Showing posts with label Christian. Show all posts
Showing posts with label Christian. Show all posts

Friday, 5 July 2019

ዮናታን ፓዦ፤ ኦርቶዶክስ ሰአሊ

ምሁራኖቻችን የዘመኑን የምዕራብ ፍልስፍና ላይ ከማተኮር እንደዚህ አይነቱን ከኢትዮጵያዊነት (ኦርቶዶሽም ሙስሊምም) የሚሄድ አስተሳሰቦችን ቢያዳምጡ ጥሩ ይመስለኛል።


Thursday, 30 May 2019

ለሁሉ ነገር እግዚአብሔርን አመስግኑ!

ታላቅ ትምህርት ከበቅርብ ያረፉት ታላቁ የግሪክ ኦርቶዶክስ አባት አሜሊያኖስ ዘ ሲሞኖፔትራ ገዳም።

http://artoklasia.blogspot.com/2019/05/thank-god-for-everything-that-happens.html

Anthony the Great is a realist. His rules or canons aren't some formula he's found and thrown to us. Each of them has something unique concerning the life of the monk and, if one is broken, everything comes crashing down. He says we have to pray without ceasing but at the same time thank God for everything that happens to us. He uses a coordinating conjunction because these two  things can't be separated, they go together. We thank God for pleasant things, but even more for something else: in life, matters don't always turn out as we would want them to. We pray, for instance, and it seems that God doesn't listen. We ask for our health, and our illness worsens. We ask God to grant us certain things and He gives us nothing. Everything's back to front.

People who don't learn to thank God for everything, especially for adversity, will never advance even an inch beyond where they were when their mothers bore them. They'll make no progress. And, of course, when their mothers bore them, such people were innocent babes, they had a natural sanctity, whereas we have cruelty, and knowledge that makes us guilty. So we have to learn to thank God. When we have bad thoughts, when our brother says something and we feel hatred within us, we must, at that very time, thank God and smile at our brother. Unless we do so, it's impossible to advance a step, because everything will seem perverse to us. And then, in particular, others and our circumstances will cause us to have bad thoughts, temptations, passions and contrariness.

Ceaseless prayer and gratitude to God for all that happens to us are the necessary conditions for a natural life. If people don't thank God for everything, they can't even pray, nor live in the monastic state. People have to be grateful for whatever happens to them in the monastery, whether that comes from their inner world or from the brotherhood, from enemies or from demons. For instance, a monk has bad thoughts which torment him. He shouldn't be worried, but should rejoice and thank God. He should say to the demon: "Get behind me, Satan" and send him on his way, or, if he refuses to leave, the monk should be able to say: "The bed's big enough for the two of us. Sleep with me. Just turn over onto the other side so that I don't have to put up with your foul breath". The demon will then leave like lightning.

Unceasing prayer and gratitude for everything are directly connected to our personal rule. In other words, anyone can perform his rule when he learns to pray ceaselessly. And anyone who performs his rule can have unceasing prayer. If he wants to separate his rule from unceasing prayer, both will come tumbling down. This is basic and we must remember it. Miss your rule for two days and you'll see that you'll forget to say "Glory to you, our God" even once a day. That's a law.

Archim. Aimilianos of Simonopetra, Νηπτική ζωή και Ασκητικοί κανόνες (Neptical life and ascetic rules), Indiktos Eds, Athens 2011, pp. 5-6.

Saturday, 27 April 2019

ክርስቶስ ተነስቷል!



