ይህንን ቪዲዮ ብትመለከቱ ጥሩ ይመስለኛል።
https://youtu.be/qSPFi8xsbBo?t=1696
ረዥም ከአንድ ሰአት በላይ የሚወስድ ቢሆንም ከላይ ባስቀመትኩት ሊንክ ጀምሮ ብታዩት ስለ ንስሃ ታላቅ ትምሕርት በተለይም ታላቅ ምሳሌ ታያችሁ።
አቶ ታደሰ ወልዴ፤ ታላቅ የኦክስፎርድ መምህር፤ ለኛ ሁሉ ንስሃ ለመግባት ምሳሌ በመሆኖ እግዚአብሔር ይስጦት።
የሰላም ክፍሌ ይትባረክ ብሎግ፤ ስለ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለኝን ትናንሽ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ። ለስሕተቶቼም በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ
Showing posts with label morality. Show all posts
Showing posts with label morality. Show all posts
Tuesday, 6 November 2018
Monday, 10 September 2018
ቤተ ክርስቲያን በፍጥነት መፅዳት አለባት
ቅዱስ ዮሃንስ አፈወርቅ ፓትሪአርክ በሆኑበት ዘመን 11 ፓፓሳትን አባረዋል ይባላል። ቅዱስ ጳውሎስ በመልክቶቹ የቤተ ክርስቲያን መሪዎች ንፅሁ የሆኑ፤ ጥሩ ምሳሌ የሆኑ እና ህዝቡን የማያሳስቱ መሆን አለባቸው ብሎ በተደጋጋሚ ጽፏል። በርካታ መልክቶቹ ውስጥ ስለቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያለን ችግር እና እንዴት መጽዳት እንዳለበት ጽፏል። በዛሬው ዘመን ይህንን የቅዱስ ጳውሎስ ምክሮችን እና የቅዱስ ዮሃንስ አፈወርቅን ምሳሌ ብንከተል ወይንም ቢያንስ ብናስብበት ጥሩ ይመስለኛል።
በቤተ ክርስቲያናችን አመራር ማለትም ጳጳሳት፤ ካህናት እና አስተዳደር በርካታ የእምነት እና ግብረ ገብ ችግሮች እንዳሉ ይታወቃል። እነዚህ ችግሮች በተለየዩ መንገዶች ባለፉት ዓመታት መጥተዋል በዝተዋል። ይህ ችግር ለቤተ ክርስቲያናችን ታላቅ ጉዳት እያመጣ እንደሆነ ይታወቃል።
ስለ የቤተ ክርስቲያን አመራር ችግሮች ስንወያይ ታላቅ ጥንቃቄ ያስፈልጋል፤
1. ግብዝነትን እና ትዕቢትን መራቅ አለብን፤ እንደ አንድ ምዕመን አመራር ላይ ጣቴን ሳተኩር የራሴን ኃጢአቴን እረሳለሁ። ለዚህ ነው ምዕመናን መሪዎችን እና የቤተ ክርስቲያን ፖለቲካን አትመልከቱ ብሎ የሚመከረው በክርስትና ህይወት።
2. መፍረድ የለብንም። አመራሮች ላይ ችግር ስናይ ሰው በመሆናችን አንዱን ታላቅ ኃጢአት «መፍረድ» ለማድረግ እንፈተናለን። «ድርጊቱ ላይ እንፍረድ ሰውዉ ላይ ግን መፍረድ የለብንም» የሚለውን ትምሕርት ብናውቅም እንረሰዋለን። መርሳት የልብንም። አመራር ሲሳሳት ብናይ በመጀመርያ ለዛ ሰው መጸለይ ነው ያለብን እና እግዚአብሔርን ሁላችንን ከኃጢአት እንዲያርቀን መለመን ነው ያለብን።
ይህን ካልኩኝ በኋላ ግን ቦትዬ ባይሆንም ለህሊናዬ አደገኛ ቢሆንም በዚህ ጉዳይ ሃሳቤን መነገሬ ጥሩ ይመስለኛል። ቅዱስ ጳውሎስ በመልክቱ እንደዚህ አይነት ጉዳዮች የ«እረኝነት» (pastoral) ጉዳዮች እንደሆኑ ገልጿል። ለምሳሌ ተደጋጋሚ ህዝብ የሚያውቀው ኃጢአቶች የሚፈጽም ካህን ወይንም ጳጳስ ካለ አለቆቻቸው ምን እናድርግ ሲሉ እንደ ዘመናዊ ፍርድ ቤት ህግን ከሞላ ጎደል በጭፍን መልኩ አያሰፍኑም። ምን ቢደረግ ነው ካህኑ የሚድነው? ምን ቢደረግ ነው ህዝቡ የሚድነው? ነገሮች ሚዛን ላይ ተደርገው መታየት አለባቸው እንጂ ጥቁር እና ነጭ አይደሉም። አራት መስፈርቶች፤ ክስተቱ፤ ሁኔታው፤ ሰዎቹ እና ዘመኑ መታየት አለበት።
በኔ እየታ በአሁኑ ዘመን ትሉቁ ጎልቶ የሚታየው መስፈርት «ዘመን» ነው። ምዕመናን በመሪዎች ስህተት በጣም ሊወዛበቡ የሚችሉበት ዘመን ነው። ዛሬ አይኑ ብዙ ነው። ወሬው እና ጫጫታው ብዙ ነው። አንድ ችግር ያለው ጳጳስ ወይንም ካህን ቶሎ ከስራ ካልተወገደ በርካታ ምዕመን በፍጥነት መሰናከል (በእምነት ማጣትም በመፍረድም) የሚችልበት ዘመን ነው። የፍጥነት ዘመን ነው። አንድ ችግር ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሲገባ በሽታው በፍጥነት ነው የሚስፋፋው እና መሰረት የሚጥለው።
ይህን በሲኖዶስ ችግራችን በደምብ አይተነዋል። አሁን በቤተ ክርስቲያን አመራሮቻችን የጉቦ፤ ሙስና እና ሌሎች የግብረ ገብ እጦት በምዕመናን ያመጣው ችግርን አይተነዋል። ከኛ ቤተ ክርስቲያን ውጭም በካቶሊች ቤተ ክርስቲያን ችልተኝነት እና መታገስ ባለፉት 30-40 ዓመት ያመጡት ችግሮችን አይተናል።
