሚሆነው? ለዚህ አንደኛው መልስ እኛ በነዚህ ቅራኔዎች ውስጥ የምንኖር ሰዎች በመሆናችን እነዚህ ግንኙነትን ደካማ የሚያደርጉ ሽኩቻዎችና ጎጂ ፀባዮች የህልውናችን አካል ስለሆኑ ይሆናል። ማለትም ባህላችን የነዚህ ቅራኔዎች ምንች ስለሆነ ነው።

ከዚህ ቀጥሎ እኔ የተገነዘብኳቸው አንዳንድ ጠባዮች ተዘርዝረዋል። አንባብያንን የምጠይቀው እነዚህን ጠባዮች እናንተም በራሳችሁ፣ በሌሎች ሰዎች፣ በስብስቦችና በመሳሰሉ ስብሰባዎች ተገንዝባችሁ እንደሆን ነው።

1. ነገርንና ግለሰብን ማቆራኘት

ይህ ግለሰብንና የግለሰብን ሃሳብ ለይቶ አለማየት ነው። ለምሳሌ አንድ ግለሰብ የተቃውሞ ሃሳብ ከሰጠ የሃሳብ ልዩነት መሆኑ ቀርቶ ግለሰቡን ለማጥቃት ይሞከራል። ተቃውሞ የተነሳበትም ግለሰብ በአንፃሩ አፀፋዊ ጥቃት ለማድረግ ይፈልጋል። በመጨረሻም የሃሳብ አለመግባባት ወደግለሰብ ጥል ይሸጋገራል።ይህም ግለሰቦች ክብርና ህልውናቸው የተጠቃ ስለሚመሰላቸው ነው። ላለመስማማት መስማማት የማይችሉ ሰዎች በግለ ሰባዊ ፀብና ሽኩቻ ይሽመደመዱና ቡድኖች ይፈርሳሉ።

2. ወገናዊነት

የፈለገው ቢሆን ለምናውቀው ወገን፣ ቤተሰብ፣ መንደር፣ ቡድንና ዘር መወገን እንፈልጋለን። ለምሳሌ ወገናችን የሆነ ሰው ከሌላ ወገን ግለሰብ ጋር ቢጋጭ የነገሩን ሁኔታ እንኳን ሳናውቅ ወገንተኛነታችንን እናሳያለን። በዚህም ቅራኔ ምክንያት ጥላቻውን አስፍተን የተቃዋሚውን ወገን፣ ቤተሰብ፣ ጓደኞች፣ የሥራ ቦታ፣ ጎሳ እናወግዛለን። ይህ ለደም መፋሰስ ምንጭ ሊሆን ይችላል። ወገናዊነት ቡድን ያፈርሳል ምክንያቱም ውሳኔዎች በወገናዊነት እንጂ በትክክለኛነታቸው ተፈፃሚነት ስለማይኖራቸው ወገናዊነት ድርጅቶችን ከፋፍሎ ድርጅቶቹን ያፈርሳቸዋል። ለምሳሌ አንድ ድርጅት ሁለት ቦታ ይከፈልና ሁለቱ ደግሞ ብዙ ቦታ እየተከፈሉ በመጨረሻም ባጠቃላይ ደርጅቱ ይፈርሳል።

3. ጥርጣሬ

በመጀመሪያ ደረጃ እርስ በእርሳችን የምንተያየው በጥርጣሬ መንፈስ ነው። በዚህም ምክንያት ጉዳት የሌላቸው ሃሳቦች እንኳን ከጀርባቸው ሌላ ነገር አላቸው ተብለው ይፈራሉ። ፍፁም የዋህ የሆነ የጓደኛ አመለካከት እንኳን በጥርጣሬ እንደ እርኩስ ሃሳብ ተተርጉሞ የዳበረ ግንኙነት ይፈርሳል። ይህ አይነት ጠባይ የደርጅቶች ውስጠ ቅራኔ መሠረታዊ ምክንያት ነው። ለእውነት ከሆነ መተማመን ከሌለ ምንም ዓይነት ድርጅት ውጤታማ ሊሆን አይችልም።