ታላቅ አባታችን ቅዱስ ዮሃንስ አፈወርቅ ወደ 1600 ዓመት በፊት በፋሲካ የሰበከው ታዋቂ ስብከት፤
እርሱ ጽኑ የእግዚአብሔር አፍቃሪ የሆነ
ለቀረበው ያማረ ድግስ በፍሰሀ ይካፈል
እርሱ ታማኝ አገልጋይ የሆነ
ወደ ጌታው ደስታ ይግባ
እርሱ በፆም ራሱን ያደከመ
በድካም ዋጋው አሁን ሃሴት ያድርግ
እርሱ ከመጀመርያው ሰአት ጅምሮ የደከመ
ዛሬ የሚገባውን ይቀበል
እርሱ ከሦስተኛው ሰአት በኋላ የመጣ
ከድግሱ በምስጋና ይካፈል
እርሱ ከስድስተኛው ሰአት በኋላ የመጣ
አይጠራጠር ምንም አያጣምና
እርሱ እስከ ዘጠነኛው ሰአት የዘገየ
አያመንታ ይቅረብ እንጂ
እርሱም በመጨረሻው በአስራሀንደኛው ሰአት የመጣ
ምንም በዘገይም እንኳን አይፍራ
ችር ለጋሽ ጌታው የመጨረሻውን ልክ እንደመጀመርያው ይቀበላልና።
በአስራአንደኛው ሰዓት የመጣውንም ከመጀመሪያው ሰዓት ጅምሮ እንደ ደከመው እኩል ያሳረፋል።
ተግባርን ይቀበላል ምኞትንም ያፀድቃል።
ሁላችሁም ግቡ እንግዲህ፤ ወደ ጌታችን ደስታ
መጀመርያ ሆነ መጨረሻ የመጣችሁ ዋጋችሁን እኩል ተቀበሉ
ሐብታምም ሆነ ደሃ ባንድነት ዘምሩ
እናንተ የፆማችሁም ሆነ ያልፆማችሁ ባንድነት ተደሰቱ
ገበታው ሞልቷል፤ ሁሉም ይብላና ይደሰት
ፍሪዳው ሰብቷል፡ ማንም ሳይጠግብ አይሂድ።
ማንም በድህነቱ አይዘን
ሁሉን አቀፍ መንግስተ ሰማያት ተገልጧልና
ማንም ስለበደሉ አማሮ አያልዝስ
የምህረት ብርሃን ከመቃብር ተነስቷልና
ማንም ሞትን አይፍራ
የመድሀኒዓለም ሞት ነፃ አውጥቶናልና።
ሞትን በሞቱ ድል ነስቷልና
ወደ ሲዖል በመውረዱ ሲዖልን አመሰቃቅሏታል
ሲዖልን በስጋ ነፍስ አጋደደ
ይህንም ነብዩ ኢሳያስ በትንቢቱ እንዲህ ብሎ ተናግሯል፡
ሲዖልም ከምድር በታች ሲያገኝህ በመራራ ነገር ቶሞላ
በመራራ ነገር ተሞላ፤ ባዶ ተደረገና
በመራራ ነገር ተሞላ፤ ተዘበበተበትና
በመራራ ነገር ተሞላ፤ ትወገደና
በመራራ ነገር ተሞላ፤ በሰንሰለት ታሰረና።
ሲዖል ስጋን አገኘሁ ብሎ እግዚአብሔርን አጋጠመው!
ምድርን ተቀበልኩ ብሎ ከገነት ጋር ተፋጠጠ!
ሞት ሆይ መርዝህ የታል?
ሲዖል ሆይ ድልህ የታል?
ክርስቶስ ተነስቷል፤ አንድተስ ሞት ሆይ ተደምሠሃል
ክርስቶስ ተነስቷል፤ ክፉዎችህም ትጥለዋል
ክርስቶስ ተነስቷል፤ መላአክትም ተደስተዋል
ክርስቶስ ተነስቷል፤ ህይወትም ነፃ ወጥቷል
ክርስቶስ ተነስቷል፤ መቃብርም ከሙታን ፀዳ
ክርስቶስ በሞት ለመነሳቱ ላንቀላፉት መባ ሆነ።
ለርሱ ይሁን ሃይል ክብርና ምስጋና ዛሬም ዘውትርም ለዘላላሙ አሜን።

The English version:

If any be a devout lover of God,
  let him partake with gladness from this fair and radiant feast.
If any be a faithful servant,
  let him enter rejoicing into the joy of his Lord.
If any have wearied himself with fasting,
  let him now enjoy his reward.
If any have laboured from the first hour,
  let him receive today his rightful due.
If any have come after the third,
  let him celebrate the feast with thankfulness.
If any have come after the sixth,
  let him not be in doubt, for he will suffer no loss.
If any have delayed until the ninth,
  let him not hesitate but draw near.
If any have arrived only at the eleventh,
  let him not be afraid because he comes so late.
For the Master is generous and accepts the last even as the first.
He gives rest to him who comes at the eleventh hour
  in the same was as him who has laboured from the first.
He accepts the deed, and commends the intention.
Enter then, all of you, into the joy of our Lord.
First and last, receive alike your reward.
Rich and poor, dance together.
You who fasted and you who have not fasted, rejoice together.
The table is fully laden: let all enjoy it.
The calf is fatted: let none go away hungry.
Let none lament his poverty;
  for the universal Kingdom is revealed.
Let none bewail his transgressions;
  for the light of forgiveness has risen from the tomb.
Let none fear death;
  for death of the Saviour has set us free.
He has destroyed death by undergoing death.
He has despoiled hell by descending into hell.
He vexed it even as it tasted of His flesh.
Isaiah foretold this when he cried:
Hell was filled with bitterness when it met Thee face to face below;
  filled with bitterness, for it was brought to nothing;
  filled with bitterness, for it was mocked;
  filled with bitterness, for it was overthrown;
  filled with bitterness, for it was put in chains.
Hell received a body, and encountered God. It received earth, and confronted heaven.
O death, where is your sting?
O hell, where is your victory?
Christ is risen! And you, o death, are annihilated!
Christ is risen! And the evil ones are cast down!
Christ is risen! And the angels rejoice!
Christ is risen! And life is liberated!
Christ is risen! And the tomb is emptied of its dead;
for Christ having risen from the dead,
is become the first-fruits of those who have fallen asleep.
To Him be Glory and Power, now and forever, and from all ages to all ages.
Amen!

