Showing posts with label corruption. Show all posts
Showing posts with label corruption. Show all posts

Monday, 4 March 2019

ተረት ተረት፤ አዲስ አበባ የኦሮሞ ገቤሬዎችን አፈናቅሏል

1. የአዲስ አበባ ህዝብ ምንም ፖለቲካዊ ውሳኔ አድርጎ አያውቅም። በኢህአዴግ (ከነ ኦህዴድ) የተገዛ ህዝብ ነበር። ስለዚህ የአዲስ አበባ ህዝብ ማንንም አላፈናቀለም። አፈናቃይ ካለ ኢህአዴግ ከነ ኦህዴድ ነው።

2. ከአዲስ አበባ የተፈናቀሉት ባብዛኛው ኦሮሞ ቢሆንም የተወሰኑ አማሮች እና የሌላ ጎሳ አባላት ነበሩ።

3. ካአዲስ አበባ ውስጥ የተፈናቀሉት ደግሞ ከሁሉም ጎሳ ነበሩ። እነዚህ የአዲስ አበባ ተፈናቃዮች ከአዲስ አበባ ዙርያ የተፈናቀሉት ገበሬዎች ይበልጥ ተበድለዋል በደልን በገንዘብ ከተረጎምነው። ከካዛንቺስ 50 ካሪሜትር ቦታው የተፈናቀለው ምናልታብት ሁለት ሶስት ሚሊዮን ብር ነው ያጣው። ከቡልቡላ የተፈናቀለው ገበሬ የዚህ ሩብም አልከሰረም።

4. ገበሬዎች እና ሌሎች «ተፈናቀሉ» ስንል መንግስት የማይመጥን ትንሽ ካሳ ሰጥቷቸው በግድ ከመሬታቸው አስነሳቸው ነው። አድግራጊው የአዲስ አበባ ህዝብ ያልመረጠው የአዲስ አበባ መንግስት ውየንም አብዛኛው ጊዜ የኦህዴድ መንግስት ነው። ገበሬውን አነስተኛ ካሳ ሰጥቶት ለኢንቬስተር በከፍተኛ ዋጋ ሽጦ ትርፉን ኪስ አስገብቷል። ለዚህ የአዲስ አበባ ህዝብ ትጠያቂ አይደለም፤ ኢህአዴግ እና ኦህዴድ ናቸው።

5. ታላቁ ግን ማንም የማያነሳው ጉዳይ የሀገራችን የመሬት ፖሊሲ ነው። መሬት የመንግስት በመሆኑ ነው ገበሬዎችም ሌሎችም የሚፈናቀሉት እና «ተፈናቀሉ» የሚባለው። አዲስ አበባ ሲሰፋ (እንደ ከተማ ይሁን እንደ metropolis) ዙርያ ያሉት ገበሬዎች ዋና ተጠቃሚ ነበር መሆን ያለባቸው፤ ይሆኑም ነበር መሬት የግል ቢሆን። አዲስ አበባ ዙርያ ያሉት ገበሬዎች ከተማው እየሰፋ ስለሄደ መሬታቸውን በእጅግ ውድ ዋጋ ሊሸጡ እና ሊጠቀሙ ይችላሉ። ቡልጋ ያለው ገበሬ የመሬቱ ዋጋ አንድ ብር በካሬ ቢሆን ይው መሬት አዲስ አበባ ዙርያ መቶ ብር ሊሆን ይችላል። በዚህ መንገድ ነው የትም ሀገር ከተማ ሲሰፋ ዙራይ ያሉት ገበሬዎች ሎተሪ እንዳሸነፉ የሚቆጠረው። ግን ኢትዮጵያ ገበሬው መረቱን መሸት ስለማይፈቀድ እና መንግስት ሲፈልግ መንጠቅ ስለሚችል ከተማ ዙርያ ያለ ገበሬ ጭራሽ ይሰጋ! ስለዚህ በዚምህ ረገድ ጥፋቱ የአዲስ አበባ ህዝብ ሳይሆን የኢህአዴግ እና ኦህዴድ የመሬት ፖሊሲ ነው። አዲስ አበባ ዙርያ ያሉ ገበሬዎች በኢህአዴግ/ኦህዴድ ምክንያት በሚሊዮኖች የሚቆጥር ብር አጥቷልና!

Friday, 22 February 2019

የለገጣፎ «ህገ ወጥነት» የማን ነው?