ስለዚህ አሁን እረኞቻችን ሚዛኑን ከትዕግስት ይልቅ ወደ ፍትነት እና ችኮላ ማድላት ያለባቸው ይመስለኛል። እንደ ዮሃንስ አፈወርቅ ጎልቶ የሚታይ ችግር ሲፈጸም ቶሎ ብሎ ህዝቡ ሳይሰናከል እርምጃ መውሰድ። በሽታው መሰረት ለመጣል እና መስፋፋት እድሉ ሳይኖረው ወድያው ማከም። ይህ በዛሬው ዘመን ለኃጢአት አድራጊውም እጅግ ይጠቅመዋል። በፍጥነት ወደ ኃጢአት ኑሮ ውስጥ ከሚገባ ቶሎ ወደ ንስሃ እንዲገባ ይረደዋል። ይህ የፍጥነት ዘመኑ በቀላሉ እንዳይቆጣጠረው ይረደዋል።
ስለዚህ የቤተ ክርስቲያን አመራሮች እባካችሁን የቤተ ክርስቲያን ጽዳት ዘመቻችንን አፋጥኑ። ችላ አንበል። ታጋሽ አንሁን። በማንም አንፍረድ በስራው ብቻ። ግን ህዝቡን ከፈተና እንጠብቅ። ግልጽና ግዙፍ ኃጢአትን የሚፈጽሙት ጳጳሳት እና ካህናትን ቶሎ ከሃላፊነት ይወገዱ እና ወደ ክርስትናዊ ህክምናቸው ይግቡ። የአሁኑ ዘመን ይህን መንገድ የሚያስገድድ ይመስለኛል።
በቤተ ክርስቲያናችን አመራር ማለትም ጳጳሳት፤ ካህናት እና አስተዳደር በርካታ የእምነት እና ግብረ ገብ ችግሮች እንዳሉ ይታወቃል። እነዚህ ችግሮች በተለየዩ መንገዶች ባለፉት ዓመታት መጥተዋል በዝተዋል። ይህ ችግር ለቤተ ክርስቲያናችን ታላቅ ጉዳት እያመጣ እንደሆነ ይታወቃል።
ስለ የቤተ ክርስቲያን አመራር ችግሮች ስንወያይ ታላቅ ጥንቃቄ ያስፈልጋል፤
1. ግብዝነትን እና ትዕቢትን መራቅ አለብን፤ እንደ አንድ ምዕመን አመራር ላይ ጣቴን ሳተኩር የራሴን ኃጢአቴን እረሳለሁ። ለዚህ ነው ምዕመናን መሪዎችን እና የቤተ ክርስቲያን ፖለቲካን አትመልከቱ ብሎ የሚመከረው በክርስትና ህይወት።
2. መፍረድ የለብንም። አመራሮች ላይ ችግር ስናይ ሰው በመሆናችን አንዱን ታላቅ ኃጢአት «መፍረድ» ለማድረግ እንፈተናለን። «ድርጊቱ ላይ እንፍረድ ሰውዉ ላይ ግን መፍረድ የለብንም» የሚለውን ትምሕርት ብናውቅም እንረሰዋለን። መርሳት የልብንም። አመራር ሲሳሳት ብናይ በመጀመርያ ለዛ ሰው መጸለይ ነው ያለብን እና እግዚአብሔርን ሁላችንን ከኃጢአት እንዲያርቀን መለመን ነው ያለብን።
ይህን ካልኩኝ በኋላ ግን ቦትዬ ባይሆንም ለህሊናዬ አደገኛ ቢሆንም በዚህ ጉዳይ ሃሳቤን መነገሬ ጥሩ ይመስለኛል። ቅዱስ ጳውሎስ በመልክቱ እንደዚህ አይነት ጉዳዮች የ«እረኝነት» (pastoral) ጉዳዮች እንደሆኑ ገልጿል። ለምሳሌ ተደጋጋሚ ህዝብ የሚያውቀው ኃጢአቶች የሚፈጽም ካህን ወይንም ጳጳስ ካለ አለቆቻቸው ምን እናድርግ ሲሉ እንደ ዘመናዊ ፍርድ ቤት ህግን ከሞላ ጎደል በጭፍን መልኩ አያሰፍኑም። ምን ቢደረግ ነው ካህኑ የሚድነው? ምን ቢደረግ ነው ህዝቡ የሚድነው? ነገሮች ሚዛን ላይ ተደርገው መታየት አለባቸው እንጂ ጥቁር እና ነጭ አይደሉም። አራት መስፈርቶች፤ ክስተቱ፤ ሁኔታው፤ ሰዎቹ እና ዘመኑ መታየት አለበት።
በኔ እየታ በአሁኑ ዘመን ትሉቁ ጎልቶ የሚታየው መስፈርት «ዘመን» ነው። ምዕመናን በመሪዎች ስህተት በጣም ሊወዛበቡ የሚችሉበት ዘመን ነው። ዛሬ አይኑ ብዙ ነው። ወሬው እና ጫጫታው ብዙ ነው። አንድ ችግር ያለው ጳጳስ ወይንም ካህን ቶሎ ከስራ ካልተወገደ በርካታ ምዕመን በፍጥነት መሰናከል (በእምነት ማጣትም በመፍረድም) የሚችልበት ዘመን ነው። የፍጥነት ዘመን ነው። አንድ ችግር ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሲገባ በሽታው በፍጥነት ነው የሚስፋፋው እና መሰረት የሚጥለው።
ይህን በሲኖዶስ ችግራችን በደምብ አይተነዋል። አሁን በቤተ ክርስቲያን አመራሮቻችን የጉቦ፤ ሙስና እና ሌሎች የግብረ ገብ እጦት በምዕመናን ያመጣው ችግርን አይተነዋል። ከኛ ቤተ ክርስቲያን ውጭም በካቶሊች ቤተ ክርስቲያን ችልተኝነት እና መታገስ ባለፉት 30-40 ዓመት ያመጡት ችግሮችን አይተናል።
ስለዚህ አሁን እረኞቻችን ሚዛኑን ከትዕግስት ይልቅ ወደ ፍትነት እና ችኮላ ማድላት ያለባቸው ይመስለኛል። እንደ ዮሃንስ አፈወርቅ ጎልቶ የሚታይ ችግር ሲፈጸም ቶሎ ብሎ ህዝቡ ሳይሰናከል እርምጃ መውሰድ። በሽታው መሰረት ለመጣል እና መስፋፋት እድሉ ሳይኖረው ወድያው ማከም። ይህ በዛሬው ዘመን ለኃጢአት አድራጊውም እጅግ ይጠቅመዋል። በፍጥነት ወደ ኃጢአት ኑሮ ውስጥ ከሚገባ ቶሎ ወደ ንስሃ እንዲገባ ይረደዋል። ይህ የፍጥነት ዘመኑ በቀላሉ እንዳይቆጣጠረው ይረደዋል።
ስለዚህ የቤተ ክርስቲያን አመራሮች እባካችሁን የቤተ ክርስቲያን ጽዳት ዘመቻችንን አፋጥኑ። ችላ አንበል። ታጋሽ አንሁን። በማንም አንፍረድ በስራው ብቻ። ግን ህዝቡን ከፈተና እንጠብቅ። ግልጽና ግዙፍ ኃጢአትን የሚፈጽሙት ጳጳሳት እና ካህናትን ቶሎ ከሃላፊነት ይወገዱ እና ወደ ክርስትናዊ ህክምናቸው ይግቡ። የአሁኑ ዘመን ይህን መንገድ የሚያስገድድ ይመስለኛል።
Wednesday, 5 September 2018
ልማት ሀገርን አይገነባም!