Thursday, 7 February 2019

በህዝብ ቆጠራው ላይ የኦርቶዶክስ አማኝ ቁጥር ከታሰበው በታች ቢሆን ምን እንል ይሆን?

በሚመጣው የህዝብ ቆጠራ ላይ የኦርቶዶክስ አማኝ ቁጥር ከታሰበው ወይንም ከሚፈለገው በታች ቢሆን እንደ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ምን እንል ይሆን? ይህን መረጃ / ሰነድ ስናገኝ ምንድነው ማድረግ ያለብን?

በመጀመርያ ደረጃ ንስሃ ነው መግባት ያለብን። የኦርቶዶክስ አማኝ ቁጥር ከመነመነ ዋናው ጥፋት የኛ የኦርቶዶክስ ምዕመናን ስለሆነ። እምነታችን፤ ክርስቶስም፤ የሃይማኖት አባቶችም አስረግጠው ይነግሩናል፤ እኛ ጥሩ ክርስቲያኖች ከሆንን እንደ ብርሃን ሌሎችን ወደ ብርሃን፤ ወደ ቃሉ፤ ወደ ክርስቶስ እናመጣለን። በአንጻሩ ጥሩ ክርስቲያኖች ካልሆንን፤ ጭለማዎች ከሆንን፤ ሌሎችን ወደ ክርስትና እንዳይመጡ እናደርጋለን። አልፎ ተርፎ ከኛም ያሉትን እንዲወጡ እናደርጋለን።

ይህን እውነት በአጭሩ ለመግለጽ የሩሲያዊው ቅዱስ ሴራፊም (ሱራፌል) ዘ-ሳሮቭ  እንዲህ ብለዋል፤

«መንፈስ ቅዱስ እንዲያድርባችሁ ከፈቀዳችሁ ዙርያችሁ ያሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ይድናሉ።»

በዚህ ጉዳይ ላይ ለተጨማሪ ማብራርያ ይህን የታወቁት የቆጵሮስ (ሊማሱ ከተማ) ጳጳስ አታናሲዮስ ቃለ ምልልስ ያንብቡ፤ http://orthochristian.com/79957.html። «ክርስቶስን የማያውቁ ሰዎች መኖራቸው የኛ (የክርስቲያኖች) ጥፋት ነው» ይላሉ። ይህ መሰረታዊ እምነታችን ነው።

በመንፈሳዊ ህግ ኃጢአት የቦታ እና የጊዜ ግድብ የለውም። የሁላችንም ኃጢአት ሁላችንንም በተለያየ መንገድ ይነካል። ለምሳሌ፤ እንዴ ወንድሜን ከበደክሉኝ ችግሩ ከኔ እና እሱ መካከል ሆኖ አይቀርም። ይተላለፋል። ወንድሜ ተበሳጭቶ ሌሎችን ይበድላል። ቤት ሲሄድ ቤተሰቡ አክሩፎ ያገኙታል። እኔ ስለበደልኩት ህይወቱን በሙሉ ቁስሉን ተሸክሞ በቁስሉ ምክንያት አስተሳሰቡም ድርጊቶቹም ሊሳባ ይችላል። ቂም ሊይዝ ይችላል። ሰውን በጥርጣሬ ሊያይ ይችላል። በዚህ መንገድ የኔ ኃጢአት እንደ ተላላፊ በሽታ ይንሰራጫል።

ክርስቲያኖች በመንፈሳዊ ህግ ኃጢአት ከቦታ ቦታ ብቻ ሳይሆን ዘመናትን ይሸጋገራል ብለን እናምናለን። ይህ ማለት ኃጢአት ለትውልድ ይተላለፋል። ይህ የሃይማኖታችን መሰረታዊ እምነት ነው። የአዳም ኃጢአትን መውረሳችን ይህን ይገልጻል። ለአዳም ኃጢአት ሃላፊነት ባይኖረንም ውጤቱን ወርሰናል። እኛም ኃጢአት በመስራታችን እንዲሁም አስተላልፈንዋል። ለምሳሌ ከወላጆቼ የወረስኩት ችግርን ተሸክሜ ለልጆቼ በትወሰነ ደረጃ አስተላልፋለሁ። ችግሩ በሃሳብ ብቻ ሳይሆን በደምም (በዲኤኔአችን) ይተላለፋል።

በመንፈሳዊ ህግ ኃጢአት በሀገር ደረጃም ይታወቃል። የእስራኤል ህዝብ ለሀገራዊ ኃጢአታቸው የታዋቁ ናቸው በራሳቸው በኦሪት ታሪክም በወንጌልም ይህ ታሪካቸው ተዘርዝሯል። ሌሎች በርካታ ህዝቦች እንደ ህዝብ ወይንም ሀገር ለኃጢአቶቻቸው ዋጋ ከፍለዋል። ዛሬም እንዲሁ ነው (https://blogs.ancientfaith.com/glory2godforallthings/2015/06/27/dostoevsky-and-the-sins-of-the-nation/)።

