Friday 1 March 2019

የአዲስ አበባ ጉዳይ እና የሃላፊነት ፖለቲካ

በተለያዩ ጽሁፎቼ የኢትዮጵያ ፖለቲካ መሰረታዊ ችግር የ«ኢትዮጵያዊነት» ጎራው ለራሱ እጣ ፈንታ ሃላፊነት አለመውሰዱ ነው ብያለሁ። ላለፉት 50 ዓመታት ተደራጅቶ ፍላጎቶቹን አጣርቶ ከማስከበር ይልቅ ህልውናውን ለሌሎች ትቷል። ሃላፊነት ለሌሎች መታው ባህል አድርጎታል። ይህ አካሄድ የ«ለቅሶ ፖለቲካ» ብሄ ሰይምዬዋለሁ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/blog-post_16.html)።

ይህ ሁኔታ ምክንያት አለው፤ የኢትዮጵያዊነት ጎራው በአብዮቱ ጀምሮ እርስ በርስ ተገዳድሎ ልሂቃኑ እራሱን አጥፍቶ እስካሁን አላገገመም። (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/1.htmlhttps://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/2.htmlhttps://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/3.htmlhttps://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/4.html)። ቢሆንም በዚህ አካሄድ መቀጠል አይቻልም። ሌሎችን «ፍላቶእ እና መብታችንን አስከብሩልን» ብለን እየለመንን መቀጠል አይቻልም።

አሁን የሚያስፈልገን ከ«ለቅሶ ፖለቲካ» ወጥተን፤ ከህጻንነት እና ብሽተኝነት ወትጠን ወደ «ሃላፊነት ፖለቲካ» መግባት አለብን። ግድ ነው፤ አማራጭ የለም። እነ ለማ ይሁን አቢይ ይሁን ህወሓት ይሁን ግንቦት 7 ይሁን አብን ወዘተ እንዲህ አድርጉልን ብለን መለመን አይቻልም። ካሁን በኋላ ሁላችንም «ይህ ይሁን»፤ «ይህ ይደረግ»፤ «እከለ ይውደም» ወዘተ ከማለት ወደ «እኔ ይህን አደርጋለው» የሚለው አመለካከት መግባት አለብን። ልመና በቃ፤ የራሴን እጣ ፈንታ እራሴ ወስነዋለው ወደሚለው መግባት አለብን።

የአዲስ አበባ ጉዳይ የዚህ የአስተሳሰብ እና ተግባር ለውጥ አስፈላጊነት በደምብ ይገልጻል (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_97.html)። ልሂቃኖቻችን እስካሁን እነ ኢህአዴግን፤ ህወሓትን፤ ኦዴፓን፤ የኦሮሞ ብሄርተኞችን፤ አዴፓን፤ ጥ/ሚ አቢይን፤ ፕሬዚደንት ለማን፤ ወዘተ እባካችሁ እንዲህ እንዲያ አድርጉ አታድርጉ እያሉ ለው ዓመት ይጮሃሉ። ግን አንድ የሚባል የአዲስ አበባ ህዝብን ጥቅም የሚያንጸባርቅ እና ለማስከበር የሚሯሯት ድርጅት የለም? የአዲስ አበባ ህዝብ ህልውናውን ለሌሎች ሰጥቶ ሌሎቹ የሚፈልጉትን ሲአደርጉ ልሂቃኑ ያለቅሳል! ይህ ምን ማለት ነው? የአዲስ አበባ ህዝብ እራሱን አደራጅቶ ፍላጎቱን እና መብቱን ዘርዝሮ ማስከበር ካልቻለ እነዚህ የማይወክሉት ተቋሞች የፈለጉትን ያደርጋሉ። ይህ እኮ እጅግ basic የሆነ ነገር ነው።

እስከ ዛሬ የኛ ልሂቃን እና ሚዲያ ይህን መሰረታዊ ጉዳይ ትተው በማልቀስ እና መለመን ነው የዋሉት። የራሳችንን ጥፋት (አለመደራጀት) ላለማየት ትብሎ ህልውናችንን አደጋ ውስጥ ከትተናል! ይህ ሁሉ ችግር ስላልተደራጀን ነው እና እንደራጅ ከማለት ሌሎች ስለሚያደርጉት እናለቅሳለን። ይህ ለቅሶ ምንም ለውጥ አላመጣም አያመጣምም። ህዝባችን በንዴት እንዲደራጅ አላደረገም። ይባስ ሌሎች ላይ ጣት በመጠቆም የራሳችንን ጥፋት እንዳናይ ስበብ ሆኖናል። ጉርጓዳችንን ይበልጥ እንድንቆፍር አድርጎናል።