እስካሁን በሰው ልጅ ታሪክ አንድ ሀገር በ«ልማት» ተመስርቶ ተገንብቶ አያውቅም። ሰዎች ከአንድ መንደር ሲሆኑ፤ የጋብቻ እና የደም ትሥስር ሲኖራቸው፤ ባህላቸው አንድ ሲሆን፤ ለመተባበር እና ለመረዳዳት ብለው በተፈጥሮአዊ በአዎንታዊ መንገድ «ሀገር» ይሆናሉ። ሃብት ፍለጋ፤ ጦርነት፤ ግጭት ወዘተም በአሉታዊ መንገድ በሀገር ምስረታ ሚና ይጫወታል። ግን «ልማት» ሀገር አይገነባም። ትሥሥር አይፈጥርም። ዝምድና አይፈጥርም። ፍቅር የለውም። ከልብ መረዳዳት አይጠይቅም። ሀገር አይገነባም።
ለማስታወስ ያህል የተወሰነ ዓመት በፊት ህዝብን የምርጫ 1997 ችግርን ለማስረሳት፤ «ጠባብ» የጎሳ ብሄርተኝነትን ለመዋጋት፤ መንግስትን ሊጥል የሚችል መሃበረሰባዊ ክፍፍልን ለማስወገድ ኢህአዴግ «ልማታዊ መንግስት» ብሎ አወጀ። ኦሮሞ፤ አማራ፤ ትግሬ፤ ሲዳማ ወዘተ ብሄር ብሄረሰቦች አንድ መሆን ባይችሉም በ«ልማት» ዙርያ አንድነት ይፈጥራሉ ወይንም ግጭት ይቀንሳሉ ተብሎ ነው «ልማት» የታወጀው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/10/ethnic-federalism-kills-meles.html)። የዚህ የልማት ዘመቻ ደግሞ ታላቁ መሪ መለስ ዜናዊ ነው ተብሎ የሳቸው ምስሎች ከነ ልማት ምስሎች ጋር በማርክሲስት አይነት ስዕሎች በየቦታው ተለጠፉ።
ልማቱ መጣ ኤኮኖሚው በፍጥነት አደገ። ግን ህዝቡ ይበልጥ ተከፋፈለ። ግጭቶች እየጨመሩ እየጠነከሩ ሄደ። ሰላም እና ፍቅር እየጠፋ ሄደ። የግብረ ገብ እጦቱ በአስፈሪ መልክ በዛ አገሩን አጠለቀለቀ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/08/blog-post_31.html)። «ልማት» ወደ «ገንዘብ» ተተርጉሞ ለገንዘብ ብለን እናታችንን የምንሸጥ ስባዊነት-ቢስ ማህበረሰብ ሆንን። ይበልጥ ተከፋፈልን። «ልማት» የሚለው መፈከር አልሰራም።
ግን አሁንም ስለ «ልማት» እንሰማለን። «ለምን አንድ ሆነን ተፋቅረን ሁላችንም ወደ ልማት አንሄድም?» ይባላል። «ሀገራችንን በጋራ እናሳድጋት» ሲባል እንሰማለን። «አንድ ከሆነን ሀገራችን እንደ ሌሎች ሀገራት ትበለጽጋለች!» ይባላል።
አዎን ልማት እና እድገት አይከፋም። ግን ልማት ሀገር እና ህዝብ አያደርግም ወደፊትም ሊያደርግ አይችልም። ሀገር እና ህዝብ የሚያደርገን «ፍቅር» እና «ሰላም»፤ «እውነተኛ ዝምድና እና ትሥስር»፤ «መደጋገፍ» እና «መረዳዳት»፤ «አባቶችንና ተውፊትን በጋራ ማክበር» ወዘተ። እነዚህ ጊዜያዊ ሳይሆኑ ዘላቂያዊ ነገሮች ናቸው። ልክ እንደ ሃብት ቤተሰብን እንደማይፈጥር እንደማይገነባ ሀገርንም አይፈጥርም አይገነባም።
ይህን ስለተረዱ ነው ጠ/ሚ አብይ አህመድን ታላቅ የሚያረጋቸው። የሳቸው ትኩረት በጊዜያዊ አላፊ ትናንሽ ነገሮች ሳይሆን በከፍ ያሉት (higher) ነገሮች ነው። ህዝባችን ከልማት በላይ ደስታ እንዲኖረው ነው የምፈልገው ብለዋል። ይህ ደግሞ ለኢትዮጵያው ትውፊታዊ አመለካከት ነው። ኢትዮጵያዊ ከገንዘብ፤ ምቾት፤ ሃባት ወዘተ ይልቅ ፍቅር፤ ሰላም፤ ፍትህ ወዘተን ያስቀድማል በሃይማኖትን እና ትውፊቱ ምክንያት። ለዚህም ነው የጠ/ሚ አብይ መልዕክት ምዕራቢያዊያንን በሚያስገርም ሁኔታ ህዝባችንን ያስደሰተው።
ስለዚህ የኛ መሪዎች እና ፖለቲከኞች እንዲሁም እኛ ብዙሃን «ልማት» የሚለውን ጽንሰ ሃሳብ ላሁን ብንተወው እና ትክክለኛ ቦታው ብንሰጠው ጥሩ ይመስለኛል። ፍቅር እና ሰላማችንን እናዳብር። ክፍፍሎቻችንን በግልጽ እና በትህትና እንወያይ። ይቅርታ እንባባል እርስ በርሳችን እንቆርቆር። ሀገርን እንገንባ። እዚህ ላይ እናተኩር። ከዛ በኋላ ልማት እንደ ሁለተኛ ምርት (byproduct) ይመጣል። ባይፈጥንም ፍቅራችን ያኖረናል።
