Saturday 27 April 2019

ክርስቶስ ተነስቷል!



ታላቅ አባታችን ቅዱስ ዮሃንስ አፈወርቅ ወደ 1600 ዓመት በፊት በፋሲካ የሰበከው ታዋቂ ስብከት፤
እርሱ ጽኑ የእግዚአብሔር አፍቃሪ የሆነ
ለቀረበው ያማረ ድግስ በፍሰሀ ይካፈል
እርሱ ታማኝ አገልጋይ የሆነ
ወደ ጌታው ደስታ ይግባ
እርሱ በፆም ራሱን ያደከመ
በድካም ዋጋው አሁን ሃሴት ያድርግ
እርሱ ከመጀመርያው ሰአት ጅምሮ የደከመ
ዛሬ የሚገባውን ይቀበል
እርሱ ከሦስተኛው ሰአት በኋላ የመጣ
ከድግሱ በምስጋና ይካፈል
እርሱ ከስድስተኛው ሰአት በኋላ የመጣ
አይጠራጠር ምንም አያጣምና
እርሱ እስከ ዘጠነኛው ሰአት የዘገየ
አያመንታ ይቅረብ እንጂ
እርሱም በመጨረሻው በአስራሀንደኛው ሰአት የመጣ
ምንም በዘገይም እንኳን አይፍራ
ችር ለጋሽ ጌታው የመጨረሻውን ልክ እንደመጀመርያው ይቀበላልና።
በአስራአንደኛው ሰዓት የመጣውንም ከመጀመሪያው ሰዓት ጅምሮ እንደ ደከመው እኩል ያሳረፋል።
ተግባርን ይቀበላል ምኞትንም ያፀድቃል።
ሁላችሁም ግቡ እንግዲህ፤ ወደ ጌታችን ደስታ
መጀመርያ ሆነ መጨረሻ የመጣችሁ ዋጋችሁን እኩል ተቀበሉ
ሐብታምም ሆነ ደሃ ባንድነት ዘምሩ
እናንተ የፆማችሁም ሆነ ያልፆማችሁ ባንድነት ተደሰቱ
ገበታው ሞልቷል፤ ሁሉም ይብላና ይደሰት
ፍሪዳው ሰብቷል፡ ማንም ሳይጠግብ አይሂድ።
ማንም በድህነቱ አይዘን
ሁሉን አቀፍ መንግስተ ሰማያት ተገልጧልና
ማንም ስለበደሉ አማሮ አያልዝስ
የምህረት ብርሃን ከመቃብር ተነስቷልና
ማንም ሞትን አይፍራ
የመድሀኒዓለም ሞት ነፃ አውጥቶናልና።
ሞትን በሞቱ ድል ነስቷልና
ወደ ሲዖል በመውረዱ ሲዖልን አመሰቃቅሏታል
ሲዖልን በስጋ ነፍስ አጋደደ
ይህንም ነብዩ ኢሳያስ በትንቢቱ እንዲህ ብሎ ተናግሯል፡
ሲዖልም ከምድር በታች ሲያገኝህ በመራራ ነገር ቶሞላ
በመራራ ነገር ተሞላ፤ ባዶ ተደረገና
በመራራ ነገር ተሞላ፤ ተዘበበተበትና
በመራራ ነገር ተሞላ፤ ትወገደና
በመራራ ነገር ተሞላ፤ በሰንሰለት ታሰረና።
ሲዖል ስጋን አገኘሁ ብሎ እግዚአብሔርን አጋጠመው!
ምድርን ተቀበልኩ ብሎ ከገነት ጋር ተፋጠጠ!
ሞት ሆይ መርዝህ የታል?
ሲዖል ሆይ ድልህ የታል?
ክርስቶስ ተነስቷል፤ አንድተስ ሞት ሆይ ተደምሠሃል
ክርስቶስ ተነስቷል፤ ክፉዎችህም ትጥለዋል
ክርስቶስ ተነስቷል፤ መላአክትም ተደስተዋል
ክርስቶስ ተነስቷል፤ ህይወትም ነፃ ወጥቷል
ክርስቶስ ተነስቷል፤ መቃብርም ከሙታን ፀዳ
ክርስቶስ በሞት ለመነሳቱ ላንቀላፉት መባ ሆነ።
ለርሱ ይሁን ሃይል ክብርና ምስጋና ዛሬም ዘውትርም ለዘላላሙ አሜን።

The English version:

If any be a devout lover of God,
  let him partake with gladness from this fair and radiant feast.
If any be a faithful servant,
  let him enter rejoicing into the joy of his Lord.
If any have wearied himself with fasting,
  let him now enjoy his reward.
If any have laboured from the first hour,
  let him receive today his rightful due.
If any have come after the third,
  let him celebrate the feast with thankfulness.
If any have come after the sixth,
  let him not be in doubt, for he will suffer no loss.
If any have delayed until the ninth,
  let him not hesitate but draw near.
If any have arrived only at the eleventh,
  let him not be afraid because he comes so late.
For the Master is generous and accepts the last even as the first.
He gives rest to him who comes at the eleventh hour
  in the same was as him who has laboured from the first.
He accepts the deed, and commends the intention.
Enter then, all of you, into the joy of our Lord.
First and last, receive alike your reward.
Rich and poor, dance together.
You who fasted and you who have not fasted, rejoice together.
The table is fully laden: let all enjoy it.
The calf is fatted: let none go away hungry.
Let none lament his poverty;
  for the universal Kingdom is revealed.
Let none bewail his transgressions;
  for the light of forgiveness has risen from the tomb.
Let none fear death;
  for death of the Saviour has set us free.
He has destroyed death by undergoing death.
He has despoiled hell by descending into hell.
He vexed it even as it tasted of His flesh.
Isaiah foretold this when he cried:
Hell was filled with bitterness when it met Thee face to face below;
  filled with bitterness, for it was brought to nothing;
  filled with bitterness, for it was mocked;
  filled with bitterness, for it was overthrown;
  filled with bitterness, for it was put in chains.
Hell received a body, and encountered God. It received earth, and confronted heaven.
O death, where is your sting?
O hell, where is your victory?
Christ is risen! And you, o death, are annihilated!
Christ is risen! And the evil ones are cast down!
Christ is risen! And the angels rejoice!
Christ is risen! And life is liberated!
Christ is risen! And the tomb is emptied of its dead;
for Christ having risen from the dead,
is become the first-fruits of those who have fallen asleep.
To Him be Glory and Power, now and forever, and from all ages to all ages.
Amen!

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!