ሰዎች ከለገጣፎ ገበሬዎች ጋር የውስጥ ውል ተፈራርመው መሬት ገዙ። የእርሻ መሬት መሸጥም መግዛትም ስለማይፈቀድ ይህ ሺያጭ ህገ ወጥ ነበር። ሆኖም ተካሄዷል።

እነዚህ አይነት ሺያጮች ሲካሄዱ የአካባቢው የኦህዴድ (ኦዴፓ) ሹማምንቶች መጀመርያ እንዳላዩ ሆኑ። ቀጥሎ የምዝበራ እድል አይተው ገቡበት። ከገበሬ እየገዙ አትርፈው መሸጥ ጀመሩ። ከገበሬዎች ገዝተው ቤት የሰሩትን ሰዎች ጉቦ ካልሰጣችሁን እናባርራችኋለን፤ መብራት ውሃ እንከለክላችኋለን ወዘተ እያሉ አስፈራሩ። በዚህ መንገድ እራሳቸውን ሃብታም አደረጉ።

የኦዴፓ ላይ ድርስ ያሉ ባለስልጣናት ይህ አይነት ነገሮች አዲስ አበባ ዙርያ እንደሚካሄድ ያውቃሉ። ለነገሩ ሁላችንም እናውቃለን።

ስለዚህ ማን ነው ህገ ወጥ?! መሬት የገዙት ሰዎች? መሬት የሸጡት ገበሬዎች? የመዘበሩ እና በጉቦ ሃብታም የሆኑት የመንግስት ሹማምንቶች? ይህ እንደሚከሰት እያወቀ ዝም ያለው የኦህዴድ አመራር?

ግልጽ ነው፤ በፈቃደኝነት የተስማሙት ሳጭ እና ገዦች በአንጻሩ ንጹህ ናቸው። ማንንም አልጎዱም። ገበሬዎቹ የራሳቸውን መሬት በፈለጉት ዋጋ ሸጡ፤ ገዦችም በተስማሙበት ዋጋ መሬት ገዙ። ይህ ሺያጭ ባይካሄድ የኦህዴድ ሹማምንቶች የገበሬዎቹን መሬት በማይገባ ትንሽ ካሳ ነጥቀው ለኢንቬስተር በውድ ዋጋ እና ጉቦ ሊዝ ያረጉት ነበር።

እነዚህ የኦህዴድ ሹማምንት እና መሪዎች ናቸው ዋና ህግ ወጦች። አዲሱ አረጋ እንዳሉት «ህግ ይከበር» ከሆነ በመጀመርያ ደረጃ የኦህዴድ ሹማምንቶች ነበር መፈተሽ እና መታሰር የነበረባቸው። ሌሎቹ፤ ገንዘብ የተቀበሉት ገበሬዎቹ እና መሬት የገዙት ሰፋሪዎቹ በለዘብተኛ መልኩ መስተናገድ ነበረባቸው።

Sunday, 10 February 2019

በ«ቤተሰብ ምጣኔ» ስም የሚፈጸመው ጉዳት



 

በ«ቤተሰብ ምጣኔ» ስም በአማራ ክልል እየተፈጸመ የነበረው ማህበረሰባዊ ጉዳት ይህ ደብዳቤ / መመርያ ይገልጻል። አንብቡት።

ከዚህ ደብዳቤ የምንረዳው ዋና ነገሮች እነዚህ ይመስሉኛል፤

፩፤ የመጀመርያ ነጥብ የድርጅቱ አንዱ ግብ (target) የወሊድ መቆጣጠርያ የሚጠቀሙ ሴቶች ቁጥር መጨምር እንደሆነ ግልጽ ያደርጋል። እነዚህ ግቦች የሚመነጩት ደግሞ ከጤና ጥበቃ ቢሮ ብቻ ሳይሆኑ በዋና ደረጃ ከለጋሾቻቸው ማለትም ከተለያዩ የውጭ ሀገር ለጋሾች እንደ ኢዩ እና ዩኤሴይድ (አንድ ምሳሌ፤ http://www.healthpolicyproject.com/index.cfm?ID=country-Ethiopia)። ይህ ማለት የክልሉ መንግስት፤ የጤና ጥበቃ ቢሮ ሃላፊዎች፤ እና የጤና ቢሮ በታቾች ለገንዘብ ብለውም እንደዚህ አይነት ጉዳት የሞላው ፖሊሲ ፈጽመዋል። አዲሱ ቅኝ ግዛት እንዲህ ነው የሚሰራው።