ለማስታወስ ያህል የተወሰነ ዓመት በፊት ህዝብን የምርጫ 1997 ችግርን ለማስረሳት፤ «ጠባብ» የጎሳ ብሄርተኝነትን ለመዋጋት፤ መንግስትን ሊጥል የሚችል መሃበረሰባዊ ክፍፍልን ለማስወገድ ኢህአዴግ «ልማታዊ መንግስት» ብሎ አወጀ። ኦሮሞ፤ አማራ፤ ትግሬ፤ ሲዳማ ወዘተ ብሄር ብሄረሰቦች አንድ መሆን ባይችሉም በ«ልማት» ዙርያ አንድነት ይፈጥራሉ ወይንም ግጭት ይቀንሳሉ ተብሎ ነው «ልማት» የታወጀው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2016/10/ethnic-federalism-kills-meles.html)። የዚህ የልማት ዘመቻ ደግሞ ታላቁ መሪ መለስ ዜናዊ ነው ተብሎ የሳቸው ምስሎች ከነ ልማት ምስሎች ጋር በማርክሲስት አይነት ስዕሎች በየቦታው ተለጠፉ።
ልማቱ መጣ ኤኮኖሚው በፍጥነት አደገ። ግን ህዝቡ ይበልጥ ተከፋፈለ። ግጭቶች እየጨመሩ እየጠነከሩ ሄደ። ሰላም እና ፍቅር እየጠፋ ሄደ። የግብረ ገብ እጦቱ በአስፈሪ መልክ በዛ አገሩን አጠለቀለቀ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/08/blog-post_31.html)። «ልማት» ወደ «ገንዘብ» ተተርጉሞ ለገንዘብ ብለን እናታችንን የምንሸጥ ስባዊነት-ቢስ ማህበረሰብ ሆንን። ይበልጥ ተከፋፈልን። «ልማት» የሚለው መፈከር አልሰራም።
ግን አሁንም ስለ «ልማት» እንሰማለን። «ለምን አንድ ሆነን ተፋቅረን ሁላችንም ወደ ልማት አንሄድም?» ይባላል። «ሀገራችንን በጋራ እናሳድጋት» ሲባል እንሰማለን። «አንድ ከሆነን ሀገራችን እንደ ሌሎች ሀገራት ትበለጽጋለች!» ይባላል።
አዎን ልማት እና እድገት አይከፋም። ግን ልማት ሀገር እና ህዝብ አያደርግም ወደፊትም ሊያደርግ አይችልም። ሀገር እና ህዝብ የሚያደርገን «ፍቅር» እና «ሰላም»፤ «እውነተኛ ዝምድና እና ትሥስር»፤ «መደጋገፍ» እና «መረዳዳት»፤ «አባቶችንና ተውፊትን በጋራ ማክበር» ወዘተ። እነዚህ ጊዜያዊ ሳይሆኑ ዘላቂያዊ ነገሮች ናቸው። ልክ እንደ ሃብት ቤተሰብን እንደማይፈጥር እንደማይገነባ ሀገርንም አይፈጥርም አይገነባም።
ይህን ስለተረዱ ነው ጠ/ሚ አብይ አህመድን ታላቅ የሚያረጋቸው። የሳቸው ትኩረት በጊዜያዊ አላፊ ትናንሽ ነገሮች ሳይሆን በከፍ ያሉት (higher) ነገሮች ነው። ህዝባችን ከልማት በላይ ደስታ እንዲኖረው ነው የምፈልገው ብለዋል። ይህ ደግሞ ለኢትዮጵያው ትውፊታዊ አመለካከት ነው። ኢትዮጵያዊ ከገንዘብ፤ ምቾት፤ ሃባት ወዘተ ይልቅ ፍቅር፤ ሰላም፤ ፍትህ ወዘተን ያስቀድማል በሃይማኖትን እና ትውፊቱ ምክንያት። ለዚህም ነው የጠ/ሚ አብይ መልዕክት ምዕራቢያዊያንን በሚያስገርም ሁኔታ ህዝባችንን ያስደሰተው።
ስለዚህ የኛ መሪዎች እና ፖለቲከኞች እንዲሁም እኛ ብዙሃን «ልማት» የሚለውን ጽንሰ ሃሳብ ላሁን ብንተወው እና ትክክለኛ ቦታው ብንሰጠው ጥሩ ይመስለኛል። ፍቅር እና ሰላማችንን እናዳብር። ክፍፍሎቻችንን በግልጽ እና በትህትና እንወያይ። ይቅርታ እንባባል እርስ በርሳችን እንቆርቆር። ሀገርን እንገንባ። እዚህ ላይ እናተኩር። ከዛ በኋላ ልማት እንደ ሁለተኛ ምርት (byproduct) ይመጣል። ባይፈጥንም ፍቅራችን ያኖረናል።
Friday, 31 August 2018
የቻይና ገብረ ገብ እጦት፤ ትምሕርች ለኢትዮጵያ
የሰው ልጅ ከወደቀ ጀምሮ የግብረ ገብ ጉድለት እንዳለው ነው። በማህበረሰብ ደረጃ የግብረ ገብ እጦት ጎልቶ የሚታይበት ደግሞ ደበቅ የሚልበት ሁኔታዎች እና ወቅቶች አሉ።
