Thursday 27 September 2018

ለምንድነው የቡራዩን ክስተት የጎሳ ማጥፋት (ethnic cleansing) ክስተት የሚባለው?

ይህን ቪዲዮ እዩት።


እንዲሁ በርካታ የቡራዩ ሰለቦች እና ምስክሮች የዘር ማጥፋት ክስተት እንደሆነ ገልጸዋል። መረጃዎቹ ቀላል ናቸው፤ ወንጀለኞቹ በአንደበታቸው ዘር እየመረጡ ነው የገደሉት እና የግድያ እና ወንጀል አየነቶቹ ማለትም ማረድ እና መድፈር የዘር ጥላቻ ያለበት የዘር ማጥፋት ዘመቻን ያመለክታሉ። ይህ ምንም ጥርጥር የሌለው እውነታ ነው።

ኦሮሞዎችም ተገድለዋል ተጎድተዋል ይባላል። ይህ የዘር ማጥፋት ክስተ መሆኑን አያስቀርም። በግርግር መሃል ይህም ተከስቶ ይሆናል። መንጋው በመጠጥም በደምም ሰክሮ ብዙ ሊያደርግ ይችላል። ግን ከመንጋ ውስጥ ዘር መርጠው እየገደሉ እንደነበሩ ሃቅ መሆኑን መሰረዝ አይቻልም።

ቅጥረኞች ናቸው ያደረጉት ይባላል። እውነት ሊሆን ይችላል። ያስኬዳልም። ቢሆንም 1) ጥላቻ የሌለባቸው ፕሮፌሽናል ቅጥረኞች የዘር ማጥፋት ምልክቶች ያሉት ግድያ እና ጭቆና ማድረግ አይችሉም! 2) «ቄሮ ነን እያላችሁ ግደሉ» ተብለው የታዘዙ ቅጥረኞች ቢሆኑ ደግሞ ኦሮሞን አይገሉም ነበር። ይልቁንስ አማራን እና ኦሮሞን ለማጣላት የተቀነጀ ሴራ በመሆኑ ከጋሞ ይልቅ አማራ ላይ ነበር የሚያተክሩት።

ስለዚህ እነዚህ ቅጥረኞች ፕሮፌሽናል ሳይሆኑ የአካባቢው ሰው እና አንዳንድ ከውጭ የሜጡ መሪዎች ናቸው። የቅጥረኛ ሴራው በአካባቢው በነበረ የጎስ ቅሬታ እሳት እና በንዚን ማቀጣጠል ነው።

ለቡራዩ ክስተት የኦሮሞ ህዝብም ይሁን ቄሮም መፈረጅ እንደሌለበት ለማንም የሰው ልጅ ግልጽ እንደሆነ እናውቃለን። አንዳንድ ክፉ አሸባሪዎች ወይንም አላዋቂ ቀንደኞች በቀር እንደዚህ አይነት ነገር አያስቡም እንኳን መናገር።

ስለዚህ ለምንድነው የቡራዩ ክስተት የዘር ማጥፋት የሚባለው? ስለነበር ነው! እውነት ስለሆነ ነው! ልክ እንደ ከሶማሌ የተፈናቀሉት ኦሮሞዎች የዘር ማጥፋት ዘመቻ ሰለቦችህ እንደነበሩት። በአዋሳ ዎላይታዎች ላይ እንደደረሰው እኩል። ጊኬኦ ላይ እንደደረሰው። አኗክ ላይ እንደደረሰው። አማራ ላይ በየቦታው እንደደረሰው። የ27 ዓመት የዘር ማጥፋት ክስተቶች ረዥም ዳታቤስ አለ። የቡራዩ ክስተት ትንሿ ናት። ልድገመው፤ ትንሿ ናት። በሶማሌ ግጭቱ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ኦሮሞዎች ነው ገቤታቸው የተባረሩት! (በነገራችን እኛ ኢትዮጵያዊነት ወዳጆች ጎፉንድሚ ለነዚህ አድርገናልን?)

ይህ የሚያሳየው የጎሳ ፌደራሊዝም የግጭት ምንጭ እንደሆነ ነው። ጎሳ በፖለቲካ ሲካተት ጸንፈኝነትን እና ግጭትን ነው የሚያመጣው። ይህ ሃቅ በዓለም ዙርያም ብኢትዮጵያም ይመሰከርለታል።

አልፎ ተርፎ ሁሉም አይነት የኢትዮጵያ ፖለቲከኞች አናምንበትም ቢሉም አምነውበታል! ሁሉም ፖለቲከኞቻችን በርካታ ጊዜአቸውን የጎሳ ግጭት አሳሳቢ ነው አብሮ መኖር አለብን በመስበክ ይውላሉ! ከነ ኦሮሞ ብሄርተኛ ፖለቲከኞች! የጎሳ ግጭት የሀገራችን ዋና ፖለቲካዊ ችግር መሆኑን ከዚ በላይ የሚገልጽ የለም!

ስለዚ የጎሳ ብሄርተኝነት እና የጎሳ ፌደራሊዝም መርዝ እንደመዋት መብት ቢሆንም ይገላል!

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!