፪፤ እነዚህን ግቦች ለመምታት በጣም ግልጽ የሆኑ ስህተቶች ተፈጽመዋል። ለምሳሌ በሁለተኛ፤ ሶስተኛ እና አምስተኛ ነጥቦች እንደሚገለጸው በረጅም ጊዜ መቆጣጠርያ ላይ የማይሆን ትኩረት ተደርጓል። የጤና ተቋሙ ገንዘቡን ለማምጣት ጸንፈኛ የሆነ አቋም እና ፖሊሲ ለማራመድ ወደኋላ አላለም። ለምሳሌ ሁሉንም ሴቶች የወሊድ መቆጣጠርያ ተጠቃሚ የማድረግ ታርጌት እና ፖሊሲ ከጫፍ የያዙ ጽንፈኝነት በቀር ሌላ ቃል ሊሰጠው ያችልም።

፫፤ ነጥብ ሰባት የጤና ጥበቃ ቢሮው እንደ ተቋምም ሰራቶኞቹም ለገንዘብ ብለው የተለያዩ የወሊድ መቆጣጠርያ እንደሚያስተዋወቁ እና ሴቶች ላይ እንደሚጭኑ በግልጽ ያስረዳል። ፖሊሲው የሚመራው ለህዝቡ ጤንነት ምን ይበጃል በሚለው መርህ ሳይሆን ምን ገንዘብ / ጉቦ ያመጣልናል በሚለው ነው። ስለዚህ የፖለሲው እና የተግባሩ አለቆች እና ወሳኞች የውጭ ሀገር ለገሾች እና የወሊድ መቆጣጠርያ ሳጭ ኩባኒያዎች ናቸው ማለት ነው።

፬፤ ይህ የብሉሹ እና የበሰበሰ አሰራር የጤና ተቋሙ ሚስኪን ሴቶች ላይ የቅስቀሳ ዘመቻ እያካሄዱ የሴቶቹ ስነ ልቦና እና ጤና የሚጎዳ ነገሮች እንዲያደርጉ እንደሚያደርግ ነጥብ ስምንት ያረጋግጣል። የጤና ጥበቃ ቢሮ ቢሮው ገንዘብ እንዲአገኝ፤ ሰራተኞቹም ለግላቸው ገንዘብ / ጉቦ / ስኮላርሺፕ እንዲያገኙ ጉዳት እንደሚፈጽሙ ግልጽ ነው።

፭፤ የአማራ ህዝብ ልሂቃኑን በደምብ መፈተሽ እና ማስተካከል እንዳለበት ግልጽ ነው። ከላይ ደጋግሜ የገንዘብ ሚና እንዴት የአማራ ጤና ጥበቃ ቢሮ የውጭ ሀገር ለጋሾች እና የመድሃኔት ሻጮች መሳርያ እንዲሆን እንዳደረገ ገለጽኩኝ። ገን ከዚም አልፎ ተርፎ በርካቶች በርዕዮት ዓለም ደረጃ በዚህ ጸንፈኛ ፖሊሲ የሚያምኑ የአማራ «የተማሩ» ልሂቃን አሉ። ከሁሉም በላይ ይህ ነው የሚያሳዝነው። ልሂቃኖቻችን በበአድ አስተሳሰብ አዕምሮአቸው ተገዝቷል። ወደ ኋላ ብለው የጠጡትን ፕሮፓጋንዳ መፈተሽም አይችሉም። የህዝብ ቁጥር ምጣኔ ከሌላ አንጻር መመልከትም አይችሉም። ህዝቡ እራሱ የራሱን የቤተሰብ ምጣኔ መወሰን እንደሚችል፤ ሃብታም በሆነ ቁጥር እራሱ የሚወልደውን ቁጥር እንደሚቀንስ፤ የቤተሰብ ምጣኔ የህዝብ ቁጥርም መቀነስ ጉዳይ አለመሆኑ፤ ወዘተ መገንዘብ የማይችል ልሂቃን ተፈጥሯል። የህዝቡን ስነ ልቦና እና ማህበረሰባዊ እሴቶች የማያውቅ ልሂቃን ተፈጥሯል። በዚህ ላይ ብዙ ስራ ሊሰራ የሚያስፈልግ ይመስለኛል።

Thursday, 7 February 2019

በህዝብ ቆጠራው ላይ የኦርቶዶክስ አማኝ ቁጥር ከታሰበው በታች ቢሆን ምን እንል ይሆን?

