Thursday 17 January 2019

የጎሳ አስተዳደር አንድ እና አንድ ችግር ነው፤ የግጭት ምንጭ ነው

ፖለቲካ በሃሳብ ብቻ ነው ምሆነ ያለበት እንጂ በጎሳ መሆን የለበትም ሲባል ዋናው ምክንያቱን አጥብቀን ማስረዳት አለብን። ምክንያቱ የብሄር ፖለቲካዊ ጥያቄ ስለሌለ አይደለም፤ ጎሳዎች ስላልተጨቆኑ አይደለም፤ የርዕዮት ዓለም ጉዳይ አይደለም። መሰረታዊ ምክንያቱ፤

«ጎሳ ወደ በፖለቲካ ሲገባ የግጭት ምንጭ ይሆናል ነው»።

ይህ ደግሞ የርዕዮት ዓለም ወይንም የቴኦሪ አመለካከት ሳይሆን በተግባር empirically በሀገራችን (ሌሎችን ሀገራት ምሳሌ ትተን) የያእነው እያየን ያለው ነው። በህወሓት ዘመን የጎሳ አስተዳደር የግጭት ምንጭ ነበር። ግጭቶቹ ሀውሓት የሰራቸው ብቻ ሳይሆኑ በርካታ ሌሎች ነበሩ። በዴሞክርሲ እጦት ሳይሆን በሌላ ምክንያቶች የተነሱ ነበሩ።

አሁን ደግሞ «ነፃነት» ባለበት የጠ/ሚ ዓቢይ ዘመን የጎሳ ግጭቶች እየቀጠሉ ነው። ይህ አስምሮ የሚያሳየው የጎሳ አስተዳደር ወይንም የጎሳ ፖለቲካ በነፃነት እና ዴሞክራሲያዊ አገዛዝም ግጭቶች የመጣል ነው።

ስለዚህ የጎሳ ፖለቲካ/አስተዳደር የግጭት ምንጭ ነው። መብት ነው። ጥያቄዎችን ያስተናግዳል። ግን ግጭት እና ጦርነት ያመጣል።

አማራጩ ምንድነው። የጎሳ ጥያቄዎች በጎሳ አስተዳደር ሳይሆን በሌላ መልኩ ይመለሱ። ለምሳሌ «የአካባቢዬ ባህል አይናድ» ከሆነ በአካባቢ ፖለቲካዊ መብቶች ይመለስ። «ቋንቋዬ ይስፈን» ከሆነ በአካባቢ ፖለቲካ እና በብሄራዊ ዴሞክራሲ መንገድ ይመለስ። ወዘተ። የጎሳ ጥያቄዎች በዚህ መልኩ ሊመለሱ ይችላሉ። እንኳን እንደ ኦሮሞ አይነት የግዙፍ ጎሳ ጥያቄ የአናሳዎችም በዚህ መልኩ ይመለሳል።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!