Tuesday 16 April 2019

በስመ አብ! አሁንም ምሁሮቻችን ይህን ስርዓት «multiculturalism» ይሉታል

ይህ ውይይት ገንቢ ይመስለኛል፤ ተመልከቱት። ግን አሁንም በርካታ ሰዎች የሚሳሳቱትን ስህተት ሰርተዋል። አሁን ያለውን multinational federalism (ይጎሳ አስተዳደር) "multiculturalism" ብለው ይጠሩታል። ይህ መሰረታዊ የቃል እና ሃሳብ አጠቃቅም ስህተት ነው።

የኢትዮጵያ ህገ መንግስት በዓለም ብቸኛ እና ጸንፈኛ የሚያደርገው በጎሳ፤ በ«ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች»፤ የተመሰረተ ነው። ይህ ሌላ ሀገር የለም። የጎሳ ፖለቲካ እና የጎሳ ምብት ሌሎች ሀገራት አሉ፤ ግን የህገ መንግስታቸው መሰረት አይደለም። እንደ ካናዳ፤ ህንድ፤ ወዘተ የጎሳ ፍላጎት፤ መብት፤ ጥያቄ፤ ወዘተ፤ የባህል እና ቋንቋ ብዝሃነት፤ የማንነት ምዝያነት ወዘተ ከኢትዮጵያ በተሻለ መንገድ ያስተናግዳሉ። ግን ይህን የሚያደርጉት የባህል እና እቋንቋ ብዝሃነት የሚያስተናግድ የዜግነት ህገ መንግስት ተጠቅመው ነው እንጂ ቀጥታ የጎሳ ሀገ መንግስት ተጠቅመው አይደለም።

ልዩመንት ምንድነው? የኢትዮጵያ ባለቤቶች ጎሳዎች ናቸው። ስለዚህ እንደ ቤኒሻንጉል አይነቱ ክልል ክልሉ የተወሰኑ ብሄር ተወላጆች ንብረት ነው ብለው በህግ መደንገግ ይችላሉ። የሌላ ብሄር ተወላጅ ቤኒሻንጉል ሲኖር እንደ ሁለተኛ ዜጋ ነው። የዜግነቱ መብቶች ከቤኒሻንጉል ጎሳ መቶች በታች ነው። ይህ ዜጋ መሬትና ቤት ካለው ከቤኒሻንጉል ጎሳዎች የተከራየው ነው። ወዘተ፤ ሁለተኛ ዜጋ ነው።

በነ ህንድ አይነቱ ሀገር ክፍለ ሀገሮቹ የተከለሉት ከሞላ ጎደል ጎሳን ታስቦ ነው። ስለዚህ በያንዳንዱ ክልል ብዙ ቁጥር ያለው ጎሳ የጎሳ መብቱን ያስፈጽማል። ለምሳሌ ቋንቋውን እና ባህሉን የክልሉ ቋንቋእና ባህል ያደርጋል። ወዘተ። ግን እዛ የሚኖር የማንኛውም ጎሳ ተወላጅ ሙሉ መብት አለው! ይህ ነው ልዩነቱ። «መጤ» አይደለም። የክልሉ እኩል ባለቤት ነው።

ይህ ልዩነት ውጤቱ ምንድነው? በጎሳ ፌደራሊዝም ጎሳ ከሁሉም በላይ ስለሆነ ግጭት ይበዛዋል። ይህን በኢትዮጵያ በደምብ አይተነዋል እያየነውም ነው (https://asfawdarguemeshal.blogspot.com/2019/03/blog-post_4.html)። የቋንቋ እና ባህል ብዝሃነት ያለው የዜግነት ፌደራሊዝም ግን ግጭት ቢኖርም ዜግነት ከሁሉም በላይ ስለሆነ ግጭቶቹ እጅግ አነስተኛ ናቸው።

ስለዚህ እንደገና... ቁንቋችንን እናስተካከል። ይህ ህገ መንግስት multiculturalism አይደለም ያመጣው። Multinationalismን ነው ያመጣው። የትም ሀገር የሌለ ጸንፈኛ experiment ነው የሚያደርገው። ይህ ሙከራ ኢትዮጵያን የግጭቶች ምህዳር አርገዋታል። አሁን የሚያስፈልገን ወደ ለዘብተኛ መንገድ ተመልሶ ወደ የቋንቋ እና የባህል ብዝሃነት ያለው በተዘዋዋሪ የጎሳ ፋልጎቶችን የሚያስተናግድ የዜግነት አስተዳደር ነው የሚያስፈልገን።


No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!