Saturday 15 September 2018

ህዝብ ፉት የፒለቲካ ውይይቶች ዛሬውኑ ይጀመሩ

ማሳሰብያ፤ ኢቢሲ በአስቸቋይ ተከታታይ የፖለቲካ ውይይቶችን አሁኑኑ ማዘጋጀት መጀመር አለበት።

1. «ፖለቲከኞቻችን» እራሳቸውን ህዝብ ፉት ማጋለጥ አለባችው። ዙርያ ጥምጥም ቀርቶ ማንነታቸውን ማየት አለብን።

2. አቋሞቻቸውንም ከመደበቅ ይልቅ ማስፈትሽ አለባቸው።

3. ፖለቲከኞቻችን ከዝግ በር ኋላ ለማሰብ 27 ዓመት ተሰጥተዋል። ያጡት ይሄን ሳይሆን የህዝቡን ሃሳብ እና ዝንባሌን ማወቅ ስለሆነ አሁኑኑ ህዝብ ፉት ይቅረቡ።

4. መጀመርያ ፕሪግራም እንቅረጽ ማለት ተገቡ አይደለም። ይህ ሂደት ፕሪግራም እንዱቀርጹ ይረዳቸዋል ያስፈልጋቸዋልና።

5. ህዝቡ ውይይትን ይልመድ። እንደ ቅንጅት ጊዜ የአንድ ወር ውይይት ሳይሆን የዓመት ዓመታት ነው የሚያስፈልገን።

6. ፖለቱከኞቻችን በሆዳቸው ውስጥ የደበቁት በተለይ ጸንፈኛ ሃሳቦች ይታዩ። ስለ ምኒልክ ሃኡልት፤ ባንዲራ፤ የጊሳ አስተዳደር፤ ጎሰኝነት፤ ጨቋኝ ተጨቋ፤ እንዴት አብረው እንደሙሰሩ ወይንም እንደሙፋጁ ይጠየቁ። ይጋለጡ ይታወቁ።

7. የሚከሰሱት እራሳቸውን ከማስረዳት እድሉ ይሰጣቸው ሳይሰሹ ይጠቀሙበት።

8. ጎሳዬን ወክዬ እደራደራለሁ የሚለውን እስቱ የመደራደር አቅሙን እንይ። ወይንም የመጋጨት አቅሙን።

9. ፖለቲከኞቻችን በዚህ መልኩ ለረዥም ጊዙእ ሳይፈተሹ ምርጫ ከተጠራ ታላቅ አደጋ ይጠብቀናል።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!