Showing posts with label solzhenitsyn. Show all posts
Showing posts with label solzhenitsyn. Show all posts

Thursday, 15 November 2018

ማን ነው የሚተርፈው?

አሉ የኢሳት ተንታኞች። በኢህአዴግ ዘመን የተከሰቱ የጭካኔ እና ሙስና ወንጀሎች ክር መተርተር ሲጀምር ማን ከኢህአዴግ እና ዙርያ ይተርፋል? ማን ያላጠፋ አለ?

ወይ ሁሉንም ማሳሰር ነው ወይንም እንደ ደቡብ አፍሪካ የእርቅ ስርዓት አቋቁሞ ፍትህ በእርቅ እንዲመጣ ማድረግ ነው ተባለ። ከነዚህ ደግሞ ሁለተኛው የእርቅ ስርዓት መንገዱ ጥሩ እና እውነት የያዘ አማራጭ ነው።

ለኔ ግን ከዚህ ሁሉ በላይ ዋናው ጓይ ይህ ነው፤ ማን ይተርፋል ብለን ስንጠይቅ ለምንድነው ስለኢህአዴግ እና ሌሎች ብቻ የምናወራው? «እኛሳ»? ጥፋት በማድረግም ባለባድረግም ነው ልንከሰስ ይገባል።

አዎን መስረቅ ጥፋት ነው። ግን የሚጎዳን አለመርዳትም እንዲሁ ጥፋት ነው። ስንቶቻችን «ብዙሃን» ባልደረቦቻችን በተለያየ መንገድ የፖለቲካ እና ማህበረሰባዊ ጥቃት ሲደርስባቸው ዝም ያልነው እና ያልረዳናቸው? ጎረቤታችን ተቸግሮ ቢያንስ «ይሄው 100ብር፤ ስለተቸገርክ ስለተጎዳህ አዝናለሁ» ያልን ስንቶቻችን ነን? እርግጥም ስንቶቻችን ነን ከጎረቤትና ባልደሮቦቻችን የከፋ ግጭት እና ቅራኔ ያለን። እርስ በርስ ተከፋፍለን ለከፋፍሎ መግዛት መንግስት እራሳችንን ያመቻቸን?!

የፖለቲካ እና ማህበራዊ ጥፋቶች የማህበሩ ማለትንም የእያንዳንዶቻችን ነው። No man is an island። ጥፋታችንን አምነን ወደ ንስሃ ከገባን ብቻ ነው እርፍት እይሚኖረን። እንጂ ዎንጀሎችን አስረን ሰላም ይመጣል ማለት ታሪክን አለማወቅ እና እራስን ማታለል ነው።

ታዋቂው ሩሲያዊ የፖለቲካ እስረኛ እንዳሉት፤
«ከእስርቤታችን አልጋ የሆነው የበሰበሰው ገለባ ላይ ጋደም ብዬ ነው ለመጀመርያ ከውስጤ የበጎ መንፈስ የተሰማኝ። ቀስ በቀስ መረዳት የጀመርኩት ይህ ነው፤ ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር በሀገሮች፤ መደቦች፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም መካከል አይደለም የሚያልፈው፤ ይህ መስመር የሚያልፈው በያንዳንዱ የሰው ልብ መኻል ነው። መስመሩ እድሜአችን በሙሉ ከውስጣችን ወደፊት ወደኋላ ይላል። በክፉ የተሞሉ ልቦችም ቢያንስ ቅንጣት ያህል ጥሩነት ይኖራል፤ ከሁሉም ጥሩ ከሚባለውም ልብ ከአንድ ጥጓ ትንሽ ክፉነት ይኖራል።
በየቦታው እየዞሩ ያሉ ክፉ ስራ የሚሰሩ ክፉ ሰዎች ቢኖሩና እነሱን ከኛ መለየትና ማጥፋት ብቻ ቢሆን ኖሮ እንዴት ቀላል ነበር? ግን ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር ከያንዳንዱ የሰው ልጅ ልብ መካከል ነው የሚያልፈውና ማን አለ ከራሱ ልብ ቁራጭ ቆርጦ ለማጥፋት ፈቃደኛ ይሆነ?»
https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/09/blog-post_30.html

Friday, 19 October 2018

የአለክሳንደር ሶልዠኒትሲን መልዕክት ለኢትዮጵያ

ታላቁ የሩሲያ ደራሲ አለክሳንደር ሶልዠኒትሲን ያሉትን በደምብ ሊገባን ይገባል፤
«ከእስርቤታችን አልጋ የሆነው የበሰበሰው ገለባ ላይ ጋደም ብዬ ነው ለመጀመርያ ከውስጤ የበጎ መንፈስ የተሰማኝ። ቀስ በቀስ መረዳት የጀመርኩት ይህ ነው፤ ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር በሀገሮች፤ መደቦች፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም መካከል አይደለም የሚያልፈው፤ ይህ መስመር የሚያልፈው በያንዳንዱ የሰው ልብ መኻል ነው። መስመሩ እድሜአችን በሙሉ ከውስጣችን ወደፊት ወደኋላ ይላል። በክፉ የተሞሉ ልቦችም ቢያንስ ቅንጣት ያህል ጥሩነት ይኖራል፤ ከሁሉም ጥሩ ከሚባለውም ልብ ከአንድ ጥጓ ትንሽ ክፉነት ይኖራል።
በየቦታው እየዞሩ ያሉ ክፉ ስራ የሚሰሩ ክፉ ሰዎች ቢኖሩና እነሱን ከኛ መለየትና ማጥፋት ብቻ ቢሆን ኖሮ እንዴት ቀላል ነበር? ግን ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር ከያንዳንዱ የሰው ልጅ ልብ መካከል ነው የሚያልፈውና ማን አለ ከራሱ ልብ ቁራጭ ቆርጦ ለማጥፋት ፈቃደኛ ይሆነ?»