ስለዚህ እንደ ግለሰብም እንደሀገርም ኃጢአቶቻችን በቦታ እና ጊዜ ይተላለፋል። ለዚህ ኃጢአቶቻችንን አምነን ንስሃ መግባት አለብን። ይህ መሰረታዊ የክርስትና እምነት ነው። እንኳን በኢትዮጵያ በዓለም ዙርያ ችግር ሲከሰት ወደ ራሳችን ተመልክትን «ምን አድርጌ ወይህም ምን ባለማድረጌ ነው ይህ የሆነው» ብለን እራሳችንን መጠየቅ አለብን።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ መእመን ቁጥር ከቀነሰ ወይንም ካልጨመረ እሄኑኑ ጥያቄ እራሳችንን መጠየቅ ነው ያለብን። አማራጭ የለንም። እውነቱ ይህ ነው። ለዚህ ችግር ሌሎችን ጥፋተኛ ማድረግ ኢ-ክርቲያናዊ አካሄድ ነው። እንደ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች «ጴንጤዎቹ»፤ «ሙስሊሞቹ»፤ ወይንም «ሴኩላሪስቶቹ» ናቸው ምእመኖቻችንን የወሰዱብን ማለት አንችልም። ወደራሳችን ብቻ ነው መመልከት ያለብን። እኛ ብርሃን ከሆንን ምንም አይሳነንም፤ ዓለም በሙሉ ወደ ክርስቶስ ይመጣ ነበር። እዚህ ላይ ነው ማተኮር ያለብን። ይመስለኛል።

Thursday, 3 January 2019

ቃለ ሕይወት ያሰማለን

ቆንጆ ትምህርት ከሩሲያዊ ቄስ አንድሬይ ካችዬቭ፤

https://russian-faith.com/explaining-orthodoxy/how-god-will-judge-those-who-dont-know-christ-n1980

Sunday, 4 November 2018

ጥብቅ ማህበራዊ ኑሮ ለሰው ልጅ ተፈጥሮው ነው

ስለ ብቸኛ (individualist) እና ማህበራዊ (collective) ማህበረሰብ ወይንም ባህል ብዙ ተተንትኗል። የቃላቶቹ ትርጉም በጣም ጥብቅ ባይሆንም ከሞላ ጎደል ግልጽ ነው። እነ አሜሪካ እና አውሮፓ የብቸኛ ማህበረሰብ ባህል አላቸው። በርካታው ሶስተኛ ዓለም የማህበራዊ ባህል ነው ያለው። የብቸኛ ኑሮ የግል መብትና ራስን በራስ መቻል ላይ ነው የሚያተሩረው። የማህበራዊ ኑሮ የሰው ልጅ ይበልጥ ለማህበረሰቡ ህገጋት እንዲገዛ ያደርጋል እና መደጋገፍ እንዲኖር ያደርጋል። ወዘተ።

አብዛኛው ጊዜ ስለ ብቸኛ እና ማህበራዊ ባህሎች ሲተነተን ባህሪአቸው፤ ጥቅም እና ጉዳታቸው፤ በፖለቲካ እና ኤኮኖሚ ያላቸው ተፅዕኖ ወዘተ ነው የሚጠቀሰው። ሰው እንደ ርዕዮት ዓለሙ ወይንም እንደ ግል ምኞቱ ይህ ከይህ ይሻላል ይላል። የአስተሳሰብ እና ፍላጎት ጉዳይ ነው የሚደረገው። ግን በዚች ዓለም ዘመናዊነት ሁሉንም መግዛቱ ስለማይቀር በርካታ ተንታኞች ሁሉ ቦታ የብቸኛ ኑሮ እንደሚሰፍን ያምናሉ።

ግን ጥንታዊው ክርስትና እነዚህን ብቸኛ እና ማህበራዊ የምንላቸውን አኳኋን እንደ እኩል አማራጭ አያቆጥራቸውም። ክርስትና የሚለው የማህበራዊ አኗኗር የሰው ልጅ ተፈጥሮ ነው (ontological)። የሰው ልጅ ህይወት ከባለንጀራው ጋር የተቆራኘ ነው። እርስ በርስ አንድነት አለን። ከኢግዚአብሔር አንድነት (communion) አለን። በዘር፤ በትውልድ፤ በሀገር፤ ከቤተሰብ ወዘተ የወረስነው ሁሉ እራሳችን በራሳችን በምኞት እና ፍላጎት ከምንወስነው ይልቅ እጅግ ግዙፍ ነው።