4. ፍርሀት

ሁሉንም ሰው እንደ አደገኛ ሰው ስለምናይ በአስተሳሰባችንና በአመለካከታችን ውስጥ ፍርሀት ይዳብራል። እንዲህ አይነት ፍርሀት ድርጅቶችን ሽባ ያደርጋቸዋል። ይህም የሚሆነው ሁሉም በፍርሀት እያመነታ ጉዳይን ከግብ ለማድረስ ወደፊት መሄድ ስለማይቻል ነው።

5. ተቆርቋሪ አለመሆን

የሌሎችን ስሜት፣ ተግባርና ሁኔታ ራሳችንን በሌላው ቦትና ሁኔታ አድርገን አለማየት ለሌላው አለመቆርቆርን ያመጣል። ተቆርቋሪ መሆን ለጤናማ ግንኙነት አስፈላጊ ነው። አንድ ሰው አንድ ነገር እንዴት ሊሰራ እንደቻለ ወይንም ደግሞ እኛ በሱ ቦታ ብንሆን ኖሮ ምን ማድረግ እነደምንችል እራሳችንን አንጠይቅም። ይህ ወደተዛባ ፍርድና ጎዶሎ ግንዛቤ ያመራና በቡድኖች ውስጥ አለመግባባትና ቅራኔን ይወልዳል።

6. ለመዳኘት ወይም ለመፍረድ መቸኮል

ለመዳኘት አለመቸኮል ለጤናማ ግንኙነት መሠረት ነው። ጥርጣሬና ለሌላው አለመቆርቆር ተደማምረው ውዝግብ ከማቅለል ይልቅ ፍርደ ገምድልነትን ያመጣሉ። አንድ ሰው እኛ የማይገባንን ነገር ካደረገ ቆይ እስቲ እኛ የማናውቀውና እሱ የሚያውቀው ነገር ሊኖር ይችላል ብለን እራሳችንን አንጠይቅም ወይንም ከፍርድ በፊት ትእግሥት አናደርግም። የነገሮችን የመሆንና ያለመሆን ሁኔታ ሳንዳስስ ለመዳኘት እንቸኩላላን። ይህ ወደተዛባ ፍርድና ግለሰባዊ ቅራኔ ውስጥ ይከተናል።

7. ስም ማጥፋትና አሉባልታ

ቅራኔዎችን ከመፍታት ይልቅ የማይግባቡን ሰዎች ላይ የስም ማጥፋት ዘመቻ እናደርጋለን። እንዲህ አይነቱ ዘመቻ በማኅበርሰባችን ውስጥ እንደሚሰራ እናውቃልን። አምታችና አሻሚ የሆኑ ነገሮችን በስነሥርዓት ሳንዳስስ ስለግለቦች የሚባለውን መጥፎ ነገር ማመን እንመርጣለን። የግለሰቦችን ክብር የሚነካ ነገር በማድረግ ግለሰቦችን ከጨወታው ውጭ እንዲሆኑ እናደርጋለን። ቀደም ብሎ እንዲህ አይነት ግንዛቤ ያለው ጭንቅላት ጥርጣሬውን የስም ማጥፋቱ ተግባር ግልፅ ያደርግለታል። እንዲህ አይነቱ አሉባልታ ብዙዎቻችን እንደምናውቀው ወደግለሰቦች ሽኩቻ፣ የቡድኖች ሽባነትና የድርጅት ውድቀት ያመራል።

8. ግልፅ አለመሆን

ግልፅነት ጤናማ ግንኙነት እንዲካሄድ ይረዳል። እኛ አስተሳሰባችንን ግልፅ ካለማድረጋችን ባሻገር የሌላውም አስተሳሰብ ግልፅ ይሆናል ብለን አንጠብቅም። ይህም በግልፅ ከተናገርኩ ምንነቴ ይታወቃል፣ እዳኛለሁ የሚለውን ፍራቻ ያመጣል። በዚህ ምክንያት ነገሮችን አድበስብሰንና በግድየለሽነት የግንኙነት ክፍተት ፈጥረን የድርጅት ውድቀትን እናመጣለን ምክንያቱም ሌሎች የተደበቀ ነገር አለ ብለው ስለሚገምቱ።