ብዙዎቻችን በኢህአዴግ አገዛዝ ዘመን በሀገራችን ታልቅ የግብረ ገብ እጦት እየታየ ነው እንላለን። ለማ መገርሳም አብይ አህመድም ይህን ጉዳይ በተደጋጋሚ ያነሱታል። ባለ ስልጣን ይጨቁናል እና ይሰርቃል፤ የመንግስት ስራተኛ ጉቦ ይጠይቃል፤ ብዙሃኑ ያጭበረብራል፤ ስርቆት፤ ግድያ፤ ማጭበርበር፤ ለሰው ግድ ዬለሽነት፤ ዝሙት፤ ርክሰት፤ ሌብነት ወዘተ። ሁላችንም ሰምተነዋል አይተነዋልም።
መፍትሄውን ለማግኘት ለምን ይህ ሆነ ብለን መጠየቅ አለብን። ስንጠይቅ በቅርብ ያረፉት ታዋቂ የቻይና የፖለቲካ ተንታኝ እና እስረኛ ሊዩ ሺያዎቦ ጥሩ መልስ ይሰጡናል። የቻይና እና የኢትዮጵያ የፖለቲካ አገዛዝ እና በማሀበረሰቡ ላይ ያሳደረው ጫና በተወሰነ ደረጃ ተመሳሳይነት አላቸው።
በቻይና አንድ አውራ ፓርቲ በሙሉ ስልጣን ይገዛል። የማይፈልጋቸውን ያስራል ይገላል (በአመት ወደ 2,000 ሰዎች በይፋ በሞት ፍርድ ይገደላሉ)። ማንም ሰው መማር ማደግ ወይንም ስልጣን መያዝ ከፈለገ ከገዥ ፓርቲው ጋር ጥሩ ወይም ቢያንሽ መልካም ግንኙነት ሊኖረው ይገባል። ከፓርቲው ጋር ጥሩ ግንኙነት ያላቸው ከሌላው ሀብረተሰብ ሃብታም እና ባለ ስልጣን ይሆናሉ። ይህ ሃብት እና ስልጣን በስራ እና እውቀት የተገኘ ሳይሆን ከፓርቲ አባል እና መሪዎች ጋር በመሻረክ ነው የሚመጣው። በዚህ ምክንያት በርካታው የሀገሪቷ ሃብት በጥቂት ሰዎች የተቆጣጠረ ነው።
እንዲሁም ሆኖ የቻይና ኮምዩኒስት ፓርቲ ህዝቡ ከስልጣን በአመጽ እንዳያወርደው ብሎ ኤኮኖሚው የገበያ ኤኮኖሚ እንዲሆን እና በፍጥነት እንዲያድግ አድርጓል። ለብዙ ዓመት ኤኮኖሚው በየአመቱ ከ10% በላይ ነው እድገቱ። በርካታ ስዎች በፍጥነት ሃብታም ሆነዋል። መካከለኛ መደቡም አድጓል። ግን የእድገት ፍጥነቱ በሃብታም እና ድሃ ያለውን ልዩነት በጣም አስፍቶ ከዓለም አንደኛ አድርጎታል (30 ዓመት በፊት በእውነተኛ ኮምዩኒዝም ዘመን እኩልነቱ በዓለም አንደኛ ነበር)። ግን ብዙ ሰው ማደግ የሚችለው ሃብት ማከማቸት የሚችለው አጭበርብሮ፤ ጉቦ ከፍሎ ወይንም ወስዶ ወይንም በተለያየ መንገድ ህግን ጥሶ ወይን ስነ መግባርን ጥሶ ነው።
በአጭሩ የቻይና መንግስት ከህዝቡ ጋር ያለው ስምምነት እንዲህ ነው፤ በፖለቲካ እና ስልጣናችን አትምጡ ከመጣችሁ እናጠፋችኋለን፤ ግን እንደፈለጋችሁ ሃብታም ሁኑ ከፈለጋችሁ ከኛ ጋር ተሻረኩ እና ስረቁ። የቻይና «ልማታዊ መንግስት» እና «አውራ ፓርቲ» አገዛዝ ርዕዮእተ ዓለም እንዲህ ነው። በህወሓት ዘመን የነበረውን በተለይ ከምርጫ 97 ወዲህ የነበረውን አገዛዝ ሊያስታውሳችሁ ይገባል። አንድ ነው።
ወደ የቻይና የፖለቲካ ተንታኙ ሊዩ ሺያዎቦ እንመለስ። ሊዩ ይህንን ልማታዊ መንግስት ሲተቹ ይህ ስርአት የሚያመጣውን የስነ መግባር እጦትን በደምብ ተንትነዋል (https://www.nybooks.com/articles/2012/02/09/liu-xiaobo-he-told-truth-about-chinas-tyranny/)። ከዚህ ጽሁፍ የተወሰነውን ተርጉሜ ከታች አቀርባለሁ…
ኅብረተሰብን በመቀየር አገዛዙን እንቀይር» በሚል ጽሁፉ ሊዩ ሺያዎቦ ለቻይና ያሉትን ተስፋዎቹን ዘርዝሯል። የፖለቲካ አንባገነንነቱ ቢቀጥልም ህዝቡ ድንቁርናውን እና መከፋፈሉን ያሸንፋል። ህዝቡ ያለውን ኢፍትሃዊ አሰራር ለመታገል አስፈላጊ የሆነውን ህብረት ይረዳል እና መተባበርን ይጀምራል። ህዝቡ አይን ያወጣ ሙስናውን እና ሹማምንቱ የሚሰራውን አድሎአዊ ስራዎችን አብሮ በህብረት እንደሚቃውም ተረድቷል። ማህበራዊ ጥንካሬ እና ስለ ህዝብ መብት ማወቅ ይስፋፋል። ዜጎች የኢኮኖሚያዊ ነፃነት ሲያገኙ መረጃ ለማግኘት እና ለመቀያየር ይቀላቸዋል።