ዛሬ እንደ በርካታ የሶስተኛ ዓለም ሀገራት በኢትዮጵያም የብቸኛ ኑሮ በ«ዘመናዊነት» እና «ልማት» በኩል አድርጎ እየመጣ ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/04/blog-post_13.html)። በተለይ በአዲስ አበባ እና በተወሰነ ደረጃ በትናንሽ ከተሞች ህብረተሰቡ ይህ የብቸኛ ኑሮ ተዕፅኖ እየተሰማው ነው። ሰው አይጠያየቅም፤ አይተዋወቅም፤ አይደራረስም፤ ልጆቹንም በደምብ አያገኝም፤ ባለመተዋወቅ ምክንያት ወንጀል ይበዛል፤ ፍቅር የለም፤ ከሰው ይልቅ ገንዘብ ወዳድ ሆኗል፤ ለባለንጀራው ግድ የለውም፤ አዛውንቶች አይጦሩም፤ ወዘተረፈ ደጋግሞ ሲባል ሁላችንም እንሰማለን። ጥሩ ነገር እንዳልሆነ እናውቃለን ግን እንደ መዓበል መቶብን በትክክል ምን እንደሆነም ችግሩን ለመቅረፍ ምን ማድረግ እንዳለብን አናውቅም።

በዚህ አጭር ጽሁፍ ማለት የምፈልገው «ይህን ችግር አንንቀው» ነው። ወጋችንን ብቻ ሳይሆን እንደ ሰው ልጅ ማንነታችንንም የሚያጠፋ ነገር ነው። በ«ሰለጠነው ዓለም» የብቸኛ ኑሮ ያመጣውን ልባዊ ቀውስ እያየን ነው። ኪስ ሙሉ ደስታ (እውነታዊ ደስታ) የለም። የሰው ልጅ ለብቸኝነት አልተፈጠረምና። ጠ/ሚ አቢይ ይህንን በተወሰነ ደረጃ እንደ ገባቸው አመልክተዋል። ግን እሳቸውም ሁላችንም ጠልቀን እንመርምረው። በታቻለ ሁኔታ በግል ኑሮዋችንም በመንግስት ፖሊሲም የብቸኝነት ኑሮ እንዳይሰፍን እንስራ። የህልውና ጉዳይ ነውና።

Thursday, 25 October 2018

የሀገራችን የኢትዮጵያ ድህነት «የንስሐ ፖለቲካ» ነው!

የንስሐ ፖለቲካ ምን ማለት ነው? «ንስሐ» በመጀመርያ ስህተትን መገንዘብ እና ማመን ማለት ነው። «ተሳስቻለሁ»፤ «አውቄም ሳላውቅም አጥፍቻለሁ»፤ «በድያለሁ»፤ «የውሸት መንገድ ተከትያለሁ» ብሎ ማመን ነው የመጀመርያ የንስሐ ተግባር።

ይህ ስህተትን ማመን ብዙ ጥቅም አለው። በመጀመርያ እውነትን እንድናውቅ እና እንድናምን ያደርጋል። ለምሳሌ አንድ ፖለቲከኛ በማርክሲዝም አምኖ ሰዎችን «ጸረ አብዮት» ናችሁ ብሎ ጨቁኗል እንበል። ይህ ሰው መሳሳቱን ሲያምን አብሮ ማርኪስዝም ውሸት ነው፤ እውነቱ ስብዓዊነት ነው ብሎ ያምናል ማለት ነው። ንስሐው እውነትን እንዲረዳ እና እንዲቀበል አደረገው።

ሌላው የንስሐ ጥቅም የመንፈስ እርካታ ነው። የስህተት እና ሓጢአት ሸክም ከባድ ነው። ይቅርታ ስንጠይቅ ይህ ግዙፍ ሸክምን እናወርዳለን ማለት ነው። ሸክሙ ሲወርድልን ስራችንን በአግባቡ እንድንሰራ ይጠቅመናል።

ሶስተኛ የንስሐ ትቅም ተጎጂን ማጽናናት ነው። የሰው ልጅ «ይቅርታ አድርግልኝ» ሲባል ልቡ ይለሰልሳል እና ይረካል። ከበቀል ወደ ሰላም ይመለሳል። ይህ የልብ እርካታ እዚህ ላይ አይቆምም። በዳዩ ይቅርታ ሲጠይቀው ተበዳዩም የራሱን ስህተቶች እንዲገነዘብ ይረደዋል። የራሱን ስህተቶች እንዲያምን እና ይቅርታ እንዲጠይቅ ይገፋፈዋል። በዚህ መንገድ የይቅርታ፤ መግባባት እና ቅራኔ መፍታት መንፈስ በማህበረሰቡ ይንሰራጫል።