Wednesday, 10 October 2018

የቅራኔ መፍታት (conflict resolution) ጉድለታችን

አንዱ ከብዙ የጠ/ሚ አብይ አህመድ ልዩ የሚያረጋቸው ችሎታዎች የቅራኔ መፍታት አቅማቸው ነው። ትዕቢት፤ ቂም፤ አሉታዊነት፤ ትቶ የሁሉንም ትቅም የሚያስከብር ለሁሉም ተመራጭ የሆነ ግባ ላይ በማተኮር ችግሮችን ፈትተዋል አሁንም እየፈቱ ይገኛሉ። ይህ አቅማቸው ከኢትዮጵያ ፖለቲካዊ መሪዎች ለዘመናት ታይቶ አይታወቅም (https://ethsat.com/2018/10/ethiopia-soldiers-show-up-unannounced-at-national-palace-pm-orders-pushups/)።

@Samuel Abebe (በዚህ ትችት ላይ https://www.facebook.com/abdurahman.ahmedin.7/posts/2120966214582614?comment_id=2121015731244329) ሁላችንም በውስጣችን የምናስበውን ታላቅ ጥያቄ ጠየቀዋል፤

«መለወጥ ስህተትን ከመቀበል ይጀምራል ይባላል ትልቅ ስህተት ተፈጽሞም ከቅንጅት አመራሮች ስህተቱን ተቀብሎ እዚህ ላይ ይህን ባንሳሳት ኑሮ የሚል አመራር እንዴት ይጠፋል? ሁሉም ወደ ሌላ ሰዉ ጣቱን ይቀስራል፡ እኛስ የትኛዉን አምነን የትኛዉን እንቀበል?»

ዋና እና ተገቢ ጥያቄ ነው። ብስለት እና እውቀት የሞላው። በማንኛውም ቅራኔ አንድ ጥፋተኛ እና ሌላው ንፁሃን የለም (there are two or more sides to any conflict)። ይህን ሃቅ ማንኛውም ስለቅራኔ የሚያውቅ ባለሙያ፤ ማንኛውም የካህን፤ ማንኛውም አስተዳዳሪ፤ ማንኛውም ወላጅ የሚያውቀው ነው። ግን ብናውቀውም እንዳማናውቀው አድርገን ነው የምንኖረው። ቅራኔ ውስጥ በተገኘን ቁጥር እራሳችንን ፍፁም ንፁህ ሌላው ፍፁም ጥፋተኛ አድርገን ነው የምንቆጥረው።

ይህ ከገባን በቅንጅት ቅራኔ ህሉም ተሳታፊዎች የተወሰነ ሚና መጫወታቸውን ሊገባን ይገባል። የፈረደበት ልደቱ ጥፋት ብቻ ሊሆን አይችልም። ዋናው ችግር የሱ ነው ቢባልም ያንን ችግር ማስተናገድ አለመቻል በራሱ ትልቅ ድክመት ነው! መታመን ያለብት እና ይቅርታ የሚጠየቅበት ድክመት ነው። ታላቅ መማርያ የሚሆን ድክመት ነው።

እንደ ቅንጅት አይነት ታላቅ ድርጅት፤ እጅግ ግዙፍ የሆነ የሀገር ሃላፊነት ያለው ድርጅት ሲፈርስ ሁሉም በአመራር ያሉት በመፍረሱ ሚና ተጫውተዋል እና ሁሉም ድክመታቸውን አምነው ይቅርታ ሊጠይቁ ይገባል። እኛም ደጋፊዎቻቸው እንዲሁም። ያደረግነውን ስህቶቻችንን ካመንን በኋላ ብቻ ነው መማር የምንችለው እና እንዳንደግማቸው ማድረግ የምንችለው።

የቅንጅት ታሪክ ከብዙ የሀገራችን ፖለቲካ የቅራኔ መፍታት አለመቻል ታሪኮቻችን አንዱ ነው። እንዳውም በኔ እምነት የፖለቲካ እና ማህበራዊ ችግሮቻችን ዋና ጎልቶ የሚታየው ምክንያት «የቅራኔ መፍታት (conflict resolution) ጉድለታችን» ነው። በዚህ ዙርያ ብዙ ተጽፏል እና ተነግሯል ግን በቂ አልተደረገም። ዛሬም የምናያቸው ነገሮች አሉ፤

1. አንድ «አቋም»፤ ርዕዮት ዓለም፤ አስተያየት ኖሮን አብሮ መስራት አለመቻል
2. የራሳችንን ጥቅም ጎድተን ቂማችንን ለመወጣት የምናደርጋቸው ስህተቶች
3. የጋራ ማሸነፍን ከመፈለግ (አሁንም የራሳችንን ጥቅም ቢጎዳም) ሌላው እንዲሸነፍ መመኘት እና መስራት
4. ፖለቲካን እንደ ሃይማኖት ፍፁም እውነት እንዳለው መቁጠር።

የፖለቲካ አካሄዳችን እንዲሻሻል ከተፈለገ ስለነዚህ ጉዳዮች መያየት እና መፍትሄ ማግኘት ግድ ነው።

ቅራኔ መፍታት ለኛ ኢትዮጵያዊያን አዲስ ነገር አይደለም። የድሮ ንጉሶቻንን አድርገውታል። ይህን የሚያስፈጽሙ በርካታ ባህላዊ መንገዶች አሉን። ከሃይማኖታችን ደግሞ መሰረታዊ ቅራኔ መፍታት ምክንያቶችንም ዘዴዎችም አሉ። ለምሳሌ በክርስትና «ንስሃ» ማለት ማለት 1) ስተትን ማመን 2) እንዳይደገም 3) ሌላው እንዲገባው 4) እራስን ለማረም 5) እራስን ለማወቅ ወዘተ። ውየንም «አለመፍረድ» ማለት 1) ለሌላው መቆርቆር (empathy) 2) የተሳሳተ ድምዳሜ ላይ ችኩሎ አለመድረስ 3) ጣት ጠኩሞ የራስን ችግር መርሳት ወዘተ።

ስለዚህ አሁን ማድረግ ያለብን እነዚህን (ምናልባት የተረሱ) ባህላዊ እሴቶችን እንደገና ማስነሳት እና ማሰራጨት ነው። ከባድ ስራ ነው ግን ምርጫ የለንም!