በሚመጣው የህዝብ ቆጠራ ላይ የኦርቶዶክስ አማኝ ቁጥር ከታሰበው ወይንም ከሚፈለገው በታች ቢሆን እንደ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ምን እንል ይሆን? ይህን መረጃ / ሰነድ ስናገኝ ምንድነው ማድረግ ያለብን?

በመጀመርያ ደረጃ ንስሃ ነው መግባት ያለብን። የኦርቶዶክስ አማኝ ቁጥር ከመነመነ ዋናው ጥፋት የኛ የኦርቶዶክስ ምዕመናን ስለሆነ። እምነታችን፤ ክርስቶስም፤ የሃይማኖት አባቶችም አስረግጠው ይነግሩናል፤ እኛ ጥሩ ክርስቲያኖች ከሆንን እንደ ብርሃን ሌሎችን ወደ ብርሃን፤ ወደ ቃሉ፤ ወደ ክርስቶስ እናመጣለን። በአንጻሩ ጥሩ ክርስቲያኖች ካልሆንን፤ ጭለማዎች ከሆንን፤ ሌሎችን ወደ ክርስትና እንዳይመጡ እናደርጋለን። አልፎ ተርፎ ከኛም ያሉትን እንዲወጡ እናደርጋለን።

ይህን እውነት በአጭሩ ለመግለጽ የሩሲያዊው ቅዱስ ሴራፊም (ሱራፌል) ዘ-ሳሮቭ  እንዲህ ብለዋል፤

«መንፈስ ቅዱስ እንዲያድርባችሁ ከፈቀዳችሁ ዙርያችሁ ያሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ይድናሉ።»

በዚህ ጉዳይ ላይ ለተጨማሪ ማብራርያ ይህን የታወቁት የቆጵሮስ (ሊማሱ ከተማ) ጳጳስ አታናሲዮስ ቃለ ምልልስ ያንብቡ፤ http://orthochristian.com/79957.html። «ክርስቶስን የማያውቁ ሰዎች መኖራቸው የኛ (የክርስቲያኖች) ጥፋት ነው» ይላሉ። ይህ መሰረታዊ እምነታችን ነው።

በመንፈሳዊ ህግ ኃጢአት የቦታ እና የጊዜ ግድብ የለውም። የሁላችንም ኃጢአት ሁላችንንም በተለያየ መንገድ ይነካል። ለምሳሌ፤ እንዴ ወንድሜን ከበደክሉኝ ችግሩ ከኔ እና እሱ መካከል ሆኖ አይቀርም። ይተላለፋል። ወንድሜ ተበሳጭቶ ሌሎችን ይበድላል። ቤት ሲሄድ ቤተሰቡ አክሩፎ ያገኙታል። እኔ ስለበደልኩት ህይወቱን በሙሉ ቁስሉን ተሸክሞ በቁስሉ ምክንያት አስተሳሰቡም ድርጊቶቹም ሊሳባ ይችላል። ቂም ሊይዝ ይችላል። ሰውን በጥርጣሬ ሊያይ ይችላል። በዚህ መንገድ የኔ ኃጢአት እንደ ተላላፊ በሽታ ይንሰራጫል።

ክርስቲያኖች በመንፈሳዊ ህግ ኃጢአት ከቦታ ቦታ ብቻ ሳይሆን ዘመናትን ይሸጋገራል ብለን እናምናለን። ይህ ማለት ኃጢአት ለትውልድ ይተላለፋል። ይህ የሃይማኖታችን መሰረታዊ እምነት ነው። የአዳም ኃጢአትን መውረሳችን ይህን ይገልጻል። ለአዳም ኃጢአት ሃላፊነት ባይኖረንም ውጤቱን ወርሰናል። እኛም ኃጢአት በመስራታችን እንዲሁም አስተላልፈንዋል። ለምሳሌ ከወላጆቼ የወረስኩት ችግርን ተሸክሜ ለልጆቼ በትወሰነ ደረጃ አስተላልፋለሁ። ችግሩ በሃሳብ ብቻ ሳይሆን በደምም (በዲኤኔአችን) ይተላለፋል።