ሌላው የንስሐ ትቅም ስህተትን አውቆ ማረምያውንም ማወቅ ነው። አንዴ ስህተታችንን ካመንን ለችግሩ መፍትሄውን ማግኘት እንችላለን። በተቃራኒው ስህተታችንን ካላመንን ችግራችንን መፍታት አንችልም። ይህ ሁላችንም የምናውቀው ነገር ነው። አንድ መሪ የተሳሳተ እርምጃዎች እየወሰደ እና ችግሮችን እያመጣ እያለ ስህተቱን ካላወቀ እና ካላመነ ችግሩ መቼም አይፈታም። ስህተትን ማመን የችግር መፍታት ቅድመ ሁኔታ ነው። ስለዚህ ስህተታችንን ካመንን መፍትሄ ይመጣል።

ስለዚህ የንስሐ ሁለተኛ ተግባር ለስህተታችን የፈጠረው ችግሩ መፍትሄ አግኝቶ በተግባር መዋል ነው። ይቅርታ ከጠየቅን እና ስህታችንን ላለመድገም ከማልን በኋላ እንደ ሁኔታው ካሳ እንሰጣለን። ካሳ ማለት የተፈጠረውን ችግር ማስተካከል ማለት ነው። ከሰረቅኩኝ መመለስ። ከጎዳሁኝ ማደስ። ከዋሸሁኝ እውነቱን መናገር፤ ካበላሸሁኝ ማስተካከ፤ ወዘተ። አልፎ ተርፎ እንደዚህ አይነት ስህተትን ደግሜ እንዳልሰራ ተገቢውን ጸሎት፤ ተግባር፤ ትምሕርት ወዘተ ማድረግ እና መፈጸም ነው ያለብኝ። ይህ ነው ችግሩን መፍታት ማለት፤ ማስተካከል እና እንዳይደገም የሚያስፈልገውን ነገሮችን ማድረግ።

ይህ ካደረግን በጠቅላላው የተበላሸውን አስተካከልን ማለት ነው። ወደ እውነት መመለስ ነው። «ወደ ራስ (እውነት ማለት ነው) መመለስ ነው»።

ንስሐን በዚህ መልኩ ከተረዳነው «የንስሐ ፖለቲካ» ጥቅሙን እና አስፈላጊነቱን መገንዘብ ቀላል ይመስለኛል። በአጭሩ ለማስቀመጥ ያህል፤ ንስሐ መግባት የችግርን መፍታት ቁንጮ ነው። ፖለቲካችንም የመሃበራዊ ሁኔታችንም በርካታ የምናውቃቸውም የማናውቃቸውም ችግሮች አሏቸው። እነዚህን ችግሮችን ምንጮቻቸውን ሳናውቅ ወይን ሳናምን እንፈታቸዋለን ማለት ሃሰት ነው። ችግሮቹ የሚፈቱት መጀመርያ ችግር እንደሆኑ ካመንን፤ የራሳችንን ድርሻ ካመንን፤ ይቅርታ ከጠየቅን፤ መፍትሔ ከፈለግን እና እራሳችንን ከቀየርን ነው። ሌላ መንገድ በሙሉ አይሰራም። አልፎ ተርፎ ይህንን መንገድ ካልተከተልን ችግሮቻችን ይቀጥላሉ እየባሱም ይሄዳሉ።

የንስሐ ፖለቲካ በተግባር በታላቅ የፖለቲካ መድረክ ያየነው በጠ/ሚ አብይ አህመድ ስራዎች ነው። ጠ/ሚ አብይ ለአለፉት የኢህአዴግ ጥፋቶች «እንደ ግለሰብ» ተሳስችያለሁ ብለው ይቅርታ ጠይቀዋል። ንስሐ ገቡ ማለት ነው። ይህ በማድረጋቸው በርካታ ስኬቶች አምጥተዋል፤

1. ስህተታቸውን ተገነዘቡ እና አመኑ። ችግሮችን በአግባቡ ስለተረዱ ወደ መፍትሄ መሄድ ችለዋል።

2. ተጎጂውን በሙሉ ይቅርታ በመጠየቃቸው ህዝቡ የመንፈስ እርካታ እንዲያገኝ አድርገዋል። ብሶት እና ቂም በመጠኑ መቀነስ ችለዋል።

3. ሌሎቻችንም ለራሳችን ጥፋቶች ይቅርታ እንድንጠይቅ አስተምረውናል። ስህተታችንን አምነን የጎዳናቸውን አዝናንተን ወደ መፍትሄ እንድንሄድ ገፋፍተውናል። መሪአችን እንዲህ ካደረገ እኛም እንችላለን ነው።

4. አንጻራዊ የብሄራዊ ሰላም አምጥተዋል። ጠ/ሚ አብይ ይቅርታ በመጠየቃቸው አብዮት እና ሁከት እንዳይመጣ አድርገዋል። ሰው ይቅርታ ጠይቆ ይቅር ብሎ በሰላም እንዲኖር ገፋፍተዋል። የ«እውነት እና እርቅ» (truth and reconciliation) አይነት ሂደት ወደፊት እንዲጀመር ሜዳውን አብጅተዋል።