አሁን ግን አንዳንዶች መራራ የሆነውን መድሃኒት ውጠን ወደ ፊት መራመድ እንዳለብን የገባቸው ይመስላል።


ከዚህ ከኢሳት ዝግጅት የአዲስ አበባ ህዝብ መዋናነት መደራጀት አለበት ትባለ። ያለመደራጀታችን ጥፋታችንን አመንን ማለት ነው፤ ይህን ማመን ነው መራራው መድሃኔት። ካመንን በኋላ ሙሉ አቅማችንን ወደ መደራጀት ስራ ማሰለፍ ነው ያለብን። ካሁን ወድያ አንዳች የልሂቃን እና ሚዲያ ደቂቃ በእሮሮ፤ ለቅሶ፤ እና ልመና መጥፋት የለበትም። ሙሉ አቅማችን ወደ መደራጀት።

ምን ማለት ነው የመደራጀት ስራ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/10/blog-post_18.html)? ብዙ ሚስጥር የለውም፤ የህዝብ የማህበራዊ እና ፖለቲካዊ መደራጀት ለሺዎች ዓመታት የተደረገ ነገር ነው። የአዲስ አበባ ህዝብ «የአዲስ አበባ ህዝቦች ድርጅት» ያስፈልገዋል። የዚህ ድርጅት (ድርጅቶች) ተእልኮ የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን ጥቅም ማስከበር ነው። ቀላል ተእልኮ ነው፤ ሌላ ጣጣ አያስፈልገውም። ድርጅቱ በርካታ (በመቶ ሺዎች የሚቆጠር) አባላት ያስፈልጉታል። ባለ ሃብቱ በደምብ መሳተፍ አለበት። ስብሰባ፤ ሰርቬ፤ ምርጫ፤ ወዘተ የሚያካሄድ መሆን አለበት። አባላቶቹ በየ ማህበራዊ ዘርፍ፤ በየ መስርያቤት፤ በዬ ሰፈሩ የሚሰሩ እና የሚኖሩ መሆን አለባቸው። ድርጅቱ ሰፊ ኔትወርክ ኖሮት «የሚፈራ» ማለትም አቅም ያለው መሆን አለበት። በተለያዩ የከተማው ጉዳዮች፤ መብራት፤ ውሃ፤ መንገድ፤ ደህንነት፤ ጤንነት፤ መፈናቀል፤ ውክልና፤ ወዘተ የሚሰራ መሆን አለበት። በዴሞክራሲያዊ መልኩ የአባላቱን ፍላቶ የሚያውቅ፤ የሚያስከበር እና የሚወክል መሆን አለበት።

ይህ ድርጅት ሲኖር፤ ዛሬ ቢኖር ስለ አዲስ አበባ ያለው ጭቅጭቅ አይኖርም ነበር። ሁሉም ተሳታፊዎች የአዲስ አበባ ህዝብ ፍላጎትን አበጥረው ያውቃሉ። የሁሉም አቋም ሰልሚታወቅ የፖለቲካ ድርድሮች በግልጽ እና በጽጋ ይካሄዱ ነበር። የለገጣፎ ሰዎች አይፈናቀሉም ነበር። ጉዳዩ ገና ሲነሳ ድርጅቱ ተሳትፎበት ድርድር ተደርጎበት በሰላም በሁሉም የሚያስማማ መልኩ ይፈታ ነበር። የኦሮሚያ «ልዩ ጥቅም» ጉዳይም እንዲሁ። ወካይ ድርጅት ቢኖርን «ልዩ ጥቅም» ብለን አናለቅስም ነበር። ድሮውኑ ተደራድረን የልዩ ጥቅም ትርጉም ላይ ተስማምተን ነገሩ በሰላም ይወሰን ነበር። ወዘተ።

የአዲስ አበባ ችግር የመጣው በህወሓት ምክንያት አይደለም። በኦሮሞ ብሄርተኞች ምክንያት አይደለም። መሰረታዊ ችግሩ የአዲስ አበባ ህዝብ እርስ በርስ ተስማምቶ አለመደራጀቱ ነው። ይህን አምነን አንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ለቅሶ እና ልመናችንን ትተን ሙሉ አቅማችንን ወደ መደራጀት ማዋል አለብን። አለበለዛ በየበታችንነት እና ተገዥነት ስሜት እንደተገዛን እንቀጥላከን። መገዛት ማለት የራስን እጣ ፈንታ ለሌሎች መተው እና በራስ ህይወት ሃላፊነት አለመውስውድ ነው። ይህ ላለፉት በርካታ ዓመታት ጉዞአችንን ይገልጻል።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!