ህዝቡ በቀላሉ መንግስት መቆጣጠር በማይችልበት መንገድ ሃሳብ እንዲቀያየር ኢንተርነት ይፈቅዳል ያጎላብታል። የምነግስት የመረጃ አፈናን አቅመ-ቢስ እያደረገ ይሄዳል። የቻይና ህብረተሰብ ነፃ መሆን የሚችለው ህብረተሰቡ ከታች (ከብዙሃኑ) ወደ ላይ ቀስ በቀስ እየተሻሻለ ሲሄድ ነው። ይህ ቀስ በቀስ የህብረተሰብ ለውጥ አገዛዙን በግድ እንዲቀየር ያደርገዋል።
ሊዩ እነዚህን ተስፋዎች እየዘረዘርም በተቃራኒው የቻይና ህብረተሰብ የመንፈሳዊ ድኻነት በአሳዛኝ መልኩ ይገልጻል። መንግስት ህዝብ ታሪክን እንዲረሳ አውጆ ለማስረሳት ትልቅ ስራ እየሰራ ነው። የቲዬንአንሜን ጭፍጨፋ (Tiananmen Massacre) ታሪክ ከአዲሱ ትውልድ አዕምሮ እንዲጠፋ ተደርጓል (ለኢትዮጵያ ተመሳሳዩ ክስተት ምርጫ 97 እና የተከተሉት ጭቆናዎች ናቸው)። የቻይና መንግስት ወጣቱ ይህን ትዝታ እንዲረሳ በጭፍን ብሄርተኝነት ይተከዋል ወጣቱ ያሉትን እውነታዊ ችግሮችን እንዲረሳ (በኢትዮጵያ context መንግስት ወጣቱን በ «ልማት» ፕሮፓጋንዳ ነው የሚሞላው) ነው። ሥን ጽሑፍ፤ መጽሔት፤ ፊልም እና ቪዲዮዎች ሁሉ በዝሙት እና ሁከት (violence) የተሞሉ ናቸው «የህብረተሰባችን የግብረ ገብ በርሃነትን» ያንጸባረቃል።
አንዳንድ የግራ ፖለቲካ አማኞች የዛሬ የቻይና የግብረ ገብ እና መንፈስ እጦትን በገበየ ኤኮኖሚው (market economy) እና ግሎባላይዛሽን (globalization) የመጣ ነው ብለው ያሳብባሉ። እነዚህም ናቸው የቻይናን ግዙፍ የሙስና ችግር ያመጡት ያላሉ። ግን ሊዩ በተቃራኒው የዛሬው ተስፋ መቁረጥ፤ ጥርጣሬ፤ እምነት ማጣት፤ ርክሰት፤ ብልግና እና ጥቅላላ የግብረ ገብ እጦትን በማኦ ዘመን ያሳብባል። የዛ የ«ንፁ» የኮምዩኒዝም ዘመን ነው የሀገሪቷን መንፈስ የዘረራት ይላል። ያ መንግስት፤
ብዙዎቻችን በኢህአዴግ አገዛዝ ዘመን በሀገራችን ታልቅ የግብረ ገብ እጦት እየታየ ነው እንላለን። ለማ መገርሳም አብይ አህመድም ይህን ጉዳይ በተደጋጋሚ ያነሱታል። ባለ ስልጣን ይጨቁናል እና ይሰርቃል፤ የመንግስት ስራተኛ ጉቦ ይጠይቃል፤ ብዙሃኑ ያጭበረብራል፤ ስርቆት፤ ግድያ፤ ማጭበርበር፤ ለሰው ግድ ዬለሽነት፤ ዝሙት፤ ርክሰት፤ ሌብነት ወዘተ። ሁላችንም ሰምተነዋል አይተነዋልም።
መፍትሄውን ለማግኘት ለምን ይህ ሆነ ብለን መጠየቅ አለብን። ስንጠይቅ በቅርብ ያረፉት ታዋቂ የቻይና የፖለቲካ ተንታኝ እና እስረኛ ሊዩ ሺያዎቦ ጥሩ መልስ ይሰጡናል። የቻይና እና የኢትዮጵያ የፖለቲካ አገዛዝ እና በማሀበረሰቡ ላይ ያሳደረው ጫና በተወሰነ ደረጃ ተመሳሳይነት አላቸው።
በቻይና አንድ አውራ ፓርቲ በሙሉ ስልጣን ይገዛል። የማይፈልጋቸውን ያስራል ይገላል (በአመት ወደ 2,000 ሰዎች በይፋ በሞት ፍርድ ይገደላሉ)። ማንም ሰው መማር ማደግ ወይንም ስልጣን መያዝ ከፈለገ ከገዥ ፓርቲው ጋር ጥሩ ወይም ቢያንሽ መልካም ግንኙነት ሊኖረው ይገባል። ከፓርቲው ጋር ጥሩ ግንኙነት ያላቸው ከሌላው ሀብረተሰብ ሃብታም እና ባለ ስልጣን ይሆናሉ። ይህ ሃብት እና ስልጣን በስራ እና እውቀት የተገኘ ሳይሆን ከፓርቲ አባል እና መሪዎች ጋር በመሻረክ ነው የሚመጣው። በዚህ ምክንያት በርካታው የሀገሪቷ ሃብት በጥቂት ሰዎች የተቆጣጠረ ነው።
እንዲሁም ሆኖ የቻይና ኮምዩኒስት ፓርቲ ህዝቡ ከስልጣን በአመጽ እንዳያወርደው ብሎ ኤኮኖሚው የገበያ ኤኮኖሚ እንዲሆን እና በፍጥነት እንዲያድግ አድርጓል። ለብዙ ዓመት ኤኮኖሚው በየአመቱ ከ10% በላይ ነው እድገቱ። በርካታ ስዎች በፍጥነት ሃብታም ሆነዋል። መካከለኛ መደቡም አድጓል። ግን የእድገት ፍጥነቱ በሃብታም እና ድሃ ያለውን ልዩነት በጣም አስፍቶ ከዓለም አንደኛ አድርጎታል (30 ዓመት በፊት በእውነተኛ ኮምዩኒዝም ዘመን እኩልነቱ በዓለም አንደኛ ነበር)። ግን ብዙ ሰው ማደግ የሚችለው ሃብት ማከማቸት የሚችለው አጭበርብሮ፤ ጉቦ ከፍሎ ወይንም ወስዶ ወይንም በተለያየ መንገድ ህግን ጥሶ ወይን ስነ መግባርን ጥሶ ነው።
