Thursday 3 January 2019

ከብሄር ብሄረሰቦች ህዝቦች ፌደራሊዝም ደጋፊዎች አንዱ የምጋራበት ነገር…

ሁልጊዜ ጥሩውን ነገር መውሰድ ነው… ደካማውን ወገን ትቶ…

የጎሳ አስተዳደር (ፌደራሊዝም) ደጋፊዎች ባህል፤ ቋንቋ እና ሌላ ማንነታችን ለራሳችን ተትቶ እውቅና ይኖረው ይላሉ። የጨርጨር ኦሮሞ የራሱን ማንነት ጠብቆ በሰላም ለመኖር ለዓመታት ታግዷል። የምኒሊክ ጦር 150 ዓመት በፊት መጥቶ አስተአደር እና ባህል ከሌላ ቦታ አምጥቶ የጨርጨር ኦሮሞ ማንነቱን ጠብቆ መኖር አልቻልም ነው። ለኔ ይህ አመለካከት የተወሰነ እውነታ አለው። ለሰው ልጅ የአካባቢ (local) ማንነቱ የተፈጥሮአዊ አስፈላጊነት አለው። የሰው ልጅ በተፈጥሮ ቤተሰብ እና መንደር ያስፈልገዋል። ይህ ተፈጥሮ ነው ብዬ አምናለሁ የሰው ልጅ ታሪክም ይህንን ይመሰክራል። አንዳንድ የጎሳ አስተዳደር ደጋፊዎች ይህን አስተዳደር የምንፈልገው የጎሳ ወይንም ይበልጥ የአካባቢ ማንነቴ እንዳይወረር ነው ሲሉ ይገባኛል። ተገቢ አመለካከት ይመስለኛል።

የማልስማማበት ነገር ግን የአካባቢ ማንነት በህግ ደረጃ የጎሳ ውየን የ«ብሄር ብሄርተሰቦች እና ህዝቦች» ይሁን በሚለው ነው። የምቃወምበት ምክንያቶችም ሁለት ቀላል እና ግልጽ ምክነያቶች ናቸው፤ 1) የአካባቢ ማንነት በጎሳ ከተመሰረተ አግላይ ነው፤ ሰውን በደም እና አጥንት ምክንያት ከአካባቢው በእኩልነት እንዳይቀላቀል ይከልላል እና 2) በጎሳ ከተመሰረተ ግጭት ያመጣል፤ ይህንን ደግሞ በቴኦሪም በ27 ዓመት ታግባር አይተነዋል አሁንም እያየነው ነው።

ስለዚህ እንዴት ነው የጨርጨር ኦሮሞ ባህሉን፤ ቋንቋውን እና የአካባቢ ማንነቱን የሚጠብቀው አስተዳደሩ የጎሳ ካልሆነ? ማለት የጎሳ አስተዳደር ደጋፊዎችን ግብ ለማሳካት እንምራ፤ ግቡን እናሳካ ግን በሌላ መንገድ። የአካባቢ ማንነት እንዲሰፍን እናድርግ ግን አለ ጎሳ አስተዳደር። እንዴት እናድርገው? አንድ ቀላል አማራጭ የዛሬውን ህገ መንግስትን ብዚህ መልኩ መቀየር ነው። «ብሄር ብሄረሰቦች እና ህዝቦች» የሚለውን በዜጋ ይቀየር። የክልል አወቃቀሩ እንዳለ ይሁኑ እንበል። ህገ መንግስቱ ላይ ለክልል ግን እጅግ ይበልጥ ለዞን እና ለወረዳ በርካታ ኃይሎች ይስጥ። ዛሬ ካለው ይልቅ አብዛኛው የመንግስት ኃይል ወደ ዞን እና ወረዳ ይውረድ። ይህ ከተደረገ የአካባቢ ማንነት በዘላቂነት ይጠበቃል።

ለምሳሌ አንድ ዞን አካባቢ አስተዳደር ቋንቋ እና የትምሕርትቤት ቋንቋ የመወሰን መብት ይኑረው። ምናልባትም የመሬት ፖሊሲ መብት ይኑረው። የአስተዳደር ዘዴ መብትም ይኑረው። ወዘተ። ብዙ መብቶች ወደ ታች ወደ ዞን እና ወረዳ መውረድ ይችላል። ይህን በማድረግ አካባቢዎች ኃይል እና ስልጣን እንዲኖራቸው ይደረጋል። መአከላዊ እና ክልላዊ መንግስቶች የራሳቸውን ፍላጎት እና ተጽዕኖ ዞን እና ወረዳዎች ላይ ተገቢ ያልሆነ ጫና ማድረግ ያችልም። የአካባቢ ባህል፤ ቋንቋ እና ማንነት በደምብ ይጠበቃል። መዓከላዊ እና ክልላዊ መንግስቶች እነዚህ ነገሮችን መንካት አይችሉም። የአካባቢ ማንነት autonomy ይጠበቃል።

አንዳንድ የጎሳ አስተዳደር ደጋፊዎች ይህ አሰራር የአከባቢ ማንነትን ሊያስከብር ያችልም ትሉ ይሆናል። በተለያየ መንገድ አዲስ አበባ፤ የምአከላዊ መንግስት፤ የክልል መንግስት ወዘተ በባህልም በሌላም ተጽዖን አድርጎ ማንነቱን ሊቀይር ይችላል ትሉ ይሆናል። ምናልባት። ግን እንዲህ ከሆነ የጎሳ አስተዳደርም ይሄንን ሊከላከል አይችልም! ጨርጨር የአካባቢ ማንነቱን ከክልሉ በጎሳ መልክ የሚቀበል ከሆነ ተቀባይ ነው ዴሞክራሲያዊ አይደለም። ስለዚህ ነጻነት የለውም። ግን ነጻነቱ ቢሰጠው እና በጎሳ ይልቅ በአካባቢ ቢሆን የጨርጨር ኦሮሞ አብዛኛ በመሆኑ አካባቢው በራሱ ባህል ይቀርጸዋል። እዛ የሚኖሩ ኦሮሞ ያልሆኑትም እኩል ዜጋ ስለሆን ደም እና አጥንታቸው ስለማይቆጠር ይህንን የአካባቢ ማንነት ይደግፉታል እና ይሳተፋሉ። Win-win ሁኔታ ነው።

እስቲ ይህን ሃሳብ አስቡበት። አውቃለሁ የኢትዮጵ ምሁራን የተማሩት በtextbook የምዕራባዊ ፍልስፍና ነውና ስለ localism፤ communitarianism ወዘተ ብዙ አስበንም ገብቶንም አናውቅም። የጎሳ መብት እንላለን ግን አሁንም ከላይ ወደ ታች መጫን ነው ፍላጎታችን። ሌላ አስተሳሰብ ግን ዞሮ ዞሮ ከላይ ወደታች። ግን እስቲ ለአካባቢዎች እውነተኛ ነጻነት እንስጣቸው። ማንም እንዳይጎዳ የዜግነት መንብት እንዲሰፍን አድርገን ግን በርካታ መብቶች ወደ ታች እናውርድ። ይህ ሃሳብ የጎሳ አስተአደር እና የዜግነት አስተዳደር ደጋፊዎችን የሚያስማማ ይመስለኛል።

(ለስህተቶች ይቅርታ በችኮላ ነው የጻፍኩት!)

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!