http://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/09/blog-post_21.html

Friday, 16 February 2018

ጨቋኝና ተጨቋኝ

እንደተረዳሁት ባለፈው ባወጣው መግለጫ ኦህዴድ የኢትዮጵያ መሰረታዊ የጭቆና ታሪክ የ«መደብ ጭቆና» ነበር እንጂ የ«ብሄር ጭቆና» አልነበረም ብሏል። ለዚህ አቋማቸው ኦህዴድን አደንቃለው አመሰግናለውም። ከረዥም ዓመታት የተሳሳተ እምነታቸው መቀየር ከባድ ነውና ጥንካሬና ህሊና ይጠይቃል። ዛሬ በሃገራችን ያለውን ከፍተኛና ኢ-ጤናማ የጎሳ ውጥረትንም ተገንዝበው የተሳሳተ ርእዮተ ዓለማቸውን ገምግመው ሃሳባቸውን ቀይረው ይህንን በይፋ ማውጣታቸው ትልቅ ነገር ነው። ደግሞ ከሌሎች አጋር ፓርቲዎቻቸው ቀድመው ይህን ማድረጋቸውም ሊደነቅላቸው ይገባል። እነ ለማ መገርሳ ለኢትዮጵያዊነት ታላቅ አስተዋጾ እያደረጉ ነው።

ሆኖም ይህ ዜና በሃገራችን መሰረታዊ የሆነ አሳዛኝ አስተሳሰብ አሁንም እንዳለ ይገልጻል? «ጨቋኝ» እና «ተጨቋኝ» እራሱ የተሳሳተ ቋንቋ ነው። ጽንሰ ሃሳብ የመጣው ከውሸትና ኢባህላዊ የሆነ የምእራባዊ የኮምዩኒስት አስተሳሰብ የመነጨ ነው። እስቲ አንድ እርምጃ ወደ ኋላ ተመልሰን ለምንድነው የሰው ታሪክ በ«ጨቋኝና ተጨቋኝ» የሚለው አስተሳሰብ መወሰን ያለበት? እንደዚህ አይነቱ አስተሳሰብ በሃሳብም ደረጃ በተግባርም ግጭት፤ ቅሬታ፤ ቂም፤ ጦርነት፤ ግድያ፤ አብዮት ወዘተ የሚያስገድድ ነው። አንድነት፤ ፍቅር፤ ይቅርታ፤ ትህትና፤ መስማማት ወዘተ የሚቃረን አስተሳሰብ ነው።

አልፎ ተርፎ ማን ግለሰብም ህብረተሰብም ፍፁም ንፁሃን ፍፁም ጥፋተኛ የሆነ የለም። እያንዳዳችን ጨቁነናል ተጭቁነናል፤ በድለናል ተበድለናል፤ ወደናል ተወደናል፤ ተስማምተናል ተጣልተናል፤ ተሳስተናል ስታታችንን አምነን ይቅርታ ጠይቀናል፤ ቂም ይዘናል ይቅርታን ተቀብለናል። በዚህ ዓለም እኔ ነኝ ንጹ ተጨቋኝ የሚል የራሱን ጥፋት ስለማይመለከት ወደ ከባድ ጥፋጡስት ይገባል ሰፊ በደልም ይፈጽማል።

በዚህ ጉዳይ ታላቅ የሩሲያ ደራሲ አለክሳንደር ሶልዠኒትሲን ያሉትን በደምብ ሊገባን ይገባል፤
ከእስርቤታችን አልጋ የሆነው የበሰበሰው ገለባ ላይ ጋደም ብዬ ነው ለመጀመርያ ከውስጤ የበጎ መንፈስ የተሰማኝ። ቀስ በቀስ መረዳት የጀመርኩት ይህ ነው፤ ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር በሀገሮች፤ መደቦች፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም መካከል አይደለም የሚያልፈው፤ ይህ መስመር የሚያልፈው በያንዳንዱ የሰው ልብ መኻል ነው። መስመሩ እድሜአችን በሙሉ ከውስጣችን ወደፊት ወደኋላ ይላል። በክፉ የተሞሉ ልቦችም ቢያንስ ቅንጣት ያህል ጥሩነት ይኖራል፤ ከሁሉም ጥሩ ከሚባለውም ልብ ከአንድ ጥጓ ትንሽ ክፉነት ይኖራል።
በየቦታው እየዞሩ ያሉ ክፉ ስራ የሚሰሩ ክፉ ሰዎች ቢኖሩና እነሱን ከኛ መለየትና ማጥፋት ብቻ ቢሆን ኖሮ እንዴት ቀላል ነበር? ግን ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር ከያንዳንዱ የሰው ልጅ ልብ መካከል ነው የሚያልፈውና ማን አለ ከራሱ ልብ ቁራጭ ቆርጦ ለማጥፋት ፈቃደኛ ይሆነ?
ሶልዘኒትሲን ኮምዩኒስት የነበሩ ወታደር የነበሩ ስታሊን ለዓመታት በሞት እስር ቤት (ጉላግ) ያሰራቸው ከሩሲያ ወደ ኦርቶዶክስ ሃይማኖታቸው የተመለሱ የሩሲያ ጀግና ነበሩ። ተጨቋኝ ነኝ ማለት የሚገባቸው ነበሩ። ለሃገረቸው ጦርነት ተዋግተው በማግስቱ የታሰሩ ናቸው። አለምንም ጥርጥር ተጨቋኝ ነኝ ማለት የሚገባቸው ነበር። ግን እስር ቤት የሌሎችን ሳይሆን የራሳቸውን ኃጢያት እንዲገለጽላቸው አደረገ! የሰው ልጅ እውነተኛ ባሕርይ እንዲረዱ አደረገ። የሰው ልጅ ችግርም እንዴት መቅረፍ እንደሚቻል ገባቸው። በጦርነት፤ በማስወገድ፤ በማባረር፤ በመወገን ሳይሆን በንስሃ፤ በመስማማት፤ በመከባበር፤ በመቻቻል ነው።

