Friday 13 July 2018

ገዱ አንዳርጋቸው እና «ነባር ብአዴኖች»

ገዱ አንዳርጋቸው ብአዴንም ኢህአዴግም ላደረጉት ጥፋቶች በሙሉ ይቅርታ ጠይቋል። ካሁን ወድያ ለህዝብ ተጠሪ እንሆናለን ህግ አክባሪም እንሆናለን አናሸብርም ብሏል። የ«ለማ ቡድንን» እና አብይ አህመድ ደግፎ ኢህአዴግንም መንግስትም እንዲቆጣጠሩት አድርጓል። የነ አቢይ አህመድ ደጋፊ ሆኖም እየሰራ ነው። ይህ ሁሉ ግልጽ ነው ሁላችንም ያየነው ነው።

ይህ ሁሉ ሆኖ ገዱ ትላንት ተነስቶ የብአዴንን ነባር አመራር አሞገሰ ተብሎ ጩሄት አይገባኝም። ምን ነው ለመፍረድ የምንቸኩለው? ሰውን ይሆን እንዲህ ያለው ብለን እራሳችችን አንጠይቅም? እኛም እንደዚህ በችኮላ እንዲፈረድብን እንወዳለን?

ጠ/ሚ አብይ አህመድ ከመቀለ ያሉትን እናስታውስ። «ዎርቅ»! «ወልቃይት የዲአስፖራ ጉዳይ አለበት»! አንዳንዶቻችን ወረድንባቸው። ለምን? የሚሉትን ያውቁ ነበር። የነበርውን ህዝብ ለማስደሰት ህወሓቶችን የፖሮፓጋንዳ አቅም ማሳጣት ነበር። የፖለቲካ ስልት ነበር። እና በውቅቱ ሰርቷል። እንኳን መከለ ሄድው የትግራይን ህዝብ አሞገሱ!

እሺ ያኔ ብዙዎቻችን አብይ አህመድን የለማ ቡድንንም በደምብ አናውቋቸውም ነበር። አሁን ግን ለብዙ ዓመት ከኢህአዴግ ውስጥ ታግለው ድርጅቱን እንደተቆጣጠሩት እናውቃለን። ዋዛ አይደሉም ከኛ ድርብ እጥፍ የሚሰሩትን ያውቃሉ እኛ ያማናውቀውን በርካታ መረጃዎች አላቸው። ስለዚህ ቶሎ ከመፍረድ እራሳችንን መቆጠብ አለብን። አላማትች አንድ ስለሆነ መደገፍ አለብን እንጂ ትናንሽ የማንስማማበት ነገሮችን ካደረጉ ማኩረፍ የለብንም። አለበለዛ አብሮ መስራት አይቻልም።

የገዱም እንደዚሁ። እነ በረከትን ያሞሳቸው። እስኪ በቃቸው ቂቤ ይቀባቸው ምን ቸገረን። ለጊዜው ለፖለቲካ ከተመቸው እሰየው። ነው አሁንም እነ በረከትን እንፈራለን ገዱ ከሃዲ ነው ብለን እንፈራለን!! እንደዚህ ከሆነ ችግራችን ካሰብነው በላይ ነው። በስመ ጥርጣሬ ክፍፍል እና አለመረጋጋት አምጥተን እንደልማዳችን ተከፋፍለን ልንገዛ ነው ማለት ነው። እስቲ ትንሽም የፖለቲካ ስልታችንን እናዳብር።

በመጨረሻ ለፖለቲካችን ገዱ ላይ መጮሁ ጥሩ ነው። የድሮዎቹን ምን ያህል እንደሚጠሉ እና ምን ያህል ቦታ እንደሌላቸው ጡረታ ብቻ እንደሚጠብቃቸው ያስረግጥላቸዋል። ግን እኔ የምፈራው ይህ ገዱ ላይ የተሰነዘረው ጩሀት እንደዚህ አይነት ስልታማ ሳይሆን የእውነት ቅሬታ እና ንዴት ነው። ባይሆን ይሻላል። ከነ ገዱ ጋር አብረን መስራት አለብን ስራቸው ጥሩ እስከሆነ ብአዴንንም ገብተን መቆጣጠር አለብን። አማራ አንድ መሆን አለበት። የ50 ዓመት እርስ በርስ መጋጨት መከፋፈል የፖለቲካ ስልት እና ትብብር አለማወቅ ማብቃት አለበት።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!