በአጭሩ የቻይና መንግስት ከህዝቡ ጋር ያለው ስምምነት እንዲህ ነው፤ በፖለቲካ እና ስልጣናችን አትምጡ ከመጣችሁ እናጠፋችኋለን፤ ግን እንደፈለጋችሁ ሃብታም ሁኑ ከፈለጋችሁ ከኛ ጋር ተሻረኩ እና ስረቁ። የቻይና «ልማታዊ መንግስት» እና «አውራ ፓርቲ» አገዛዝ ርዕዮእተ ዓለም እንዲህ ነው። በህወሓት ዘመን የነበረውን በተለይ ከምርጫ 97 ወዲህ የነበረውን አገዛዝ ሊያስታውሳችሁ ይገባል። አንድ ነው።
ወደ የቻይና የፖለቲካ ተንታኙ ሊዩ ሺያዎቦ እንመለስ። ሊዩ ይህንን ልማታዊ መንግስት ሲተቹ ይህ ስርአት የሚያመጣውን የስነ መግባር እጦትን በደምብ ተንትነዋል (https://www.nybooks.com/articles/2012/02/09/liu-xiaobo-he-told-truth-about-chinas-tyranny/)። ከዚህ ጽሁፍ የተወሰነውን ተርጉሜ ከታች አቀርባለሁ…
ኅብረተሰብን በመቀየር አገዛዙን እንቀይር» በሚል ጽሁፉ ሊዩ ሺያዎቦ ለቻይና ያሉትን ተስፋዎቹን ዘርዝሯል። የፖለቲካ አንባገነንነቱ ቢቀጥልም ህዝቡ ድንቁርናውን እና መከፋፈሉን ያሸንፋል። ህዝቡ ያለውን ኢፍትሃዊ አሰራር ለመታገል አስፈላጊ የሆነውን ህብረት ይረዳል እና መተባበርን ይጀምራል። ህዝቡ አይን ያወጣ ሙስናውን እና ሹማምንቱ የሚሰራውን አድሎአዊ ስራዎችን አብሮ በህብረት እንደሚቃውም ተረድቷል። ማህበራዊ ጥንካሬ እና ስለ ህዝብ መብት ማወቅ ይስፋፋል። ዜጎች የኢኮኖሚያዊ ነፃነት ሲያገኙ መረጃ ለማግኘት እና ለመቀያየር ይቀላቸዋል።
ህዝቡ በቀላሉ መንግስት መቆጣጠር በማይችልበት መንገድ ሃሳብ እንዲቀያየር ኢንተርነት ይፈቅዳል ያጎላብታል። የምነግስት የመረጃ አፈናን አቅመ-ቢስ እያደረገ ይሄዳል። የቻይና ህብረተሰብ ነፃ መሆን የሚችለው ህብረተሰቡ ከታች (ከብዙሃኑ) ወደ ላይ ቀስ በቀስ እየተሻሻለ ሲሄድ ነው። ይህ ቀስ በቀስ የህብረተሰብ ለውጥ አገዛዙን በግድ እንዲቀየር ያደርገዋል።
ሊዩ እነዚህን ተስፋዎች እየዘረዘርም በተቃራኒው የቻይና ህብረተሰብ የመንፈሳዊ ድኻነት በአሳዛኝ መልኩ ይገልጻል። መንግስት ህዝብ ታሪክን እንዲረሳ አውጆ ለማስረሳት ትልቅ ስራ እየሰራ ነው። የቲዬንአንሜን ጭፍጨፋ (Tiananmen Massacre) ታሪክ ከአዲሱ ትውልድ አዕምሮ እንዲጠፋ ተደርጓል (ለኢትዮጵያ ተመሳሳዩ ክስተት ምርጫ 97 እና የተከተሉት ጭቆናዎች ናቸው)። የቻይና መንግስት ወጣቱ ይህን ትዝታ እንዲረሳ በጭፍን ብሄርተኝነት ይተከዋል ወጣቱ ያሉትን እውነታዊ ችግሮችን እንዲረሳ (በኢትዮጵያ context መንግስት ወጣቱን በ «ልማት» ፕሮፓጋንዳ ነው የሚሞላው) ነው። ሥን ጽሑፍ፤ መጽሔት፤ ፊልም እና ቪዲዮዎች ሁሉ በዝሙት እና ሁከት (violence) የተሞሉ ናቸው «የህብረተሰባችን የግብረ ገብ በርሃነትን» ያንጸባረቃል።
«ቻይና የተስፋ መቁረጥ እና ጥርጣሬ ዘመን ውስጥ ገብታለች ማንም በምንም አያምንም… የኮምዩኒስት ፓሪቲ መሪዎቹም አባላቶቹም በራሳቸው ፓርቲ ፕሮፓጋንዳ ማመን ትተዋል። በመርህ፤ ስነ መግባር፤ እምነት መመራት ትተን አሁን በገንዘብ እና አለማዊ ነገር ሆናል «እምነታችን»። የቻይና ኮምዩኒስት ፓርቲ ልክ የለሽ የማያቋርጥ ፕሮፓጋንዳ ትዝታ እና ታሪክ የለለው ትውልዶች ፈጥሯል…አንዳንድ ምዕራባዊ ሊበራሎች የማኦ ጥብቅ ዘመን ሲፈርስ የዝሙት ነፃነት ይመጣ እና እንደ ቦምብ የህብረተሰባዊ እና ፖለቲካዊ ነፃነት ያመጣል ብለው ይገምቱ ነበር። አሁን ግን ሊዩ እንደሚለው የ«ዝሙት ፌሽታ» ሀገሪቷን አጥለቅልቆታል። ሀገሪቷን በዝሙት፤ ሁከት እና ስግብግብነት ሞልቶታል። ህብረተሰቡ በረዥም ዓመታት ጭቆና እና ውሸት ፕሮፓጋንዳ ምክንያት የግብረ ገቡን ማጣት ነው ይህ ሁሉ የሚያሳየው። «ድሮ ለፖለቲካዊ አብዮት ያበደው ዛሬ ለገንዘብ እና ዝሙት አብዷል» ይላል ሊዩ።