በመንፈሳዊ ህግ ኃጢአት በሀገር ደረጃም ይታወቃል። የእስራኤል ህዝብ ለሀገራዊ ኃጢአታቸው የታዋቁ ናቸው በራሳቸው በኦሪት ታሪክም በወንጌልም ይህ ታሪካቸው ተዘርዝሯል። ሌሎች በርካታ ህዝቦች እንደ ህዝብ ወይንም ሀገር ለኃጢአቶቻቸው ዋጋ ከፍለዋል። ዛሬም እንዲሁ ነው (https://blogs.ancientfaith.com/glory2godforallthings/2015/06/27/dostoevsky-and-the-sins-of-the-nation/)።

ስለዚህ እንደ ግለሰብም እንደሀገርም ኃጢአቶቻችን በቦታ እና ጊዜ ይተላለፋል። ለዚህ ኃጢአቶቻችንን አምነን ንስሃ መግባት አለብን። ይህ መሰረታዊ የክርስትና እምነት ነው። እንኳን በኢትዮጵያ በዓለም ዙርያ ችግር ሲከሰት ወደ ራሳችን ተመልክትን «ምን አድርጌ ወይህም ምን ባለማድረጌ ነው ይህ የሆነው» ብለን እራሳችንን መጠየቅ አለብን።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ መእመን ቁጥር ከቀነሰ ወይንም ካልጨመረ እሄኑኑ ጥያቄ እራሳችንን መጠየቅ ነው ያለብን። አማራጭ የለንም። እውነቱ ይህ ነው። ለዚህ ችግር ሌሎችን ጥፋተኛ ማድረግ ኢ-ክርቲያናዊ አካሄድ ነው። እንደ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች «ጴንጤዎቹ»፤ «ሙስሊሞቹ»፤ ወይንም «ሴኩላሪስቶቹ» ናቸው ምእመኖቻችንን የወሰዱብን ማለት አንችልም። ወደራሳችን ብቻ ነው መመልከት ያለብን። እኛ ብርሃን ከሆንን ምንም አይሳነንም፤ ዓለም በሙሉ ወደ ክርስቶስ ይመጣ ነበር። እዚህ ላይ ነው ማተኮር ያለብን። ይመስለኛል።

Thursday, 10 January 2019

ግብዝነት ያጠፋል

"Correct faith does not benefit anything, when life is corrupted."

St. John Chrysostom

ከቤተ ክርስቲያን ሰው ካፈነገጠ፤ እምነት ካጣ፤ ከብርሃን ወደ ጭለማ ከገባ፤ ለነዚህ ሁሉ ዋና ምክንያት የኛ የቤተ ክርስቲያን ምዕመናን እና አመራር ግብዝነት ነው። ቤተ ክርስቲያን ባለእንጀራህን ክርስቶስ እንደሚወዳችሁ ውደዱ ብላ ታስተምራለች። እኛ ግን በተለያየ ደረጃ ይህን እውነታዊ ትዕዛዝ አንፈጽምም። «ግብዞች» ነን። ይህን ባለማድረጋችን ወንድም እህቶቻችን ቤተ ክርስቲያንን እንዳያምኑ እና ወደ ፈተና እንዲገቡ እናረጋለን። ለዚህም ነው ክርስቶስ ግብዝነትን ለይቶ የወቀሰው። ሁላችንም ኃጢአተኞች ነን። ግን ግብዝነታችን በበዛ ቁጥር እራሳንን (ቤተ ክርስቲያንን) እጅግ እየጎዳን እንሄዳለን ሰውንም እናሳስታለን። (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2017/11/blog-post.html)

ይህንን ትምሕርት ተከትሎ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ሲኖዶስ የራስ ማጽዳት ዘመቻውን አጠንክሮ እና እንደ ዋናው እና መጀመርያ ስራቸው ይያዙት ብዬ በአቅሜ እለምናለሁ። ዛሬ ሚሊዮኖች አማኝ ናቸው። ቤተ ክርስቲያኖች ይገነባሉ። ነገ በግብዝነታችን ምክንያት ሁሉም ሌጠፋ ይችላል። ይህ እንዳይሆን እራሳችንን እናጽዳ።

