Showing posts with label wisdom. Show all posts
Showing posts with label wisdom. Show all posts

Wednesday, 30 June 2021

የቶክስ ማቆም ውሳኔውና የጎሳ ብሔርተኝነት አደጋ

ስሜታዊና በፖለቲካ ያልበሰልን ስለሆንን የትግራይ ህዝብ ከህወሓት ጋር ወግኗል እንላለን። ይህ አመለካከት እጅግ simplistic ነው። በሕብረ ብሔሪዊ ሀገራት የህዝቡ ታማኝነት ከፊል ለሀገሩ ከፍል ለጎሳው/ብሔሩ ነው። ሀገሪቷ ጤናማ (ሰላማዊ) የምትሆነው የህዝቡ ታማኝነት ከጎሳው ይልቅ ወደ ሀገሩ ቢያደላ ነው። ለምን ሲባል የሀገርና የጎሳ ፍላጎትና ጥቅም አልፎ አልፎ ሊለያዩ ይችላሉ። ጎበዝ ፖለቲካኞች ካሉ እነዚህን ልዩነቶች የሳንሳሉና ወደ ሁሉንም የሚጠቅም መንገድ ያመራሉ። ምንም ቢጥሩ ግን አለመስማማት አይቀርም። ስለዚህ ህዝቡ ከጎሳው ይልቅ ሀገሩን የሚያስቀድም ከሆነ፤ ማለት የጎሳ ብሔርተኝነት ስሜት እናሳ ከሆነ፤ በጎሰና በሀገር ያሉት ልዩነቶች በቀላሉ ይፋታሉ። ካልሆነ ግን ሀገሪቷ የግጭት ስፍራ ትሆናለች።

አሁን በትግራይ የምናየው ይህ ነው። ለ57 አመት ለትገራይ ህዝብ የተሰበክለት የጎሳ ብሔርተኝነት ዋጋ እያስከፈለ ነው። ከ 57 አመት በፊት የትግራይ ህዝብ የጎሳ ብሔርተኝነት ስሜት አልነበረውም ማለት አይደለም። ግን ስሜቱ በየጊዜው እየጨመረ ሄደና አሁን ከመጠን በላይ ትግራዊ ጎሳውን ከሀገሩ በደምብ የስቀድማል።

የጎስንነት ስሜት ተቀያያሪ ነው። 69 ዓመት በፊት ኤርትራዊያን ከኢትዮጵያ ጋር እንቀላቀል አሉ። 41 ዓመት በሗላ ከ90% በላይ እንገንጠል አሉ! ፖለቲካ፤ ኤኮኖሚ፤ ግጭት ወዘተ የሰውን ስሜት ይቀይራል። የጎስኝነት ስሜቹን መመለሱ ቀላል አይደለም። ብዙ ጊዜ አይቻልም። 

ሰባት ወር በፊት መንግስት አብዛኛው የትግራይ ህዝብ ልብ የት እንደሆነ መገመት ብቻ ነበር የሚችለው። የጎሳ ብሔርተኝነት ስሜቱ ምን ደረጃ ላይ ነው? ሰላም፤ ፍትህና የኤኮኖሚ እርዳታ ከሰጠነው የሀገሩ ስሜት ከጎሰኝነቱ እንዲያይል ማድረግ ይቻላል ወይ? መሞከሩ ነው የሚያዋጣው ብሎ ወስነ መንግስት። ሞክረና አልቻለም። ወደ ሁለተኛው አማራጭ ዞረ። ብዙ ሰዎች፣ ቤተሰቦች፣ መንዶሮች ዋጋ ይከፈላሉ ልክ እንደ የኤርትራ መገንጠል።

በዚህ ምክንያት በሕብረ ብሔራዊ ሀገራት የጎሳ ብሔርተኝነት እንዳይበዛ መንግስት ሁልጊዜ መጠንቀቅ አለበት። ያለውን የገንዘብ፣ የፖሊሲ፣ የኃይል አቅም በሙሉ ተጠቅም የጎሳ ስሜትና ፍላጎት እንዲከበርና ሀገራዊነት እዲያይል መደረግ አለበት።

Tuesday, 12 March 2019

የሰከነ አስተያየት ስለ ዓቢይ እና ኦዴፓ

ስሜታዊ መሆን አይበጅም... ይህን የፍፁም ፈቃዱ ትክክለኛ ትንታኔ ያንብቡ።

(https://www.facebook.com/fitsum.fikadu.96/posts/2138544319567816)

