Tuesday 25 September 2018

ግንቦት 7 የህዝብ ግንኙነቱን ያጎልብት

ግንቦት 7 የ«ኢትዮጵያዊ ብሀርተኝነት» ዋናው (እክካሁን) የፖለቲካ ድርጅት በመሆኑ ለሀገራችን ህልውና ታላቅ ሚና መጫወት ይኖርበታል። ግን የሚገባውን ሚና ለመጫወት አንድ አንድ ድክመቶቹን ማስተካከል ይኖርበታል።

በሰሞኑ የእውን (real)፤ የዜና እና ማህበራዊ ሚዲያ ግርግር የግንብቶ 7 የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ድክመቶች ጎልተው የታዩ ይመስለኛል። ድክመቶቹ፤

1. ምንም መልዕክት አያስተላልፍም
2. መልዕክቶች ካስተላለፈም ከተለያዩ ሰዎች ዥንጉርጉር የሆኑ መልዕክቶች ናቸው
3. የሚመጡት መልዕክቶች የድርጅቱን አላማ የሚያደናቅፉ ናቸው
4. አጄንዳ መሪ ከመሆን አጄንዳ ተከታይ ይመስላል (instead of setting the agenda, always in reaction mode)

1. በአሁኑ ዘመን ማንኛውም የለህዝብ አስተያየት የሚያገባው ተቋም ለህዝብ መልዕክቶች ቶሎ ብሎ ማሰራጨት አለበት። በኦነግ አቀባበል ግርግር፤ በቡራዩ ክስተት፤ በአዲስ አበባው የህዝብ አፈሳ ወዘተ ግንቦት 7 በፍጥነት አጫጭር የሆኑ የድርጅቱን አስተያየት እና ግብ የሚያንጸባርቁ መልዕክቶችን ማስተላለፍ ነበረበት ግን አላደረገም። ባለማድረጉ ህዝብ ለመረጃ ወደ ሌሎች ምንጮች እንዲሄድ አድርጓል። ሌሎች ደግሞ በደስታ የማይሆን ፕሮፓጋንዳ ለህዝቡ ያንሰራጫሉ። ይህ ለግንቦት 7 አደጋ ነው።

2. ግንቦት 7 የሚያንስተላለፉት መልዕክቶች ደግሞ የተለያዩ ናቸው። ለምሳሌ እኔ ያነበብቋቸው ከአንዳርጋቸው ጽጌ እና ከነአምን ዘለቀ ትንሽ ተመሳሳይ የሆኑ አለ። ግን ደግሞ ሙሉነህ እዮኤል ስለ ስልክ ጠለፋ የሚያተኩር መልዕክት አስተላለፈ። አንድ official መልዕክት ሊኖር ይገባ ነበር ከዛ ሌሎቹ ያንን ቴማ የሚከተሉ መሆን ነበረበት። ለምሳሌ ዋና ቴማ «ስራችንን በደምብ እየሰራን ነው ተረጋግቶ ስራችንን መቀጠል ነው» ከሆነ ሁሉም መልዕክቶች ይህንን ማንጸባረቅ አለባቸው።

3. የሙሉነህ እዮኤል መልዕክት ጥሩ ነገሩ የድርጅቱ አመራር የተሰሩትን የግንቦት 7 አባላትን ጠየቁ የሚለው ነው። ግን ስለ ስልክ ጠለፋ ያስተላለፈው መልዕክት ከግንቦት 7 አላማ ተጻራሪ ይመስለኛል። አሁን የግንቦት 7 ዋና ስራ አቅም ግንባታ (capacity building) የሆነ ይመስለኛል። ድጋፍ፤ አባላት፤ ገንዘብ እና የሰው አቅም ማጎልበት ነው። ለዚህ ደግሞ ሰውዉ እንዲረጋጋ እና ፖለቲካውን እንዳይፈራ ማድረግ ያስፈልጋል። ሁሉን የጊዜያዊ ክስተቶች (short term events) በቀላሉ እንደወሰዱ እና ከዋና አላማ እንዳያዘናጉ ማድረግ ነው ያለበት። ለምሳሌ ስለ ስልክ ጠለፋ፤ መንግስት ስልክን እንደሚጠልፍ የታወቀ ነው። በተለይም የተቃዋሚ ስልኮችን። ግንቦት 7 ሀገር ውስጥ ሲገባ ይህንን ጠንቅቆ ያውቃል። ገና በርካታ የነባር ኃይል ደጋፊዎች አሉ በመንግስቱ። እነሱም አዲሶቹም ለድህንነት እና ፖለቲካቸው የስልክ ጠለፋን ይፈልጉታል። ስለዚህ የተቃዋሚ ስልክ ተጠለፈ ብሎ መአስደንገጥ አያስፈልግም። ይህ ህዝብን ያስፈራራል መፍራቱ ደግሞ ከግንቦት 7 ፍላጎት የሚጻረር ነው። ግንቦት 7 ከሁሉም ነገር በላይ ዛሬ ህዝቡ ፖለቲካን እንዳይፈራ እና ከሱ ስር እንዲሳተፍ ነው የሚፈልገው። «የሁሉም ስልክ ይጠለፋል እንኳን የነኦነግ ስልክም ተጠለፈ» ማለት ነው። አሁን ወደ ስራችን እንመለስ ነው።

4. ምንም አዲስ ወይንም አስደናቂ ዜና ባይኖርም ግንቦት 7 በየቀኑ የሚዲያ አጄንዳ የሚመራ መልዕክት ማስተላለፍ አለበት። በተለይም ስለ ሰላም፤ ፍቅር፤ መደራጀት፤ ስብሰባ፤ አቅም ግንባታ ወዘተ። እንደዚህ አይነት አካሄድ ግንቦት 7 በህዝቡ እምኔታ እንዲያገኝ ይረደዋል (it breeds familiarity and trust)። ይህ ደግሞ አባላት እና አቅም ለመሰብሰብ አስፈላጊ ነው።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!