እስቲ ግብዝነትን በሌላ ምሳሌ እንመልከተው… በሀገራችን መሃበረሰብ ማመንዘርም ማስገደድ/መስረቅም ኃጢአት እና ነውር ነው። ሆኖም የሃገራችን ሴቶች በተለይ ከተማ ዙርያ አንዳንድ ወንዶች ሲያመነዝሩ፤ ከኛ ጋር ካልወታሽ መስርያቤቱ እንዳይቀጥርሽ አደርጋለው ሲሉ፤ ሚስቶቻቸውን ሲደበድቡ ወዘተ ይሰማሉ ወይንም ያያሉ። ይህ ሁሉ በባህላችን በወጋችን ክፉ የሚባሉ ነገሮች ሆነው ግን ይከሰታሉ። ይህን እያየች ያደገች ሴት በቀለም ትምሕርት ገፍታ ሄዳ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ አንዱ የ«ፌሚኒዝም» ፍልስፍናን አቅፋ ጣኦት ታደርጋለች። ለምን በዚህ ታምኛለሽ ካልናት ባህላችን በጅምላ ጭፍጭፍ ታደርጋለች። ለምን? ግብዝ የሆነ የራሱን እሴቶች የማያከብር ህብረተሰብ መካከል ስላደገች። ልክ ያንን «ተቃራኒ» ስታገኝ ሮጣ አቀፈችው።

አያችሁ የግብዝነት ጉዳት። እንታገለው። ወደ ማንነታችን ወደ እውነት የሆኑት እሴታችን እንመለስ። አለበለዛ ሀገራችንንም ማንነታችንንም እናጣለን።

Monday, 19 November 2018

የቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ አሁንም ኋላ እንዳይቀር፤ የሙስና ማስወገድ ስራውን ያፋጥን

ወራት በፊት የሀገራችን ፖለቲካ አውንታዊ ለውጦች እያመጣ እያለ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ እራሱን በቅድምያ አላስተካከልም። ፖለቲካው ከተቀየረ በኋላ በፖለቲከኞች (እነ ጠ/ሚ አቢይ) ግፊት እና ማበረታታት ቤተ ክርስቲያን ወደ ትክክለኛ ሰላም መንገድ ገባች። የቤተ ክርስቲያናችን ሲኖዶስ ከመምራት ፋንታ ተከታይ ሆነ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/02/blog-post_15.html)። ያሳዝናል። ግን መከተሉም እራሱ ተመስገን ነው።

አሁን ደግሞ መንግስት የፍትህ እና ሰላም ስራዎች በሰፊው እየጀመረ ነው። ያለፉትን ጥፋቶች ከነ ሙስና እንዲመረመሩ እና ሰላም፤ ፍትህ እና እርቅ እንዲመጣ ሂደቶች እና መዋቅሮች እያቋቋመ ነው። በቤተ ክርስቲያናችን የሚፈፀም የነበረው ኢሰባዊነት እና ሙስና ይታወቃል። የምርመራ ስራዎች በትንሹ የተጀመሩ እንደሆነ ይታወቃል። ግን ስራው ገና ነው፤ መዋቀራዊ አልሆንም እና ለመላው ሀብረተሰብ ግልጽ እንዲሆን አልተደረገም።

አሁንም ቤተ ክርስቲያን ከመምራት ፋንታ ኋላ ቀር ሆኖ እንዳይገኝ። ሙስና እና ሌሎች ኢ-ክርስቲያናዊ ድርጊቶች ቤተ ክርስቲያኗን ማለትም ምዕመኗንም እጅግ እንደሚጎዳ በታሪክ የታወቀ ነገር ነው። የህልውና ጉዳይ ነው። ይህ ስለሆነ ቤተ ክርስቲያን አሁንም መንግስትን ቀድማ እራሷን ማጽዳት አለባት። ለመላው ሀገራችን ምሳሌ መሆን አለባት።

ስለዚህ ቤተ ክርስቲያንን ከሙስና እና ሌሎች ኃጢአቶች የማጽዳታ ዘመቻ አሁኑኑ ጠንክሮ መጀመር አለበት። ይህ ካልሆነ መንፈሳዊ ጉዳቱ እጅግ የከፋ ነው የሚሆነው።