ይህ ሩሲያዊ ሶልዠኒትሲን የዘመኑን «ጭቋኝና ተጨቋኝ» አስተሳሰብን ትተው የእውነትን ባህላዊ የኢትዮጵያዊ አስተሳሰብ ነው የገለጹት። ሩሲያዊው ኦርቶዶክስ ባህላችንን ያስታውሱን። ለምንናውም የኢትዮጵያ ባህል፤ ማንኛውም ሃይማኖት፤ ይህ የ«ጨቋኝና ተጨቋኝ» ርእዮተ ዓለም በአድ ነው። በአድ ነው። ሚስኪኖቹ የጃንሆይ ተመሪዎች ወደ ሃገራችን ከምእራብ ሃገራት ያመጡት መርዝ ነው። መርዙን እናውጣው። ወደ እራሳችን እንመለስ።

Thursday, 4 January 2018

Freeing Political Prisoners

Undoubtedly most of you have heard that the Ethiopian government is going to free all political prisoners, or pardon those who have broken laws concerning treason and terrorism, or some such thing. Anyway, it appears that many of the known political prisoners will be freed.

This is a great measure. I don't think anyone could say otherwise. A lot of these folks have been suffering cruelties at the hands of the security apparatus, cruelties unbecoming Ethiopia. The Ethiopian tradition is, as practiced in the past, honour and civility and magnanimity. Political prisoners, even those who were a grave threat to the ruling monarch, were imprisoned, preferably far away, on Mount Wehni for example, but given a comfortable imprisonment, if there is such a thing. Modern torture, or ancient torture for that matter, was unthinkable. If anyone even happened to hear of such a thing, they would have immediately thought it dishonourable and dismissed it out of hand.

So, this is a step that shows magnanimity, honour, and civility, it's good for the country, but most of all, it is good for the prisoners, who have been bearing on their shoulders the guilt of all of us Ethiopians.

Nevertheless, a note of caution. Remember what happened that last time several high-profile political prisoners were released. The opposition descended into a downward spiral from which it has not recovered to this day. And yes, I am not forgetting the release of Birtukan Mideksa, but I shudder to recall it and what she went through in the prison. All I can say is, may God bless her and keep her and may God forgive us for what we have done to her and all the unknown Birtukans out there.

I humbly urge all of us Ethiopians to keep in mind today that Rome was not built in a day, and when the EPRDF deigns to do something good and noble is not the time to shout and scream for it to step down from power. There is nobody to replace the EPRDF. Our past 50 years of history, including our elite's long suicide from 1960 to 1991 as well as the EPRDF's monopoly on power has made sure that the protests of the grassroots have no viable elite to lead them. Today is the time to renew our efforts to work on feasible, yes, feasible, politically realistic projects to improve our political and social environment. In our little small circles. We're not all kings and we're not meant to be. A good deed is worth a thousand good words. The line between good and evil cuts through all our hearts. Let's point our fingers at ourselves, particularly those of us in the diaspora who have betrayed our country by leaving it, and see how we can fix ourselves and our surroundings. Maybe then we can build a solid grassroots capable of growing and nurturing a political elite that is a viable foil and partner for the EPRDF.

Friday, 17 November 2017

Courageous Ethiopians

My previous post was from a chapter in Father Arseny: Priest, Prisoner, Spiritual Father, a book about a Father Arseny, a Russian Orthodox priest-monk who was imprisoned for long periods of time in the Soviet gulags (prisons) and who became a known spiritual father to many.  (The book is available in Amharic at bookstores in Addis Ababa.)

Father Arseny, along with much of the clergy of the Russian Orthodox Church who were not outright murdered, was sent to the worst of the gulags to die as a sort of slow death sentence. In the prison were also political prisoners and criminals, all of whom, understandably, hated the Soviet government and thought the government responsible not only for their imprisonment but also for all their problems and the problems of the country.

In the chapter I posted, while in prison, Father Arseny is asked to participate in a discussion among inmates about the Soviet government, and is specifically asked to condemn the Soviets unreservedly for all the suffering they have caused. They expected that he, as a prisoner of the Soviets, and moreover as a clergyman of the Russian Orthodox Church, which was targeted for destruction by the Soviets, would like them express extreme hatred for the Soviets and blame them for everything wrong in the country.

However, Father Arseny, in true Orthodox fashion, points the finger not at the other - at the Soviets - but the self - himself, his fellow clergyman, and the laity. He says, in short, that if the clergy and laity did not rebel so much against God before the revolution, then the revolution would not have even happened. In other words, it was the sins of the Orthodox clergy and laity that brought about the Soviets. His true and courageous stand left his fellow prisoners speechless.

I have met a few such courageous Ethiopians, and I do not count myself among them, who accept responsibility and hold themselves, in whatever capacity, accountable for what has and is happening in Ethiopia. They do not blame the government, past or present, the Woyane or Tigre or ERPDF, or Shaebia, or "Oromos" or OLF, or Amharas or donkeys, or communists or thieves, etc. for Ethiopia's problems. They point the finger at themselves.

And then, because they point the finger at themselves, they do what they can, with whatever minute capacity they have, to set things aright. By taking responsibility, they empower themselves - they do not see themselves as interested bystanders but as stakeholders with a role to play.

Some people ask me what they can do. What can a simple layman do? Well, I say, if (and this is a big if) you consider yourself an Ethiopian (and not an American or Swede or something) , and if you think you have positive ideas, or perhaps a good civic attitude, or positive moral outlook, then live in Ethiopia and let your positive ideas and good civic attitude and moral outlook permeate their surroundings.

Would this be effective, is the next question. What does effective mean? Will it turn the whole country around? No, of course not, but who are we to think that we can. In all humility, I can affect perhaps my family, friends, maybe neighbourhood. That's about it. If I expect any more then I'm being unrealistic at best, delusionally prideful at worst. Why, even our great leaders have much less influence that we think because of the enormous influence exerted upon them.

So we will not turn our country around, but we might help and influence  a person or two or more. And if everyone does that, as Seraphim of Sarov said: "Acquire the Spirit of Peace and a thousand souls around you will be saved."

