Friday 4 January 2019

የአብን መሪዎች ትምክሕተኛ ናቸው!

https://www.facebook.com/seyoum.teshome/videos/1916214778447833/

ሙሉውን ቃለ ምልልስ አላየሁትም ግን… የአብን መሪዎች ክርስቲያን ታደለ እና በለጠ ሞላ ትምክተኛ ነን ሲሉ ይታያል። እስቲ ከዚህ ጥርውን ወገን ልውሰድ…

ባለፉት ረዥም ረዥም ዓመታት የጎሳ ብሄርተኞች አማራ ወይንም «የአማራ ግዥ መደብ» ዋና ጨቋኝ ነው ብለው ሲሰብኩ አብሮ ቋንቋችንን መርዘዋል። «አድሃሪ»፤ «ነፍጠኛ»፤ «ትምክሕርተኛ»፤ «ጠባብ» የሚሉትን ቃላቶች ለአሉታዊ እና ሃሰተኛ ትርክት ተጠቅመዋል። የ«ጨቋኝ ተጨቋኝ» ትርክትን ሽጠውልናል።

የትርክቱን ሃሰትነት ለማስረገጥ እግረ መንገዳችን እነዚህ ቃላቶችን መልሰን ማዳን አለብን። ማሸማቀቅያ እንዲሆኑ መፍቀድ የለብንም። አንዳንድ አማራዎች በተለይም ወደ አብን የሚሳቡት ለረዥም ዓመታት እነዚህን ስድቦች ሲሰሙ ስሜታቸው እጅግ ተነክቷል። የበታችነት እንዲሰማቸው ተደርጓል። ለዚህም ነው አዎ በአማራነቴ እመካለሁ የሚሉት። አላፍርበትም ነው። ካሁን ወድያ ይህ ቃል ኃይል የለውም ነው። ልድገመው፤ ካሁን ወድያ ይህ ቃል ኃይል የለውም ነው።

ይህ ጥሩ ነገር ነው። አብኖች፤ ቀጥሉበት! (ግን የውሃ ልክ አይነት ያልሆነ ነገር ተውው!)

ይህን ሁሉ ስል በአብን የአማራ ብሄርተኝነት እና በበርካታ የሚሪዎቻቸው አቋም ጭራሽ አልሳማማም። ግን ዛሬ እረፍት ልስጣቸው እና ጥሩ ወገኑን ልጥቀስ።

No comments:

Post a Comment

ለሀሳብዎ አመሰግናለሁ!