Monday, 27 November 2017

ማንን እንሰዋ

በ2012 ጠቅላላ ስብሰባቸው የቻይና ኮምዩኒስት ፓርቲ መሪዎች ለህልውናቸው ብለው በሙስና ላይ ታላቅ እርምጃ መውሰድ እንዳለባቸው ተረድተው የእርምጃ ውሳኔ ወሰዱ። እርምጃቸው ሺ ዢንፒንግን  መሪ (ፕሬዚደንት) መሾምና የጸረ ሙስና «ሚኒስቴር»፤ ክፍል ወይ ቢሮ ሳይሆን ሚኒስቴር» ማቋቋም ነበር። ፕሬዚደንት ሺ ሙስናንና ጸረ መልካም አስተዳደርን እዋገለሁ ዋናው ጉዳዬም አደርገዋለሁ በማለት ለምርጫ ቀረበ። የኮምዩኒስት ፓርቲ ሹማምንት ይህን አውቀው ተስማምተው መረጡት።

ልምን? የጸረ ሙስና ዘመቻ እራሳቸውን ሊጎዳ ሊያከስር ሊያሳስርም እንደሚችል እያወቁ እንዴት የጸረ ሙስና ዘመቻ እንዲካሄድ ፈለጉ? ምክነያቱ ሙስና ፓርቲውን (አባላቱን) እጅግ እየጎዳና ህልውናውን ሊያጠፋ እንደሚችል ስለተረዱ ነው። የተለያዩ መሪዎቻቸውም በዪፋ እንደዚ ብለው ግመው ተናግረው ነበር፡ « ፓርቲአችንም ሀገራችን በሙስና ምክነያት ሊፈርሱ ይችላሉ» ብለዋል።

ስለዚህ ፓርቲው ፈርሶ ሁላችንም ከምንሞት ሙስናን ቀንሰን ህዝባችንን አባብለን ፓርቲው ይትረፍ አብዛኞቻችን እንትረፍ ግን አንዳንዶቻችን በተለይ ሙስና ውስጥ እጅግ የሰመጡት ደግሞም የማንፈልጋቸው ባልደረቦቻችን ይውደቁ ይታሰሩ። ይህ ነበር የቻይና ኮምዩኒስት ፓርቲ ሹማምንት አስተሳሰብ ፕሬዚደንት ሺን ሲመርጡት። ሰውነታችን ሙሉ በሙሉ ከሚሞት ትንሽ እንድማ ነው።

ከመረጡት በኋላ ሃይሉን ማንቀሳቀስ ጀመረና አብዛኛው ካሰበው በላይ ደም ፈሰሰ። ብዙ ሰው ተሰወ። እንግዲህ እንደዚህ አይነቱ ሰፊ እቅድ ሁልግዜ እንደተጠበቀው አይሄድም። ሆኖም ፕሬዚደንት ሺ ተእልኮዋቸውን በሞላ ጎደል አሟሉ።

እንዲሁም በኢትዮጵያ ከህወሃት ጠቅላላ ስብሰባ የሚካሂደው በችይና ኮምሁኒስት ፓርቲ 2012 ስብሰባ የተካሄደው ነው። ሙስና እየገደለን እንደሆነ እናውቃለን፤ ሙስናን ማጥፋት አለበን፤ ግን ከማህላችን ማንን እንሰዋ?! ፖለቲካው በዚህ ዙርያ ነው። ስብሰባውም ሳምንታት የሚፈጀው ለዚህ ነው! ህወሃት መትረፍ ከፈለገ ይህን እርምጃ መውሰድ አለበት ግን ውሳኔው ከባድ ነው።

በኔ ሚስኪን እይታ የተወሰኑ ዋና ሹማምንት መውደቅ አለባቸው። እስር ይሁን በሙስና የተገኘውን ሃብት መንጠቅ ይሁን ተገቢውና ውጤታማ እርምጃ አላውቅም ግን ህዝቡ ይህን ይጠብቃል። መዋቀሩም ይህ መድሃኒት ያስፈልገዋል። የወደፊት ሙሰኞችን ተጠንቀቁ ይቅርባትሁ የሚለው ምልእክት በትክክል የሚደርሳቸው ታላላቅ ሹማምንት ከወደቁ ብቻ ነው።

ከዛም ቀጥሎ ግን ከዚህ በፊት እንደጠቀስኩት የሙስናን ደረጃ በቋሚነት ዝቅ አርጎ ለመጠበቅ የ100% መመሪያውን ኢህአዴግ መሰረዝ አለበት። ከፌደራል ምክር ቤት እስከ ቀበሌ የኢህአዴግ ሹማምንት ስራውን በደምብ ካልሰራ በህዝብ ድምጽ ብልጫ ከስልጣን ሊወርድ እንደሚችል ማወቅ አለበት። ይህ ነው ዋናው የሙስና መቋቋሚያ መንገድ።