ቁምነገሩ ጦርነቱን ማሸነፍ ነው

በቅድምያ በአደጋው ለተጎዳነው ሁሉ ፈጣሪ መፅናናት ይሁነን እላለሁ።አዎ እርሱው ፈጣሪ ኢትዮጵያዬን እንዲህ ካለው ሃዘን ሁሌም ይጠብቅልን እያልኩ በሰሞኑ የፖለቲካችን ፈተና ዙሪያ እንዲህ እንደሚከተለው ልል ወድጃለሁ።

የዶ/ር አብይ ቡድን ማለቴ ቲም ለማ ሃገርን አንድ ለማድረግ ከፍተኛ ትግልና ውጥረት ውስጥ ሆኖ ይታየኛል።ጁሃር (ኦነግ፣ ቄሮ) እነርሱን (ማለትም ቲም ለማን) ከኦሮሞ ህዝብ ጋር ለማጣላት ጠንክሮ እየሰራ መሆኑን አምናለሁ። እነርሱም ይህ ስለገባቸው ህውሃትን ቀስ በቀስ ድባቅ የመቱበትን ያንኑ የተለመደ ለዘብተኛ የሚመስል ግን ውስጠ ወይራ አካሄዳቸውን እየተገበሩበት ይገኛሉ። እነዚህ ብልህ መሪዎች መሬት እስከሚይዙ ድረስ ለህውሃት ተገዢና ተልመጥማጭ መስለው እንዴት አዘናግተው በጡረታ ስም ገሸሽ በማድረግ ከዚያም ጊዜ ጠብቀው እነዛኑ አይነኬ መሣይ የህውሃት መሪዎች ወደ ማሰር ውስጥ እንደገቡ ሳስብ፤ ይሄ በስሜት የሚነዳው ህዝባችን በሚፈልገው ፍጥነት ባለመሄድ ውስጥ ውጤት እንዳለ ያሳዩኛል።የእነዚህ ሰዎች አካሄድ ልክ እንደ ሺቭ ኬራ አባባል ዓይነት ነው።ማለትም፦ አሸናፊነት ማለት እያንዳንዱን የጦር ግንባር ማሸነፍ ማለት ሳይሆን ጦርነቱን ማሸነፍ ማለት ነውና።

ጁሃር በዚህም በእዛም ብሎ፤ "እኛ ከየኦሮሞ ህዝብ ጥቅምና አጀንዳ ይልቅ የምናስቀድመው የኢትዮጵያ ህዝብን አጀንዳና ጥቅም ነው" ብለው ዛሬውኑ በአደባባይ እንዲናገሩ ለማድረግ ያልወጋጋቸው ቦታ የለም። ም/ቱም ለእርሱ እንዲህ ማስባል ማለት እነርሱን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እስካሁንም በጥርጣሬ እያያቸው ካለው ከቄሮና ፅንፈኛ የኦሮሞ ብሄርተኞች ጋር ሙሉ ለሙሉ ማቆራረጥ እናም ቦታቸውን (ምርጫ ባስፈለገ ጊዜም ሆነ በአዘቦቱ ጊዜ) በኦነግ ማስቀማት ብሎም የእራሱን ርካሽ ተወዳጅነት በአክራሪ ኦሮሞ ብሄርተኞቹ መካከል ያለስጋት ማስፈን መሆኑን ስለሚያውቀው ነው።በከፍተኛ ፈተናና ጫና ውስጥ ያሉት ኢትዮጵያውያኑ ብልሆቹ መሪዎች ግን ገብቷቸዋልና፤ ቪዥናቸውን ከዳር ማድረስ እንዳለባቸው ስለሚያውቁ መረጋጋት ያለበትን በማረጋጋትና ባላንስ በመስራት ስራ ላይ ናቸው።