Friday, 30 September 2016

ጥፋት አለብኝ ብዬ ካላመንኩኝ «ወያኔ» ነኝ!

2009/1/19 ዓ.ም. (2016/9/29)

ከዲያስፖራ እየኖርኩኝ ስጋዊ ምቾቴን አጠናቅቄ ህሊናዬ እየወቀሰኝ ሀገር ቤት ያሉትን ወንድሞች እህቶቼን ታገሉ እላለሁ። ሀግሬን እወዳለሁ እላለውንጂ ያሳደገችኝ ብትሆንም ለሷ ያለኝን ሃላፊነት ከተውኩኝ ቆይቻለሁ። ክጃታለሁ ጥያታለሁም። ሆኖም ግን ሀገሬን መበደሌ አይታየኝም። ስለሌሎችን ኅጢአትና በደል እጮሀለው እንጂ። ከአይኔ ያለውን ግንድ አላየውም የሌላውን ጉድፍ ብቻ ነው የሚታዬኝ።

ምሬቴ ትንሽ በመሆኗ ምክንያት አጥሬን መግፋት መብቴ ነው እላለሁ! ገፈዋለሁ፤ ከጎረቤት ጋርም እጣላለሁ፤ መንገድንም አጠባለሁ። ለሰፈሩ ችግር እያመጣሁኝ ነው። ግን የእለት ወሬዬ ስለ ቀበሌአችን ሹማምንት የምስና ባህሪ ነው። አይኔ ውስጥ ግንድ የለም።

እውነት ነው፤ ሲያስፈልግ ጉቦ ሰጣለሁ። መብቴን ለማስከበር ብቻ ሳይሆን የማይገባኝን ለማግኘትም። ምን ይደረግ፤ የሀገራችን እውነታ ነው ብዬ እራሴን አታልላለው። ግን መሪዎቻችን እንዴት ሞራል ቢስ ናቸው ብዬ አማርራለሁ።

አንዱ የኦርቶኦክስ መሰረታዊ እምነት ሁላችንም ለሁሉም ሰው ኅጢአት በተወሰነ ደረጃ አስተዋጾ እድርገናልና ሃላፊነት አለብን የሚል ነው። ኅጢአቶቻችን የተገናኙም የተወራረሱም ናቸው። ይህንን ለማብራራት ያህል የታወቀው ሩሲያዊ ደራሲ ፊኦዶር ዶስቶኤቭስኪ በ«ካራማዞቭ ወንድማማቾች» የጻፈውን ጥቅስ እንመልከት። ታላቁ የሃይማኖት አባት ዞሲማ ልጆቻቸውን ሲመክሩ እንደዚህ አሉ፤
«አንድ ሰው በዚህ ዓለም ከሚኖሩት በሙሉ የባሰ ኅጢአተኛ እንደሆነ ሲያምን፤ በተጨማሪም ከሁሉም ሕዝብ ፊት ጥፋተኛ እንደሆነ...፤ ለዓለምም ለያንዳንዱ ሰውንም ኅጢአት እና ጥፋት እንዳለበት ስያምን ነው የ(ክርስቲያናዊ) አንድነት ድላችንን ማስመዝገብ የምንችለው..።
«ሁላችሁም ልባችሁን በደምብ አዳምጡና ለራሳችሁ ሳትሰለቹ ንስሐ ግቡ። እስከ ተጸጸታችሁ ድረስ ኅጢአታችሁ የጎላ ቢመስላችሁም አትፍሩት...።
«በጸሎታችሁ እንደዚህ አስታውሷቸው፤ «አምላካችን ሆይ የሚጸልይላቸው የሌሏቸውንም ላንተ መጸለይ የማይፈልጉትንም አድናቸው» ብላችሁ ጸልዩ። እንደዚህም ቀጥሉ «አምላኬ ሆይ እኔ ከሁሉም የባሰ ርኩስ ነኛ፤...»»
በተጨማሪ ባለፈው ጽሁፌ የጠቀስኩት በጾቪዬት እስር ቤት የተሰቃዩት አለክሻንደር ሶልዠኒትሲን ከእስር ቤት ሆነው የጻፉትን እንደገና ልጥቀስ፤

ከእስርቤታችን አልጋ የሆነው የበሰበሰው ገለባ ላይ ጋደም ብዬ ነው ለመጀመርያ ከውስጤ የበጎ መንፈስ የተሰማኝ። ቀስ በቀስ መረዳት የጀመርኩት ይህ ነው፤ ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር በሀገሮች፤ መደቦች፤ የፖለቲካ ፓርቲዎችም መካከል አይደለም የሚያልፈው፤ ይህ መስመር የሚያልፈው በያንዳንዱ የሰው ልብ መኻል ነው። መስመሩ እድሜአችን በሙሉ ከውስጣችን ወደፊት ወደኋላ ይላል። በክፉ የተሞሉ ልቦችም ቢያንስ ቅንጣት ያህል ጥሩነት ይኖራል፤ ከሁሉም ጥሩ ከሚባለውም ልብ ከአንድ ጥጓ ትንሽ ክፉነት ይኖራል።
«በየቦታው እየዞሩ ያሉ ክፉ ስራ የሚሰሩ ክፉ ሰዎች ቢኖሩና እነሱን ከኛ መለየትና ማጥፋት ብቻ ቢሆን ኖሮ እንዴት ቀላል ነበር? ግን ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር ከያንዳንዱ የሰው ልጅ ልብ መካከል ነው የሚያልፈውና ማን አለ ከራሱ ልብ ቁራጭ ቆርጦ ለማጥፋት ፈቃደኛ ይሆነ?»
ሶልዠኒትሲን በመታሰራቸው፤ በእስር ቤት ለደረሰባቸው በደልና ስቃይ፤ ያሰሯቸውን የዘመኑን መንግስት መሪዎች፤ የፍርድ ቤት ዳኞች፤ የደህንነት አዛዦች፤ ወዘተ ብቸኛ ጥፋተኛ አድርገው ሊቆትሩ ይችሉ ነበር። ማንናችንም ደካሞች በሳቸው ቦታ ብንሆን እንደዛ ነበር የምናስበው።