5. ይቅርታ፤ ትህትና እና ሃላፊነት መውሰድን በማንጸባረቃቸው የህዝብን እምኔታ አገኝተዋል።

የጠ/ሚ አብይ የ«ንስሐ ፖለቲካ» ከሞላ ጎደል በታላቁ ስኬታማ ሆኗል። አንድ ወይንም ሁለት ዓመት በፊት የአምባገነናዊ አገዛዛችን በዚህ መልኩ አለ አብዮት እና አለ ሁከት ይቀየራል ብንባል ሁላችንም አናምንም ነበር። የማሆን ነገር ነው እንል ነበር። ይህ ያልጠበቅነው ታላቅ ድል አለ «ንስሐ ፖለቲካ» አይሳካም ነበር።

እንደሚመስለኝ ከዚህ ታላቅ ትምሕርት መማር ያለብን «ኢትዮጵያ ብሄርተኝነት»፤ «አንድነት» ወይን የ«ዜግነት ፖለቲካ» የምናራምደው ጎራ ነን። ደጋግሜ እንደጻፍኩት ይህ የፖለቲካ ጎራ በርካታ የሀገራችን ፖለቲካ ችግርን ያመጣ ነው። በጃንሆይ ዘመን ተሃድሶ ማድረግ ባለመቻሉ፤ ግማሹ ማርክሲስት ሆኖ አብዮት እና ሁከት በማምጣቱ፤ እርስ በርስ በመጨራረሱ፤ በኢህአዴግ ዘመን አብሮ ስርቶ ተገቢ የተቃዋሚ ኃይል ማደራጀት ባለመቻሉ፤ ወዘተ (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2018/07/blog-post_15.html)። እስከ ዛሬ የ«ኢትዮጵያዊነት ኃይሉ» መቢገባን ደረጃ መደራጀት አልቻልንም። ግንቦት 7 ነው ያለው ግን እሱም ከሚገባው እጅግ ትንሽ እና አቅም ያነሰው ድርጅት ነው። የሀገራችን እምብዛም ብዙሃን በ«ኢትዮጵያዊነት» የሚያምን ሲሆን ልሂቃኑ እና ፖለቲከኛው ይህን ብዙሃን ወክሎ ሊያደራጅ አልቻልም። የልሂቃኑ የክሽፈት ታሪኩ ተጭኖታልና።

የንስሐ ፖለቲካ ይህን የተጫነውን መንፈስ ያወርድላታል ብዬ አምንዳለው። ልክ እንደ ለነ ጠ/ሚ አብይ እንዳረገው። እንደ ግንቦት 7 አይነቱ ድርጅት ወደ ኋላ ሄደው እንደ ድርጅት፤ መሪዎቻቸው እንደ ግለሰብ፤ እራሳቸውን ፈትሸው ያደረጉትን ስህተቶች አምነው በይፋ ቢናገሩ ይበጃል። ስህተቱ ትንሽም ሊሆን ይችላል፤ ቅራኔን መፍታት አለመቻል ይሆናል። ግን ይህ ፍተሻ እጅግ ጠቃሚ ነው የሚሆነው። መማርያ ይሆናል።

ታሪክን በአግባቡ ፈትሾ ያሉን ችግሮች ከየት እንደተነሱ ማወቅ አስፈላጊ ነው። ይህ ሲደረግ የሁላችንም ጥፋት ይታያል። ችግሩን በህወሓት ብቻ መለጠፍ ተገቢ አይደለም እውነትም አይደለም። እንደዚህ አይነት የህጻን አስተያየት ነው ችግሮቻችን በአግባቡ እንዳይታወቁ እና እንዳይፈቱ የሚያደርገው። የራስ ሃላፊነትን ማምለጫ መንገድ ነው። ለሀገራችን ችግር ሁላችንም ትልቅ ሚና ተጫውተናል፤ በመስራትም ማለመስራትም። ይህ መታመን እና መነገር ያለበት ይመስለኛል። ይህን ካደረግን ችግሮቻችንን በደምብ አውቀን ትክክለኛውን መፍትሄዎችን እናገኛለን። በህዝቡም እምኔታ እናገኛለን። ከስህተት መማር እና መሻሻል ባህል እናደብራለን። የትህትና ባህል እናደብራለን። የሃላፊነት መውሰድ ባህል እናዳብራለን። ጠ/ሚ አብይ እንደሆኑት ስኬታማ እንሆናለን።