በደህና የኑሮ ሁነታ ያደገው ከ«ቲዬንአንሜን» ቀጥሎ የተወለደው ትውልድ አሁን እንደ አላማ ያለው የመንግስት ሹም መሆን (አስፋው፤ በጉቦ ሃብታም ለመሆን)፤ ሃብታም መሆን ወይንም ውጭ ሃገር መሄድ… ስለ ታሪካዊ ስቃዮች መስማት አይፈልጉም ትዕግስቱ የላቸውም… «ታላቁ እርምጃ» (ወደ 40 ሚሊዮን የሞቱበት ማኦ የፈጠረው ርሃብ "The Great Leap Forward")፤ «ባህላዊ አብዮት» (አንዱ የቻይና ቀይ ሽብር "Cultural Revolution")፤ የቲዬንአንሜን ጭፍጨፋ። ለአዲሱ ትውልድ እነዚህን የመንግስት ጥፋቶች ማንሳት እና የህብረተሰባችን «ጭለማ ወገን» ማሳየት አስፈላጊ አይደለም። የራሳቸውን የሞልቃቃ አኗኗር እና የመንግስትን ፕሮፓጋንዳ ተጠቅመው ቻይና ታላቅ ተራምዳለች ማለት ይሻላቸዋል።»
አንዳንድ የግራ ፖለቲካ አማኞች የዛሬ የቻይና የግብረ ገብ እና መንፈስ እጦትን በገበየ ኤኮኖሚው (market economy) እና ግሎባላይዛሽን (globalization) የመጣ ነው ብለው ያሳብባሉ። እነዚህም ናቸው የቻይናን ግዙፍ የሙስና ችግር ያመጡት ያላሉ። ግን ሊዩ በተቃራኒው የዛሬው ተስፋ መቁረጥ፤ ጥርጣሬ፤ እምነት ማጣት፤ ርክሰት፤ ብልግና እና ጥቅላላ የግብረ ገብ እጦትን በማኦ ዘመን ያሳብባል። የዛ የ«ንፁ» የኮምዩኒዝም ዘመን ነው የሀገሪቷን መንፈስ የዘረራት ይላል። ያ መንግስት፤
«ኢ-ሰባዊ እና ገብረ ገብ የሌለው ነበር። የማኦ አምባገነናዊ መንግስት ሰዎችን መንፈሳቸውን እንዲሸጡ ሰውነታቸውን እንዲከዱ አድርጓል። ባለቤትን መጥላት፤ አባትን ማውገዝ፤ ጓደኛን መካድ፤ ተጎጂን ይበልጥ ምጉዳት፤ ጥሩ ኮምዩኒስት ለመባል ማንኛውም ነበር ማለት። ልክ እና ገደብ ያልነበረው አለማቆም ጨፍላቂ የሆነው የማኦ የፖለቲካ እርምጃዎች መሰረታዊ የሆኑትን የቻይና ህዝብ ስነ መግባሮችን አጠፋ።»ከማኦ በኋላ ይህ አካሄድ ቢቀንስም አለ። ከቲዬንአንሜን ጭፍጨፋ በኋላ መንግስት ህዝቡ እንዲረሳው ጣላቅ ፕሮፓጋንዳ እና ሽብር አራመደ (አስፋው፤ ልክ እንደ ኢህአዴግ ከምርጫ 97 በኋላ እንዳረገው ሰውው ትዝታ እንዳይኖረው ስለ «ልማት» ብቻ እንዲያስብ)። ህዝቡ ህሊናውን ክዶ ለምንግስት ተገዢነቱን እንዲያሳይ ተገደደ። «ቻይና ህዝቧ ለህሊናው የሚዋሽ ሀገር ከሆነች በምን ተዓምር ነው ጤናማ ግብረ ገብ ያለው ህብረተሰብ መገንባት የሚቻለው?» ሊዩ ይቺን ምዕራፍ እንደዚህ ደመደመው፤
«ቻይናን ያረከሳት ዛሬ የምናየው በሀገሪቷ ዙርያ የሰፈነው የግብረ ገብ እጦት ምንጩ የማኦ ኢ-ሰባዊ ዘመን ነው። በዚህ ዘመን የዝሙት ማሳደድ ዘመቻ ለአምባገናናዊ ስረዓቱ እጅግ ይጠቅመዋል። ህዝቡ በልማት እየተጠቀመ ቢሆንም ወደ ፖለቲካ እንዳያስብ ያደርገዋል። የዝሙት «ነፃነት» ዴሞክራሲን ከማምጣት ይልቅ የድሮ የመሳፍንቶቻን የዝሙት ጥንቅን ነው የሚመልሰው… ይህ የዛሬዎቹን አምባገነኖችን በጣም ይመቻቸዋል። ከዘመናት ግብዝነት ያመጣውን ገብረ ገብ መበስበስ እና የፖለቲካ ጭቁና ጋር አብሮ ይሄዳል። ህዝቡ የፖለቲካ ነፃነት ከመጠየቅ በርክሰት እንዲጨማለቅ ያረገዋል።»በሌላ ጽሁፍ ይህ እንዴት ኢትዮጵያን እንዲሚመለከት እወያያለሁ።
Labels:
China,
Liu Xiaobo,
morality,
responsibility,
ሊዩ ሺያውቦ,
ሙስና,
ስነ መግባር,
ቻይና,
አምባገነንነት,
ወንጀል,
ዝሙት,
ጉቦ,
ግብረ ገብ,
ግድዬለሽነት
Subscribe to:
Posts (Atom)