ግን እየተሰቃዩም ቢሆን ይህን ቀላሉ የውሸት መንገድን ከመከተል እውነትን መረጡ። እውነትን ፈለገው ህሊናቸውን ተጠንቅቀው መርምረው የራሳቸውም ግድፈት እንዳለ ተገነዘቡ። ከነዛ ክፉዎች እንደማይሻሉ አመኑ።

ሶልዠኒትሲን በሁለተኛ ዓለም ጦርነት ጀግና ወትደር ነበሩ። ሀገሬን እንደዚህ አገልግዬ እንዴት በማግስቱ ለማይረባ ምክንያት እታሰራለሁ ነበር በመጀመርያ ያሰቡት። ግን ህሊናቸውን ሲመረምሩ ከጦር ሜዳ የሰሩትንና ሲሰራ አይተው ዝም ያሉትን ግፍ አስታወሱ። ሀገርን በመከላከል አሳበው ህሊናቸውን እንዴት እንደሸጡ አስተዋሉ። አብረዋቸው የታሰሩትንን የመንግስት ሰለቦች ሲመለከቱም ምንም ንጹ የሚመስሉትም በተወሰነ ደረጋ ተመሳሳይ የህሊና ሽያጭ እንዳካሄዱ ተገነዘቡ።

ከዝ ቀጥሎ የበደሏቸውን ሲመለከቱ በፊት የነበራቸው እነሱ ክፉ እኔ ንጹ የሚለው አስተሳሰባቸው ውሸት እንደሆነ ገባቸው። በዳዮቻቸውም እንደራሳቸው በተለላየ አታላይና የማይረባ ምክንያት ህሊናቸውን ሽተዋል። ስንቱ ናቸው በስመ ሀገር ወዳድነት እንደ ሶልዠኒትሲን አይነቱን የሀገር ከሃዲ ብለው ያሳሰሩት። እነዚህ «እውነት አማኞች» ርዕዮት ዓለማቸውን እንደ ሃይማኖት አድረገው የሚያምኑበት ስለሱ ምንም ለማድረግ ወደኋላ አይሉም ነበር። ሶልዠኒትሲን እነሱን ሲያዩ እራሳቸውን አዩ።

የመጨረሻ ግንዛቤአቸው ንስሃ መግባት እንዳለባቸው ነበር። ንስሃ ቢገቡ በራሳቸው ብቻ ሳይሆን በባልደረቦቻቸው በሙሉ የደረሰው እንደማይደርስ ገባቸው። በሶቪዬት ህብረት የሚገኙት ሀገራት በሙሉም ሰላምና እውነታዊ መንግስት ሊያገኙ የሚችሉት በዚህ አይነት መንገድ ብቻ እንደሆነ ተገነዘቡ። ሌሎቻችንም እንደዚህ አድርገን እንድናስብ ጋበዙን።

እሺ፤ የምጨረሻ ጥቅስ ከአባ ዶሮቴዎስ፤
«አንድ ሰው በእግዚአብሔርን ፊት እራሱን በደምብ ቢመረመረ ለሚደርስበት ያለው በደል ባተግባር፤ በሃሳብ፤ በንግግር፤ በፀባይ፤ ወይም በባህሪይ ሃላፊነት እንዳለበትና ከፊል ተጠቅያቂ እንደሆነ ይገለጽለታል።»
እንዲሁም ለኢትዮጵያ ችግሮች ሁሉ፤ የፖለቲካ ችግር ተጨምሮ፤ ሁላችንም ኢትዮጵያኖች አስተዋጾ አድርገናል ሃላፊነትም አለብን ብለን ማመን አለብን። ቀጥሎ ይህን ሃላፊነት ብንወታው ችግሩ ይፈታል ብለን ማመን አለብን። አባ ዶሮቴዎስ እንዳሉት እራሳችንን ተጠንቅቀን በኢግዚአብሔር ፊት እንመርምር። ይህ ወደ ሰላምና እውነት ብጨኛው መንገድ ነው።

Wednesday, 14 September 2016

ከጎረቤቱ ጋር የተጣላ «ወያኔ» ነው!

2009/1/4 ዓ.ም. (2016/9/14)

የጎረቤታሞቾ ልጆች ይጣላሉ። አንዱ ሌላውን የትምህርት ቤት መጸሐፌን ሰረቀ ብሎ ይከሰዋል። ወሬው ወደ ወላጅ ጆሮ ይደርሳል። የተከሳሹ ቤተሰብ እንዴት ልጃቸው ልጃችንን ሌባ ይላል ብለው ጎረቤቶቻቸውን ይቀየማሉ። በዚህ ተነስቶ የሁለቱ ጎረቤታሞቾ ግንኙነት መበላሸት ይጀምራል። ሐሜትና ክስ መመላለስ ይጀምራሉ። በተዘዋዋሪም በቀጥታም መሰዳደብ ይጀምራሉ። አንዱ ሌላውን እንደ «ጠላት» ይቆጥራል። ጓደኞቻቸውም ይወግናሉ።

አብዮቱ ከነበልባል ወደ እሳት እየተፋፋመ ነው። አንዱ ቤተሰብ የጠላት ጎረቤታቸውን ልጅ ኢህአፓ ነው እያሉ ማስወራት ይጀምራሉ። ልጁ ታስሮ ይወሰዳል ይሰቃያል ይገደላልም። ታሪክ ልጁን የደርግ ሰለባ አድርጎ ይመዘግበዋል። እውነቱ ግን የጎረቤት ሰለባ መሆኑ ነው። ደርግ መሳርያ ብቻ ነበር።

በትምህርት ቤቱ ሰራተኞች መካከል ምንጩ የተረሳ የቆየ ጸብ አለ። ሰራተኞቹ ለሁለት ተከፍለዋል፤ ዋናው አስተዳዳሪው አንድ ወገን ይዟል፤ ምክትል አስተዳዳሪው ሌላውን ወገን ይዟል። ጦርነት አይደለም፤ ትምህርት ቤቱ ይሰራል ልጆቹም ይማራሉ። ግን ውስጥ ለውስጥ ችግር አለ፤ ትምህርት ቤቱ በሐሜትና ሹክሹክታ መንፈስ ተይዟል።