አልፎ ተርፎ የ«ንስሐ ፖለቲካ» ከባህል እና ከወጋችን አብሮ የሚሄድ በመሆኑ ድል የመሳካት እድሉ ከፍ ያለ ነው። «ህዝባችን የዴሞክራሲ ባህል የለውም» ይላሉ የዘመኑ ምሁራናችን። «ገና መማር አለብን እና የስነ ልቦና ለውጥ ያስፈልጋል» ይባላል። ለኔ ይህ አስተያየት የሚመነጨው ከሀገራችን ባህላዊ እሴቶችን በአግባቡ አለማወቅ እና አለመፈተሽ ነው። ከ«ምዕራብ ዓለም» የጫነብን ፕሮፓጋንዳ ማመን ነው ይህ አስተያየት የሚመጣው። ግን የጢ/ሚ አብይ ስኬታማ ስራ የሚያሳየው የኛ የትህትና፤ የይቅርታ፤ የንስሐ፤ እሴቶች በፖለቲካችን ታላቅ አውንታዊ ሚና መጫወት እንደሚችሉ ነው። ሌላ (የምዕራብም) ሀገር መፈጸም የማይቻል ድል ነው የጠ/ሚ አብይ አካሄድ ያመጣው! የት ሀገር ነው መሪ ለሌላ የፈጸመው ሳይሆን ለራሱ ስህተቶች ይቅርታ የሚጠይቀው? የት ሀገር ነው እንደዚህ በቀላሉ ህዝቡ ይቅርታውን የሚቀበለው?! የት ሀገር ነው ትህትና ያሚያንጸባርቅ መሪ የሚወደደው? ይህ አካሄድ ሀገራችን የሰራው ምክንያት ከሃይማኖቶቻችን ቀጥታ የመጡ እሴቶችንም ስለተጠቀመ ነው። ስለዚህ የንስሐ ፖለቲካ በመሰረታዊ ደረጃ ኢትዮጵያዊ አካሄድ ነው። የኢትዮጵያዊነት ፓርቲዎች፤ ይህን የንስሐ ፖለቲካ እንስራበት!

Monday, 15 October 2018

አንድ የቅዱስ ዮሃንስ አፈወር ጥቅስ

«ስፖርት የሚከታተሉ ሰዎች የታወቀ ስፖርተኛ ከመንደራችሁ መጥቷል ከተባለ ይህን ስፖርተኛ፤ ችሎታውን እና ጥንካሬውን ለማየት ብለው ወዳለበት ይሮጣሉ። በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ተመልካቾች የተሞሉ ስታዲየሞች አሉ። እነዚህ ተመልካቾች አንዳች ነገር እንዳያመልጣቸው ብለው እስኪደክማቸው ድርስ አያናቸውንም አዕምሮአቸውንም አትኩረው ስፖርቱን ይመለከታሉ። እንዲሁም የታወቀ ዘፋኝ ከመንደራቸው እንደሚገኝ ከሰሙ ሰዎች ያላቸውን አንገብጋቢም የሆነ ጉዳዮቻቸውን ሁሉ ትተው ዘፋኙን ለማየት ይሄዳሉ። ዜማውን እና ግጥሙን ተጠንቅቀው ያዳምጣሉ። ለታዋቂ ተናጋሪም ሰው እንዲሁ ያደርጋሉ በጭብጨባ እና እልልታ ይቀበሉታል እና ያስተናግዱታል። ታድያ ተናጋሪዎችን፤ ዘፋኞችን እና ስፖርተኞችን ሰዎች እንዲህ አትኩረው የሚከታተል ከሆነ ምን አይነት ቅንዓት እና ጽናት ሊኖረን ይገባ ይሆን ሰው በኢግዚአብሔር ፀጋ ከገነት ሆኖ ሲያስተምርን?»

ቅዱስ ዮሃንስ አፈወርቅ፤ «የዮሃንስ ወንጌል ትርጓሜ» ክፍል 1

"People who watch sports, when they hear that a famous athlete is in town, run to watch him, and all his skill and strength. And there are stadiums full of ten of thousands, all straining their eyes and minds so that they don't miss anything. Or if a famous musician passes through their area, people drop everything, even necessities and urgent business, to sit listening attentively to the words and the music. People will do the same thing for a renown speaker and receive them with clapping hands and cheering. And if in the case of rhetoricians, musicians, and athletes, people pay such close attention, what degree of zeal and earnestness should we display when a man is speaking from heaven with the Grace of God on his tongue?"

St. John Chrysostom (+407AD), On the Gospel of John, Homily 1

Monday, 1 October 2018

በሌሎች መፍረድ

ሁል ጊዜ ሌሎች ሰዎችን ጥሩ ካልሆናችሁ ብለን የምንጠብቀው የራሳችንን ድክመት በነሱ ላይ እየጫንን ስለሆነ ነው። እራሳችን ጥሩ መሆን እንፈልጋለን። ግን ባለመቻላችን ምክንያት ሌሎችን ጥሩ ካልሆናችሁ ብለን እንጫናለን። ይህን አስተሳሰብ ተከትለን አብዛኛው ጊዜ እንጨነቃለን፤ በሌሎች እንበሳጫለን እና እንፈርዳለን። ሆኖም ሁሉንም ነገር በፀሎት ማሸነፍ ይቻላል።

ቅዱስ ፖርፎሪዮስ
Elder St Porphyrios, 'Wounded by Love'