ኢትዮጵያውያኑ መሪዎች አዲስ አበባን ለኢትዮጵያውያን ሁሉ ብቻ በእኩል እንድትሆን እንደሚመኙ ግልፅ ማሳያው እኮ፤ መጀመሪያውኑ የኮንዶሚኒየም ዕጣ ማውጣታቸው ነው።ከዚህ በተጨማሪም አገር ሰላም ብሎ የኮንዶሚኒየም እጣ ያወጣው ደግሞ የኦዴፓ አባላቸው ማለትም ታከለ ሆኖ ሳለ ወዲያውኑ የጁሃር ጫጫታ ወደ ደም ማፋሰስ ሊሻገር መሆኑ ሲገባቸው፤ ፅንፈኞቹን ለማረጋጋትና የኦሮሞን ህዝብ ለማሳመኛ የሚሆናቸውን ጊዜ ለመግዛት የሆነ ዓይነት መግለጫ "በሌላኛው" የኦዴፖ ገፅ አውጥተው ጉዳትን ተከላክለዋል። ዳሩ ግና በስሜት የሚንቀለቀለው የህዝባችን አካል ጠረጠራቸው። እነርሱ ግን ምንተዳቸው፤ ግባቸው የብሄር ፖለቲካን ከኢትዮጵያ ምድር ለመጨረሻ ጊዜ ማጥፋት ነውና፤ ይኸው ውጥናቸው ሲሳካ ለሁሉ ምላሽ ይሆነናል በሚል ተስፋ አሁንም ዋና ስራቸው ላይ ናቸው። አዎ በብሄር ፖለቲካ ሃገራቸውን እንዲህ ቁምስቅሏን በማሳየት እያንገላታት ያለውን ኢህአዴግንም ሆነ ኦዴፓቸውን ፍርስርስ አድርገው በህብረብሄራዊ ፓርቲ መተካት ደግሞ፤ የለዘብተኛ መሳይ አካሄዳቸው የመጨረሻ ግብ በዚያውም የጁሃርም ሆነ የኦነግ አሊያም የወላጃቸው የህውሃት ወይም ደግሞ የሌሎች ዘረኛ መሰሎቻቸው ሁሉ ሃሳቦች ግብአተ መሬት እንዲሁም የኢትዮጵያዬ ትንሳዔ መሆኑ ገብቷቸዋልና፤ ለስኬቱ ትግልና ጫና ውስጥ ናቸው። እኛስ የት ነን?

Tuesday, 23 October 2018

ብስለት የሞላው ውይይት

ይህንን ውይይት ጠንቅቃችሁ አዳምጡት ብዬ እለምናለሁ።

https://www.youtube.com/watch?v=PY9RFsmu_ks

የተነሱት ዋና ዋና ነጥቦች፤

1.ዛሬ ያለንበት ፓለቲካዊ እና ማህበረሰባዊ ሁኔታ እና ችግሮች 27 ወይን 44 ወይን 50 ዓመት የፈጠረው አይደለም። ከዛ በፊት ያለን የረዥም ዓመታት ታሪክም አስተዋጾ ያለው ነው። ይህን አውቀን ነው ወደ እውነት እና ትክክለኛ መፍትሄ ምድረስ የሚቻለው።

2. ራስን መመርመር ግድ ነው። ችግሮቻችን በመንግስት እና በፖለቲከኞች ምክንያት ነው የመጣው ማለት ልክ አይደለም። እውነት አይደለም። ሁሉም ዜጋ በራሱ በኩል ሚና ተጫውቷል እና ላለፈውም ለወደፊቱም ሃላፊነት መውሰድ አለበት።

3. ፖለቲካ አንድ የማህበረሰባዊ ኑሮ ክፍል ነው። በመሆኑ ሁሉ ዜጋ በአቅሙ እና በአግባቡ መሳተፍ አለበት። እናት እንደ እናት፤ አባት እንደ አባት፤ ልጅ እንደ ልጅ፤ ሃይማኖት መሪ እንደ ሃይማኖት መሪ፤ ምሁር እንደ ምሁር፤ ሰራተኛ እንደ ሰራተኛ ወዘተ።

4. የግብረ ገብ እጦት ታላቅ ችግር ነው እና ሊሰራበት ይገባል። እንደማንኛውም ችግር ይህ ችግር የሚፈታው መጀመርያ አመጣጡ፤ ምክንያቱ እና ምንጩ ሲታወቁ እና ሲታመኑ ነው።

5. ለውጥ ማለትም ወደ የተሻለ ፖለቲካ እና ማህበራዊ ሁኔታ መቀየር ጊዜ ይፈጃል። ትዕግስት ይጠይቃል። ምርጫ እና ተመሳሳይ ስርዓቶች አለ ቅድመ ዝግጅት እና የአስተሳሰብ ለውጥ ጎጂ ነው የሚሆኑት።

6. ዛሬ ከሞላ ጎደል የፖለቲካ «ነፃነት» አለ። ቋሱ በኛ በህዝቦቹ ሜዳ ነው ያለው። ችግር ካለ መፍታት የኛ ሃላፊነት ነው። ሃላፊነታችንን እንደ ዜጎች መቀበል ግድ ነው። በሌላ ለምሳሌ በመንግስት ባሳበብ አብቅቷል።