ኢህአዴግ ስልጣን በቅርብ ይዞ ለአብዮታዊ ዴሞክራሲ እንቅፋት ለሆኑትን «ነፍጠኖች» ከመንግስት ስራ እያባረረ ነው። ምክትል አስተዳዳሪው የሱ «ጠላት» ጎራ የሆኑትን በውሸት ትምክህተኞች ነፍጠኞች ብሎ ለመንግስት ይጠቁማቸዋል ከሰራም ይባረራሉ። ኢህአዴግ አባረራቸው ተብሎ ታሪክ የሚዘግበዋል። ግን ይህን ጉዳት ያደረሱባቸው ባልደረቦቻቸው ናቸው። ኢህአዴግ መሳርያ ብቻ ነበር።

ትምህርት አይሆነውም የሚባል ልጅ ከሰፈራችን አለ። ቤተሰቡም ዘመዶቹም ትምህርት ቤቱም ካህኑም አይረዱትምም አይረዱትም። ጭራሽ ይለቅፉታል ይሰድቡታል ይተቹታል። ልጁ እያደገ ሲሄድ ብሶትና ምሬት ያለው ከራሱ ጋር የተጣላ የዝቅተኝነት ስሜት ያለው ጎረምሳ ይሆናል።

ከምርጫ 97 በኋላ ሰላማዊ ሰልፎች እየተካሄዱ እያለ ፌዴራል ፖሊስ እየዞሩ ህዝብን እያሰሩ ነው። ይህንን ብሶት የተሞላው ልጅ ከሰፈርህ የሰልፉን አስተባባሪዎች የሆኑትን ጠቁምልን በቋሚነትም ጠቋሚያችን ሁንልን ብለው ይጠይቁታል። ልጁ ተስማምቶ በርካታ የሰፈር ልጆችን ይጠቁማል። እስረኞቹም ቤተሰቦቻቸውም ይሰቃያላኡ። የታሰሩት የተሰቃዩት ታሪክ ሲመዘገብ እንደ ኢህአዴግ ሰለቦች ይመዘግባቸዋል። ግን ጠቋሚው ባይጠቁማቸው ምንም አይደርስባቸውም ነበር። ልጁ አሁንም የሰፈሩ «ጠቋሚ» ትብሎ ይታወቃል።

ምርጫ 97 ሊደርስ አቅራብያ አቋማቸው ተመሳሳይ የሆኑት የተቃዋሚ ፓርቲዎች አንድ ግንባር ፈጥረው እራሳቸውን «ቅንጅት» ብለው ሰይመው ምርጫውን ይወዳደራሉ። አሸንፉም። መንግስት ግን አላሸነፋችሁም አመጽም ማስነሳት ሞክራችኋል ብሎ ያስራቸዋል። ከዓመት በላይ ታስረው ከእስር ቤት ሲወጡ ባመረረ የእርስ በርስ ጥል ይለከፋሉ። በጸባቸው ምክንያት የነፃነት ንቅናቄውንም እንዲፈርስ ያደርጋሉ። እርስ በርስ ቢጣሉም የነፃነት ትግሉን ብያከሽፉትም «ውያኔ» በድሎናል ብለው ያለቅሳሉ።

አምባገናናዊ መንግስት በካላሉ ካስቀመጥነው «አምባገነን» የሚባለው የአብዛኛው የህዝብ ድጋፍ ስለሌለው ነውና የራሱን ፍላጎት ህዝቡ ላይ ስለሚጭንባቸው ነው። አብዛኛውን ቢወክልማ ምን «አምባገነን» ያስብለዋል። ኢህአዴግ አምባገነናዊ ነው ካልን የትንሽ ሰው ቁጥር ድጋፍ ነው ያለው ማለት ነው። የትንሽ የሰው ቁጥር ድጋፍ ያለው መንግስት ደግሞ አብዛኛ የሆነውን ህብረተሰብ መግዛት የሚችለው ይህ ህዝብ እርስ በርስ ለመከፋፈልና ለመገዛት ፈቃደኛ ከሆነ ብቻ ነው! «ፈቃደኛ» የሚለውን ቃል የተጠቀምኩት አውቄ ነው። ምክንያቱም አንድ ህብረተሰብ «ተከፋፈል» ትብሎ መታዘዝ አይቻልም። እራሱ ነው ልከፋፈል ውይም አልከፋፈል ብሎ የሚወስነውና።

ይህ መከፋፈል ነው ኢህአዴግን እስካሁን በስልጣን ላይ ያቆየው። ስለዚህ የኢህአዴግ ኢትዮጵያን እስካሁን መግዛት ሃላፊነቱን መሸከም ያለበት በገዛው ፈቃድ የተከፋፈለው የአገሪቷ ህብረተሰቡ ነው። 

ከላይ ያስቀመጥኳቸው ምሳሌ ታሪኮች ይን ይገልጻሉ። እርስ በርስ ሲጣላ ሲጠላ ሲቃረን የዋለ ህዝብ እንዲህ ይላል «ለጎረቤቴ ወይም ለወንድሜ ያለኝ ጥላቻ ለአምባገነኑና ለአምባገነኑ ጭካኔ ካለኝ ጥላቻ ይበልጣል፤ አምበገነኑ ይግዛኝ!» ታድያ የፖለቲካ ችግር ምንጭና ሃላፊነት ዬት ነው? ከ«ዎያኔ» ነው ወይስ ከኛ ኢትዮጵያ ህዝብ ነው?። ከኛ እንደሆነ ግልጽ የሆነ ይመስለኛል። የችግሩ መንጭም እኛው ነን፤ ሃላፊነቱም የኛው ነው፤ መፍትሄውም ከኛው ነው።

