Thursday 24 January 2019

በረከት ስመዖን፤ የድክመታችን መለክያ

ሃብታሙ አያሌው እንዳለው ፍትህ መታየቱ ጥሩ ነው። ሆኖም ለበረከትም፤ ለቤተሰቦቹም፤ ለኢትዮጵያም አዝናለሁ።

እንደ ኢትዮጵያዊ አፍራለሁ። እንደ ሀገር እንደ በረከት፤ ታደሰ፤ አዲሱ፤ መለስ ወዘተ አይነት አስተሳሰብ ያላቸውን ሰዎችን ማፍራታችን ያሳፍራል። መቶ እጥፍ የሚያሳፍረው ግን እንደዚህ አይነት አስተሳሰብ ያላቸው ሰዎችን መሪዎቻችን እንዲሆኑ መፍቀዳችን ነው።

ሌላ ላይ መፍረድ ቀላል ነው ግን ልክ አይደለም አዋጪም አይደለም። ሃላፊነት የወሰደ ብቻ ነው ህይወቱን በትክክል መምራት የሚችለው። እኛም እንደ ኢትዮጵያዊያን በነ በረከት መኖር እና ስልጣን መያዝ ሃላፊነት መውሰድ አለብን። በተለይም የፖለቲካ መደባችን ከጃንሆይ ዘመን ጀምሮ ያደረግነው ተደጋጋሚ ጥፋቶችን አይተን፤ አምነን፤ ህፍረታችንን አምነን፤ ተቀብለን፤ ንስሃ መግባት አለብን።

ከበረከት ስመዖን መማር የሚገባኝ ይህ ነው ብዬ አምናለሁ።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!