9. ቂም መያዝና መቀየም

ቂመኛነት ከባህላችን የመነጨ ስለሆነ ቂም እንይዝና ይቅር ማለትን እንደድክመት እናየዋለን ምክንያቱም ሁሉም እንደአደገኛ ስው ስለሚታይ ነው። በቡድን ስራዎች ውስጥ ሁሌም አለመግባባት ሊኖር ስለሚችል ቂም የምንይዝ ከሆነ ምንም አይነት ውጤታማ ሥራ መሥራት አይቻልም።

10 ምቀኝነት

በብዙ መንገድ ሰዎች ከኛ ተሽለው ሲገኙ እንደነሱ ተሽሎ ለመገኘት ከመጣር ይልቅ እነሱ እንደኛ እንዲሆኑ ወደታች እንጎትታቸዋለን። ይህ የሚሆነው፣ ሲደመር ዜሮ እንደሚሆን የሂሳብ ስሌት እንዱ ሀብታም የሚሆነው ሌላው ደሀ ስለሆነ፣ አንዱ ደስተኛ የሆነው ሌለውን ስላሳዘነ ነው ከሚል ግንዛቤ ሊሆን ይችላል። ይህ ዓለም የተወሰነ ሀብት፣ ደስታና የመሳሰሉት ነገር እንዳለው አድርገን እናይና ሁላችንም ድርሻችንን እንጠይቃለን። በመሆኑም ሰዎች የከበሩት የሆነ ወንጀል ሠርተው ሲሆን ያጡት ደግሞ ተረግመው ነው ብለን እናስባለን።

11. ግትርነት

መቻቻልን የምናየው እንደድክመት ነው። የመቻቻልና የመደራደር ፅንሰ ሃሳብ ለወደፊቱ ውጤታማ ጥረቶች የመሠረት ድንጋይ መሆኑን አንረዳም። እንዲያውም መቻቻልን የምናየው እንደተሸናፊነት ነው።

12. አጉል ይሉኝታ

ይህ ሌላውን ሰው ላለማስቀየም የሚወሰድ ባህለዊ እርምጃ ነው። የግለሰቦችን ወይንም የቡድኖችን ሕልውና ላለመንካት ሲባል ከእውነት የራቀ ሃሳብ ወይንም ድርጊትን ሳናስተካክል ወይንም ሳናርም ስለምናልፍ ሁሉም እርስ በርሱ እንዳይተማመን ይሆናል። ለእውነት መቆም የተፈጠሩትን ብቻ ሳይሆን ሊፈጠሩ የሚችሉ ችግሮችን ሁሉ ሊያቃልል ይችላል።

13. አስመሳይነት

ራስን አለመሆንና እንደሳንቲም ሁለት ገፀታ ይዞ መጓዝ በቡድን አባሎችና ደርጅቶች ውስጥ ከፍተኛ አደጋ ያመጣል። የማናውቀውን እናውቃለን፣ የሌለንን አለን ካልን ሥራችን ልብወለድ እንጂ ተጨባጭ ነገሮችን ሊያንፀባርቅ የሚችል አይ ሆንም። በመሆኑም እንዲህ አይነቱ ጠባይ መጋለጥና መቆም ይኖርበታል።

በመጨረሻም እነዚህ ከላይ የተገለፁት ፀባዮች በኛ በኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን በሌላው የሰው ዘር ውስጥ በመጠኑ የሚገኙ የስነ ልቦና ባህርያት ናቸው። ነገር ግን እነዚህ ፀባዮች አሁን እኛ ካለንበት ድህነትና የማህበራዊ ቀውስ ውስጥ ለመውጣት በምናደርገው ትግል ላይ ያላቸው ጎጂ ሚና ታውቆ አስፈላጊውን እርማት ማድረግ ይኖርብናል። የተሻለ ሥርአት ለማምጣት የአስተሳሰብ ለውጥ ማድረግ እንደሚያስፈለግ ማወቅ አለብን።