የታወቁት የሶቪዬት (የሩሲያ) ጸሃፊ አሌክሳንደር ሶልዠኒትሲን ለረጅም ዓመታት በ«ጉላግ» ከሚባለው የሶቪዬት «የሞት» እስር ቤቶች በፖለቲካ ምክንያት ታስረው ነበር። የሶቪዬት የኮምዩኒስት አምባገነናዊ መንግስት እስከ 20 ሚሊዮን ሰዎች (ከ160 ሚሊዮን የህዝብ ቁጥር) ወደነዚህ የጉልበት ስራ የስቃይና የሞት እስርቤቶች ልኮ ነበር።

ሶልዠኒትሲን ጀግና የሆኑ ሀገራቸውን ያገለገሉ ወታደር ነበሩ። ቢሆንም መንግስቱና በተለይ ሹማምንቱን ወቀስክ ተብለው ታሰሩ። ከእስር ቤት ሆነው እንደማንኛውም የህሊና እስረኛ «ለምን ታስረርኩኝ» «ምን አይነት ጭካኞች ናቸው» የሚሉትን ሃሳቦች ያንሸራሽሩ ነበር። ግን ከእስር ቤት ሆነው ስለ እስራ ዘመናቸው ሲመዘግቡ ከታች የተጠቀሰውን ታላቅ ሃሳብ ተገለጸላቸው፤ በታወቀው «የጉላግ አርኪፔላጎ» መጸሃፍ ሳፉት (ትርጉም የኔ ነው)፤

ከእስርቤታችን አልጋ የሆነው የበሰበሰው ገለባ ላይ ጋደም ብዬ ነው ለመጀመርያ ከውስጤ የበጎ መንፈስ የተሰማኝ። እውነቱን ቀስ በቀስ እንደዚህ እንደሆነ መረዳት ጀመርኩኝ፤ ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር የሚያልፈው በሀገሮች፤ በመደቦች፤ በፖለቲካ ፓርቲዎችም መካከል አይደለም፤ ይህ መስመር የሚያልፈው በያንዳንዱ የሰው ልብ መኻል ነው። መስመሩ እድሜአችን በሙሉ ከውስጣችን መለስ ከለስ ይላል። በክፉ የተሞሉ ልቦችም ቢያንስ ቅንጣት ያህል ጥሩነት ይኖራቸዋል፤ ከሁሉም ጥሩ ከሚባለውም ልብ ከአንድ ጥጓ ትንሽ ክፋት ይኖራታል።

በየቦታው እየዞሩ ያሉ ክፉ ስራ የሚሰሩ ክፉ ሰዎች ቢኖሩና እነሱን ከኛ መለየትና ማጥፋት ብቻ ቢሆን ኖሮ እንዴት ቀላል ይሆን ነበር! ግን ጥሩና ክፉን የሚለየው መስመር ከያንዳንዱ የሰው ልጅ ልብ መካከል ነው የሚያልፈውና ማን አለ ከራሱ ልብ ቁራጭ ቆርጦ ለማስወጣት ፈቃደኛ ይሆነ?

በዚህ አባባላቸው ሶልዠኒትሲን የሚሉት የአምባገነናዊ ስረዓት የገዢና የመሪ ውጤት ሳይሆን የያንዳንዱ ሰው ድክመትና ጠፋት ውጤት ነው። ይህ አስተማሪ አባባል የዛሬውን የኢትዮጵያ ፖልቲካ ሁነታ በደምብ ይገልጻል።

ቅድም እንዳልኩት ኢህአዴግ አናሳ ድጋፍ ነው ያለው። በተጨማሪ ከለሎች አምባገነናዊ ስረዓት አናሳነቱ የተለየ ነው። ለምሳሌ የሶቪዬት መንግስት አናሳ ድጋፍ ቢኖረውም ይህ ደጋፍ በጎሳ የተመሰረተ አልነበረም። ስለዚህ የሶቪዬት ህዝብ ተጨቆኛለሁ ሲል በራሴ ወገን በሶቪዬቶች ነው የተጭቆንኩት ብሎ ነበር የሚያስበው። የኢህአዴግ አገዛዝ ግን አናሳ ብቻ ሳይሆን በጎሳ የተመሰረተ ነው። ህገ መንግስቱም አስተምረውም እንደዚህ ነው። ህዝቡም እንደዚህ ነው የሚመለከተው። የሰው ልጅ ባህሪ ደግሞ በራሱ ወገን ቢገደል ይሻለዋል በሌላ ወገን ወይም ጎሳ ከሚጨቆን! ስለዚህ የኢህአዴግ የጎሳ አገዛዝ ከሌላው አማገነናዊ ስረዓት ይበልጥ ህዝብ ቅራኔና አመጽ የተጋለጠ መሆን ነበረበት።

ይህን አመዛዝነን ከተረዳን ለኢህአዴግ በስልጣን መቆየት እኛ ኢትዮጵያዊያን ዋና ምክንያት መሆናችንን ይገባናል። አንድነት ያለው ህብረተሰብ ብንሆን እርስ በርስ ብንስማማ ብንተሳሰብ ብንፋቀር ኢህአዴግ ድሮ ወድቆ ነበር። በተጨማሪ ማለት የምንችለው ኢህአዴግ በኃይል ሊገዛን አይችልም በኃይል ገዝቶንም አያውቅም! በኛ እርዳታ፤ ትብብርና ፈቃድ ነው እየገዛን ያለው። የኛ ጥፋትና ሃጥያት ነው የኢህአዴግ አገዛዝ ምሶሶ። ስለዚህም ኢህአዴግን የፈጠርነው የምናቆመውም እኛ ከሆንን የምናፈርሰውም የምናጠፋውም እኛው ነን የምንሆነው። ውግያና ተመሳሳይ ቀውጥ አያስፈልግም፤ ከጎረቤቴ ጋር አልጣላም ማለት ብቻውን በቂ ነው። እንደዚህ ካረግን የኢህአዴግ ይፈርሳል። እርግጠኛ ነኝ በርካታ የኢህአዴግ አባላትም ያንን ሸክማቸውን የሚያወርዱበትን ቀን በጉጉት የጠብቁታል!