Thursday 26 July 2018

ጉዞው ረዥም ነው

የዛሬው ግድያ የመጀመርያው አይደለም ግን በቅርብ ስለሆነ የተወሰነ ነፃነት የሰፈነው ስለ በፊቶቹ ገና ብዙ አልሰማንም። እኔ እንደ አብዛኛው ብዙሃን ከመንግስት ነክ ነገር ሩቅ ብሆንም በቅርቤ እንደዚህ አይነት ግድያ አጋጥሞኛል።

ያለፈው ነሐሴ ከጎተራ አዲስ አበባ ያለው ሃለሉያ ሆስፒታል ሆኜ አንድ ሰው እንደዚሁ በታቀደ ግድያ በጥይት ተመትቶ ሆስፒታሉ ገባ። ከተወሰነ ቀን በኋላ ሞተ። ከዘዶቹ እንደሰማሁት ምዋቹ ከኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ከጓደኞቹ ጋር ሆነ ሲመለስ ተኳጾች መቱት አንድ ጓደኛው ተጎድቶ አመለጠ።

ማን ሊገለው ይፈልግ ይሆን ሲባል ሟቹ በሙስና ጉዳይ ለመንግስት አካል መረጃ ሰጥቷል አሁንም ሊሰጥ ነበር አሉ። ቢሆንም ለኔ እንደዚህ አይነት "professional" ግድያ መኖሩ አስገረመኝ ምናልባትም አስደነገጠኝ። ብሀገራችን ያልተለመደ ነው በተለይ ፖለቲከኛ ባልሆነ ሰው ላይ።

ይህ ታሪክ ከዚህ በፊት ስላጋጠመኝ የዛሬው ግድያ በጣም አላስደነገጠኝም። ብዙዎች እንዳሉት ወደሽር ወቅት ገብተን ይሆናል ከዚህ ለመውጣት ጊዜ ይፈጃል። አዲሱ አመራር ስለ ደህንነት ነክ ጉዳዮች ከሁላችንም በላይ አውቂ ስለሆኑ መደረግ ያለበትን አበጥረው የሚያውቁ ይመስለኛል። ማድረግ መቻሉ ግን ሌላ ጉዳይ ነው።

ከኛ ከብዙሀኑ የሚጠበቀው አንድነት ነው። በፊትም ችግራችን አንድ አለመሆን ነው አሁንም እንዲሁ። በፊትም ችግራችን ሳር በመቀንጠስ እርስ በርስ መጣላት ነው አሁንም እንደዚሁ። የተከፋፈለ ቤት ይፈርሳል ወይንም በዚህ ጉዳይ አኳያ ለሽብር የተጋለጠ ነው። ስለዚህ ሰከን ያለ የፖለቲካ አካሄድ ለሁላችንም ይበጃል። እንበርታ፤ ጉዞው ረዥም ነው።

ግን ከሁሉም በላይ ለአቶ ስመኘው ነፍስ ይማር ቤተሰቡን ጽናት ይስጣቸው።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!